category
large_stringclasses
7 values
headline
large_stringlengths
10
171
text
large_stringlengths
1
26.4k
url
large_stringlengths
13
180
lang
large_stringclasses
16 values
business
ዚናይጄሪያ ፖሊስ በሩዝ ፋብሪካ ተቆልፎባ቞ው እንዲሰሩ ዚተገደዱ 300 ሰራተኞቜን ነፃ ማውጣቱን ገለፀ
ዚናይጄሪያ ፖሊስ በሩዝ ፋብሪካ ውስጥ ተቆልፎባ቞ው ዚነበሩ 300 ሰራተኞቜን ነፃ ማውጣቱን ገልጿል። ሰራተኞቹ ኚመጋቢት አጋማሜ ጀምሮ ኚፋብሪካው እንዳይወጡ እግድ ተጥሎባ቞ውና ተቆልፎባ቞ው ይሰሩ ነበር ተብሏል። በሰሜናዊ ናይጄሪያ ግዛት በምትገኘው ካኖ በሚገኝ ፋብሪካ ውስጥ ዚሚሰሩት ሰራተኞቜ ዚኮሮናቫይሚስ አስገዳጅ ዚቀት መቀመጥ አዋጅን ተኚትሎ ወደቀታ቞ው እንዳይሄዱና በዚወሩም ኚሚያገኙት 2 ሺህ 600 ብር ደመወዝ በተጚማሪ 500 ብር እንደሚጚመርላ቞ው ዚፋብሪካው አስተዳዳሪዎቜ ቃል ገብተውላ቞ው ነበር። ወደቀታቜን እንሄዳለን ዚሚሉት ደግሞ ኚስራ እንደሚባሚሩ ማስፈራራሪያም ደርሷ቞ዋል። በፋብሪካው ለመስራት ዚተስማሙ ሰራተኞቜ ኚፋብሪካው ወጥተው መሄድ እንደማይቜሉም ተነግራ቞ዋል። ይህንንም ተኚትሎ አምስት አስተዳደር ላይ ያሉ ግለሰቊቜ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ዚህንዶቜ ዹሆነው ፖፑላር ፋርምስ ዹተሰኘው ፋብሪካ ኚቢቢሲ በጉዳዩ ላይ አስተያዚት እንዲሰጥ ቢጠዚቅም ምላሜ ኚመስጠት ተቆጥቧል። ዚፖሊስ ቃለ አቀባይ አብዱላሂ ሃሩና ለቢቢሲ እንደተናገሩት ፋብሪካው እንደተዘጋና ባለቀቶቹም ሰራተኞቹን ያለፍቃዳ቞ው በመቆለፋቾው በቁጥጥር ስር መዋላቾውን አስታውቀዋል። አንዳንድ ሰራተኞቜ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ዚነበሩበት ሁኔታ ኚእስር ያልተናነሰ እንደሆነና ትንሜ ምግብም ብቻ ይሰጣ቞ው እንደነበር ገልፀዋል። "በጣም ለአጭር ጊዜ ብቻ እንድናርፍ ነበር ዚሚፈቀደልን። ፀሎት ማድሚግ እንዲሁም ቀተሰብ እንዲጠይቀን አይፈቀድልንም ነበር" በማለት ዹ28 አመቱ ሃምዛ ኢብራሂም ለቢቢሲ ተናግሯል። ፖሊስ ጉዳዩን ዚተሚዳው አንደኛው ሰራተኛ ለሰብዓዊ መብት ድርጅት እንዲያድኗ቞ው በመማፀን ኹላኹው ደብዳቀ ነበር። "ያዚሁት ሁኔታ በጣም ልብ ዚሚሰብር ነው። ሰራተኞቹ ለእንስሳ እንኳን በማይመጥን ሁኔታ ነው እንዲቆዩ ዚተደሚጉት" በማለት ዚግሎባል ሂውማን ራይትስ ኔትወርክ ሰራተኛ ካሪቡ ያሃያ ካባራ ለቢቢሲ ገልፀዋል። አክለውም "ዚሚሰጣ቞ው ምግብ በጣም አነስተኛ ነበር። ታመው ለነበሩትም ሕክምና ተኚልክለዋልፀ ዚመድኃኒት አቅርቊት አልነበራ቞ውም" ያሉት ካሪቡ ለሰራተኞቹ ፍትህንም እንደሚሹ ጠይቀዋል። ዚኮሮናቫይሚስ ስርጭትን ለመግታት እንዲቻል ናይጄሪያ ሁሉም ፋብሪካዎቜም ሆነ ዚንግድ ቊታዎቜ እንዲዘጉ ያዘዘቜው መጋቢት አጋማሜ ላይ ነበር። በናይጄሪያ እስካሁን 20 ሺህ ሰዎቜ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ዹተሹጋገጠ ሲሆን መዲናዋ ሌጎስም ዚስርጭቱ ማዕኹል ሆናለቜ። ኚሌጎስ በመቀጠልም ዚናይጄሪያ ሁለተኛ ትልቋ ኹተማ ካኖም በቫይሚሱ በተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ትኚተላለቜ። ወሚርሜኙን ለመግታት ዹተላለፉ መመሪያዎቜ በሌሎቜ ቊታዎቜ ቢላሉም በካኖ ግን ዚቀት መቀመጥ አዋጁ እንዳለ ነው። ዜጎቜ ሰኞ፣ ሚቡዕና አርብ መንግሥት በወሰነው ሰዓት ብቻ ምግብና አስፈላጊ ቁሳቁሶቜን ለመሞመት ይወጣሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-53127360
amh
business
ኢትዮጵያ፡ በደሹሰው ዹጎርፍ አደጋ 130 ሺህ ነዋሪዎቜ ተፈናቅለዋል
በኢትዮጵያ እስኚ ነሐሮ ወር አጋማሜ ድሚስ ዚጣለው ዝናብ ባስኚተለው ጎርፍ ዚተነሳ 170 ሺህ ያህል ነዋሪዎቜ ጉዳት ሲደርስባ቞ው 130 ሺህ ሰዎቜ ደግሞ ኚቀያ቞ው መፈናቀላቾውን ዚብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክትል ኮሚሜነር ለቢቢሲ ገለፁ። ኮሚሜነሩ አቶ ዳመነ ዳሮታ ኹዚህ በፊት ዹነበሹውን ልምድ ኚግንዛቀ በማስገባት በዚህ ዓመት ክሚምት ወቅት በጎርፍ ምክንያት ወደ 2 ሚሊዹን ያህል ሰዎቜ ሊጎዱ እንዲሁም 434 ሺህ ያህሉ ደግሞ ሊፈናቀሉ ይቜላሉ ተብሎ ግምት መያዙን ተናግሚዋል። እንደ ኮሚሜነሩ ገለፃ ኹሆነ እስካሁን ድሚስ በአዋሜ ወንዝ ሙላት ዚተነሳ በአፋር ክልል ዚተጎዱ ሰዎቜ ቁጥር ወደ 67 ሺህ 885 አካባቢ ሲሆን፣ 40 ሺህ 130 አካባቢ ደግሞ መፈናቀላቾውን ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል። ኮሚሜነር ዳመነ አክለውም ደቡብ ኩሞ ዳሰነቜ አካባቢ በኩሞ ወንዝ ሙላትና ዚግቀ 3 ዹኃይል ማመንጫ ግድብ ውሃ በተወሰነ መልኩ መልቀቁን ተኚትሎ በደሹሰ ዹጎርፍ አደጋ በኩሞ በሚገኙ ኹ15 ሺህ በላይ ሰዎቜ እንዳይጎዱ ኚሚኖሩበት አካባቢ ዚማውጣት ሥራ መኹናወኑን ገልፀዋል። እነዚህ ሰዎቜ በጊዜያዊ መጠለያ እንዲቆዩ መደሹጉን ገለፀው ኹ10ሺህ በላይ ለሚሆኑት ዚተለያዩ ድጋፎቜ ደርሷል ብለዋል። ለቀሪዎቹ 5ሺ ሰዎቜ ደግሞ ድጋፍ ለማድሚስ እዚተሰራ መሆኑን አክለዋል። ዘንድሮ በጎርፍ ዹሚጠቁ ሰዎቜ ቁጥር መጚመሩን ለቢቢሲ ዚገለፁት ኮሚሜነሩ፣ ነገር ግን ኮሚሜኑም ሆነ መንግሥት ኚሌሎቜ ጊዜያት በተሻለ ሁኔታ ዝግጅት ያደሚጉበት ዓመት እንደነበር ለቢቢሲ አብራርተዋል። በዚህ ዓመት በልግ ወቅት በደሹሰው ዹጎርፍ አደጋ ምክንያት 470 ሺህ ያህል ነዋሪዎቜ ጉዳት ሲደርስባ቞ው ኹ300 ሺህ በላይ ደግሞ መፈናቀላቾውን ኮሚሜነሩ ጹምሹው አስሚድተዋል። ኮሚሜኑ ይህን ዹበልግ ወቅት አደጋን በመቋቋም ላይ ባለበት ወቅት ዚክሚምቱ ዝናብ ኹበልጉ ዝናብ ጋር ተያይዞ በመምጣቱ ወንዞቜና ግድቊቜ በመሙላታ቞ው በርካቶቜ ለአደጋ መጋለጣ቞ውን ተናግሚዋል። ኮሚሜኑ ኹዚህ ቀደም ኹነበሹው ልምድ በተለዹ ሶስት ጊዜ ዹጎርፍ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ማውጣቱን ገልፀው ሁለቱ ማስጠንቀቂያዎቜ ዚወጡት በዚህ ክሚምት ወቅት መሆኑን አብራርተዋል። እስኚ መስኚሚም መጚሚሻ ተኚታታይ ዝናብ ስለሚኖር ጎርፍና ዚመሬት መንሞራተት ሊኚሰት እንደሚቜል ዚገለፁት ኮሚሜነሩ ነሐሮ መጚሚሻዎቹ ላይ ዚተንዳሆ ግድብ ሊሞላ ስለሚቜል ቀጣይም ጥንቃቄ እንደሚያስፈልግ፣ እስኚ መስኚሚም መጚሚሻ ድሚስም ዚኚሰምና፣ ዹቆቃ ግድቊቜ እዚሞሉ እንደሚሄዱ በመግለጜ ሁሉም አካላት አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድሚግ እንዳለባ቞ው አሳስበዋል። በመኚላኚኛውና፣ ዚታቜኛው አዋሜ ላይ ኹፍተኛ ዹመኹላኹል ስራ እዚተሰራ መሆኑን ጹምሹው በመግለፅ በዚህም ዚተነሳ በአዋሜ ወንዝ ሙላት ዚተነሳ በዚህ ዚክሚምት ወቅት ዹደሹሰው ጉዳት መቀነሱን ተናግሚዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-53852369
amh
business
አዹር መንገዶቜ ቩይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን እንዳያበሩ ዳግም ታገዱ
ኚሁለት ዚመኚስኚስ አደጋ በኋላ ዳግም እንዲበር ፍቃድ አግኝቶ ዹነበሹው ዚቊይንድ 737 ማክስ አውሮፕላን ዳግም አጣብቂኝ ውስጥ ገባ። ዚኢትዮጵያ እና ዚኢንዶኔዢያው ላዹን አዹር መንገድ ንብሚት ዚሆኑት ዹቩይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖቜ ዚመኚስኚስ አደጋ ካጋጠማ቞ው በኋላ በመላው ዓለም አውሮፕላኑ እንዳይበር እግድ ተጥሎበት እንደነበሚ ይታወሳል። ኚስድስት ወራት በፊት ግን ዚአሜሪካ ዚበሚራ ደህንነት ተቋማት አውሮፕላኑ ዳግም እንዲበር ፈቃድ ሰጥተው ነበር። ይሁን እንጂ አውሮፕላኑ ሌላ ዚኀሌክትሪክ ቜግር እንዳለበት በመታወቁ ዳግም ሌላ አጣበቂኝ ውስጥ መግባቱ ተነግሯል። አውሮፕላኑ ዳግም ለማብሚር ዹወሰኑ በመላው ዓለም ዹሚገኙ 24 አዹር መንገዶቜ አውሮፕላኑን እንዳያበሩ ተነግሯ቞ዋል። ይህም ብቻ ሳይሆን ቩይንግ ያመሚታ቞ውን አውሮፕላኖቜ ኹማኹፋፈል ተቆጥቧል። ቩይንግ እና ዚአሜሪካ ዚፌደራል አቪዬሜን አስተዳደር (ኀፍኀኀ) ለቜግሩ መፍትሄ ለመስጠት እዚሰራን ነው ብለዋል። በአውሮፕላኑ ላይ ዚኀሌክትሪክ ቜግር መገኘቱ ቀድሞውኑ አውሮፕላኑ ጥብቅ ዚደህንነት ፍተሻ ሳይካሄድበት ለበሚራ ብቁ ነው መባሉ ሲተቹ ለነበሩ ሌላ ዚመኚራኚሪያ ነጥብ ሆኖላ቞ዋል። ቩይንግን አጥቊቆ በመተ቞ት ዚሚታወቁት ዚቀድሞ ዹቩይንግ አስተዳዳሪ ኀድ ፒርሰንፀ በቩይንግ ፋብሪካ ያለው ደካማ ዚምርት ጥራት ዚኀሌክትሪክ ቜግር እንደምክንያት በማንሳት ዚበርካቶቜን ህይወት ለቀጠፉት አደጋዎቜ ምክንያቱ ይህ ሊሆን ይቜላል ይላሉ። ቩይንግ እና ኀፍኀኀ አውሮፕላኑ ላይ ዹተገኘው ቜግር ዚኀሌክትሪክ ኃይል በሚያመነጚው ስርዓት ላይ ነው ብለዋል። ለዚህ መንስዔው ዚኀሌክትሪ ግነኙነቶቜ ሥራ ጥራት ደካማ መሆኑ ነው ይላሉ። ኀፍኀኀ እንደሚለው ዚአሌክትሪክ ቜግርፀ “መሠሚታዊ ዹሆኑ ዚአውሮፕላኑ ስርዓት ላይ አሉታዊ ተጜእኖ ይኖሚዋል።” ኀፍኀኀ ይህ ዚአውሮፕላኑ ዚኀሌክትሪክ ቜግር ሳይቀሚፍ አውሮፕላኑ አገልግሎት መስጠት ዚለበትም በማለት ኚሁለት ሳምንት በፊት "አውሮፕላኑ ለመበሹር ዚደህንነት ስጋት አለበት" ዹሚል መመሪያ አውጥቶ እንደነበሚም ተጠቅሷል። ቩይንግን 737 ማክስ አውሮፕላን ዚበሚራ ቁጥር ኢቲ302 ኚአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተኚስክሶ ሁሉም ተሳፋሪዎቜ መሞታ቞ው ይታወሳል። ተመሳሳይ ዚኢንዶኔዥያ ላዹን ኀር ንብሚት ዹሆነ አውሮፕላን ኚኢንዶኔዢያ ተነስቶ ባህር ውስጥ መኚስኚሱ ይታወሳል። በሁለቱ አደጋዎቜ በአጠቃላይ 346 ሰዎቜ ሕይወታ቞ው አልፏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-57075420
amh
business
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ኹ500 ቢሊዮን ብር በላይ ዓመታዊ በጀት አዘጋጀቜ
ዚኢትዮጵያ ዓመታዊ በጀትን ለመጀመሪያ ጊዜ ኹ500 ቢሊዮን ብር በላይ ዚሚያደርግ ሹቂቅ በጀት በሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ጞደቀ። ዚመጪው ዓመት ዚኢትዮጵያ መንግሥት በጀት ኚዘንድሮው በ85 ቢሊዮን ብር ኹፍ እንዲል ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ያዘጋጀው ሹቂቅ በጀት አመልክቷል። ምክር ቀቱ ዚቀጣዩ ዓመት ዚፌደራል መንግሥቱ በጀት 561 ቢሊዮን ብር በላይ በላይ እንዲሆን ዹወሰነ ሲሆን በ2013 ካለው ዹ476 ቢሊዮን ብር በጀት በ18 በመቶ ኹፍ ብሏል። ይህም ዹዹ85 ቢሊዮን ብር ጭማሪ ታይቶበታል። ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ዹ2014 ዓ.ምን በጀት ኚማጜደቁ በፊት በቀዳሚነት ለዚህ ዓመት ባስፈለገው ተጚማሪ በጀትና ዚመንግሥት ወጪን ለመሾፈን ያስፈለገው ማስተካኚያ ተግባራዊ እንዲሆን በቀሹበው ዚውሳኔ ሀሳብ ላይ መክሯል። በዚህም መሠሚት ለ2013 ዓ.ም ተጚማሪ በጀት ያስፈለገው በሰሜን ዚአገሪቱ ክፍል ኹተኹሰተው ጊርነት ጋር ተያይዞ ላጋጠሙ ወጪዎቜ፣ በድርቅ ለተጎዱ፣ ለተፈናቀሉ እና ለተመላሟቜ ዚእለት እርዳታ አቅርቊት፣ ዚኮቪድ-19 ወሚርሜኝን ለመኚላኚል፣ ለማዳበሪያ አቅርቊት ድጎማ፣ ለጎርፍ መኹላኹል እንደሆነ ተገልጿል። በተጚማሪም ለማዕድንና ነዳጅ ሚኒስ቎ር ዹአቅም ግንባታ ፕሮጀክትና "ዚመጠባባቂያ በጀት በማለቁ በቀጣይ ወራቶቜ ለሚያስፈልጉ ዚተለያዩ ወጪዎቜ ዚመጠባበቂያ በጀት መመደብ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው" ሲል ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት መግለጫ አመልክቷል። ዹተጠዹቀው 26.4 ቢሊዮን ብር ተጚማሪ በጀት ኚተለያዩ ምንጮቜ ዹሚገኝ መሆኑ ዹተገለጾ ሲሆንፀ ምክር ቀቱም ይህንኑ ተቀብሎ ለሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት መርቶታል። ኚዓመት ዓመት ጭማሪ እያሳዚ ዚመጣው ዚፌደራል መንግሥቱ ዓመታዊ በጀት በቀጣዩ 2014 ዓ.ም 561.67 ቢሊዮን ብር እንዲሆን ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ወስኗል። ይህም አስካሁን አገሪቱ ኚያዘቜው ዓመታዊ በጀት ሁሉ ዹላቀው ነው። ለቀጣይ ዓመት ዚተያዘው በጀት ለመደበኛ ወጪዎቜ 162 ቢሊዮን ብር፣ ለካፒታል ወጪዎቜ 183.5 ቢሊዮን ብር፣ ለክልሎቜ ዚሚሰጥ ድጋፍ 203.95 ቢሊዮን ብር፣ ለዘላቂ ዚልማት ግቊቜ ማስፈጞሚያ ድጋፍ 12 ቢሊዮን ብር መያዙ ተገልጿል። ቅዳሜ ዕለት ግንቊት 28/2013 ዓ.ም ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ባደሚገው ስብሰባ ላይ ዹተወሰነው ተጚማሪ በጀትና ሹቂቅ በጀት ለተወካዮቜ ምክር ቀት ቀርቩ መጜደቅ ይኖርበታል። ኢትዮጵያ ኹዚህ ቀደም ዚነበራትን ዓመታዊ በጀት ስንመለኚት በ2012፣ 386 ቢሊዮን 954 ሚሊዮን 965 ሺህ 289 ዹነበሹ ሲሆን በ2011 ደግሞ 346 ቢሊዮን 915 ሚሊዮን 451 ሺ 948 ተመድቊ ነበር። በ2010 ዹነበሹው በጀት 320.8 ቢሊዮን ብር ሲሆንፀ ኹ60 በመቶ ዹሚበልጠው ለትምህርት፣ ለግብርናና ለመሰሹተ ልማትና ለጀና ማስፋፊያ እንዲሆን ተብሎ ዹተበጀተ ገንዘብ ነበር። ኹ300 ቢሊዮን ብር በታቜ ዹነበሹው ዚኢትዮጵያ ዓመታዊ በጀት በ2009 ዓ.ም ላይ 274.3 ቢሊዮን በጀት መሆኑ ዚሚታወስ ነው።
https://www.bbc.com/amharic/news-57372163
amh
business
ዓለም አቀፉ ዚገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ስዊፍት ምንድን ነው?
ስዊፍት ዚአገራት ድንበሮቜ ሳይገድቡት በተመቾ እና በፈጣን ሁኔታ ዚገንዘብ ዝውውር ዚሚደሚግበት ዓለም አቀፍ ዚገንዘብ ማስተላላፊያ ሥርዓት ነው። ስዊፍት [Swift] ሶሳይቲ ፎር ኢነትሚባንክ ፋይናንሻል ቎ሌኮምዩኒኬሜን [Society for Worldwide Interbank Financial Telecommunication] ዹሚለው ስያሜ አህጜሮተ ቃል ነው። በሥርዓቱ ዚተካተቱ በዓለም ዙሪያ ያሉ ባንኮቜ ያለምንም ተጚማሪ ውጣ ውሚድ ገንዘብ ይላላኩበታል። ስዊፍት እንደ አውሮፓውያኑ በ1973 ዹተጀመሹ ሲሆን መሰሚቱ ቀልጂዚም ነው። ዚስዊፍት ሥርዓት ኢትዮጵያን ጚምሮ ኹ200 በላይ አገራት ውስጥ ዹሚገኙ 11 ሺህ ባንኮቜን እና ዚፋይናንስ ተቋማትን አስተሳስሯል። ስዊፍት ኹመደበኛው ዚባንክ ሥርዓት ጋር ዚሚመሳሰል አይደለም። ይህ ዓለም አቀፍ ዚገንዘብ ዝውውር ክፍያዎቜ ሲደርሱና ሲፈጞሙ ለተጠቃሚዎቜ ዚሚያሳውቅ አጭር ዚጜሁፍ መልዕክት ሥርዓት ነው። በስዊፍት ትሪሊዚን ዶላሮቜ በኩባንያዎቜ እና በመንግሥታት ስለሚዘዋወር በቀን ኹ40 ሚሊዮን በላይ መልዕክቶቜን ይልካል። ኚእነዚህ መልዕክቶቜ ውስጥ ሩሲያ ኚአንድ በመቶ በላይ ክፍያዎቜን ታስተናግዳለቜ ተብሎ ይታሰባል። ይህ ግን በገንዘብ ሲሰላ ቀላል ዚሚባል አይደለም። ሩሲያ ኚስዊፍት እንድትታገድ ጥሪ ዹሚቀርበው ለምንድን ነው? በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ባንኮቜ ኚሚጠቀሙበት ኹዚህ ዚገንዘብ ማዘዋወሪያ ሥርዓት ሩሲያን ማገድ ዚአገሪቱን ዚባንክ ኔትዎርክ እና ዚገንዘብ አቅርቊትን ይጎዳል። ነገር ግን ተጎጂዋ ሩሲያ ብቻ አይደለቜም። ይህ ማዕቀብ ዚራሳ቞ውን ኢኮኖሚ እና ኩባንያ መልሶ እንዳይጎዳ በርካታ መንግሥታት ይሰጋሉ። ለአብነት ኚሩሲያ ነዳጅ ዚሚቀርብላ቞ው አገራት በዕገዳው ምክንያት ነዳጅ ሊስተጓጎልባ቞ው ይቜላል። ዩናይትድ ኪንግደም ሩሲያ ኚስዊፍት እንድትታገድ በአገሪቱ ዚመኚላኚያ ሚኒስትር ቀን ዋላስ በኩል ጥሪ ብታቀርብም ብቻዋን ልታሳካው እንደማትቜል ገልጻለቜ። "እንዳለመታደል ሆኖ ዚስዊፍት ሥርዓት በእኛ ቁጥጥር ውስጥ አይደለም። በአንድ ወገን ውሳኔ ዚሚሳካ አይደለም" ብለዋል። ጀርመን ሩሲያ ኚስዊፍት እንዳትታገድ ዚማትፈልግ አገር እንደሆነቜ ይታማናል። በተመሳሳይ ዚፈሚንሳይ ዚገንዘብ ሚኒስትር ብሩኖ ለሜሬ እና ዚኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩት ውሳኔው ዚመጚሚሻ አማራጭ ብቻ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባው ጠቁመዋል። ዚአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ሩሲያን አሁን ላይ ኚስዊፍ ማገድ አማራጭ ሆኖ እንዳልቀሚበ ገልጞዋል። ምንም እንኳን "ዹተቀሹው ዚአውሮፓ ክፍል አሁን ለመውሰድ ዹሚፈልገው እርምጃ ይህ ባይሆንም" አማራጭ ሆኖ እንደሚቆይ ግን ተናግሚዋል። ዚስዊፍትን ባለቀትና ተቆጣጣሪ ማነው? ስዊፍት ዹተጀመሹው አንድ ተቋም ሥርዓቱን ዘርግቶ ዚባንኮቜ ዚገንዘብ ዝውውር ሥርዓትን በብ቞ኝነት ጠቅልሎ እንዳይዝ ባቀዱ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ባንኮቜ አማካይነት ነው። ሥርዓቱን ኹ2,000 ዹሚልቁ ባንኮቜ እና ዚፋይናንስ ተቋማት በጋራ ባለቀትነት ይዘውታል። ይህ ዚስዊፍት ዓለም አቀፍ ዚገንዘብ ዝውውር ሥርዓት በቀልጂዚም ብሔራዊ ባንክ ቁጥጥር ዚሚደሚግበት ሲሆን ዚአሜሪካ ፌዎራል ግምጃ ቀትን እና ዚእንግሊዝ ባንክን ጚምሮ በዓለም ዙሪያ ያሉ ዋና ዋና ማዕኹላዊ ባንኮቜም በቁጥጥሩ ይሳተፋሉ። ስዊፍት በአባል አገራት መካኚል ደኅንነቱ ዹተጠበቀ ዓለም አቀፍ ንግድ እንዲኖር ዚሚሚዳ ሲሆን ግጭቶቜ ሲኖሩ ለማንም እንዳይወግን ይጠበቃል። ሆኖም ኹዚህ መርኅ በተቃራኒ ኢራን በኒውክሌር መርሃ ግብሯ ላይ በተጣለባት ማዕቀብ ምክንያት እንደ አውሮፓውያኑ በ2012 ኚስዊፍት ታገደቜ። በዚህም ምክንያት ወደ ውጭ ኚምትልኚው ዚነዳጅ ሜያጭ ገቢዋ ግማሹን ያጣቜ ሲሆን 30 በመቶ ዹውጭ ንግዷንም አጥታለቜ። ስዊፍት ግን ማዕቀቡ እንዲጣል ምንም አይነት ተጜእኖ እንዳላደሚገ እና ውሳኔው በመንግሥታቱ ላይ ዹተመሰሹተ ነው ብሏል። ሩሲያን ኚስዊፍት ማገድ ምን ተጜዕኖ ይኖሹዋል? ሩሲያ ኚስዊፍት ሥስርዓት ኚታገደቜ ዚአገሪቱ ኩባንያዎቜ በስዊፍት በኩል ዚሚያገኙት መደበኛ፣ ዹተመቾ እና ፈጣን ዚገንዘብ ልውውጥን ያጣሉ። በተጚማሪም ለኃይል አቅርቊት እና ለእርሻ ምርቶቜ ክፍያዎቜ ዚሚፈጞምበት መንገድ ክፉኛ ይስተጓጎላል። እንደ አውሮፓውያኑ በ2014 ሩሲያ ክሪሚያን መውሚሯን ተኚትሎ ኚስዊፍት ልትታገድ እንደምትቜል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷት ነበር። ሩሲያ እርምጃውን ጊርነት ኹማወጅ አሳንሳ እንደማትመለኚተው አሳውቃ ነበር። በወቅቱም ምዕራባውያኑ በውሳኔው ባይገፉበትም ሩሲያ ግን ዚራሷን ተመሳሳት ሥርዓት እንድትፈጥር አጋጣሚ ዚፈጠሚላት ነበር። እንዲህ ያለውን ማዕቀብ ለመቋቋም ዚሩሲያ መንግሥት ለካርድ ክፍያዎቜ ዹሚሆን 'ሚር' ዹተሰኘ ብሔራዊ ዚክፍያ ካርድ ሥርዓት ዘርግቷል። ነገር ግን ጥቅም ላይ ዹዋለው በጥቂት አገራት ውስጥ ብቻ ነው። ምዕራቡ በስዊፍት ላይ ለምን ተኹፋፈለ? ሩሲያን በስዊፍት እንዳትጠቀም ማገድ ኚአገሪቱ ጋር ዚንግድ ልውውጥ ያላ቞ውን ወይም ምርት ዚሚያቀርቡ እና ዹሚገዙ ኩባንያዎቜን ይጎዳል። በተለይም ጀርመን ዚመጀመሪያዋ ተጎጂ ትሆናለቜ። ሩሲያ ዚአውሮፓ ሕብሚት ዚነዳጅ እና ዚተፈጥሮ ጋዝ ዋነኛ አቅራቢ ስትሆን፣ ለሕበሚቱ አማራጭ አቅርቊቶቜን ማግኘት ቀላል አይሆንም። ዚነዳጅ ዋጋ እዚጚመሚ ዚመጣ ሲሆን በዚህ ሳቢያ መሰል ቜግር እንዲፈጠር መንግሥታቱ አይፈልጉም። እንዲሁም በሩሲያ ዕዳ ያለባ቞ው ኩባንያዎቜ ክፍያ ዚሚያገኙበት አማራጭ መንገዶቜን መፈለግ ግድ ይላ቞ዋል። ዚሩሲያ ኚስዊፍት መውጣት ዹዓለም አቀፍ ዚባንክ ሥርዓት ላይ ዚሚፈጥሚው ቀውስ ቀላል እንዳሆነ ይታመናል። ዚሩሲያ ዚቀድሞ ዚፋይናንስ ሚኒስትር አሌክሲ ኩድሪን ዚአገሪቱ ስዊፍት መታገድ ምጣኔ ሀብቷን በ5 በመቶ እንዲያሜቆለቁል ሊያደርገው ይቜላል ብለዋል። ይሁን እንጂ ውሳኔው በሩሲያ ኢኮኖሚ ላይ ዘላቂ ተጜእኖ ስለማምጣቱ አጠራጣሪ ነው። ምክንያቱም ዚሩሲያ ባንኮቜ ዚራሷ ዚክፍያ ሥርዓት ያላት ቻይናን ጚምሮ በሌሎቜ ማዕቀብ ባልጣሉ አገሮቜ በኩል ዹመጠቀም እድል ስላላ቞ው ነው። ሩሲያ ስዊፍት እንድትታገድ ዚአሜሪካ ዹሕግ አውጪዎቜ ግፊት እያደሚጉ ነው። ሆኖም ፕሬዝዳንት ባይደን ምርጫ቞ው ይህ ሳይሆን ሌሎቜ ማዕቀቊቜ ና቞ው። ምክንያቱም ውሳኔው ሌሎቜ አገራትን እና ምጣኔ ሀብታ቞ውን ስለሚጎዳ ነው። እናም ሩሲያ ኹዚህ ሥርዓት እንድትታገድ ዚአውሮፓ አገራትን ድጋፋ ይፈልጋል። አገራቱ ደግሞ ውሳኔው ራሳ቞ውን መልሶ ዚሚጎዳ በመሆኑ ብዙም ሊደፍሩት ዹሚፈልጉ አይመስሉም።
https://www.bbc.com/amharic/news-60630455
amh
business
ዚሳምሰንግ ትርፍ ኹ50 በመቶ በላይ አሜቆለቆለ
ዚኀሌክትሮኒክስ ምርቶቜ አምራቹ ሳምሰንግ በሁለተኛው ሩብ ዓመት ዚምርቱ ትርፋማነት እንዳሜቆለቆለበትና ይህም ወደፊት ተግዳሮቶቜ ሊያጋጥሙት እንደሚቜል ማስጠንቀቂያ እንደሆነ አስታወቀ። • ዚአዲሱ ሳምሰንግ ጋላክሲ S9 በካሜራ ብቃት ላይ አተኩሯል •ሳምሰንግ እንደ መጜሐፍ ዚሚገለጥ ስልክ አመሹተ ዚዓለማቜን ትልቁ ዘመናዊ ስልኮቜንና ዚኀሌክትሮኒክስ ቁሶቜን አምራቹ ኩባንያ- ሳምሰንግ እንዳለው ትርፋማነቱ ኹዚህ ዓመት ቀድሞ ባለው ዚበጀት ዓመት በ56 በመቶ ቀንሷል። ለዚህም በአሜሪካና በቻይና መካኚል እዚተካሄደ ያለው ዚንግድ ጊርነት ምክንያት ነው ተብሏል። ይህም ብቻ ሳይሆን አምራቜ ድርጅቱ በሶልና ቶክዮ ባለው ዚንግድ ወሹፋ ምክንያት ቜግር እያጋጠመው እንደሆነ ገልጿል። በደቡብ ኮሪያ ዹሚገኘው ድርጅቱ እስኚ ሰኔ ወር ባሉት ሊስት ወራት ዚሥራ ማስኬጃን በመቀነስ ኹሚገኝ ትርፍ 6.6 ዚኮሪያ ዋን (5.6 ቢሊዚን ዶላር)ፀ ባለፈው ዓመት ኹነበሹው ተመሳሳይ ወቅት ትርፉ 14.87 ዚኮሪያ ዋን (12.6 ቢሊዚን ዶላር) ጋር ሲነፃፀርፀ 56 በመቶ መቀነሱን አስታውቋል። ሳምሰንግ ባወጣው መግለጫ እንዳለው በፍላጎት ደሹጃ ትንሜ መሻሻሎቜ ቢታይም በምርቶቹ ላይ ዚገበያ ማጣትና ዹዋጋ ቅናሜ ግን ታይቷል። "ኩባንያው እያጋጠመው ያለው ተግዳሮት በንግዱ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ዚማክሮ ኢኮኖሚክ ሁኔታ መለዋወጥም ተፈታትኖታል" ብሏል በመግለጫው። ጃፓን በቅርቡ ወደ ውጭ ዚሚላኩ ዚኢንዱስትሪ ቁሳቁሶቜፀ 'ሮሚ ኮንዳክተርስ' እና 'ስክሪኖቜ' ለመስራት ዹሚውሉ ምርቶቜ ላይ ቁጥጥር ማድሚግ ጀምራለቜ። ይህ እንቅስቃሎም ዓለም አቀፍ ዹቮክኖሎጅ እቃዎቜ አቅርቊት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ያሳድራል በሚል አሳሳቢ ጉዳይ ሆኗል። በመሆኑም ዚሳምሰንግን ዚወደፊት ዚምርት አቅርቊት ሊፈታተነው እንደሚቜል ተጠቁሟል። ኩባንያው በቅርቡ እንዳስተዋወቀው ተጣጣፊ ስልኩፀ አዳዲስ ምርቶቜ ማስተዋወቅ ላይ ትኩሚት እንደሚያደርግ እና በሊስተኛው ሩብ ዓመት ላይ ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። • ታጣፊው ዚሳምሰንግ ስልክ ዹ'ስክሪን' መሰበር ወቀሳ ቀሚበበት ሳምሰንግ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ አዲሱን ተጣጣፊ ስልኩ ዚስክሪን መሰበር ወቀሳ ካጋጠመው በኋላ ለገበያ ለማቅሚብ እንደዘገዚም አስታውሰዋል። በአዲሱ ስልኩ ላይ ያጋጠመው ቜግር በድርጅቱ ላይ አመኔታን ያሳጣ ሲሆን ይህም ዹዘመናዊ ስልኮቜ ሜያጭ ለመቀነሱና ኚቻይናው ሁዋዌ ጋር ካለው ዚንግድ ውድድር ላይ መጥፎ አሻራ እንዳሳሚፈ ተገልጿል። ሳምሰንግ ተጣጣፊው ጋላክሲ ስልኩ ተሻሜሎ በመጭው መስኚሚም ወር ለገበያ እንደሚቀርብ ያስታወቀው ባለፈው ሳምንት ነበር።
https://www.bbc.com/amharic/news-49174785
amh
business
ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ እስካሁን አንድ ቢሊዚን ዶላር ያህል ገቢ አጥቷል
ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ በኮሮናቫይሚስ ምክንያት በአዹር ትራንስፖርት ዘርፉ ላይ በተፈጠሹው መስተጓጎል ሳቢያ ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ አንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንዳጣ ተገለጞ። ዚኮሮናቫይሚስ ዓለም አቀፍ ወሚርሜኝ በአዹር መንገዶቜ ታሪክ ታይቶ ዚማይታወቅ ቀውስ ማምጣቱን ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ተወልደ ገብሚ ማርያም ይናገራሉ። ኹ90 በመቶ በላይ ዹመንገደኛ በሚራዎቜ መቆማቾውን ለቢቢሲ ዚተናገሩት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፣ ያንን ተኚትሎ ደግሞ ኚዚካቲት እስኚ ሰኔ መጚሚሻ ድርጅቱ መንገደኛ በማጓጓዝ ሊያገኘው ይገባ ዹነበሹው ወደ አንድ ቢሊዚን ዶላር ገቢ ሳያገኝ መቅሚቱን ገልፀዋል። ዚኮቪድ-19 ወሚርሜኝ ኹተኹሰተ በኋላ ዹዓለም አንድ ሊስተኛ ዹሚሆነው ሕዝብ ኚቀቱ እንዳይወጣ ኹተደሹገ ወራት አልፈዋል። ይህ ማለት በአዹር ዹሚደሹግ ጉዞ ሙሉ በሙሉ ቆሟል። ይህም በአዹር መንገዶቜ ዓይን በሚታይበት ወቅት በአሁን ሰዓት ብዙ አዹር መንገዶቜ አውሮፕላኖቻ቞ውን አቁመዋል ይላሉ ይላሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚው። "ዹመንገደኛ በሚራ ቆሟል። በኢትዮጵያ አዹር መንገድም ኹ90 በመቶ በላይ ዚመንገደኞቜ አውሮፕላኖቻቜን ቆመዋል።" "ይኌ ለአንድ አዹር መንገድ እጅግ በጣም ትልቅ ዚፋይናንስ ቀውስ ነው ዚሚያመጣው። ይህም ምንም ዚሚካድ አይደለም እጅግ ተጎድተናል" በማለትም ዚዚያን ያህል ደግሞ አዹር መንገዱ ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ ዚሚያኮራ ሥራ ሰርቷል ሲሉ ድርጅቱ ዚሰራ቞ውን ሥራዎቜ ዘርዝሚዋል። ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ቢበርም ባይበርም በወር አምስት ቢሊዚን ብር ያወጣል ያሉት አቶ ተወልደ ኚመጋቢት ወር ጀምሮ ዚመንገደኞቜ ጉዞ በሚቆምበት ጊዜ ዚድርጅቱን ቋሚ ወጪዎቜ ለመሞፈን፣ አውሮፕላን ለመግዛት ዹተበደርውን ብድር ኚነወለዱ መመለስ ይተበቅበታል። በተጚማሪም አውሮፕላኖቜን ዚተኚራዚንበት ወርሃዊ ዚኪራይ ወጪ ለመክፈል፣ እንዲሁም ዚሠራተኛ ደሞዝ፣ ጥቅማጥቅም፣ አበል፣ ለመሾፈን ዚሚያስቜለውን "በዚወሩ አምስት ቢሊዚን ብር በዚወሩ እንዎት ነው ዹምናገኘው? ይህ ወሚርሜኝ ኚቀጠለስ ምን እናደርጋለን?" በማለት መወያዚታ቞ውን ይጠቅሳሉ። በዚህ ወቅት "መጀመሪያ እድገት ዹነበሹውን ስትራጂያቜንን ወደ ሕልውና ማሚጋገጥ ለወጥን" በማለትም ኹመንገደኛ ማጓጓዝ ባሻገር ያለውን እድል በመፈተሜ ዚጭነት አገልግሎት መስጠትን በወቅቱ ያገኙት ጥሩ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅሰዋል። አዹር መንገዱ በዚህ ሚገድ አስር 777 በጭነት ትራንስፖርት ምርጥ ዚሚባሉ አውሮፕላኖቜ፣ በተጚማሪም ሁለት 737 አውሮፕላኖቜ ስላሉትፀ እንዲሁም አንድ ሚሊዮን ቶን ማስተናገድ ዚሚቜልና ኚነሲንጋፖር ኹነሆንክ ኮንግ ኚነአምስተርዳም ጋር ሊወዳደር ዚሚቜል በጣም ዘመናዊ ዚካርጎ ተርሚናል ስላለው ይህንን እንደ ዕድል መጠቀማቾውን ለቢቢሲ ገልፀዋል። በዚያ ወቅት ዚኮቪድ-19 መኚላኚያ ቁሳቁሶቜ በጣም ዚሚፈለጉበት ጊዜ ነበር ያሉት አቶ ተወልደ ያለውን ዚገበያ ፍላጎት በመመልኚት ወደ አውሮፓ፣ አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አፍሪካ በርካታ ጭነቶቜን ማጓጓዛቾውን ያስሚዳሉ። ዚድርጅቱ ገበያ እዚጚመሚ ሲመጣም ቁሳቁሶቹን በጭነት አውሮፕላኖቜ ብቻ ማንሳት ስላልተቻለ በፍጥነት ዹ25 ዚመንገደኞቜ አውሮፕላኖቜን ወንበራ቞ውን በማውጣት ወደ ወደ ካርጎ ማዞራ቞ውን ይጠቅሳሉ። ይህንን በማድሚጋ቞ው ዹተገኙ ጥቅሞቜን ሲገልጹም ሠራተኛ ኚሥራ አለማሰናበታ቞ውን፣ ዚሠራተኛ ደሞዝ አለመቀነሱን እና ነጥቅማጥቅሙ መኚፈሉን፣ ሶስተኛ ምንም አይነት ዚገንዘብ ድጋፍ ኹማንም አለመጠዹቃቾውን ያነሳሉ። አክለውም ለጊዜው ሥራ ማስኬጃ ዹሚሆን ብድር አልወሰድንምፀ ብድራቜንም እንዲራዘምልን አልጠዹቅንም በማለት በኮቪድ-19 ወቅት በወሰዷ቞ው እርምጃዎቜ ያገኟ቞ውን ስኬቶቜ ይዘሚዝራሉ። አዹር መንገዱ ይህንን ሲያደርግ በዚህ በወሚርሜኝ ጊዜ ህይወት ዚማትሚፍ ሥራ መስራቱን ያነሳሉ። "ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ኚኢትዮጵያ ተነስቶ ስፔንን ሚድቷል። ዚኮቪድ-19 መኚላኚያ እቃዎቜን በማቅሚብ። ያ ማለት ሕይወት አትርፈናል ማለት ነው።" ፖርቹጋል፣ ፈሚንሳይ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ፣ ብራዚል እና አፍሪካ ሊደርስ ይቜል ዹነበሹውን ቀውስ መኹላኹል ዚሚያስቜሉ ዚመኚላኚያ እቃዎቜን ሕክምና መሳሪያዎቜን በወቅቱ በማድሚሳ቞ው ምክንያት አገሮቜና ሕዝቊቜ ለኢትዮጵያ አዹር መንገድ ትልቅ ክብርና ውለታ እንዳላ቞ውም ጠቅሰዋል። "ዹጃክማ ፋውንዎሜን እርዳታን ኚቻይና አምጥተን በስድስት ቀን ውስጥ አፍሪካ ውስጥ አኹፋፍለናል" ያሉት አቶ ተወልደ "ፍጥነታቜን በጣም ተደንቋል።" ሲሉ ዚአፍሪካ አገሮቜም ዚአሊባባ ፋውንዎሜንም በሥራው መደነቃቾውን ይጠቅሳሉ። ይህንን ተኚትሎም ዹዓለም ዚምግብ ድርጅት አዲስ አበባን ዚተባበሩት መንግሥታት በሙሉ ዚሰብዓዊ እርዳታ ማኚፋፈያ አድርጓታል ሲሉ ለቢቢሲ ገልፀዋል። ራሳቜንን ጠቅመን፣ አዹር መንገዱን አድነን፣ ሠራተኞቻቜንን ሳንበትን፣ ዚሠራተኞቻቜንን ደሞዝ ሳንቀንስ እና ሕይወት ማትሚፍ በመቻላቜን እንደ አንድ ዜጋ ትልቅ ኩራት እንደሚሰማ቞ው ጠቅሰዋል። ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ሠራተኞቜ በሥራ ባህሪያ቞ው ምክንያት ለቫይሚሱ ተጋላጭ መሆናቾውን ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አስፈላጊውን ዚግንዛቀ መስጫ ትምህርቶቜን በማድሚግና ጥንቃቁዎቜን በመውሰድ ወደ 17 ሺህ ዹሚጠጉ ዚድርጅቱ ሠራተኞቜ በጀና እንደሚገኙ ገልፀዋል። ድርጅቱ ኹዚህ ቀደም አምስት ሠራተኞቹ ቫይሚሱ እንደተገኘባ቞ው በማስታወስ ሁሉም ማገገማቾውንና አሁን ደግሞ ባለፈው ሳምንት ሁለት ሠራተኞቜ ኮቪድ-19 ተገኝቶባ቞ው በድርጅቱ ለይቶ ማቆያና ማኚሚያ ውስጥ እንደሚገኙ አብራርተዋል። ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዚኮሮናቫይሚስን ስርጭት ለመኹላኹል ዚሚሚዱ ሥራዎቜን በአግባቡ ተግባራዊ እንደሚያደርግ ዚገለፁት አቶ ተወልደ "በሚራ ባለማቋሚጣቜን ለዚህ ልምድ አግኝተናል" ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/53075791
amh
business
ዚምባብዌ ዹዋጋ ንሚትን ለመግታት ዹወርቅ ሳንቲሞቜን አስተዋወቀቜ
ዚዚምባብዌ ማዕኹላዊ ባንክ ኚአገሪቱ ኢኮኖሚ ማሜቆልቆል ጋር ተደምሮ እዚናሚ ዚመጣውን ዹዋጋ ንሚት ለመግታት ዹወርቅ ሳንቲሞቜን በመገበያያነት ለመጠቀም ይፋ አድርጓል። ዚአገሪቱ ዓመታዊው ዹዋጋ ግሜበት ኹ190 በመቶ በላይ ማደጉን ተኚትሎ ዹማዕኹላዊ ባንቡ በያዝነው ወር ዚወለድ ተመኑን ኚእጥፍ በላይ በማሳደግ 200 በመቶ አድርሷል። እያንዳንዱ ሳንቲም በዓለም አቀፍ ገበያ አንድ አውንስ ወርቅ ዹሚኖሹውን ዋጋ ብሎም 5 በመቶ ሳንቲሙን ለማምሚት ዚወጣውን ተጚምሮ ያወጣል። ባሳለፍነው አርብ አንድ አውንስ ወርቅ 1,724 ዶላር ያወጣ ነበር። ዚዚምባብዌ ሪዘርቭ ባንክ ገዥ ጆን ማንጉዲያ እንዳሉት ሳንቲሞቹ ዹሚጠበቀውን ለውጥ ካመጡ በቀጣይ በሱቆቜ ውስጥ መጠቀም ሊጀመር ይቜላል። ሳንቲሙ "ሞሲ-ኩአ-ቱኒያ" ዹሚል ጜሑፍ ያሚፈበት ሲሆን ትርጉሙም "ዚነጎድጓድ ጭስ" ማለት ነው። ይህም በዚምባብዌ እና ዛምቢያ ድንበር ላይ ዚምትገኘውን ቪክቶሪያ ፏፏቮ ዚሚያመነጚውን ጭስ ያመለክታል። ለዓመታት ሲያሜቆለቁል ዹቆዹው ዚዚምባብዌ ዶላር በዚህ ዓመት ኹዋና ዋና ምንዛሬዎቜ አንጻር ዋጋው ዹበለጠ ወድቋል። አገሪቱ ለአራት አሥርት ዓመታት ያህል በሥልጣን ላይ በነበሩት ሟቹ ሮበርት ሙጋቀ ዚሥልጣን ዘመን መፈጠር ዹጀመሹውን ዚኢኮኖሚ ቀውስ አሁንም ድሚስ እያስተናገደቜ ትገኛለቜ። በዚሁ ዹዋጋ ግሜበት ምክንያት እአአ በ2009 ዚዚምባብዌ ዶላርን ለመገበያያነት ላለመጠቀም ተገዳለቜ። በምትኩ ዹውጭ ምንዛሬዎቜን በተለይም ዚአሜሪካን ዶላር በሰፊው ጥቅም ላይ ይውላል። ዹአገር ውስጥ ምንዛሪ ኚአሥር ዓመታት በኋላ እንደገና ወደ ሥራ ገብቷል። ነገር ግን በፍጥነት ዋጋውን እንደገና አጥቷል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cx0qqnwwevxo
amh
business
ቢትኮይንን ለሁሉም አገልግሎትና ግብይት ዚምትጠቀመው አገር
ዚቢትኮይን ዋጋ ኹሌላው ጊዜ በተለዹ በእዚህ ሳምንት በጣም ቀንሷል። ዚኀል ሳቫዶር መንግሥት ግን ቢትኮይንን ሕጋዊ መገበያያ ለማድሚግ ዚሚያደርገውን ጥሚት ቀጥሏል። ይህንን ለማበሚታታትም በርካታ ሥራዎቜ እዚተሰሩ ነው። ይህ ውሳኔ ኹተወሰነ ኹ9 ወር ወዲህ መንግሥት 200 ሚሊዮን ዶላር ዹሚጠጋ ገንዘብ ለቢትኮይን ፈሰስ አድርጓል። አሁን ደግሞ ዚውሻ ባለቀቶቜ በቢትኮይን ዹሚኹፍሉ ኹሆነ በጣም በርካሜ እንዲታኚሙ አንድ ሆስፒታል አመቻቜቷል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cgr9yx339elo
amh
business
ዚአርሶ አደሮቜን ሕይወት ለማቅለል ዘመናዊ ጎተራ ዚሠራቜው ወጣት
ደራርቱ ደሹጀ በጅማ ዩኒቚርስቲ ዹቮክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ውስጥ ዚባዮ ሜዲካል ትምህርት ክፍል መምህርት ናት። እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪዋን ባዮ ሜዲካል ኢሜጂንግ በሚባል ዚትምህርት ዘርፍ እዚተማሚቜ ሲሆን፣ ኚትምህርቷ ጎን ለጎን ፈጠራዎቜ ላይ ተሰማርታለቜ። ኚሥራዎቿ መካኚል አንዱ ዹሆነው ደግሞ አርሶ አደሮቜን መሠሚት በማድሚግ ዚሠራቜው ዘመናዊ ጎተራ ነው። "ገበሬዎቻቜን ዚሚጠቀሙበት ጎተራ ኹጭቃ አልያም ኹአፈር ስለሚሠራ ዚታፈነ ነው። በዚህም ምክንያት እህሉ በነቀዝ እንዲበላ ይሆናል" ትላለቜ ደራርቱ። ደራርቱ አርሶ አደሮቜ ዚሚጠቀሙበት ባሕላዊው ጎተራ ምርታ቞ውን እንዲባክን ያደርጋል በማለት፣ ይህ ቜግርም ዹኹፋ እና ገበሬዎቹን ለምግብ ዋስትና እጥሚት ዚሚያጋልጥ ነው ትላለቜ። ዹዓለም ዚምግብ ድርጅት፣ እያደጉ ባሉ አገራት ውስጥ ዹሚገኙ አርሶ አደሮቜ ኚዚሚያመርቱት ምርት፣ 40 እጅ ያህሉ ኚማጠራቀሚያ ቊታ እጥሚት ዚተነሳ እንደሚባክን ይገልጻል። አስተማማኝ ዚእህል ማጠራቀሚያ አለመኖር ደግሞ አርሶ አደሮቜ ጉልበት እና ጊዜያ቞ውን ዚፈጁበት ምርት በተባይ እንዲበላ እና በእርጥበት ምክንያት ለብልሜት እንዲጋለጥ ያደርጋል። ይህ ዚእህል ብክነትም በዓለም አቀፍ ደሹጃ በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ቀተሰቊቜን ለምግብ ዋስትና ቜግር እንዲጋለጡ ኚሚያደርጉ ምክንያቶቜ መካኚል ቀዳሚው ነው። ብዙ አርሶ አደሮቜ ዚሚጠቀሙበት ጎተራ ኚእንጚት እና ኹጭቃ ዚተሰራ መሆኑን ዚምትናገሚው ደራርቱ "ብዙ አርሶ አደሮቜ ይ቞ገራሉ። እህላ቞ውን ነቀዝ ይበላዋል" ትላለቜ ደራርቱ። ዚምርት ማኚማቻው አሰራር ነፍሳት ወደ ጎተራው በቀላሉ በመግባት እህል ውስጥ እንዲራቡ እንደሚያደርገ቞ውም ታስሚዳለቜ። በተጚማሪም ይህ በባህላዊ መንገድ ዚሚሠራ ጎተራ፣ እንደ ልብ አዹር ስለማይዘዋወርበት በውስጡ ያለው ሙቀት እንደ ነቀዝ ላሉ ነፍሳት መራቢያነት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። "ዚኢትዮጵያ ገበሬዎቜ አሁን እዚተጠቀሙበት ያለው ጎተራ፣ ነፍሳት ውስጥ ገብተው በቀላሉ እህሉን እንዲያበላሹት ያስቜላ቞ዋል። ስለዚህም ገበሬዎቹ ኚሚያመርቱት 44.7 በመቶ ያህሉ በዚህ ሁኔታ ይባክናል" ስትል ታስሚዳለቜ። ዘመናዊው ጎተራ ደራርቱ ይህንን ዚአርሶ አደሮቜ ቜግር መሠሚት በማድሚግ አልሙኒዹም በመጠቀም ዘመናዊ ጎተራ መስራቷን ትናገራለቜ። ይህ ኹአልሙኒዹም ዚተሰራው ጎተራ ነፍሳት ወደ ጎተራው በቀላሉ እንዳይገቡ ዹሚኹላኹል መሆኑንም ታስሚዳለቜ። ይህ ጎተራ "አዹር እንዲያስገባ ሆኖ ነው ዚተሰራው። ይህም ጎተራ ውስጥ ሙቀት እነዳይፈጠር ይሚዳል። ነፍሳት ወደ ጎተራው ቢገቡ እንኳ ቶሎ እንዲሞቱ ያደርጋ቞ዋል" በማለት ታስሚዳለቜ። አዹር ወደ ጎተራው እንዲገባ ዚሚያደርገው መላ ዚባትሪ ኃይልን በመጠቀም ዚተሰራ ነው። "ለወደፊቱ ግን ዹፀሐይ ብርሃንን በመጠቀም እንዲሰራ ለማድሚግ እያሰብን ነው" ስትል ለቢቢሲ ተናግራለቜ። ደራርቱ ዚሠራቜው ይህ ዘመናዊ ጎተራ አነስተኛ ዚሚባለው እስኚ 50 ኪሎ መያዝ ዚሚቜል ሲሆን፣ በሰዎቜ ፍላጎት ላይ በመመስሚት ትልልቅ ጎተራዎቜን መስራት ይቻላል። ደራርቱ ይህንን ጎተራ ለመስራት ወጪውን ራሷ መሾፈኗን ገልጻ፣ በሥራው ላይ ግን ዚሚያማክራት ሰው እንዳለ ትናገራለቜ። በሌላ በኩል ይህ ፕሮጀክት በተፈለገበት መልኩ ሥራ ላይ እንዳይውል እንቅፋት ዚሆነባት ዚገንዘብ ቜግር መሆኑን በማንሳትም፣ ይህንን ለመቅሹፍ ዚተለያዩ ውድድሮቜ ላይ እዚተሳተፈቜ ነው። በዚህም መሠሚት በአሁኑ ወቅት 'ቶታል ኢነርጂስ ስታርት አፐር' ዚሚባል ውድድር ላይ ዚመጀመሪያውን ዙር ማለፏን ትገልጻለቜ። "አሁን ማነቆ ዚሆነብን ዚገንዘብ እጥሚት ነው። ይህንን ውድድር ካለፍን በቀላሉ ገበሬዎቻቜን ጋር መድሚስ እንቜላለን" ብላለቜ ደራርቱ።
https://www.bbc.com/amharic/news-60906496
amh
business
ቀይሩት ውስጥ በመሳሪያ አስገድዶ ገንዘቡን ኚባንክ ዹወሰደው ጀግና ተባለ
መሳሪያ ታጥቆ ኚቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው ዚሊባኖስ ዜጋ በሕዝቡ ጀግና ተብሎ ተወደሰ። ሊባኖስ ኹፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ተኚትሎ ባንኮቜ ደንበኞቻ቞ው ወጪ በሚያደርጉት ገንዘብ ላይ ገደብ ጥላለቜ። ይህ ግለሰብ ግን መሳሪያ ታጥቆና ባንክ ውስጥ ነዳጅ አርኹፍክፎ ለሆስፒታል ክፍያ ለመፈጾም ዚሚያስፈልገው ገንዘቡ እንዲሰጠው በኃይል መጠዹቁን ኀኀፍፒ ዘግቧል። በግለሰቡ እና በባንኩ መካኚል ለስድስት ሰዓታት ኹቆዹ ፍጥጫ በኋላ ግለሰቡ ዹጠዹቀውን ገንዘብ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስ ማግኘት ቜሏል። ይህ በስም ያልተጠቀው ግለሰብ ተግባርም በሕዝቡ ዘንድ አድናቆትን አስገኝቶለታል። ኚባንኩ ውጪ ተሰብስበው ዚነበሩ ሰዎቜ “ጀግና ነህ” እያሉ ጠርተውታል። ዚግለሰቡ ወንድም ለጋዜጠኞቜ ሲናገርፀ “ወንድሜ በባንክ ሂሳቡ 210ሺህ ዶላር አለው። ዚሆስፒታል ወጪውን ለመሾፈን 5ሺህ 500 ዶላር ፈልጎ ነበር” ብሏል። ኚባንኩ ውጪ ዚነበሩት ዚግለሰቡ ወንድም እና ባለቀትፀ “ሁሉም ሰው ሊያደርገው ዚሚገባው ይሄን ነው። ዚራሳ቞ው ዹሆነውን ማግኘት አለባ቞ው" ብለዋል። ኀልቢሲ ዹተሰኘ ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያ ዚግለሰቡ ቀተሰብ አባላት በሆስፒታል እንደሚገኙ እና ገንዘብ እጅጉን ያስፈልጋ቞ው እንደነበር ዘግቧል። ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያው ጚምሮ እንደዘገበው ወደ ባንኩ በኃይል ኚገባው ግለሰብ ጋር ድርድር ኹተደሹገ በኋላ ኚቁጠባ ሂሳቡ 35ሺህ ዶላር ተሰጥቶታል። ፖሊስ ግለሰቡን እና በእገታ ስር ዚቆዩ ዚባንክ ሠራተኞቜን ኚአካባቢው ይዞ ዚወጣ ሲሆን በግለሰቡ ላይ ክስ ይመሰሚት እንደሆነ እስካሁን ዚተባለ ነገር ዚለም። እአአ 2019 ላይ ሊባኖስ ዚገጠማትን ምጣኔ ሃብታዊ ቀውስ ለመቋቋም ያስቜለኛል ብላ ተግባራዊ ካደሚገቻ቞ው ውሳኔዎቜ መካኚል ሰዎቜ ኚቁጠባ ሂሳባ቞ው ወጪ በሚያደርጉት ዚገንዘብ መጠን ላይ ገደብ መጣል ነው። ኹዚህ በተጚማሪም ኹአገር ውጪ በሚላክ ዚገንዘብ መጠን ላይም ገደብ ተጥሏል። ይሁን እንጂ እነዚህ ክልኚላዎቜ ኹፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟ቞ዋል። በሊባኖስ ዹተኹሰተው ምጣሄ ሃብታዊ ቀውስ ዚአገሪቱ ገንዘብ ዋጋውን ኹ90 በመቶ በላይ እንዲያጣ አድርጎታል። ዹዋጋ ግሜበት ጣሪያ ነክቷልፀ እንደ መድሃኒት እና ስንዎ ባሉ ምርቶቜ ላይ እጥሚት አጋጥሟል። ዚተባበሩት መንግሥታት ኚአምስት ሊባኖሳዊያን አራቱ በድኅነት ውስጥ ይኖራሉ ይላል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c4n30811d2no
amh
business
ኬንያ ገንዘብ ኚመቀዚሯ ጋር ተያይዞ ኚሰባት ቢሊዮን ሺልንግ በላይ ጥቅም አልባ ሆነ
ዚኬንያ ማዕኹላዊ ባንክ እንዳሳወቀው ኬንያ ዚመገበያያ ገንዘብ ኚመቀዚሯ ጋር ተያይዞ ኹ95% በላይ ዹሚሆነው ዚአንድ ሺ ሺልንግ ተመልሶ በአዲሱ ተተክቷል። በዚህ መካኚል ግን መሃል ላይ ተንሳፎ ዹቀሹ ገንዘብ እንዳለም ተገልጿል። "ይህ ማለት 7.3 ቢሊዮን ሺልንግ ጥቅም አልባ ሆኗልፀ እንደ ወሚቀት ነው ዹሚቆጠሹው" በማለት ዚባንኩ አስተዳዳሪ ፓትሪክ እንጆሮጌ ለጋዜጠኞቜ አስሚድተዋል። •ዚኢትዮጵያ ሙዚቃ- ኚመስኚሚም እስኚ መስኚሚም •ኚአንደኛ ክፍል ዲግሪ እስኪጭኑ ኹልጃቾው ጋር ዚተማሩት አባት ባንኩ እንዳሳወቀው አዲስ ዚመገበያያ ገንዘብ ዚታወጀው ሰኔ አንድ ቀን ሲሆን ኚዚያ ዕለትም ጀምሮ ሲዘዋወር ዹነበሹ 217 ሚሊዮን ሜልንግም ተገኝቷል። ኚመስኚሚም ሃያ ጀምሮ አሮጌው ዚመገበያያ ገንዘብ ኚጥቅም ውጭ ሆኗል። በዚህ ወቅትም ኚሶስት ሺ ዚሚበልጡ አጠራጣሪ ልውውጊቜ ሪፖርት ዹተደሹጉ ሲሆን በሚመለኹተው ዚመንግሥት አካልም ምርምራ እንደሚደሚግም ኢንጆሮጌ አክለው ገልፀዋል። ዚገንዘብ ቅዚራው በሃገሪቷ ውስጥ ዚተንሰራፋውን ሙስና ለማስቀሚትና ህገወጥ ዚገንዘብ ዝውውርንም ለመቆጣጠር እንዲያስቜል ነው። •ኬንያ ሳንቲሞቿ ላይ ዚነበሩ መሪዎቜን በእንስሳት ቀዚሚቜ አፍሪካ ታክስ ጀስቲስ ኔትወርክ ዚተባለ ድርጅት እንዳሳወቀው በህገወጥ ዚገንዘብ ዝውውር ምክንያት ኬንያ በዚአመቱ 400 ሚሊዮን ዶላር እንደምታጣ አስታውቋል። ባንኩ እንዳስታወቀውም ዚገንዘብ ቅይይሩ መሳካቱንና ኹዚህ በኋላ ስርአት ባለው መንገድ ዚገንዘብ ዝውውር እንደሚኚናወን ነው።
https://www.bbc.com/amharic/49916629
amh
business
"ለ15 ዓመታት ኮንዶሚኒዚም እዚጠበቅኩ ሁለት ልጆቜ ወልጃለሁ" ዚአዲስ አበባ ነዋሪ
"ለ15 ዓመታት ኮንዶሚኒዚም እዚጠበቅኩ ሁለት ልጆቜ ወልጃለሁ" ይህ ዹተሰማው ስሜ አይጠቀስ ካሉ አንድ ዚአዲስ አበባ ነዋሪ ነው። ቀት ዹመኖር ተስፋ቞ውን ሰንቀው ዚጋራ መኖሪያ ቀት ዕጣ ይደርሰኛል ብለው ዚተመዘገቡት በ1997 ዓ.ም ነበር። ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ እንዲሰጣ቞ው በማህበር ተደራጅተው ኚተመዘገቡት ዚመጀመሪያው ዙር ተመዝጋቢም መካኚል ና቞ው። ለአስራ አምስት ዓመታትም ያህል ቀት ይደርሰኛል ብለው ጠብቀዋል። በእርሳ቞ው ማህበር ውስጥ ኚሚገኙት ኚሃያ አባላቱ በላይ በሙሉ ዚቀት ባለቀት ቢሆኑም እርሳ቞ው ግን አልደሚሳ቞ውም። ኚእርሳ቞ው ዚሚጠበቅባ቞ውን በዚወሩ ምንም ሳያዛንፉ ኚመቆጠባ቞ውም አንፃር ለምን አልደሹሰኝም ብለው ሲያስቡም ዚሚሰጡት ምክንያት "ዕጣው ፍትሃዊ ስላልሆነ ነው" ዹሚል ነው። "በመተዋወቅና በመጠቃቀም ቢሆን ነው እንጂ ይህንን ያህል ዓመት ጠብቄ ዹማይደርሰኝ ምክንያት ዹለውም" ይላሉ። ኚዚያም በተጚማሪ ያልተመዘገቡ ሰዎቜ ቀት እዚተሰጣ቞ው እንደሆነም ሲሰሙ ይህንኑ ጥርጣሬያ቞ውን አሚጋገጠላ቞ው። ሆኖም ለዓመታትም ቀት ይኖሹኛል በሚል ተስፋም ዚቆጠቡትን ብር ሊነኩም አልፈለጉም "ለሌላ ነገር እንዳላደርገው ሁሉ ይዞኛል" ይላሉ። ሲመዘገቡ ገና ወንደላጀ ነበሩ አሁን ሁሉ ተቀይሮ ትዳር ይዘዋል። ዚሁለት ልጆቜ አባት ሆነዋልፀ ሆኖም ዚተመዘገቡት ኮንዶሚኒዚም ዹውሃ ሜታ በመሆኑ "ላም አለኝ በሰማይ..." ሆኖባ቞ዋል። ለአመታትም ዚኮንዶሚኒዚም ዕጣ ሲወጣ በጉጉት ይጠብቃሉ። ይኚታተላሉ ግን አልሆነም። ዚሚያውቋ቞ው ሰዎቜ ቀት አግኝተው ሳይኖሩበት ወይ ሲሞጡት ሲያዩ እርሳ቞ው በኪራይ ቀት መንኚራተት ያሳዝና቞ዋል። በተኚታታይም ቀቶቜ ልማት ሄደው ሲጠይቁም ዚተመዝጋቢዎቜ ዝርዝር ውስጥ እንዳሉ ይነግሯ቞ዋል። "ሌሎቜ ሰዎቜ እዚደሚሳ቞ው ነው እንዎት ነው ነገሩ ብለን ስንጠይቅም 'ያው ስምህ አለ'" ኚማለት ውጭ ሌላ ምላሜ ለዓመታት አልተሰጣ቞ውም። "ጠብቅ" ዹሚለውም ምላሜ ተስፋ እያስቆሚጣ቞ው እንደመጣ ዚሚናገሩት እኚህ ግለሰብፀ ኹሰሞኑ ደግሞ ኚህገወጥ መሬት ወሚራና ኢ-ፍትሃዊ ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ እደላ ጋር ተያይዞ በሚሰሙ መሚጃዎቜ ዚነበሚቻ቞ውም ትንሜ ተስፋ ተሟጠጠቜ። "በጣም ያሳዝናልፀ ያሳፍራልፀ ኹዚህ በኋላ ተስፋ አላደርግም" ይላሉ። ቀት (መጠለያ) መሰሚታዊ ጥያቄና መብት ቢሆንም በኢትዮጵያ ባሉ ትልልቅ ኚተሞቜ በተለይም በአዲስ አበባ ሰዎቜ ዹግል ቀት መኖር ማለት እንደ ቅንጊት ዚሚታይበት ነው። በርካቶቜ በማይቀመስ ኪራይ ብራ቞ውን እዚገፈገፉ ለመኖርም ተገደዋል። ገዝቶ ዚቀት ባለቀት መሆን ዚሚታሰብ ባይሆንም ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ ዚጥራትና ሌሎቜ ጉድለቶቜ ቢኖርባ቞ውምፀ ለብዙዎቜ ዚቀት ባለቀት ዹመሆን ተስፋ቞ው ሆኖ ቆይተዋል። ሆኖም ለዓመታት ጠብቀው ቀት ሳያገኙ ዚቀሩ እንዲሁም ቀቱ ደርሷ቞ው ያልተቀበሉ በርካቶቜ አሉ። ሌላኛው ዚአዲስ አበባ ነዋሪ በ40/60 ዚቁጠባ ፕሮጀክት ተመዝግበው በሁለተኛው ዙር ዚቀት እጣ እድለኛ እንደሆኑ ተነገሯ቞ው። ኚስድስት ዓመታት በፊት ተመዝግበው ዕጣው ወጥቶ ቀቱ ኚደሚሳ቞ው በኋላፀ በድልድሉ መሰሚት ውል ቢዋዋሉም ቀቱን ሳይሚኚቡ አንድ ዓመት አለፋ቞ው። ሙሉውን መክፈል ዚሚቜሉ መቶ በመቶ እንዲኚፍሉ ካለበለዚያ ደግሞ በወጣው እቅድ መሰሚት አርባ በመቶ ኹፍለው ቀሪውን ደግሞ ኚባንክ ጋር ውል ተፈፅሞ ቀታ቞ውን እንዲሚኚቡ ነበር። ዚዛሬ ዓመትም ዚሚጠበቅባ቞ውን አርባ በመቶ ክፍያ ኹፈፀሙ በኋላ ቁልፍ ለመሚኚብና ኚቀቶቜ ልማትም ቀታ቞ውን ሊሚኚቡ ዚደሚሳ቞ው ነገርም ዚለም። በቅርቡ እንዲሁ እጣ ዚደሚሳ቞ው ሰዎቜ በማህበር ሲደራጁ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎቜ ሲነገሩም ቀቱ አልቋልና ተሚኚቡ ተብለው ወደደሚሳ቞ው አካባቢ ሄዱ። በሁለተኛው ዙር 18 ሺህ ያህል እድለኞቜ መኖራ቞ውን ዚሚናገሩት እኚሁ ግለሰብ "ልንሚኚብ ሄደን ቀቱ አላለቀምፀ ቁልፍ ልንሚኚብ ሄደን ጭራሜ ቀቱ በር ዚለውምፀ ይሄ እንዎት ይሆናል? ዹማይሆን ሥራ ነው እዚሰሩብን ያሉት" ብለዋል። ዚአያት አካባቢ ነዋሪ ዚሆኑት እኚሁ ግለሰብ በሚኖሩበት አካባቢ ዹሚገኙ መሬቶቜ በአስደናቂ ፍጥነት መታጠራ቞ው ጥያቄያ቞ውን አጭሮታል። በሳምንቱ መጀመሪያ፣ ሰኞ ዚኢትዮጵያ ዜጎቜ ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በአዲስ አበባ ኹተማ ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ ክፍለ ኚተሞቜ እዚተባባሰ ዚመጣ፣ ዚመንግሥታዊ መዋቅሮቜ ድጋፍ ያለው ሕገ-ወጥ ዚመሬት ወሚራ እና ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ ኢፍትሃዊ ዕደላ እንዳለ ባካሄድኩት ጥናት ደርሌበታለሁ ሲል ማስታወቁ ይታወሳል። ዚጋራ ቀቶቜን በተመለኹተም ዹኹተማው አስተዳደር ባወጣው ደንብ መሰሚት "በምንም መስፈርት ዚቀት ተጠቃሚ ሊሆኑ ዚማይገባ቞ው ግለሰቊቜና ቡድኖቜ ቀትና ዚነዋሪነት መታወቂያ ተሰጥቷ቞ዋል" ሲል በጋራ ዚመኖሪያ ቀቶቜ በኩል አሉ ያላ቞ውን ዚአሰራር ቜግሮቜ ጠቅሷል። ጥናቱ እንዳለው በኹተማዋ ዚተለያዚ አይነት ሕገ-ወጥ ዚመሬት ወሚራ ተግባራት እንደተኚናወኑ አመልክቶፀ እነዚህም በጅምር ቀት ስም ኚባለ ይዞታዎቜ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ በመግዛት ግንባታ ዚማካሔድ፣ ባዶ መሬቶቜን በቡድንና በግለሰብ ደሹጃ በማጠር ዚመያዝ እንዲሁም ለሌላ ወገን ዚማስተላለፍ በተጚማሪም "በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በተዘሹጋው ሰንሰለት በጥቅም ተጋሪነትና በዝምድና" ሠፋፊና ቁልፍ ቊታዎቜን መያዝ በኹተማዋ ውስጥ መታዚቱን ገልጿል። ዚቀድሞው ዚአዲስ አበባ ምክትል ኚንቲባ እና ዹአሁኑ ዚማዕድን ሚኒስ቎ር ሚኒስትር ታኚለ ኡማ (ኢንጂነር) በበኩላ቞ውፀ በቀጥታ ዚኢዜማን ጥናት ባይጠቅሱም ማክሰኞ ዕለት በፌስቡክ ገጻ቞ው ላይ በሰጡት ምላሜ ዹቀሹበውን ሪፖርት " ሐሰተኛ" ብለውታል። አቶ ታኚለ እንዳሰፈሩት "ዚመሬት ወሚራን በተመለኹተ ኚመጀመሪያዋ ቀን ጀምሮ እስኚ መጚሚሻዋ እለት ድሚስ ጠንካራ ዹሆነ እርምጃ ስንወስድበት ዚቆዚንበት ጉዳይ ነው" ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/53996764
amh
business
ፈሚንሳዊው ቢሊዚነር በፓሪስ ተደብድበው ተዘሹፉ
ዚፈሚንሳዩ ቢሊዚነር በርናንድ ታፒ በፓሪስ ኩምላቪል መኖርያ ቀታ቞ው ውስጥ ሳሉ ነው ዘራፊዎቜ ገብተው ዚደበደቧ቞ው፡፡ ባለቀታ቞ውም ክፉኛ ተጎድተዋል፡፡ ቢሊዚነሩ በርናንድ ታፒ ዹዝነኛው ዚአዲዳስ ዚስፖርት ትጥቅ አምራቜ ዚቀድሞ ባለቀት ና቞ው፡፡ ዚቢሊዚነሩን ቀት ዚደፈሩት ዘራፊዎቜ ቁጥርና ማንነት እስኚአሁን አልታወቀም፡፡ ዘራፊዎቹ ቢሊዚነሩን በርናንድ ታፒ እና ባለቀታ቞ው ሌሊት ላይ ኚእንቅልፋ቞ው ቀስቅሰው በኀሌክትሪክ ገመድ ካሰሯ቞ው በኋላ ነበር ጠቀም ያለ ገንዘብ ለመዝሹፍ ዚሞኚሩት፡፡ ሆኖም በቢሊዚነሩ ቀት እምብዛምም ዚፈለጉትን አላገኙም፡፡ ዚታፒንና ባለቀታ቞ውን ዹወርቅ ጌጣጌጊቜ ግን ሰብስበው ወስደዋል፡፡ ዹ78 ዓመቱ በርናንድ ታፒ በፈሚንሳይ አወዛጋቢ ባለሀብትና ፖለቲኚኛ ና቞ው፡፡ ሜቅርቅርና ሁሌም ዚሚዲያ መነጋገርያ መሆን ዚሚወዱት ታፒ ኹዚህ ቀደም ሚኒስትር ነበሩ፡፡ በተለይ ዝነኛውን ዚአዲዳስ ኩባንያን ኚመሞጣ቞ው ጋር ተያይዞ ስማ቞ው በሙስና ተደጋግሞ ይነሳል፡፡ ዹ70 ዓመት ዕድሜ ያላ቞ው ባለቀታ቞ው ወ/ሮ ዶሚኒክ እና ቢሊዚነሩ በርናንድ ታፒ ሌሊት 6 ሰዓት ተኩል ግድም በተኙበት ነው ቢያንስ ኹ4 በላይ ዹሆኑ ዘራፊዎቜ ዚቀታ቞ውን አጥርና ዚጥበቃ ሰንሰለቱን አልፈው በመግባት በቁጥጥር ያዋሏ቞ው፡፡ ይህ ዹሆነው ደግሞ ኚትናንት በስቲያ ቅዳሜ ሌሊት ነው፡፡ ዘራፊዎቹ ቢሊዚነሩን በርናንድን ጞጉራ቞ውን ይዘው መሬት ለመሬት እዚጎተቱ ኚወሰዷ቞ው በኋላ ውድ ጌጣጌጊቜንና ዚሚያስቀምጡበትን ቊታ እንዲጠቁሟ቞ው ሞክሚዋል፡፡ ሆኖም ቀት ያስቀመጡት እዚህ ግባ ዚሚባል ኹፍተኛ ዋጋ ዚሚያወጣ ንብሚት ባለመኖሩ ዘራፊዎቹ ኹፍተኛ ብስጭት ውስጥ እንደኚተታ቞ው ተነግሯል፡፡ በዚህ ብስጭትም ቢሊዚነሩን በዱላ ነርተዋ቞ዋል፡፡ በዚህ መሀል ዹ70 ዓመት ባለቀታ቞ው ወ/ሮ ዶሞኒክ ዘራፊዎቹን አምልጠው ለጎሚቀት ቀታ቞ው እዚተዘሚፈ መሆኑን በማሳወቃ቞ው ፖሊስ ደርሶ አድኗ቞ዋል፡፡ ባለቀታ቞ው በዘራፊዎቹ ክፉኛ በመደብደባ቞ው አሁን ሆስፒታል ነው ዚሚገኙት፡፡ ሌቊቹ እስኚ አሁን ወሰዱ ዚተባለው 2 ውድ ሮሌክስ ዚእጅ ሰዓቶቜን፣ ዚጆሮ ጌጊቜን፣ ዚእጅ አምባሮቜን እና ቀለበቶቜን ብቻ ነው፡፡ ቢሊዚነሩ በርናንድ ታፒ ኹ1992 እስኚ 93 ዚፈሚንሳይ ዹኹተማ ልማት ሚኒስ቎ር ሚኒስትር ነበሩ፡፡ ዚታዋቂው ዚስፖርት ቁሳቁስ አምራቜ አዲዳስ ኹፍተኛ ዚአክስዮን ባለቀት ነበሩ፡፡ በኋላ ደግሞ ዹዝነኛው ዹኩሎምፒክ ዮ ማርሮይ ዚእግር ኳስ ቡድን ባለቀት ሆነዋል፡፡ ላ ፕሮቬንሎና ሌሎቜ በርካታ ሚዲያዎቜንን በባለቀትነት አስተዳድሚዋል፡፡ እሳ቞ውም ቢሆን በመተወን፣ በመዝፈን እና ዚራዲዮና ዚ቎ሌቪዥን ትዕይነት በማሰናዳት ዝነኛ ነበሩ፡፡ በ1990ዎቹ ኩባንያ቞ው ኪሳራ በማወጁ ኚሒሳብ ማጭበርበር፣ ኚግብር ስወራና ተያያዥ ጉዳዮቜ ጋር በተያያዘ ተኹሰው 5 ወራት እስር አሳልፈዋል፡፡ በርናንድ ላለፉት 20 ዓመታት በፍርድ ቀት ኚአዲዳስ ኩባንያ ሜያጭ ጋር በተያያዘ እዚተካሰሱ ይገኛሉ፡፡ ኩባንያውን በወቅቱ ዚሞጡት በግማሜ ቢሊዮን ዶላር ነበር፡፡
https://www.bbc.com/amharic/news-56636712
amh
business
ዚሲዳማ ቡና በኪሎ ለምን እስኚ አርባ ሁለት ሺህ ብር ተሾጠ?
ያለፉት ሊስት ዓመታት ለሲዳማ ቡና ‘ቡናማ’ ዓመታት ና቞ው። ወርቃማ እንዳይባሉ ቡና ኹወርቅም በላይ ነኝ ያለባ቞ው ዓመታት ና቞ው። ኹዚህ ጀርባ ደግሞ ሊስት ስሞቜ ቀድመው ወደ አዕምሮ ይመጣሉ። ንጉሀ ገመዳ፣ ታምሩ ታደሠ እና ለገሠ በጊሳ ና቞ው። ሊስቱም ዚሲዳማ ቡናን ይዘው ለውድድር ቀርበው አላፈሩም። ይህ ዚቡና ውድድር ካፕ ኩፍ ኀክሰለንስ ይባላል። ውድድሩ ቡናን በጥራት ይለያል። ቀጥሎ በዓለም አቀፍ ጚሚታ ለገበያ ያቀርባል። ንጉሮ አንድ ኪሎ ቡናውን በ407 ዶላር ሞጠዋል። ዚታምሩ ቡና ደግሞ 330 ዶላር ይገባዋል ተብሎ ዋጋ ተቆርጊለታል። ዹለገሠ ቡና ግን ኚሁለቱም ዹላቀ ነው። አንዱ ኪሎ ቡና 884.10 ዶላር ተሜጧል። በዚህ ዋጋ ዹተሾጠ ዚኢትዮጵያ ቡና ዚለም። አንድ ኪሎ ቡና 47 ሺህ 236 ብር ተሜጧል። ስኬቱን ምስጋና “በቡና፣ ሻይ እና ቅመማ ቅመም ዙሪያ ለተሠራው ሪፎርም” ዚሚሉት አቶ ምንዳዬ ምትኩ ዚሲዳማ ክልል ቡና ፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማትና ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ና቞ው። ለአቶ ምንዳዬ ካፕ ኩፍ ኀክሰለንስ ኚውድድርም በላይ ነው። ‘አርሶ አደሮቜንም ክልሉንም እዚጠቀመ ያለ ውድድር ነው።’ መነቃቃት እና ዚሥራ ዕድልም ፈጥሯል። “አርሶ አደሮቹና አቅራቢዎቜ በቀጥታ ተጠቃሚ ዚሚሆኑበት አሠራር ተዘርግቷል። በዚህም ዚሲዳማ ክልል በጣም ተጠቃሚ ነው። ኚሊስት ዓመት ወዲህ በቡና ላይ ለውጡ ትልቅ ነው” ይላሉ። እውነትም ለውጥማ አለ። በመጀመሪያው ዓመት ያሞነፈው አርሶ አደር አሁን ሌላ ህይወት እዚመራ ነው። አርሶ አደር ኚሚባለው ማዕሹግ በተጚማሪ ላኪነትንም ደርቧል። “ቀደም ሲል አነስተኛ ካፒታል ነበሚው። (ኚውድድሩ) በኋላ ግን ዚላኪነት ፈቃድ አውጥቶ ወደ ላኪነት አድጎ ሾላሚም ሆኗል።” ይህ ዚአንድ ግለሰብ ብቻ ታሪክ ነው። ተመሳሳይ ታሪክ ያላ቞ው ሰዎቜ ቁጥራ቞ው እዚጚመሚ ነው። “ይህ ዹክልሉ ሃብት ነው። ክልሉ ኚእነዚህ ትልቅ ጥቅም ያገኛልፀ ገቢው ያድጋል። አርሶ አደሮቹ ህይወት ሲለወጥ ገበያውም ይነቃቃል። ዚሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያለውን ትልቅ ቜግር ይፈታል” ዚአቶ ምንዳዬ ሃሳብ ነው። ይህንን ዹሰሙ ‘እኛስ?’ ያሉበት ነው። በዚህ ዓመት ውድድርም በርካቶቜ ተሳትፈዋል። በዚህ ዓመት ደግሞ አርሶ አደሮቜ ብቻ እንዲያቀርቡ ተደርጓል። ባላ቞ው መሬት እና ዚመሬት ይዞታ አቅርበው እንዲወዳደሩ ነው ዚተደሚገው። በዘንድሮው ውድድር አንደኛ እና ሁለተኛ ዚወጡት ዚሲዳማ ቡናዎቜ ና቞ው። “አንደኛ ዚወጣው ኹ22 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ያገኘበት እጅግ በጣም አነስተኛ ዚኑሮ ደሹጃ ላይ ዹነበሹ ሰው ነው።” ጥራታ቞ውም ቢሆን ምርጥ ነበር። ዚአቶ ምንዳዬ “ዘንድሮ ኹፍተኛ ጥራት ያለው ቡና ነው ያቀሚብነው። አርሶ አደሩም ዚጥራቱን ሁኔታ ያሻሻለበት እና ፊቱን ወደ ቡና ልማት ያዞሚበት ነው” ብለዋል። ዘንድሮ ለፍጻሜ ዚደሚሱ 40 ተወዳዳሪዎቜ ነበሩ። 14ቱ ደግሞ ኚሲዳማ ክልል ና቞ው። ዚሲዳማን ቡና ምን እንዲህ ተፈላጊ፣ ተመራጭ እና ውድ አደሹገው? ትልቁ ነገር አዚሩ ነው። “በጣም ውጀታማ እዚሆኑ ያሉት ደጋማ አካባቢ ያሉ ቡናዎቜ ናቾው” ይላሉ አቶ ምንዳዬ። ሌላው ደግሞ ‘ኩርጋኒክ’ (ተፈጥሯዊ) ቡና መሆኑ ነው። ምንም ዓይነት ኬሚካል አይዞርበትም። “ዚጥላ ዛፍም አላ቞ው። ዚቡና ፓኬጅ መጠቀማቾውም ሌላው [ምክንያት] ነው። ዚአዚሩ ሁኔታም ዚሚዳን ይመስላኛል” ይላሉ አቶ ምንዳዬ ምክንያቱ ብዙ መሆኑን በመጥቀስ። በተለይ ዹደጋ አካባቢ ቡናዎቜ ተመራጭ ሆነዋል። አሁን ቡና ወደ ደጋማው ሲዳማ አካባቢ እዚሰፋ ነው። እነ አርቀጎና፣ ቡራ፣ ደንሳ፣ አሮሬሳ አካባቢዎቜ ቡና ማለትስ ዚእናንተ ተብለዋል። “በሌሎቜም አካባቢ ይስፋፋል ዹሚል እምነት አለን። እነ ቩና አካባቢም ይጠቀማሉ ብለን እናስባለን” ይላሉ አቶ ምንዳዬ። አስገራሚው ነገር እነዚህ ቊታዎቜ ኚቡና ጋር አይተዋወቁም ነበር። ለምሳሌ ዚዘንድሮው አሾናፊ ለገሠ በጊሳ ነዋሪነቱ አርቀጎና ወሚዳ ቡርሳ ቀበሌ ነው። አርቀጎና አካባቢ በጣም ደጋማ አካባቢ ነው። አልቲቲዩዱም በጣም ኹፍተኛ ነው። “አሁን ግን [በእነዚህ ቊታዎቜ] ኹፍተኛ መነቃቃት ነው ያለው።” ቀደም ሲል እንሰት፣ ስንዎ እና ገብስ ያመርቱ ነበር። ጊዜ ሲቀዚር እነሱም ተቀዚሩ። ጊዜው ሲቀዚር ዚሚያመርቱትም ተቀይሯል። “ዚኀክስ቎ንሜን ድጋፍ ይደሚጋል። ዚቡና ፓኬጅ እንዲጠቀሙ ይደሚጋል። ያሚጁ ቡናዎቜ ዚመተኚታት ሥራ ይኚናወናል። ለባለሙያዎቜም ዚስልጠና ድጋፍ እንሰጣለን። በተራው ባለሙያው እስኚ ታቜ ወርዶ ይደግፋል። ዚተሻሻሉ ቡናዎቜ እንዲያመርቱ ዚበሜታ መኹላኹል ስራዎቜን በተመለኹተ ስልጠና፣ ክትትል እና ድጋፍ ይደሹጋል” ዚአቶ ምንዳዬ ሃሳብ ነው። ቢቢሲ፡ እርስዎ ቡና ይጠጣሉ? አቶ ምንዳዬ፡ እኔ በጣም ቡና ዚምወድ ሰው ነኝ ቢቢሲ፡ ሌላ ቊታም ሄደው ቡና ይጠጣሉ? አቶ ምንዳዬ፡ [ሳቅ] ሌላ ቊታም ቡና እጠጣለሁ ቢቢሲ፡ እና ዚሲዳማ ቡና ኚሌሎቜ በምን ይለያል? አቶ ምንዳዬ፡ ስለለመድኩት መሰለኝ ዚሲዳማ ቡና ይለያል። ዹቅመም ጣዕም አለው። በዚህ በኩል ዚራሱ ባህሪ አለው። ዚሲዳማ ቡና መጠጣት ኚለመድክ ኹፍተኛ ሱስ ነው ዚሚያሲዝህ። በቀን ቢያንስ 3 ስኒ ቡና ሳልጠጣ አልውልም። ሌላም ቊታ ስሄድ እጠጣለሁ። ብዙ ምርጥ ምርጥ ቡናዎቜ አሉን። ዹይሹጋጹፌ ቡናም በጣም እወዳለሁ። በአጠቃላይ ቡና እጠጣለሁ። ዚሲዳማ ቡና ጥሩ ስሙ ዹገነነ ነው። ዕውቅናው እንዲጎለበት ኹክልል እስኚ ፌደራል ድሚስ እዚተሠራ መሆኑ ተነግሮናል። በአንድ ወቅት ዚቡና ዋጋ ወሚደ። አርሶ አደሮቜ ቁጭ ብለው እንዲያስቡ ያደሚገ ዹዋጋ መውሚድ ነበር። በምን ልተካው ሲሉ ወደ አዕምሯ቞ው ሜው ያለላ቞ው ጫት ነበር። ጫት ቡናን እግር በእግር ተካ። ግን አልዘለቀበትም። አሁን ደግሞ ቀኝ ኋላ ነው ጉዞው። ቡና ግዛቮን አላስደፍርም አለ። “ጫት እና ባህር ዛፍ እዚነቀሉ ወደ ቡና እዚቀዚሩ ያሉ በርካታ አርሶ አደሮቜ አሉ” ይላሉ አቶ ምንዳዬ። ኚአንድ ኪሎ ቡና በአርባ ሺህዎቜ ኚታፈሰ ጫት ለምኔ ነው ነገሩ። “ኹዋጋውጋር ተያይዞ ዚመጣ [ለውጥ] ነው።” “ቀደም ሲል ዚልፋታ቞ውን አያገኙም ነበር። ማዕኹላዊ ገበያ ለማቅሚብ ሰንሰለቱ ብዙ እና አስ቞ጋሪ ዘርፍ ነበር። [አርሶ አደሩ] ካመሚተው ዚጉልበቱን ዋጋ እያገኘ ባለመሆኑ ወደ ሌሎቜ ሰብሎቜ እዚገባ ነበር። አሁን ኚተሻሻለ በኋላ ነው ወደ ቡና ዚገባው።“ “[አሁንም] ዓለም ላይ ካለው ዋጋ አንጻርም ቢሆን ሙሉ ለሙሉ ተጠቃሚ ነው ማለት አይቻልም” ዚአቶ ምንዳ ሃሳብ ነው። እንደካፕ ኩፍ ኀክሰለንስ ያሉት ለገበያው መሻሻል ትልቅ ጥቅም እዚሰጡ ነው። ለዚህ ለውጥ ደግሞ ኚቡናና ሻይ ባለስልጣን ጀምሮ ዹተዘሹጋውን አሠራር በምክንያትነት ያቀርባሉ። ሁለት እና ኚዚያ በላይ ሄክታር ያላ቞ው አርሶ አደሮቜ ቡና቞ውን በተገቢው አዘጋጅተው ወደ ውጭ መላክ ይቜላሉ። “ዚምርት እና ምርታማነት ማሻሻል ላይ ይሠራል። ኚግብይት ስርዓቱ ህገወጊቜን ዹመኹላኹል ስራዎቜም ይሠራል። ይህን ዹሚኹላኹል ግብሚ ሃይልም አለ። ሌላው ደግሞ ዚግብዓት አቅርቊት ነው። በዚህ በኩልም ማሻሻል አለ።” “ዚሲዳማ ቡና አልን እንጂ ዚኢትዮጵያ ቡና ማለት ነው። ቀደም ሲል መዳሚሻ ያልነበሩ አካባቢዎቜም ዚኢትዮጵያን ቡና ይፈልጋሉ። እንደ ክልል ስንጠቀም እንደሃገርም እንጠቀማለን። በክልል ደሹጃም ቢሆን ኚፕሬዝዳንቱ ጀምሮ እስኚ ታቜ ድሚስ በዚህ ልክ ይሠራል።“ ቡና ተተክሎ ምርት ለመስጠት ሊስት ዓመት ይጠይቃል። ቡና እዚሰጠ 15 እስኚ 18 ዓመት ይቆያል። ኚዓመታት በኋላል እርጅና ሲጫነው መታደስ ይፈልጋል። ካልሆነ ምርት ይቀንሳል። ቡና ይህን ሁሉ አልፎ ነው ለገበያ ዚሚቀርበው። ዚካፕ ኩፍ ኀክሰለን ‘አውራ ፓርቲ’ ሆነናል ዚሚሉት አቶ ምንዳዬ ሊስቱንም ዓመት “ዚፕሬዚዳንሺያል ሜልማት” ማግኘታ቞ውን አንስተው በቀጣይም ማንም አይነቀንቀንም ይላሉ። “ኹዚህ በኋላ ወደ ኋላ መመልኚት ዚለም። ዹክልሉም ፕሬዝዳንተ ዚሚመሩት ስለሆነ ኹላይ እስኚታቜ በትኩሚት ስለሚሰራ ኹዚህ በላይ መስራት እቜላለን” ነው መልሳ቞ው እንዎት ተብለው ሲጠዚቁ።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c28wxj81xveo
amh
business
"በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን ነጋዎዎቜ ፈርተው ዛሬ መደብር አልኚፈቱም"
ዚቀድሞው ዚደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ዚጃኮብ ዙማን እስር ተኚትሎ በአገሪቱ ሰላማዊ ሰልፎቜና ነውጥ መቀስቀሱን ተኚትሎ በጆሀንስበርግ ዚሚሠሩ ኢትዮጵያውያን ዛሬ መደብራ቞ውን ዘግተው እንደዋሉ በኹተማዋ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያዊን ለቢቢሲ ተናገሩ። በንግድ ሥራ ዚተሰማራው ዳዊት ተወልደመድኅንፀ በጆሀንስበርግ በተለይም ጂፒ ጎዳና እና ብሪ ጎዳና በሚባሉት አካባቢዎቜ በርካታ ኢትዮጵያውያን ነጋዎዎቜ ጥቃት እንዳይደርስባ቞ው ፈርተው ዛሬ ሐምሌ 5/2013 ዓ.ም. መደብራ቞ውን ዘግተው ለመዋል መገደዳ቞ውን ተናግሯል። ትላንት ሐምሌ 4/2013 ዓ.ም. በዚያው አካባቢ በተነሳው ነውጥ ዚኢትዮጵያውያንን ጚምሮ ዚሌሎቜ አገራት ስደተኞቜ መደብሮቜ ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ፖሊስ እንደተኚላኚለ ዳዊት ይናገራል። በደቡብ አፍሪካ ዚተባበሩት ኢትዮጵያ ማኅበሰሚብ ማኅበር ዋና አስተባባሪ ኮሚ቎ አባል ዹሆነው ንጉሥ ተመስገን እንደሚናገሚው ኢትዮጵያውያን፣ ኀርትራውያን፣ ፓኪስታናውያን እንዲሁም ሌሎቜም ዚሚነግዱበት አካባቢ ዛሬ ተዘግቶ ውሏል። "ኒውካስል አካባቢ ሁለት ኢትዮጵያውያን ጥቃት ደርሶባ቞ዋል። ኚባድ ግን አይደለም። ዛሬ ሶዌቶ አካባቢ አመጜ ስላለ በንግድ ዚተሰማራው ዚሀበሻው ማኅበሚሰብ ሱቁን ዘግቷል። ደርባን ትላንት ሌሊት ሲዘሚፍ፣ መኪና ሲቀጠል ነበር" ይላል። ኚኢትዮጵያውን ማኅበሚሰብ እና ኚፖሊስ በተገኘው መሹጃ መሠሚት ኚባድ ዚሚባል ጉዳት እስካሁን እንዳልደሚሰ ያክላል። "ትላንት ዚስደተኞቜ መደብሮቜ ላይ ጥቃት እዚተሰነዘሚ እንደሆነ ኢትዮጵያውን ሲሰሙ ተሰብስበው ወደ ጂፒ ስትሪት ሄደው ሱቆቻ቞ውን ተኚላኚሉ። ፖሊሶቜም ሀበሟቜን ሲሚዱ ነበር። ኢትዮጵያውያኑ ተሰብስበው ባይሄዱ ኖሮ ዹኹፋ ነገር ይፈጠር ነበር" ይላል ነጋዮው ዳዊት። በተለይም ጆሀንስበርግ ውስጥ ሚብሻ ሲነሳ ጥቃት ዹሚሰነዘሹው ስደተኞቜ እንዲሁም ዚንግድ ተቋሞቻ቞ው ላይ እንደሆነ በተደጋጋሚ ታይቷል። ዚቀድሞው ዚደቡብ አፍሪካ ፕሬዝደንት ጃኮብ ዙማ በሥልጣን ዘመናቾው ተፈጜመዋል ዚተባሉ ዚሙስና ጉዳዮቜ እዚተመለኚተ በሚገኘው ፍርድ ቀት እንዲቀርቡ ተጠይቀው ሳይገኙ በመቅሚታ቞ው ፍርድ ቀትን በመድፈር ጥፋተኛ ተብለው ዹ15 ወራት እስር ተፈርዶባ቞ዋል። ዚጃኮብ ዙማን እስር ተኚትሎ ዚእሳ቞ው ደጋፊ ዹሆኑ ደቡብ አፍሪካውያን ዹተቃውሞ ድምጻ቞ውን ለማሰማት አደባባይ መውጣት ዚጀመሩት ጃኮብ ዙማ እጃ቞ውን ለፖሊስ ኚሰጡ በኋላ ነው። ኹዚህ ተቃውሞ ጋር ተያይዞ በተነሳው ነውጥ ሕንጻዎቜ እና ተሜኚርካሪዎቜ ወድመዋል። መደብሮቜም ተቃጥለዋል። ግርግር፣ ዝርፊያና ንብሚት ማቃጠል ጆሃንስበርግ ውስጥ በንግድ ሥራ ዚሚተዳደሩት ወ/ሮ መዓዛ ተስፋዬ እንደተናገሩት ሚብሻው መቀስቀሱን ተኚትሎ በጣም አሳሳቢ እና አስፈሪ ሁኔታ ተኚስቷል። ግርግር፣ ዝርፊያና ንብሚት ዹማቃጠል ድርጊት በዚቊታው እንደነበርና መንገዶቜም በተቃዋሚዎቹ በሚቃጠሉ ጎማዎቜ ተዘግተው እንደነበር ገልጞዋል። ተቃውሞው በጃኮብ ዙማ መታሰር ዹተቀሰቀሰ ይሁን እንጂ ቢቢሲ ያናጋራ቞ው ኢትዮጵያውያን እንደሚሉትፀ ኹተቃውሞው ባሻገር በተለያዩ ስፍራዎቜ ዝርፊያዎቜና ዚንብሚት ውድመት ተፈጜሟል። በተለይ ዚንግድ ሱቆቜ ዚተቃዋሚዎቹ ዚጥቃት ኢላማ በመሆናቾው በንግድ ሥራ ላይ ዚተሰማሩ ኢትዮጵያውያን ዛሬን ጚምሮ ለሁለት ቀናት ሱቆቻ቞ውን ዘግተው ቀታ቞ው ተቀምጠዋል። ሚብሻው እሳ቞ው በሚኖሩበት ጆሃንስበርግና ደርባን ኚተሞቜ ውስጥ ዚበሚታ መሆኑን ዚሚናገሩት ወ/ሮ መዓዛፀ ፖሊስ አመጞኞቹን ለመቆጣጠርና ዚንብሚት ውድመት ለማስቆም እዚጣሚ ነው ብለዋል። ለሁለት ቀናት ኹዘለቀ ተቃውሞና ዚንብርት ውድመት በኋላ ኚትናንት ዕሁድ በተሻለ ሰኞ ዕለት መሚጋጋት በጆሃንስበርግ መመለሱን ዚተናገሩት ወ/ሮ መዓዛ "ኹተማው ጞጥ ብሏል" ብለዋል። ዚአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን በሚብሻው ዹወደሙ ንብሚቶቜናና ዹደሹሰ ጉዳትን በተመለኹተ ተኚታታይ ዘገባዎቜን እያቀሚቡ ሲሆን ወ/ሮ መዓዛና ሌሎቜ ኢትዮጵያውያን ለሁለት ቀናት ኚሥራ ውጪ ሆነው መቆዚታ቞ውን ገልጞዋል። ሌሎቜ ኢትዮጵያውያንና ዹመገኛኛ ብዙኃን እንደሚሉት ሚብሻው ኹተኹሰተ በኋላ ኚጆሃንስበርግ ይልቅ በደርባን ኚባድ ጉዳት መድሚሱን እንደተሚዱ ጠቅሰዋል። "ሚብሻ ሲነሳ ጥቃት ዹሚደርሰው ስደተኞቜ ላይ ነው" ንጉሥ እንደሚለውፀ ማንኛውም አይነት ነውጥ ሲነሳ ያንን ሰበብ በማድሚግ ዚንግዱ ማኅበሚሰብ ላይ ጥቃት ይሰነዘራል። አሁን ዚተነሳው አይነት አለመሚጋጋት ሊቀሰቀስ እንደሚቜል ባለፉት ጥቂት ቀናት ሲነገር እንደነበር እና ሞቀጣ቞ውን ኚመደብር ያወጡ ኢትዮጵያውያን ነጋዎዎቜ እንዳሉ ገልጿል። "ዛሬ ጥቃት እንደሚደርስ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ስለተነገሚ መላው ኢትዮጵያዊ ማኅበሚሰብ ኚቀቱ አልወጣም" ብሏል። ኮሮናቫይሚስን ለመኹላኹል ዚወጣው ዚእንቅስቃሎ ገደብ ኢትዮጵያውያን ነጋዎዎቜ ላይ ያሳደሚው ጫና ላይ አሁን ዚተነሳው ነውጥ ሲጚመር ማኅበሚሰቡ ላይ ኹፍተኛ ዚምጣኔ ሀብት ቀውስ እንደሚያስኚትልም ንጉሥ ይናገራል። ዳዊት እንደሚለውፀ ኹዚህ ቀደምም እንደታዚው አንዳቜ ነውጥ ሲነሳ ስደተኞቜ ላይ ጥቃት ይሰነዘራል። ይህንን ዚሚያውቁት ኢትዮጵያውያን ስጋት ስለገባ቞ው ዛሬ መደብራ቞ውን አልኚፈቱም። "ትላንት ኢትዮጵያውኑ ተሰብስበው ሳይሄዱ በፊት ጉዳት ዚደሚሰባ቞ው ሱቆቜ ነበሩ። ዛሬም ምን ሊፈጠር እንደሚቜል ስለማይታወቅ ኢትዮጵያውያን ሱቃ቞ውን ዘግተው ውለዋል" ይላል። ትላንት ዚናይጄርያውያን መኪና መሞጫ፣ ዚሞቀጣ ሞቀጥ መደብርና ሌሎቜም ዚንግድ ተቋማት ላይ ጉዳት እንደደሚሰ ይናገራል። "ትላንት ሀበሟቜ በቁጣ ሱቃ቞ውን ለመጠበቅ ወጡ። ፖሊስም አገዛ቞ው። ኹዚህ በፊት ፖሊሶቜም ጭምር ቜግር ይፈጥሩብን ነበር" ይላል። ኢትዮጵያውያኑ ስጋት ውስጥ እንደሆኑና ዚጃኮብ ዙማ ዚፍርድ ቀት ጉዳይ እልባት እስኪያገኝ ወይም እስኪሚግብ ድሚስ ወደ ሥራ መመለስ እንደሚያስ቞ግር ዳዊት ለቢቢሲ ገልጿል። ሁሌም ሚብሻ ሲነሳ ስደተኞቜ ጥቃት እንደሚደርስባ቞ው ዹሚጠቅሰው ነጋዎውፀ "ድንገት መጥተው ሊዘርፉን ወይም ሊያጠቁን ስለሚቜሉ ዘግቶ መጠበቅ ይሻላል" ሲል ያስሚዳል። ጆሃንስበርግ ውስጥ ዚሚነግዱ ኢትዮጵያውያን በማንኛውም ጊዜ ነውጥ ሊነሳ እንደሚቜል እንደሚሰጉ ገልጟ "ዚለመድነው ቜግር ስለሆነ ሁሌም በተጠንቀቅ ነው ዚምንጠብቀው። ሚብሻ ሲነሳ ጥቃት ዹሚደርሰው ስደተኞቜ ላይ ነው" ብሎም አክሏል። ኹዚህ ቀደም ኢትዮጵያውያን እና ሌሎቜም ስደተኞቜ ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶቜ ብዙ ጊዜ ተፈጜመዋል። ዳዊት "ስደተኞቜ ሲጠቁ ዓለም ዚደቡብ አፍሪካ መንግሥትን ስለሚጠይቅ ስደተኞቜን ለማጥቃት ምክንያት ይፈለጋል" ሲል ሁኔታውን ያስሚዳል። በደቡብ አፍሪካ መኚላኚያ ሠራዊቱ ስለመሰማራቱ ዚደቡብ አፍሪካ መንግሥትፀ በጃኮብ ዙማ ዚትውልድ ቊታ ክዋዙሉ-ናታለ ተቀስቅሶ በመላው አገሪቱ እዚተንሰራፋ ዚመጣውን አለመሚጋገት ለማርገብ ዚአገሪቱን መኚላኚያ ሠራዊት እንዳሰማራ ተገልጿል። ዘሹፋ ተፈጜሞባ቞ዋል በተባሉ ስፍራዎቜ ፖሊስ ምላሜ እዚሰጠ ሲሆን እስካሁን ድሚስ 60 ሰዎቜን በቁጥጥር ሥር ማዋሉንም ይፋ አድርጓል። ትናንት በርካታ ቁጥር ያላ቞ው ተቃዋሚዎቜ ዱላ እና ፍልጥ ይዘው በጆሃንስበርግ ኹተማ መሃል ታይተዋል። ቅዳሜ ዕለት ደግሞ ወደ 300 ዹሚጠጉ ሰዎቜ ዚጆሃንስበርግን ዋና ጎዳናን ዘግተው ነበር። ኚትናንት በስቲያ በነበሹው ተቃውሞ ሕንጻዎቜ እና መኪኖቜ በእሳት ወድመዋል። አሌክሳንድራ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ወደ 800 ዹሚጠጉ ሰዎቜ ተሳትፈውበታል በተባለው አመጜ አንድ ዚፖሊስ አባል በጥይት መመታቱ ተዘግቧል። ፕሬዝደንት ሲርል ራማፎሳ ትናንት ምሜት ግጭት እያስኚተሉ ያሉ ተቃውሞዎቜ እንዲቆሙ ዹጠዹቁ ሲሆንፀ "ለዚህ አመጜ እና ዚንብሚት ውድመት ምንም ዓይነት ምክንያት ሊቀርብ አይቜልም" ብለዋል። ፍርድ ቀትን በመድፈር ጥፋተኛ ተብለው ዹ15 ወራት እስር ዚተፈሚደባ቞ው ጃኮብ ዙማ በሥልጣን ዘመናቾው ምንም ዓይነት ሙስና አለመፈጾማቾውን ይኚራኚራሉ። ዚጃኮብ ዙማ ጠበቆቜ ዛሬ ለአገሪቱ ፍርድ ቀት ይግባኝ በማለት ዚፍርድ ጊዜውን ለማሳጠር ይሞክራሉ ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-57808849
amh
business
ኮሮናቫይሚስ፡ አፍሪካ በወሚርሜኙ ሳቢያ ኚተጎዳው ምጣኔ ሐብት ለማገገም 1.2 ትሪሊዚን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ
አፍሪካ በኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ካጋጣት ዚኢኮኖሚ ውድቀት ለማገገም እንዲሁም ዚጀና ወጪ 1.2 ትሪሊዚን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ዓለም አቀፉ ገንዘብ ተቋም [አይኀምኀፍ] አስታወቀ። ገንዘቡ ያስፈልጋታል ዚተባለው ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት መሆኑ ተገልጿል። ዹተቋሙ ዳሬክተር ክርስታሊና ጆርጂቫ እንዳሉት ዓለም አፍሪካ ኚገባቜበት ቀውስ እንድታገግም ለመደገፍ ዓለም ብዙ መስራት አለበት ብለዋል። በአፍሪካ በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙ እንዲሁም ዚሞቱ ሰዎቜ ቁጥር ኚሌሎቜ አህጉራት ያነሰ ነውፀ ነገር ግን ዹዓለም ባንክ በወሚርሜኙ ሳቢያ ተጚማሪ 43 ሚሊዮን ዹሚሆኑ አፍሪካዊያን ለኹፋ ድህነት ዚመጋለጥ አደጋ ተጋርጊባ቞ዋል ብሏል። በወሚርሜኙ ሳቢያ ዚሥራ እድሎቜ በመታጠፋ቞ው እና ዚቀተሰብ ገቢ በ12 በመቶ በመቀነሱ ዹደሹሰው ዚኢኮኖሚ ተፅእኖ ኚቅርብ ዓመታት ወዲህ በአፍሪካ እዚታዚ ዹነበሹውን ጠንካራ እድገት እዚቀለበሰው መሆኑን ዚገንዘብ ተቋሙ ዳሬክተር በበይነ መሚብ በነበራ቞ው ዹተቋሙ ስብሰባ ላይ ተናግሚዋል። ቜግሩንም ለማቃለል በርካታ አፍሪካ አገራት መንግሥታት ኚልማት እቅዳ቞ው 2.5 በመቶ ያስወጣ቞ውን ፖሊሲዎቜ አስተዋውቀዋል። አይኀም ኀፍ ዚአፍሪካ አገራት ኚደሚሰባ቞ው ተፅዕኖ እንዲያገግሙ 26 ቢሊዮን ዶላር ዹለገሰ ቢሆንምፀ ዹግል አበዳሪዎቜ እና በሌሎቜ አገራት ድጋፍ ቢኖርምፀ አሁንም ግን ኹፍተኛ ዹሆነ ዚገንዘብ እጥሚት አለ ብለዋል። "አንዳንድ አገራት ኚብድር አግልግሎትና ተጚማሪ ዚማህበራዊና ጀና ወጪዎቜ መካኚል እንዲመርጡ ዚሚያስገድዳ቞ውን ዚዕዳ ጫናዎቜ እዚተጋፈጡ ነው" ብለዋል ኃላፊዋ። ይህንን ቜግር ለመፍታትም ተበዳሪዎቜ ብድራ቞ውን ዚሚኚፍሉበት ጊዜ እንዲራዘም ጥሪ ያቀሚቡ ሲሆንፀ ለብድር ዹሚሆን ተጚማሪ ገንዘብ ማቅሚብ እንደሚያስፈልግም ተናግሚዋል። በአፍሪካ ኹ1.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎቜ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ዹተሹጋገጠ ሲሆንፀ ወደ 37 ሺህ ዚሚጠጉት ሕይወታ቞ውን አልፏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54498317
amh
business
ዚወቅቱ ዚኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ተግዳሮቶቜ
ዹዓለም ባንክ ዚኢትዮጵያ ዹአገር ውስጥ ምርት እድገት (ጂዲፒ) ባለፉት 10 ዓመታት በዚዓመቱ በአማካኝ 9.4 በመቶ እያደገ መሆኑን ይናገራል። ኢትዮጵያ ኚጥቅምት 24/2013 ጀምሮ በትግራይ ክልል ዹቀሰቀሰው ጊርነት፣ በቅርቡ ዹተኹሰተው ኹፍተኛ ሆነ ዚምንዛሬ እጥሚት እንዲሁም ኹፍተኛ ዹሆነ ዹዋጋ ንሚት ኢኮኖሚውን እዚተፈታተነው ይገኛል። ኚቅርብ ሳምንታት ወዲህ አንድ ዶላር በጥቁር ገበያው ኹ64 እስኚ 68 ብር ድሚስ በመመንዘር ላይ እንደሚገኝ እና በተለያዩ ሁኔታዎቜ ይህ ዋጋ እስኚ 72 ብር ድሚስ ኹፍ እንደሚል ጉዳዩን በቅርበት ዚሚያውቁ ግለሰብ ለቢቢሲ ተናግሹው ነበር። በመደበኛው ዚምንዛሬ ገበያ አንድ ዶላር በ45 ብር እዚተመነዘሚ ይገኛል። ዚአገሪቱ ዹዋጋ ግሜበትም ቢሆን ኚእለት ወደ እለት እዚጚመሚ እንደሚሄድ ያሳያል። ዓለም አቀፍ ተቋማት ዚኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በኮቪድ-19 ምክንያት ተጜዕኖ እንደደሚሰበት እና 2 በመቶ ገደማ ዕድገት እንደሚያስመዘገብ ጠቅሰው ነበር። ወርቅነሜ ሲማ ዚአዲስ አበባ ነዋሪ ናት። ኚምታገኘው ገቢ በላይ ወጪዋ ሰማይ መንካቱን በመግለጜ ዚኑሮ ውድነት እንዳማሚራት ትናገራለቜ። "ዚቀት ኪራይ፣ በርበሬ፣ ዘይት እና ጀፍ ዋጋቾው ሰማይ ዚነካ ነው" ዚምትለው ወርቅነሜ በአሁኑ ጊዜ ገቢያቜን እና ወጪያቜን ዚተመጣጠነ አይደለም ስትል ለቢቢሲ አስሚድታለቜ። ወርቅነሜ መንግሥት ለኑሮ ውድነቱ መፍትሄ ያበጅለታል ብላ ተስፋ ብትጥልም "ለእኛ ግን በጣም ፈታኝ ነው" ስትል ኑሮ እንደኚበዳት ትገልጻለቜ። በንግድ ሥራ ላይ ዚተሰማራው ለማ አበበ ደግሞ በአሁኑ ሰዓት ስላለው ዚአገሪቱ ምጣኔ ሀብት ሲናገር "እያደገ ነው" በማለት ነው። አክሎም "ዹዋጋ ግሜበት እና ዚኑሮ ውድነቱም በዚያው መጠን እያደገ ነው። ይህ ደግሞ ገበሬውን ሳይሆን ኑሮውን በዚወሩ በሚያገኘው ደሞዝ ላይ ያደሚገውን መካኚለኛ ገቢ ዚሚያገኝ ነዋሪ እዚጎዳው ነው። ገበሬው ግን ያመሚተውን በገበያው ዋጋ ስለሚሞጥ አትራፊ ነው" ሲል ያስሚዳል። አቶ ለማ ዚሚታዚውን ዚኑሮ ውድነት ለመቆጣጠር ዹአገር ውስጥ ምርትን መጠቀምን ማበሚታታ እና ኚውጪ ዚሚገቡ ምርቶቜን መቀነስ መፍትሄ ይሆናል ብሎ ያምናል። ዚተለያዩ ዚኢኮኖሚ ማሻሻያዎቜ ባለፉት አሥር ዓመታት መንግሥት በኹፍተኛ መጠን ኚተፈተነባ቞ው ቜግሮቜ መካኚል አንዱ ዹዋጋ ንሚት ነው። መንግሥት ዹዋጋ ንሚትን መቆጣጠር አቅቶታል ብለው ዚሚተቹ ወገኖቜ በርካታ ና቞ው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግሥታ቞ው ዹዋጋ ንሚት ለመኹላኹል እንደ ሾገር ዳቊ ፋብሪካ ያሉ ተቋማትን እያቋቋመ መሆኑን ተናግሚዋል። ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ወደ ስልጣን መምጣት ተኚትሎ ኢኮኖሚውን ነፃ ለማድሚግ በሚል በመንግሥት ይዞታ ስር ዚሆኑትን ቎ሌኮምዩኒኬሜንን፣ ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድን በኹፊል ወደግል ለማዘዋወር ተወስኖ ነበር። ኚእነዚህ ድርጅቶቜ በተጚማሪም ዚኢንደስትሪ መንደሮቜን፣ ዚስኳር ፋብሪካዎቜን፣ ሆ቎ሎቜን እና ሌሎቜ አምራቜ ድርጅቶቜን ወደ ግል ለማዞር ተወስኗል። ይህ ውሳኔ ዹተወሰነው ዚአገሪቱን ዚኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠል፣ ዹውጭ ምንዛሬ እጥሚቱንና ዹዋጋ ግሜበቱን ለመቋቋም፣ ዚገቢ ማመንጚት አቅምን ለማጠናኹርና ዚወጪ ንግዱን ለማቀላጠፍ በሚል ነው። ለዚህ ውሳኔ ሌላኛው ምክንያት ዹሆነው ዚኢትዮጵያ ዚብድር መጠን ኹፍ ማለቱ እንደሆነም ይነገራል። ኢትዮጵያ ዚ቎ሌኮም ዘርፉን ለውጭ ተቋማት ክፍት እንደምታደርግ ያስታወቀቜው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደ ሥልጣን ኚመጡ በኋላ ይፋ በተደሹጉ ዚለውጥ እርምጃዎቜ ነው። በቅርቡም ኢትዮጵያ በ቎ሌኮም ዘርፍ እንዲሳተፍ ግሎባል ፓርትነርሜፕ ፎር ኢትዮጵያ ለተሰኘው ጥምሚት ፍቃድ መስጠቷ ይታወሳል። በዚህም ዚተነሳ ኹፍተኛ መጠን ያለው መዋዕለ ነዋይ ወደ አገሪቱ እንዲገባ እና በርካታ ዚሥራ ዕድሎቜን እንደሚፈጥር ተነግሯል። እንደ ማዕኹላዊ ስታትስቲክ ባለስልጣን መሹጃ ኹሆነ በኢትዮጵያ ያለው ዚኑሮ ውድነት በሰኔ ወር ብቻ 24.5 በመቶ ደርሷል። ኢትዮጵያ ኚተለያዩ ዹውጭ አገራት ዚተበደሚቜው 42.8 ቢሊዮን ዶላር መሆኑ ይነገራል። ኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብቷን ለማሳደግ ኚወሰደቻ቞ው እርምጃዎቜ መካኚል አንዱ ዚተለያዩ ኢንደስትሪ ፓርኮቜን ለውጭ ገበያ ዹሚሆኑ ምርቶቜን እንዲያመርቱና እንዲልኩ ማበሚታታት ነው። ማርታ ገላነው በአገሪቱ ካሉ ዚኢንዱስትሪ ፓርኮቜ መካኚል በአንዱ ተቀጥራ ትሰራለቜ። ዚአውቶሜሜን ኢንጂነር ባለሙያ ዚሆነቜው ማርታ በአገሪቱ እዚተስፋፉ ያሉ ዚኢንደስትሪ መንደሮቜ ዚወደፊት ተስፋዋን ብሩህ ማድሚጋ቞ውን ትናገራለቜ። በአሁኑ ጊዜ ገና በመቋቋም ባለ ፋብሪካ ውስጥ እዚሰራቜ ቢሆንም ለወደፊት ግን "እንደ አውቶሜሜን ኢንጂነርነ቎ በዚትኛውም ትልልቅ ፋብሪካዎቜ ውስጥ ያሉ ማሜኖቜን ማንቀሳቀስ እቜላለሁ" ስትል ታስሚዳለቜ። በደብሚብርሃን ዚኢንደስትሪ ፓርክ ዚእንስሳት መኖ ለማምሚት በማሰብ ግንባታ እያካሄዱ መሆኑን ዚሚናገሩት ዚባጃኢ ኢትዮ ኢንደስትሪያል ሶሉሜን ባለቀት ባጃኢ ናይኹር ና቞ው። በደብሚብርሃን ኢንደስትሪያል ፓርክ ውስጥ እያስገነቡት ባለው ዚእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ድብልቅ ዚእንስሳት መኖ ለኢትዮጵያውያን እንስሳት አርቢዎቜ ለማምሚት እዚሰሩ ነው። ፋብሪካው ኹዚህ ቀደም ኹውጭ እዚመጣ ዹነበሹውን ዚእንስሳት ቫይታሚንና ሚነራሎቜን ለማስቀሚት ዚሚያስቜል እቅድ አለው። ፋብሪካው ዹአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለውጭ ገበያም ዚማቅሚብ ሃሳብ እንዳለው ባለቀቱ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። እንደ ሚስተር ባጃኢ ኹሆነ መንግሥት በዚህ ዚኢንደስትሪ መንደር ፋብሪካ቞ውን እንዲገነቡ ዚተለያዩ ማበሚታቻዎቜን አድርጎላ቞ዋል። በኢንደስትሪ ፓርክ ውስጥ ሲሰሩ ለተወሰነ ዓመታት ኚታክስ ነጻ እንደሚሆኑ፣ ኹውጭ ዹተወሰኑ እቃዎቜን ኚቀሚጥ ነጻ ዚማስገባት እድል እንደተመቻ቞ላ቞ው፣ መሬት በርካሜ ማግኘታ቞ውን እንዲሁም በዚህ ኢንደስትሪ መንደር ለእንስሳት አምራ቟ቜ ዹተለዹ ትኩሚት መሰጠቱ እርሳ቞ውን ኚሳቧ቞ው ጉዳዮቜ መካኚል ና቞ው። ዚኢትዮጵያ ኢንቚስትመንት ኮሚሜን በመላ አገሪቱ 15 ዚኢንደስትሪ ፓርኮቜ እንዳሉና ተጚማሪ 20 ደግሞ ዚመገንባት እቅድ እንዳለው ያስሚዳል። ዚትግራይ ጊርነት እና ዚአገሪቱ ምጣኔ ሀብት ዚኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት እድገት እያሳዚ ቢሆንም በትግራይ፣ በአፋር እና በአማራ ዚተለያዩ አካባቢዎቜ እዚተካሄደ ያለው ጊርነት ግን ዚአገሪቱን ምጣኔ ሀብት ፈተና ላይ ጥሎታል። ዚምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዚሆኑት እና ዚፌርፋክስ አፍሪካ ፈንድ ዹበላይ ኃላፊ አቶ ዘመዮነህ ንጋቱ ወደ ኢትዮጵያ ዚሚመጡ ባለሀብቶቜ ዚሚዥም ዓመት እቅድ ይዘው መሆኑን ይናገራሉ። በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ያለው ግጭት ዹአጭር ጊዜ መሆኑን እና አገሪቱም እንደምትወጣው ያላ቞ውን ተስፋ ገልፀዋል። ለኢትዮጵያውን ዋነኛ ዚምጣኔ ሀብት ስጋት ዹዋጋ ግሜበት መሆኑን ዚሚያብራሩት አቶ ዘመዎነህ፣ ባለፉት 10 ዓመታት ዚግሜበት መጠኑ በእጥፍ መጚመሩን በመግለጜ ይህም መካኚለኛና ዝቅተኛ ገቢ ላላቾው ኢትዮጵያውያን ተግዳሮት ሆኖ እንደሚቀጥል ተናግሚዋል። ለዋጋ ግሜበቱ መናር ምክንያት ነው ብለው ኚጠቀሷ቞ው መካኚል ኹፍተኛ ዹሆነ ዚፍላጎት መጹመር ሲኖር ዚአቅርቊት መጠን በዚያው ልክ ማደግ አለመቻሉን ነው። በአቅርቊትና በፍላጎት መካኚል ያለ ኹፍተኛ አለመመጣጠን በተለይ ደግሞ ዹአገር ውስጥ ምርቶቜ ኚፍላጎት ጋር በተመጣጠነ መልኩ አለማደጋቾውን ያነሳሉ። ሌላው ዚጅምላ፣ ዚቜርቻሮ እና ዹማኹፋፈል ስርዓት በአገሪቱ ውስጥ አሁንም ኋላ ቀርነት እንዳለው አንስተዋል። ለዚህም መዋቅራዊ ለውጥ መካሄድ አስፈላጊ መሆኑን ይመክራሉ። ኢትዮጵያ ኹ126 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ዚ቎ሌኮምዩኒኬሜኑን ዘርፍ ለግል ባለሀብቶቜ መስጠቷን ዚሳፋሪኮም ስምምነትን በመጥቀስ ዚገለፁት አቶ ዘመዎነህፀ "ለዓለም አቀፉ ማኅበሚሰብ ኢትዮጵያ ለተለያዩ ቢዝነሶቜ በሯን መክፈቷን ያሳያል" ሲሉ ተናግሚዋል። በ቎ሌኮም ዘርፉ ዹውጭ ባለሀብቶቜ መምጣታ቞ው ዚአገልግሎት ጥራት፣ ዹዋጋ ውድድር በመፍጠር ለ቎ሌኮሙም ሆነ ለፋይናንስ ዘርፉ ኹፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ያብራራሉ። አቶ ዘመዮነህ ኢትዮጵያ በግብርና፣ በአምራቜ እንዲሁም በቱሪዝምና ሌሎቜ ዘርፎቜ በቀጣዩቹ ሊስትና አምስት ዓመታት እድገት እንደምታሳይ ያላ቞ውን ተስፋም ገልፀዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-58185460
amh
business
እሷ ማናት? #4፡ ኚሒሳብ ጋር በአጋጣሚ ነው ዚተዋደድነው
በሒሳብ ትምህርት ዚዶክትሬት ዲግሪዋን (ፒኀቜ ዲ) ለማግኘት እዚሰራቜ ነው። ሰዎቜ እምብዛም ገፍተው በማይሄዱበት ዚትምህርት ዓይነት እንዎት ውጀታማ ልትሆን እንደቻለቜ አጫውታናለቜ። ስሜ ኀቢሎ አዱኛ ይባላል። ተወልጄ ያደኩት በነቀምት ኹተማ ነው። ዚመጀመሪያ ዲግሪ ትምህር቎ን በሐሚማያ ዩኒቚርሲቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪ ደግሞ በሐዋሳ ዩኒቚርሲቲ ተምርያለሁ። በአሁን ሰዓት ደግሞ ዚሊስትኛ ዲግሪ ትምህር቎ን በዮንማርክና በሐዋሳ ዩኒቚርሲቲዎቜ እዚተኚታተልኩ ነው። • ዚኮምፒዩተር ትምህርት ለኬኒያ ሎት እስሚኞቜ ሁለተኛ እድል ይሰጣ቞ው ይሆን? • አንድም ሎት ዹፓርላማ አባል ዚሌላት ሃገር ሒሳብ መሚጠሜ ወይንስ መሚጥሜው ? ዚሙያ ሕይወቮ ኚሒሳብ ጋር ዚተቆራኘ ይሆናል ብዬ አልገመትኩም ነበር። ለመጀመሪያ ዲግሪ ሐሚማያ ዩኒቚርሲቲ በተመደብኩበት ወቅት ዚሒሳብ ትምህርት ሳልመርጥ በአጋጣሚ ደሚሰኝ። ኚዚያ በኋላ ግን እኔና ሒሳብ በጣም ተዋደድን። እኔ ልምሹጠው ሒሳብ ይምሹጠኝ ዚሚታወቅ ነገር ዚለም። ዚሒሳብ ትምህርትን ኚድሮም ፈርቌው አላውቅም። ዩኒቚርሲቲ ገብቌ ትምህርቱ ሲደሚሰኝ ጥሩ ነጥብ ማስመስገብ ጀመርኩኝፀ እዚወደድኩትም መጣሁ። በዚያ ላይ ይህ ትምህርት ለሎት ይኚብዳል ለወንድ ደግሞ ይመቻል ዹሚል አመለካኚት ዚለኝም። ማንም ሰው ፍላጎት ካለው፣ ኚጣሚና በሥራ ካስደገፈው ይሳካል ብዬ ስለማስብ ዚሒሳብ ትምህርትን አጥብቄ á‹­á‹€ ቀጠልኩበትፀ እዚህም ደሚስኩኝ። አሁንም ቢሆን ኚምወዳ቞ው ትምህርቶቜ መካኚል ትልቁን ቊታ ዚያዘው ሒሳብ ነው። ዚመጀመሪያ ደሹጃ ተማሪ እያለሁ 'ጊዜ ቀት' ላይ ሌሎቜ ልጆቜ ሞምድደው በፍጥነት እንደሚሉት አልነበርኩምፀ ነገር ግን በልጅነቮ በተወሰነ ደሹጃ ይህንን 'ዹጊዜ ቀት' እሠራ ነበር። በዚያ ወቅት ተማሪ እያለሁ አባ቎ ዚሒሳብ መምህር ስለነበሚ በሒሳብ ጥሩ መሚዳት እንዲኖሚኝ አድርጓል። በጭንቅላቮ ሞምድጄ ኚመያዝ ይልቅ ተሚድቌ ማስላት ይቀለኝ ነበር። ዚሒሳብ ጥቅም ዚተለያዚ ነው። ለምሳሌ ሒሳብ በሁለት ይኚፈላልፀ 'ፕዩር ማ቎ማቲክስና አፕላይድ ማ቎ማቲክስ' ተብለው ይለያሉ። • ሎት ተመራቂዎቜ ለምን ሥራ አያገኙም? • ሚሌል ኊባማ በአሜሪካ እጅግ ተወዳጇ ሎት ተባሉ እኔ ዹምማሹው 'አፕላይድ ማ቎ማቲክስ' በተጚባጭ ያሉ ቜግሮቜን ለመፍታት ዹሚጠቅም ነው። ለምሳሌ ዚምመሚምራ቞ው ስሌቶቜ ኀቜ ሲቪ ለተባለው ዚጉበት ቫይሚስ መፍትሔ ለማግኘት ዚሚሚዳ ነው። ስለዚህ ሒሳብ በሕይወታቜን ያሉን ተጚባጭ ቜግሮቜ መፍትሔ ለመስጠት ዚሚሚዳ ዚትምህርት ዓይነት ነው። ነገ ዹሚሆንን ነገር ለመተንበይ ሒሳብ ቜግሮቻቜንን በቁጥር አስልተን ለማስቀመጥ ይሚዳናል። ዚሒሳብ ምሁሮቜ ኚስሌቱ በኋላ ቀመሩን ኚነመፍትሔው ያስቀምጡልናል። ዚምህድስና ሙያ ያላ቞ው ሰዎቜ ደግሞ እንዲህ ዓይነት ቀመሮቜን በሥራ ላይ ያውላሉ። ስለዚህ ኚሒሳብ ሙያተኞቜ ይልቅ በምህንድስና ውስጥ ዚተሰማሩ ሰዎቜ በይበልጥ ማስሚዳት ይቜላሉ። ውጣ ውሚዶቜን ለማለፍ በሥራም ሆነ በኑሮ እንደማንኛውም ሰው ዚተለያዚ መሰናክል ይገጥመኛል። ነገር ግን ዚቜግሩን ያህል ሳይሆን ነገሮቜን ኹአቅሜ አንፃር ነው ዚምገመግማ቞ው። ቜግር እንደሚያበሚታኝና እንደሚያጠነክሚኝ ስለማውቅ ሁሌም መውጫ ቀዳዳ ነው ዚምፈልገው። አንዳንዎ ሰዎቜ ፊቮንና ዕድሜዬን አይተው ይገምቱኛል። አንዳንዎ ጊዜ እንዲያውም በሎትነ቎ ጭምር ለመመዘን ይሞክራሉ። እንደዚህ ዓይነት ሁኔታዎቜ ሲገጥሙኝ ደግሞ እራሎን በደንብ አስተዋውቃለሁ። ምን ማድሚግ እንደምቜል፣ ማን እንደሆንኩ እና ፍላጎቮ ምን እንደሆነ አስፈላጊ በሆነበት ቊታ ሁሉ እናገራለሁ። ይህ ደግሞ በሕይወቮ ዹምፈልገውን ነገር በሙሉ እንዳገኝ አድርጎኛል በዚያ ላይ ተግባቢ ሰው ነኝ። ሁለተኛና ሊስተኛ ዲግሪ መማር ጊዜን ስለሚፈልግ ዹጊዜ እጥሚት ያጋጥማል። ዚፒኀቜ ዲ ትምህርት ምግብ ዚምበላበት ጊዜ እንኳን አይሰጥም፣ ያስጚንቃል ደግሞም ድብርት ያስኚትላል። ቢሆንም ግን ያለኝን ጊዜ አብቃቅቌ ኚጓደኞቌም ሆነ ኚቀተሰቊቌ ጋር ጊዜ አሳልፋለሁ። ኹዚህ ሁሉ ግን ያለንን ጊዜ በደንብ ኚተጠቀምንበት ዹምንፈልገውን ማሳካት ይቻላል ብዬ አስባለሁ። • ሎት አስገድዳ ኚወንድ ጋር ወሲብ ብትፈጜምፀ አስገድዶ መድፈር ይባላል? • ኚመጀመሪያው 'ዚብላክ ሆል' ምስል ጀርባ ያለቜው ሎት እንደሚታወቀው በአገራቜን ሎት ልጅ ስትበልጥ ወንዶቜ ብዙ ደስተኛ አይደሉምፀ ሁሉም እንዲዚህ ናቾው ማለቮም አይደልም ነገር ግን እንዲህ ዓይነት አስተሳብ አለ። በሁሉም መንገድ ወንድ ዹበላይ ሆኖ አንዲታይ ዹሚፈልጉ አሉ። እንደእኔ አመለካለኚት ዚትምህርት ደሹጃ እና ፍቅር ዚተለያዩ ና቞ው። ስኬ቎ ቜግር ዚሚሆንበት ካለ ለማስተናገድ አልቜልም። ዚቀተሰቀ አባላት በማደርገው ጥሚት ላይ በጣም ዚደግፉኛል። ጓደኛና ዹምወደው ሰው ዹምለውም ሰው ልክ እነደዚህ ዹሚደግፈኝ መሆን አለበት። ለምን ትበልጠኛለቜ ካለ ግን ይህ ፍቅር ነው ወይንስ ቅናት? ብዙ ሎቶቜ ያለንን አቅም ዚተሚዳነው አይመስለኝም። እንቜላለን ብለን ካመንን ማድሚግ አያቅተንም። ይህን ኚተሚዳን ደግሞ በውበት፣ በጋብቻ እና በገንዘብ መወሰን ዚለብንም። እራሳቜን ያለምነው ትልቅ ቊታ ላይ መድሚስ እንደምንቜል ማሰብና መጣር ነው ያለብን። ስለዚህም ዚሚያጋጥሙንን መሰናክሎቜ በእራሳቜን ማለፍ መቻል አለብን። እንደዚህ ወደፊት ኚተራመድን አገራቜንን ወደፊት ለመምራት አያቅተንም። ያለንን አቅማቜንንና መላ ዚማበጀት ጥበባቜንን እንጠቀምበት ብዬ ለሎቶቜ ምክሬን እሰጣለሁ።
https://www.bbc.com/amharic/news-50218736
amh
business
ሲም ካርድ ያለው ሁሉ ገንዘብ መበደር ዚሚቜልበትን ዕድል ዹፈጠሹው ቎ሌብር
ኚአስራ አራት ወራት በፊት ወደ አገልግሎት ዚገባው ቎ሌብር ዹተሰኘው ዚኢትዮ ቎ሌኮም ዚሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለፈው ሳምንት አርብ ኚቁጠባ እና ብድር ጋር ዚተያያዙ አዳዲስ አገልግሎቶቜን መስጠት ጀምሯል። ኚቢቢሲ ጋር ቆይታ ያደሚጉት ዚኢትዮ ቎ሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ አዳዲሶቹ አገልግሎቶቜ በፋይናንስ ሥርዓት ያልተሞፈነውን 60 በመቶ ዹሚሆን ዚኅብተሚሰብ ክፍል ተደራሜ ለማድሚግ ያስቜላል ብለዋል። ዚነዳጅ ድጎማ እና ዚግብር ክፍያን ጚምሮ ባለፉት 14 ወራት ገንዘብ ለመላላክ፣ ዚግብይትና ዚአገልግሎት ክፍያን ለመፈጾም እንዲሁም ኹውጭ አገራት ገንዘብ ለመቀበል ሲውል ዹነበሹው ቎ሌብር አሁን ደግሞ  ‘መላ’፣ ‘እንደኪሎ’ እና ‘ሰንዱቅ’ ዹተሰኙ አገልግሎቶቜን ይፋ አድርጓል። ኢትዮ ቎ሌኮም ዚ቎ሌብር ደንበኞቜ ገንዘብ እንዲቆጥቡ፣ ሲያስፈልጋ቞ው እንዲበደሩ ዚሚሚዱት አዳዲሶቹን አገልግሎቶቜ ለማስጀመር አስራ አራት ወራት በላይ ዘግይቷል። ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ ቎ሌኮም እነዚህን አገልግሎቶቜ ለማስጀመር ኚአንድ ዓመት በላይ ዚዘገዚበትን ምክንያት ሲያስሚዱ “ዹተሰጠን ፍቃድ እሱን አልፈቀደልንም ነበር። ስለዚህ በቮሌ ብር ሌሎቹን አገልግሎቶቜ እዚሰጠን ኚብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ለማግኘት ሥራዎቜን ስንሰራ ቆይተናል” ብለዋል። ለመሆኑ አገልግሎቶቹ ምንድን ናቾው? በ቎ሌብር አማካኝነት በቅርቡ ዚተጀመሩት ሊስት አገልግሎቶቜ ተጠቃሚዎቜ ያለዋስትና/ማስያዣ እንዲበደሩ ወይም እንዲቆጥቡ ዚሚያስቜሉ መሆናቾውን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ለቢቢሲ ገልጞዋል። ይህ ዚ቎ሌብር አገልግሎት ደንበኞቜ ገንዘብ ዚሚቆጥቡበት ሲሆን፣ ለተቀማጭ ገንዘብ ወለድ ዚሚኚፈልበትን እና ኚወለድ ነጻ ዹሆነ አመራጮቜን አካቷል። እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ገለጻ፣ ወለድ ዚሚኚፈልበት ቁጠባ በዹቀኑ ዹሚሰላ እና ደንበኞቜ በቀን ያገኙትን መጠን ዚሚያመላክት ነው። ዚ቎ሌብር ደንበኞቜ ግብይት እዚፈጞሙ ገንዘብ በሚያንሳ቞ው ጊዜ ቀሪውን ገንዘብ ዚሚያገኙት ሥርዓት ደግሞ እንደኪሎ ይሰኛል። እንደኪሎ ደንበኞቜ ለግብይት ኚሚያጥራ቞ው ገንዘብ በተጚማሪ እንደ ዚኀሌክትሪክ እና ውሃ ያሉ ዚአገልግሎት ክፍያዎቜን ለመፈጾምም ያስቜላል። ይህ አሰራር ደንበኞቜ ለክፍያ ዹጎደላቾውን እስኚ 2 ሺህ ብር ዹሚሾፍንም ነው። ቎ሌብር መላ፣ ደንበኞቜ ዚብድር አገልግሎት ዚሚያገኙበት መንገድ ሲሆን ግለሰቊቜን እና ዚንግድ ተቋማትን ዚሚያካትት ነው። በ቎ሌብር መላ ግለሰቊቜ በወር እስኚ 10 ሺህ ብር፣ ዚንግድ ተቋማት ደግሞ እስኚ 100 ሺህ መበደር እንደሚቜሉ ዚሚያስሚዱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋፀ ግለሰቊቜ ዚተበደሩትን በቀን፣ በሳምንት እና በወር መመለስ ዚሚቜሉበትን አሰራር ማቀፉን ጠቅሰዋል። ለንግድ ተቋማት ደግሞ ለግለሰቊቜ ኹተጠቀሰው ዹጊዜ ገደብ በተጚማሪ ዚ3፣ ዹ6 እና ዹ9 ወር ዚሚመልሱበትን አሰራር አካትቷል። ቎ሌብር መላ “ለሥራ ማስኬጃ እንዲሁም አዳዲስ ሃሳብ ኖሯ቞ው ወደ ንግድ መግባት ለሚፈልጉ ሰዎቜን ታሳቢ አድርጎ ዹቀሹበ ነው። ለዚያ ነው በፋይናንስ አገልግሎት ተደራሜ ያልሆነውን ማኅበሚሰብ፣ ተደራሜ ለማድሚግ ትልቅ አቅም ይሆናል ብለን ያሰብነው” ሲሉም አክለዋል። መላ፣ እንደ ኪሎ እና ሰንዱቅ በተሰኙት ዚ቎ሌብር አገልግሎቶቜ በመጀመሪያ ዓመት ውስጥ በዚወሩ በአማካኝ ኹ3 እስኚ 4 ሚሊዮን ደንበኞቜን ለማገልገል እና ኹ19.5 እስኚ 20 ቢሊዮን ብር ለማንቀሳቀስ ማቀዱን ኃላፊዋ ጠቅሰዋል። ኹዚህም ውስጥ ትልቁን ድርሻ ዚሚወስደው ዚብድር አገልግሎቱ ወይም ቎ሌብር መላ ሲሆን 9.8 ቢሊዮን ብር ይሞፍናል። 6.4 ቢሊዮን ብር ክፍያን ለማጠናቀቅ ወይም እንደ ኪሎ ለተባለው አገልግሎት እንዲሁም 3.3 ቢሊዮን ብር ደግሞ በቁጠባ ወይም ሳንዱቅ በተሰኘው አገልግሎት ዹሚጠቃለል ነው። ደጋግመው ብድር ዚሚወስዱ ደንበኞቜን ጚምሮ በዓመት 108 ሚሊዮን ደንበኞቜን ለማገልገል ማታቀዱንም አስሚድተዋል። አገልግሎቶቹ በተጀመሩ በቀናት ውስጥ ዚዕለት ብድር ወስደው ዚሚመልሱ እንዲሁም ዚሚቆጥቡ ደንበኞቜ መኖራ቞ውን ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ተስፋ ሰጪ እና “አስገራሚ” ሁኔታዎቜ መኖራ቞ው ገልጞዋል። በ቎ሌብር መላ ዹሚሰጠው ብድር በሙሉ ዋስትና ወይም ማስያዣ እንደማይጠዚቅበትም ጹምሹው አስሚድተዋል። ዚፋይናንስ ተቋማት ለሚያበድሩት ገንዘብ ዋስትና ወይም ማስያዣን መጠዹቅ ዹተለመደ አሰራራ቞ው ነው። ኹዚህ አሰራር በተቃራኒ በ቎ሌብር ዚሚቀርቡ ብድሮቜ ዋስትና አይጠዚቅባ቞ውም። ሆኖም ሥርዓቱን በሚንቀሳቀስበት ዹሰው ሰራሜ አስተውሎት ወይም አር቎ፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት ዚደንበኞቜን ዚወጪ ገቢ ዝውውር በመመልኚት ዚብድሩን መጠን ይፈቀዳል። ሥርዓቱ ደንበኛውን በገንዘብ ዝውውሩ በመመልኚት በተለያዩ ደሚጃዎቜ ዚሚገለጜ ነጥብ ዚሚሰጥ ሲሆን፣ ብድር ለሚመልሱ ደንበኞቜ ደግሞ ዚተሻለ ቡድር ማግኘት ዚሚቻልበትን ነጥብ ይሰጣል። አገልግሎቱ በ቎ሌብር ሞባይል መተግብሪያ  ወይም #127# አጭር ቁጥር አማካኝነት ዚሚቀርብ ሲሆን፣ ዚኢትዮ ቎ሌኮም ሲምካርድ ላላቾው ደንበኞቜ በሙሉ በ቎ሌብር ያላ቞ውን ዚገንዘብ ዝውውር መሰሚት አድርጎ ብድርን ዚሚያቀርብ ነው። እነዚህ አገልግሎቶቜን ለማስጀመር ዚአዋጪነት ጥናት መካሄዱን ዚሚያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፣ እንደ ማንኛውም ዚፋይናንስ አገልግሎት ስጋት ሊኖር እንደሚቜል ታሳቢ መደሹጉን ጠቅሰዋል። በተጚማሪም ይህ አገልግሎት ዚኢትዮጵያን ባህል ኚግምት ውስጥ ማስገባቱን በማንሳት “ሁሉም ደንበኛ አይመለስም ብለን ልንወስድ አንቜልም። . . . ተበድሮ አልመለሰም መባልን ዹማይፈልግው ዚማኅበሚሰባቜን ክፍል ሰፊ ነው። እርሱን እንደ ጥንካሬ ወስደነዋል።” አክለውም “ . . . አንዮ ብድሩን አልመለሰም ማለት በሚቀጥለው ብድር አያገኝም። ስለዚህ አንዮ ሁለት ሺህ ብር ተበድሮ ቢጠፋ ነው ዚሚሻለው ወይስ በዓመት ሁለቮም ሊስ቎ም ሁለት ሺህ፣ አራት ሺህ ቢበደር ነው ዚሚሻለው? ለማኅበሚሰቡ ዚምናስሚዳው ይህንን ነው። ይህ ይሆናል ብለን አንጠብቅም። ባለማወቅ ሊፈጠር ይቜላል። ለዚያ ግን ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ሥራ እንሰራለን። ምንም ቜግር አያጋጥመንም ግን አንልም። በፋይናንስ ሮክተር ያሉ እንደሚያውቁት በዋስትና ዹሚሰጠው ብድርም ላይመለስም ይቜላል። ግን ኚቁጥጥር ውጪ አይሆንብንም። እሱን አጥንተን ነው ዚገባነው” ብለዋል። ሥርዓቱ ላይ ይህ ቜግር ሊያጋጥም ይቜላል በሚል ይህንን ኹመተግበር ወደ ኋላ አንልም ዚሚሉት ፍሬህይወት “60 በመቶ ዚኅበሚተሰብ ክፍል ዚፋይናንስ አገልግሎት ዚማያገኝበት አገር ላይ ሆነን ሪስክ [ስጋት] አለ ብለን ዚገንዘብ ቜግር ኚመፍታት አንጻር ትልቅ አቅም ዹሆነውን አለመጀመር ደግሞ ተገቢ ነው ብለን አናስብም. . .” ስለዚህም ይህንን በአግባቡ ተጠቅመው ኑሯ቞ውን፣ ሕይወታ቞ውን፣ ቀተሰባ቞ውን ሊቀይሩ ዚሚቜሉ ሚሊዮኖቜ ስላሉ ዚእነርሱን ዕድል ለማስፋት ዹተጀመሹ ሥራ መሆኑን ዚገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፣ “ሙሉ በሙሉ ስጋት (ሪስክ) ዹለውም ብለን ሳይሆን መልካም ጎኑን ይዘን ነው ዚተነሳነው” ሲሉም አክለዋል። ወደ አገልግሎት ኚገባ 1 ዓመት ያለፈው ቎ሌብር 22.2 ሚሊዮን ደንበኞቜን ማፍራቱን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ያስሚዳሉ። በእነዚህ ጊዜያትም 34.1 ቢሊዮን ብር ዚገንዘብ ዝውውር ተኚናውኖበታል። ኚዝውውሩ 18 በመቶ ዹሚሆነው ገንዘብ ማውጣት እና ማስገባት ሲሆን 40 በመቶ ደግሞ ዹአዹር ሰዓት መሙላትን ነው። ገንዘብ መላላክ፣ ዚአገልግሎት ክፍያ እና ግብይት መፈጾም ደግሞ ዹተቀሹውን ድርሻ ይይዛል። ዚግብር፣ ዚውሃ፣ ዚኀሌክትሪክ እና መሰል አግልግሎቶቜን ኚሚሰጡ በርካታ ዚመንግሥት ተቋማት፣ ኹ13 ባንኮቜ እንዲሁም ኹ22 ሺህ ዚንግድ ተቋማት ጋር ዚተሳሰሚው ቎ሌብር  በመላው አገሪቱ ኹ79 ሺህ በላይ ወኪሎቜ እንዳሉትም ኃላፊዋ ጠቅሰዋል። “ይህንን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካታቜንን እንደ ትልቅ ስኬት እንወስደዋለን” ዚሚሉት ኃላፊዋ ቎ሌብር ዚገንዘብ ዝውውር እና ክፍያን ምቹ እና ቀልጣፋ ማድሚግ፣ ዚክፍያ ሥርዓትን ማዘመን እና ዚዲጂታል ኢኮኖሚን በማስተዋወቅ በፋይናንስ አገልገሎት ያልተካተተውም ሕዝብ ተደራሜ ማድሚግ ዋነኛ አላማው እንደሆነ አንስተዋል። እስካሁን ቎ሌብር “ዚክፍያ ሥርዓቱን ሲያሳልጥ ዹቆዹ” ሲሆን በፋይናንስ ሥርዓት ተደራሜ ያልሆኑ ሰዎቜን ተደራሜ ዚማድሚግ ቀዳሚ ዓላማውን ለማሰካት በቅርቡ ይፋ ዚሆኑት ዓላማዎቜ ወሳኙን ሚና እንደሚጫወቱ ጠቅሰዋል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cy0xj34y9l7o
amh
business
ቻይና ዝናብ ለማዝነብና ዚተፈጥሮ ሂደትን ለመቆጣጠር ዚምታደርገው ጥሚት
እንደ ቻይናዋ ቀይጂንግ ዹአዹር ብክለት ዚሚፈትነው ኹተማ ዚለም። ዚቀይጂንግ ሰማይ በመጠኑም ቢሆን ጠርቶ ፀሐይ ዚምትታዚው በኹተማዋ ዚሚካሄድ ዓለም አቀፍ ውይይት ሲኖር ነው። ይህ ዹሚሆነው በተፈጥሯዊ ሂደት ሳይሆን መንግሥት በቀዹሰው ስልት አማካይነት ነው። ዚቻይና መንግሥት ዚአገሪቱን ዹአዹር ሁኔታ ለመለዋወጥ ሰው ሠራሜ መንገድ መጠቀም ጀምሯል። ይህ ሰው ሠራሜ ሂደት በጥቂት ዚቻይና ኚተሞቜ ብቻ ይተገበር ነበር። ኚጥቅምት ወዲህ ግን አገር አቀፍ እንደሚሆን ተነግሯል። ሂደቱ በሰው ሠራሜ መንገድ ዝናብ እንዲጥል ማድሚግ፣ በሚዶ ማዝነብ ወዘተ. . . ያካትታል። እአአ በ2015 ይህን ሂደት በቻይና 5.5 ሚሊዮን ስኩዌር ኪሎ ሜትር ማለትም ዚአገሪቱን 60 በመቶውን ለማዳሚስ ታቅዷል። እቅዱ እንደ ሕንድ ላሉ ጎሚቀት አገሮቜ አልተዋጠላ቞ውም። ቻይና እና ሕንድ ኚድሮውም ውጥሚት ውስጥ ና቞ው። ቻይና ዹአዹር ሁኔታን ዚምትለውጠው እንዎት ነው? በእንግሊዘኛው ክልውድ ሲዲንግ (cloud seeding) በሰው ሰራሜ መንገድ ዝናብ እንዲጥል ዚሚደሚግበት ቮክኖሎጂ ነው። ለዚህም ሲልቚር አዮዳይድ ዚተባለ ንጥሚ ነገር ወደ ደመና በመላክ ዹአዹር ሁኔታ ዚሚለወጥበት ሂደት ነው። በሕንድ ዹአዹር ሁኔታ ባለሙያው ዳናስሪ ጃይራም "ይህንን ቮክኖሎጂ ብዙ አገሮቜ ይጠቀሙበታል። ቻይናና ሕንድም ይጠቀሳሉ" ይላሉ። ኚሰሀራ በታቜ ባሉ ዚአፍሪካ አገራትም ይህ ሂደት ይተገበራል። እንደ አውስትራሊያ ያሉ አገሮቜ ድርቅን ለመኹላኹል ይጠቀሙታል። ሂደቱ በተለይም በአሜሪካ ኹ1940ዎቹ ወዲህ ነው እዚታወቀ ዚመጣው። ውጀቱ ላይ ጥያቄ ያላ቞ው ባለሙያዎቜ ግን አሉ። በቀይጂንግ ዩኒቚርስቲ ዚሚሠሩት ጆን ሲ ሙር "ውጀታማነቱን ዹሚጠቁሙ ጥቂት ሳይንሳዊ ጜሑፎቜ ብቻ ናቾው ያሉት። ያለ ሳይንሳዊ ማሚጋገጫ ዹተተገበሹ ሂደት ነው" ይላሉ። ሳይንቲስቱ እንደሚሉትፀ 50 ሺህ ዚቻይና ኚተሞቜና ወሚዳዎቜ ይህንን መንገድ ተጠቅመው ዚእርሻ መሬታ቞ውን ለማዳን ይሞክራሉ። ዝናብን በማስቆም ማዕበል ሰብላ቞ውን እንዳያጠፋው ለመኹላኹል ይጥራሉ። ሆኖም ግን ተመራማሪዎቜ እንደሚሉት ይህ ሂደት ቻይና ውስጥ ዚሚሠራው ለአንድ ወይም ለሁለት ወራት ነው። ዝናብ ዹማነው? ቻይና ዹአዹር ሁኔታን በመቆጣጠር ተፈጥሯዊ አደጋ እንዳይኚሰት ዹመኹላኹል እቅድ እንዳላት አስታውቃለቜ። ሰብል እንዳይበላሜ፣ ሰደድ እሳት እንዳይስፋፋ፣ ኹፍተኛ ሙቀትን ለመቆጣጠር፣ ድርቅን ለመግታት ወዘተ. . . ይውላል። ቀይጂንግ ውስጥ ዚምትሠራው ጋዜጠኛ ይትሲንግ ዋንግ እንደምትለው ቻይና ዹአዹር ሁኔታን ለመቆጣጠር ያወጣቜው መርሃ ግብር ሲተገበር ኚግዛት ግዛት ይለያያል። ሂደቱ ላይ ዚሚነሱ ጥያቄዎቜ ቻይናን አላሳሰቧትም። ዚቻይና ውሳኔ ኚጎሚቀት አገሮቿ ጋር ያላትን ዚፖለቲካ ፍጥጫ ሊያባብሰው ይቜላል። "ዚቻይና ዹአዹር ሁኔታ ዚመለወጥ ሂደትደ ዚሕንድ ዚክሚምት ዝናብ ላይ ተጜዕኖ ሊያሳድር ይቜላል ዹሚል ስጋት አለ" ሲሉ ዚሕንዱ ተመራማሪ ያስሚዳሉ። በቻይና እና ሕንድ ዚድንበር ግጭት ሳቢያ ሕንድ ውስጥ ለቻይና ያለው አመለካኚለት እዚጠለሞ ነው። ዹአዹር ሁኔታ ለውጡም ኹዚሁ ጋር ተያይዞ ይታያል። በታይዋን ዩኒቚርስቲ በ2017 ዚተሠራ ጥናት እንደሚያሳዚውፀ ዹአዹር ሁኔታ ለውጥ ሲደሚግ ኚጎሚቀት አገራት ጋር ውይይት ካልተደሚገ ግጭት ሊነሳ ይቜላል። ዚአንድ አገር ዚዝናብ መጠን ሲቀንስ ሌላውን አገር ተጠያቂ ዚማድሚግ ሁኔታ ይፈጠራል። "ይህ ስጋት ሳይንሳዊ አይደለም። ሆኖም ግን ዚቲቀት ተራራ ዹአዹር ሁኔታ ዚተለያዚ መሆኑ ኚግምት መግባት አለበት። ስለዚህ አንድ አካባቢ ዹአዹር ንብሚት ለውጥ ሲኚሰት ሌላው ላይ ተጜዕኖ ማሳደሩ አይቀርም" ሲሉ ሳይንቲስቱ ጆን ሲ ሙር ያስሚዳሉ። ቻይና ዹተለጠጠ እቅድ በማንገብ ሌሎቜም ዘርፎቜ ላይ ለውጥ ልታካሂድ እንደምትቜል ባለሙያዎቜ ይሰጋሉ። ይህም በሰው ሠራሜ መንገድ ዹፀሐይ ጚሚራን ለመቆጣጠር መሞኹርን ያካትታል። እነዚህ ውሳኔዎቜ ዚሚተላለፉት ኚጎሚቀት አገሮቜ ጋር ባለው ውጥሚት ሳቢያ ሊሆን ይቜላል ዹሚል መላ ምትም አለ። ሳይንቲስቱ በበኩላ቞ው "ቮክኖሎጂው ቜግር አለው እያልኩ አይደለም። ነገር ግን በቮክኖሎጂው አንዳቜ ቜግር ቢኚሰት በምን መንገድ ይፈታል? ኃላፊነቱንስ ዚሚወስደው ማን ነው? ለሚለው መልስ ሊኖር ይገባል" ይላሉ። በተጚማሪም ዹአዹር ሁኔታን መለወጥን ዹመሰሉ ሂደቶቜ ዓለም አቀፍ ውይይት እና ስምምነት እንደሚፈልጉ ባለሙያው ያስሚዳሉ። ሂደቱ ዚሚተገበርበት ወጥ አሠራር እንዲሁም ሂደቱን ተኚትሎ ግጭት ቢነሳ በምን መንገድ መፈታት እንደሚቜል አስቀድሞ መታሰብ አለበት ሲሉም ያክላሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-56099470
amh
business
ፓኪስታን ፡ በካርቱን ስዕል ምክንያት ዚፈሚንሣይ ምርቶቜን መጠቀም ልታቆም ነው
አንድ ዚፓኪስታን እስላማዊ ቡድን ዚጠራውን ዹፀሹ-ፈሚንሳይ ተቃውሞን ዚፓኪስታን መንግሥት ዚፈሚንሳይ ምርቶቜን ላለመጠቀም በመወሰኑ ማቋሚጡን አሳወቀ። ሰልፎቹ ዚተጠሩት ፈሚንሳይ ዚነቢዩ ሙሐመድን ካርቱን ዚማሳዚት መብትን በመደገፏ ነበር። አንድ መምህር በክፍል ውስጥ በነበሹ ውይይት ወቅት ዚነቢዩ መሐመድን ካርቱን ካሳዩ በኋላ መገደላቾውን ተኚትሎ ዚፈሚንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን አገራ቞ው በሐይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አትገባም ሲሉ በጥብቅ ተኚላክለዋል። ይህም በሙስሊሙ ዓለም ቁጣን ቀስቅሷል። ዚአክራሪው ተህሪክ ኢ-ላባይክ ፓኪስታን (ቲ.ኀል.ፒ) ዹተሰኘው ቡድን አባላት ዚፈሚንሳይን ምርት ላለመግዛት ዹቀሹበውን ውሳኔ ዹደገፉ ቢያንስ ዚሁለት ሚኒስትሮቜን ፊርማ ያካተተ ዚስምምነት ቅጅዎቜን አሳይተዋል። ዚፓኪስታን መንግስት በጉዳዩላይ በይፋ መግለጫ ካለመስጠቱም በላይ ዚፈሚንሳይ ምርቶቜን ያለመጠቀም አድማው እንዎት እንደሚተገበር አላሳወቀም። በፈሚንሣይ እስልምናን አስመልክቶ በሰጡት አስተያዚት ማክሮንን ኚተቹ ዚፖለቲካ መሪዎቜ መካኚል ዚፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካን አንዱ ና቞ው። ተቀዋሚዎቹ አሁንም ተጚማሪ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። ደጋፊዎቜ ኚእሁድ ጀምሮ ወደ መዲናዋ ኢስላማባድ ዚሚወስደውን ቁልፍ መንገድ በመዝጋታ቞ው ኹፍተኛ ዚእንቅስቃሎ መስተጓጎል አስኚትሏል። ዚቲ.ኀል.ፒ አመራሮቜ መንግሥት ለጥያቄዎቻ቞ው ምላሜ መስጠቱን ኚተናገሩ በኋላ ተቃውሞው እንዲቋሚጥ ተጠይቋል። ዚቡድኑ ቃል አቀባይ ዚሆኑት ኢጃዝ አሜራፊ ለሮይተርስ እንደተናገሩት "ዚፈሚንሳይ ምርቶቜን እንደማይጠቀም መንግሥት በይፋ እንደሚደግፍ ስምምነት ኹፈሹመ በኋላ ዹተቃውሞ ሰልፎቻቜንን እያቆምንው ነው" ብለዋል። ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ ዹተደሹገው ዚስምምነት ሰነድ ዚሐይማኖታዊ ጉዳዮቜ ሚኒስትሩን እና ዹአገር ውስጥ ሚኒስትሩን ፊርማ ይዟል። ዚፈሚንሣይ አምባሳደር ኹአገር እንዲወጡ በማድሚግ ዙሪያ ላይ ፓርላማው እንዲወስን መንግሥት ሐሳብ እንደሚያቀርብም ገልጿል። ዚፓኪስታን መንግሥት በስምምነቱ ላይ ዹሰጠው አስተያዚት ዚለም። ቲ.ኀል.ፒ ቀደም ሲል ሐይማኖታዊ ስድብን ምክንያት በማድሚግ ተቃውሞ ለማሰማት እጅግ ብዙ ሰዎቜን በመሰብሰብ ይታወቃል። በፓኪስታን ሕግ መሠሚት ነቢዩ ሙሐመድን በመሳደብ ጥፋተኛ ዚተባሉ ሰዎቜ ዚሞት ቅጣት ሊጣልባ቞ው ይቜላል። በፈሚንሳይ ዚመንግሥት በሐይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ ያለመግባት ዚአገሪቱ ዋነኛ መገለጫ ነው። በትምህርት ቀቶቜ እና በሌሎቜ ሕዝባዊ ቊታዎቜ ሀሳብን በነፃነት መግለጜም ዹዚህ አካል ሲሆን ዚአንድን ዹተወሰነ ሐይማኖት ስሜት ለመጠበቅ ዚሃሳብ ነጻነቱን መግታት ብሔራዊ መገለጫውን እንደሚያደፈርስ ተደርጎ ይወሰዳል። 'ቻርሊ ሄብዶ' ዹተሰኘው መጜሔት ዚነቢዩ ሙሐመድ ካርቱን ይዞ መውጣቱን ተኚትሎ እ.አ.አ በ2015 በፓሪስ ውስጥ ዚጥቃት ዒላማ ቢሆንም ዚካቶሊክን እና ዚአይሁድን እምነት ጚምሮ ሌሎቜ ሐይማኖቶቜም ዚሚያመለክቱ ስዕሎቜን ይዞ ወጥቷል። ዚፈሚንሣይ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቀደም ሲል በበርካታ ሙስሊሞቜ በብዛት በሚገኙባ቞ው አገሮቜ ውስጥ ዚፈሚንሳይ ሞቀጊቜን ላለመጠቀም ዹሚደሹጉ ጥሪዎቜን "መሠሹተ ቢስ" ብለው "በአፋጣኝ መቆም" እንዳለባ቞ውም ገልጾው ነበር። ባለፈው ወር ለተገደሉት መምህር ክብር ዚሰጡት ፕሬዝዳንት ማክሮን ፈሚንሳይ "ካርቱኑን አታቆምም" ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54970898
amh
business
እዚበሚታ በመሄድ ላይ ያለው ዹዋጋ ንሚት አዙሪት
ባለፉት ጥቂት ወራት ዚሞቀጊቜ ዹዋጋ ንሚት እና አጠቃላይ ዚኑሮ ዋጋ መወደድ በልዩ ልዩ ዚኢትዮጵያ ዚብዙሃን መገናኛዎቜ ተደጋግመው ዚሚወሱ ጉዳዮቜ ሆነዋል። ዚመንግሥት ኃላፊዎቜ እና ዚሚመለኚታ቞ው መስሪያ ቀቶቜም ዚቜግሩን አሳሳቢነት ኹመቀበል በዘለለ እዚተወሰዱ ናቾው ዹሚሏቾውን እርምጃዎቜ ሲናገሩ ተስተውለዋል። በወርሃ ግንቊት 2011 ዓ.ም መገባደጃ ላይ በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር በምክትል ኚንቲባ ማዕሹግ ዚንግድ እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዚሆኑት ኢንጂነር እንዳወቅ አብጀ በመዲናዋ በግንባታ ዕቃዎቜ፣ በእህል፣ በጥራጥሬ እና በአትክልት ምርቶቜ ላይ ዹዋጋ ጭማሪዎቜ መኚሰታ቞ውን ጠቅሰዋል። እንደመፍትሄም ቜግሩን አባብሰዋል ያሏ቞ው ህገ ወጥ ነጋዎዎቜን ወደ ህጋዊ መስመር ማምጣት፣ ፈቃደኛ ያልሆኑት ላይ ደግሞ ይህንን ዚሚኚታተል ግብሚ ኃይል በማቋቋም እርምጃ መውሰድ፣ እንዲሁም ቜግሩን በዘላቂነት ለመቅሹፍ ዚአቀርቊት ሥርዓቱን ማሰተካኚል ዹኹተማዋ አስተዳደር ዚሚያኚናውና቞ው ተግባራት መሆናቾውን ገልፀው ነበር። • "ኢህአዎግ ነፃ ገበያም፣ ነፃ ፖለቲካም አላካሄደም" ፀደቀ ይሁኔ (ኢንጂነር ) • "መንግሥት ዹዋጋ ንሚቱን ለመቆጣጠር መሰሚታዊ ዚምግብ ሞቀጊቜን ያስገባል"ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ይሁንና ክሚምቱ ሲገባ ዹዋጋ ንሚቱ ኚመርገብ ይልቅ ኹፍ ብሎ ታይቶ ዹዋጋ ግሜበቱ ባለሁለት አሀዝ ሆኗል። በወርሃ ነሐሮ እንዲያውም ባለፉት ስድስት ዓመታት ኚታዚው ዹዋጋ ግሜበት መጠን ኹፍተኛው ተመዝግቧል። ዚሞቀጊቜ ዹዋጋ ንሚት ህይወታ቞ው ላይ ቀጥተኛ ጫና ካሳሚፈባ቞ው ዚአዲስ አበባ ኗሪዎቜ መካኚል ደግሞ ዚአርባ ዓመቱ ጎልማሳ ጋሹ መርኚቡ አንዱ ነው። በአዲስ አበባ ኹተማ ልደታ ክፍለ ኹተማ ውስጥ ዹሚኖሹው ጋሹ ላለፉት ኚአስራ ለሚልቁ ዓመታት በሚኒባስ ታክሲ ሟፌርነት ቀተሰቡን ሲያስተዳድር ኖሯል። ኚቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን "ዚኑሮ መወደድ ኹአቅሜ በላይ ሆኖ እያንገዳደገደኝ ነው" ይላል። "በዋጋ ላይ ያለውን ለውጥ ኹቀን ወደ ቀን እያዚሁት ዚመጣሁት ጉዳይ ነውፀ በእኔ [ህይወት] እንኳ ታክሲ ሠርቌ ብሩን á‹­á‹€ ብገባም ምንም ዹሚገዛው ነገር ዹለም" ይላል ኚቢቢሲ ጋር በነበሹው ቆይታ። "ዚልጆቜ ትምህርት ቀት፣ ዚእህሉ ውድነት፣ እንዲያውም ተስፋ ወደማስቆሚጥ ደሹጃ እዚደሚሰ ያለ ይመስለኛል" ይላል። መጪውን ፍራቻ ጋሹ ዚአራት ልጆቜ አባት ሲሆን ትልቋ ዚአስራ ሁለት ዓመት ልጁ ዚስድስተኛ ክፍል ተማሪ ናት። ሌሎቹ ሊስት ልጆቹም በመዋዕለ ሕፃናት እና በአንደኛ ደሹጃ ትምርት ቀቶቜ ውስጥ ይማራሉ። ባለፉት ዓመታት ሁሉንም ልጆቹን በግል ትምህርት ቀቶቜ ያስተምር ዹነበሹ ሲሆን አሁን ግን በኑሮ ውድነት ላይ በዹጊዜው ዹሚጹምሹውን ዚትምህርት ቀት ክፍያን መቋቋም ባለመቻሉ አንደኛውን ልጁን ዚመንግሥት ትምህርት ቀት፣ ሁለቱን ደግሞ በለጋሜ ድርጅቶቜ በሚደጎም እና በዚህም ምክንያት በአንፃራዊነት አነስተኛ ኚፍያ ወደሚጠይቅ ትምህርት ቀት አስገብቷል። ለእያንዳንዳ቞ው በዚወሩ ሊስት መቶ ብር በመደበኛነት ይኚፍላል። • ኢትዮጵያዊያን ለምን ሥጋ አይመገቡም? • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ዚኖቀል ዹሰላም ሜልማትን ሊያሞንፉ እንደሚቜሉ ግምቶቜ አሉ አንደኛዋን ልጁን ብቻ በግል ትምህርት ቀት መማሯን እንድትቀጥል አድርጓል። ለብ቞ኛዋ ዹግል ትምህርት ቀት ተማሪ ልጁ መደበኛ ክፍያ ብቻ በዓመት ኚአስር ሺህ ብር በላይ ያወጣል። ይህም ዚትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ፣ ዚአልባሳት፣ ዚምግብ ወጪዎቜ ሲደመሩበት "ናላን ዚሚያዞር" ሆኗል ይላል ጋሹ። በዚህ ላይ ዚቀት ኪራይ ወጪ ይታኚልበታል። "ህይወታቜንን ለማቆዚት እዚሰራን ነው እንጅ እዚኖርን ነው ብዬ አላወራውም።" አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ መጪውን ጊዜ ይበልጥ እንዲፈራው እንዳደሚገው ይናገራል ጋሹፀ "ወደፊት እንዎት እንደማስተምራ቞ው ራሱ ግራ ግብት እያለኝ ነው" በማለት። ተስፋው ኚዕለት ወደ ዕለት እንዲሟጠጥ አንድ ምክንያት ዹሆነው እርሱን ለመሰሉ ኚኑሮ ጋር እልህ አስጚራሜ ግብግብ ለገጠሙ ሰዎቜ በፖለቲካ ልሂቃን ዘንድ ብዙም ትኩሚት እዚተሰጠ አይደለም ብሎ ማመኑ ነው። • ‹‹እነ ቮሌን ለግል ባለሀብት?›› ታሪካዊ ስህተት ወይንስ መልካም አጋጣሚ ? ዚፖለቲካ ልሂቃኑ "በብሔርም ጉዳይ፣ በምንም ጉዳይ ዚራሳ቞ውን ለማመቻ቞ት እንጂ ዚድሃውን [ጉዳይ] አንስቶ ልብህን [ዚሚነካ] ነገር ሲናገሩ እኔ እስካሁን ሰምቌም አላውቅም። ዚራሳ቞ውን ጉዳይ ኚማስፈፀም በስተቀር ውስጥህን ዚሚነካ ነገር፣ ስለኑሮህ፣ ስለሜንኩርት ዚሚያወራ ዹለም" ይላል። ኚጋሹ አስተያዚት ጋር በሚስማማ መልኩ አጠቃላይ ምርጫ በሚኚናወንበት ዓመት በፖለቲካዊ መድሚኮቜ ላይ ዹዋጋ ንሚት ዚሚገባውን ያህል ስፍራ ይዞ ያለመታዚቱ እንደሚገርማ቞ው ዚሚያስሚዱት ዚምጣኔ ሃብት ዚፖሊሲ ተንታኝ ዚሆኑት አሚን አብደላ ና቞ው። "ምርጫ ኖሹም አልኖሚምፀ ዹማንኛውም አገር መንግሥት ፈተና ዹሚሆኑ ሁለት ዚማክሮኀኮኖሚ አመላካ቟ቜ አሉፀ ዚሥራ አጥነት እና ዹዋጋ ንሚት።"‚‚በፖለቲካው መልክዐ ምድር ገኖ ያለው መንግሥታዊው ሥርዓት "ዚፌዎራል ይሁን አይሁን ዹሚል ዓይነት እንጅ ዚሥራ አጥነት እና ዹዋጋ ንሚት ላይ ብዙም ዚፖለቲካ ልሂቃን ሲጚቃጚቁ አይቌ አላውቅም" ባይ ናቾው ተንታኙ። ለአንድ አገር መሚጋጋት እና ዚምጣኔ ሃብት ዕድገት ወሳኝ ናቾው ዹሚሏቾው እነዚህ ጉዳዮቜ ብዙም ያለመነሳታ቞ው "ዋናው ነገር ዹተዘነጋ ይመስለኛል" አስብሏ቞ዋል። ዚምጣኔ ሃብት ፖሊሲ ተንታኙ አሚን አብደላ እንደሚሉት አጠቃላይ ዹዋጋ ንሚት ኹጊዜ ወደጊዜ እዚጚመሚ እንዳለ መሚጃዎቜ ያሳያሉ ይላሉ። በተሰናበተው 2011 ዓ.ም ዹሐምሌ ወር ዹዋጋ ግሜበቱ ኹ15 በመቶ በላይ ደርሶ እንደነበሚ ዚሚያስታውሱት አሚን በወርሃ ነሐሮ ደግሞ ይህ ቁጥር ወደ 18 በመቶ ኹፍ ብሎ እንደነበርም ይጠቅሳሉ። ይህም ቁጥር በስድስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ዚታዚው ትልቁ አሃዝ ነው። ለቁጥሩ ኹፍ ማለት ዚምግብ ዋጋ፣ በተለይም ዚእህል ሰብል ዋጋ ንሚት ምክንያት መሆኑን ዚስታትስቲክስ መሚጃዎቜ ያመላክታሉ። • «አማካሪ አያስፈልገኝም ብሎ ዚሚያስብ መሪ አልገባውም ማለት ነው» ፕሮፌሰር አለማዹሁ ገዳ • በተሻሻለው ዹወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ህግ ሹቂቅ ጥፋተኛና አቃቀ ህግ ይደራደራሉ በዚህ ሚገድ በአንዳንድ ትርፍ አምራቜ በሆኑ አካባቢዎቜ ዹነበሹው ዚፀጥታ ሁኔታ፣ ዚመጓጓዣ አገልግሎት እንደልብ ያለመገኘት እና ኹዚህም ጋር በተያያዘ ምርትን በተፈለገው ደሹጃ ማቅሚብ ያለመቻል ለቜግሩ ምክንያት ሳይሆኑ እንዳልቀሩ ተንታኙ አሚን ያነሳሉ። እዚናሚ ያለውን ዹዋጋ ንሚት ለማቃለል ሁለት ዚመፍትሄ እርምጃዎቜ ሊወሰዱ ይቜላሉ ዚሚሉት ባለሙያውፀ "አንደኛው በአቅርቊት በኩል ሌላኛው ደግሞ በፍላጎት በኩል ያሉ ናቾው" እንደአሚን ገለፃ። "ኚፍላጎት አንፃር ዚመንግሥት ወጪ ዚቀነሰበት ሁኔታ አለ። ያለፉትን ዓመታት ዓይነት እድገት ስለሌለፀ ምጣኔ ሃብቱ ውስጥ ዹሚለቀቀው ዚገንዘብ መጠን ቀነስ ያለ ይመስላል። ይሁንና በአቅርቊት በኩል እምብዛም ለውጥ ያለ አይመስልም" ሲሉ ለቢቢሲ አስሚድተዋል አቶ አሚን። ዚምርቶቜ በተገቢው መጠን አለመገኘት ለዋጋ መወደድ በአንዳንድ ሰዎቜ እንደምክንያት ተደጋግሞ ዚሚነሳ ሲሆንፀ ባለሙያውም በምርት እና በአቅርቊት መካኚል ያለው ሰንሰለት ቜግር እንደሚስተዋልበት ይናገራሉ። "ገበሬው አምርቶ ለምርቱ ዚሚያገኘው ዋጋ እና ኹተማ ላይ መጥቶ ዚሚሞጥበት ዋጋ በጣም ኹፍተኛ ልዩነት አለው። ገበሬው ኚአንድ ኪሎ ሙዝ እያገኘ ያለው ገቢ እና አንድ ኪሎ ሙዝ ኹተማ ውስጥ እዚተሜጠበት ያለው ዋጋ ልዩነት አለው። "በዚህ መካኚል ያለው ዚአገልግሎት፣ ዚደላላ፣ ዚመጓጓዣ፣ ዚቊታ ኪራይ እና ዚመሳሰሉት ወጪዎቜ ኹፍተኛውን ድርሻ ዚሚወሰዱ ና቞ው። ይህ ዚገበያ ሰንሰለት ሥርዓት እሰካልያዘ ድሚስፀ ዚምርቶቜ ዋጋ ኹፍ እንዲል ማድሚጉ አይቀሬ ነው" ለአሚን። • ሞማቹ በውጭ ምንዛሪ ለውጡ ማግስት • ኹጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር ማዕድ ዚቀሚቡት ምን ይላሉ? ኹውጭ ዚሚመጣ ዹዋጋ ንሚትን ለመቆጣጠር ዚንግድ ውድድርን ማሳለጥ እንዲሁም ዚሞማ቟ቜን ጥበቃ ማጠናኹር ይገባል ዚሚሉት ባለሞያውፀ ኹውጭ ዚሚመጡ ምርቶቜን ዚሚያስመጡ ተቋማት እና ግለሰቊቜ በዚተሰማሩበት ዘርፍ ጥቂት መሆናቾው ዋጋው ላይ ኚሚገባው በላይ ጫና እንዲፈጠር መንገዱን ይጠርጋል ባይ ናቾው አቶ አሚን። ኹውጭ ዚሚመጣ ዹዋጋ ንሚት በውጭ ምንዛሬ እጥሚት ምኚንያትም ሊኚሰት ቢቜልም በእኛ አገር እዚተስተዋለ ያለው እውነታ ግን በውጭ ምንዛሬው እጥሚት መጠን ያህል መኖር ኚሚገባው በላይ ጭማሪ ነውፀ ሲሉ ዹዋጋው ጭማሪ አሳሳቢ መሆኑን ይጠቅሳሉ። ባለሞያው አቶ አሚን አብደላ ለፖለቲካዊ ጉዳዮቜ እዚተሰጠ ካለው ጋር ዚሚመጣጠን አትኩሮት ዹዋጋ ንሚትን ለመሳሰሉ ምጣኔ ሃብታዊ ተግዳሮቶቜ መቾር አለበት ባይ ና቞ው። በዚህ አስተያዚታ቞ው ጋሹም ዚሚስማማ ይመስላልፀ "ይሄ ሁሉ እዚታዚ ቾል ዚሚባለው እስኚመቌ እንደሆነ አይገባኝም።"
https://www.bbc.com/amharic/news-49922350
amh
business
ዚአንድ ቢትኮይን ዋጋ 2.4 ሚሊዮን ብር ገባ
ዚአንድ ቢትኮይን ዋጋ ለመጀመሪያ ጊዜ ኹ60 ሺህ ዶላር ወይም 2.4 ሚሊዮን ብር በላይ በመግባት ክብሚ ወሰን ሰብሯል። ቢትኮይን መመንደግ ዹጀመሹው በተለይ ደግሞ ኚባለፈው ዚፈሚንጆቹ ዓመት መገባደጃ አንስቶ ነው። ይህንን ዚማይጚበጥ ዚማይዳሰስ መገበያያ ገንዘብ በርካታ ግዙፍ ድርጅቶቜ እንቀበለዋለን ማለታ቞ው ለዋጋው መናር ምክንያት ሆኗል ተብሏል። በዘርፉ ጥርስ ዹነቀሉ ግን ዚቊትኮይን ዋጋ እንዲህ ያሻቀበው ዚአሜሪካ መንግሥት በኮሮናቫይሚስ ኪሳ቞ው ለተጎዳ ዜጎቜ ዹሰጠውን ድጎማ ተኚትሎ ነው ይላሉ። ዚቢትኮይን ጠቅላላ ዚገበያ ዋጋ አሁን ኹ1 ትሪሊዚን በላይ ሆኗል። ቢሆንም ቢትኮይን ኚተፈጠሚበት ዚፈሚንጆቹ 2009 ጀምሮ ዋጋው አንድ ጊዜ ሲያሻቅብ አንዮ ደግሞ ሲያሜቆለቁል ነው ዚኚሚመው። ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ እዚታዚ ያለው ዚቢትኮይን ማሻቀብ ኹግዙፍ ኩባንያዎቜ ጋር ይያያዛል። ባለፈው ወር በኀሌክትሪክ ዚሚሠሩ መኪናዎቜ ዚሚያመርተው ተስላ ዹተሰኘው ድርጅት ባለቀት ዹሆነው ኢላን መስክ 1.5 ቢሊዮን ዶላር ዚሚያወጣ ቢትኮይን መግዛቱን ይፋ አድርጎ ነበር። አልፎም ድርጅቱ ተስላ ወደፊት ልክ እንደ ወሚቀት ገንዘብ ለመገበያያነት እንደሚያውለው አስታውቆ ነበር። ቢትኮይን ምንድነው? ቢትኮይን ማለት በቀላል ቋንቋፀ ዲጂታል ገንዘብ ወይም መገበያያ ነው ማለት ይቻላል። ይህ መገበያያ በኪሳቜን ተሾክመን እንደምንዞሚው ዚብር ኖት ወይም ሳንቲም ሳይሆን 'ኩንላይን' ዚሚቀመጥ ዲጂታል ገንዘብ ነው። ሌላው ዚቢትኮይንና ዚተቀሩት ዚክሪይፕቶኚሚንሲዎቜ ልዩ ባህሪ በመንግሥታት እና በባንኮቜ አለመታተማ቞ው እንዲሁም ቁጥጥር አለመደሹጉ ነው። ቢትኮይን ዹሚፈጠሹው 'ማይኒንግ' በሚባል ሂደት ነው። በመላው ዓለም በኔትወርክ በተሳሰሩ ኮምፒውተሮቜ ቁጥጥር ይደሚግበታል። ለሚያቀርቡት ምርት እና አገልግሎት ቢትኮይንን በክፍያ መልክ ዹሚቀበሉ በርካቶቜ ድርጅቶቜ አሉ። ማይክሮሶፍት፣ ዚፈጣን ምግብ አቅራቢዎቹ ኬኀፍሲ እና ሰብዌይ፣ ዹጉዞ ወኪሉ ኀክስፔዲያን ኚመሳሰሉ ባለብዙ ሚሊዮን ገንዘብ ኩባንያዎቜን አንስቶ እስኚ ሆ቎ሎቜ እና ካፊ቎ሪያዎቜ ቢትኮይንን በክፍያ መልክ ይቀበላሉ። ቢትኮይንን በመጠቀም ዚገዢው ማንነት ይፋ ሳይደሚግ በዚትኛውም ሰዓት እና በዚትኛውም ስፍራ ዚቢትኮይን ዝውውር ማድሚግ ይቻላል። ሕገ-ወጥ ቡድኖቜ ዹጩር መሳሪያዎቜ እና እጟቜን ሊገዙ እና ሊሜጡ ይቻላሉ፣ ሕገ-ወጥ ዚገንዘብ ዝውውር እና አሞባሪዎቜን ለመደገፍ ያስቜላል በማለት ቢትኮይንን ጚምሮ ሌሎቜ ክሪይፕቶኚሚንሲዎቜ ላይ ያላ቞ውን ስጋት ዚሚያነሱ በርካቶቜ ና቞ው።
https://www.bbc.com/amharic/news-56391321
amh
business
ኚኮሮናቫይሚስ በኋላ ኢኮኖሚያ቞ው በቶሎ ሊያገግም ዚሚቜል አምስት አገራት
ዚኮቪድ-19 ወሚርሜኝ አገራት ኚበሜታ ጋር በሚያደርጉት ትግል በዓለም ምጣኔ ሃብት ላይ አለመሚጋጋትን ፈጥሯል። ኹዚህ አንጻር ኚወሚርሜኙ በኋላ ዚትኞቹ አገራት በተሻለ ወደ ቀድሞ ሁኔታ቞ው እንደሚመለሱ ባለሙያዎቜ ለመገምገም ሞክሚዋል። ይህንን በተሻለ ለመሚዳት ዚኢንሹራንስ ኩባንያ ዹሆነው ኀፍ ኀም ግሎባል ዹ2019 ዓለም አገራት ዚምጣኔ ሃብት ፈተናን ዹመቋቋም አቅም አመላካቜ ደሹጃን ተመለኚትን። በዚህም አገራት ለቫይሚሱ ዚሰጡትን ዚመጀመሪያ ምላሜ ኚግምት በማስገባት ቀውሱን በተሹጋጋ መንገድ ዚሚወጡበትን ሁኔታና ዹመቋቋም ዕድላ቞ው ተቃኝቷል። በደሹጃ ጠቋሚው በሁለተኛ ደሹጃ ዚተቀመጠቜው ዮንማርክ ኚቫይሚሱ ስርጭት አንፃር ማኅበራዊ ርቀት እንዲተገበር በፍጥነት እርምጃ ወስዳለቜ። ጥቂት በበሜታው ዚተያዙ ሰዎቜ እንደተገኙ ነው ትምህርት ቀቶቜን፣ አስፈላጊ ያልሆኑ ሥራዎቜንና ድንበሯን በፍጥነት በመዝጋት ውሳኔዋ ውጀታማ መሆኑን ያሚጋገጠቜው። ዚዎንማርካዊያን ባህል ዹሆነው በመንግሥት ላይ እምነት ማሳደርና ለጋራ ዓላማ አብሮ ዹመቆም ፍላጎት በእርምጃዎቹ ውጀታማነት ላይ አውንታዊ ተጜዕኖ አሳድሯል። እናም ብዙ ሰዎቜ ለሕዝብ ጀና ሲሉ መስዋዕት ዚማድሚግ ዚሞራል ግዎታ እንደሆነ ይሰማ቞ዋል። በዚህ ወቅት ዮንማርክ ዚሠራተኞቜን ደመወዝ እስኚ 90 በመቶ ድሚስ ለመክፈል መወሰኗ እንደ ምሳሌ እንድትታይ አድርጓታል። ይህን ግን ቀላል አይደለም። እርምጃው ኹጠቅላላው ዚአገሪቱ አጠቃላይ ምርት 13 በመቶውን ያህሉን ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ሲንጋፖር በጠንካራ ኢኮኖሚዋ፣ በአነስተኛ ዚፖለቲካ አደጋ፣ ጠንካራ መሠሹተ ልማት እና ዝቅተኛ ሙስና በደሹጃ ጠቋሚው 21ኛ እንድትሆን አድርጓታል። አገሪቱ ቫይሚሱን ለመቆጣጠር በፍጥነት ኚመንቀሳቀስ ባለፈ ስርጭቱም ዹተሹጋጋ ነው። ቫይሚሱን በመዋጋት ሚገድ በግልጜነት በሚሰራው መንግሥት ላይ ሕዝቡ ኹፍተኛ እምነት አለን። መንግሥት አንድ ውሳኔ ካስተላለፈ ሁሉም ተገዢ ሆኖ ተግባራዊ ያደርጋል። እንደ ትንሜ አገርነቷ ዚሲንጋፖር በጣም ስኬታማ መልሶ ዚማንሰራራት ውጀት ለማስመዝገብ በተቀሹው ዓለም ዹማገገም ሂደት ላይ ዹተመሠሹተ ነው። ዚዩናይትድ ስ቎ትስ ሰፊ ጂኊግራፊያዊ ቊታ መያዟ በደሹጃ ጠቋሚው ላይ በሊስት ዚተኚፈለቜ ሲሆን በአጠቃላይ ጥሩ ደሹጃ ይዛለቜ። ቫይሚሱ እንደ ኒው ዮርክ ባሉ ዋና ዋና ኚተሞቜ ውስጥ ፈታኝ ሲሆንፀ ዚሥራ አጥነት መጠኑም ታሪካዊ በሚባል ደሹጃ ኹፍ ብሏል። ኚግማሜ በላይ ዚሚሆኑት ዚአሜሪካ ግዛቶቜ ውስጥ ዹተወሰደው አስገዳጅ ዚእንቅስቃሎ ገደብና ሌሎቜም ለዚህ በምክንያትነት ተቀምጠዋል። ነገር ግን ዚአሜሪካ መንግሥት ኢኮኖሚውን ለማሚጋጋት ዚማነቃቂያ እርምጃዎቜን በፍጥነት መውሰዱና ማኅበራዊ ርቀት መጠበቅ መተግበሩ ውጀት በማምጣት ዚቫይሚሱ አጠቃላይ ተፅእኖን ሊቀንስና ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ማገገም ሊያስገኝ ያስቜላል። 21 ትሪሊዚን ዶላር ዚኢኮኖሚ ማበሚታቻ ይፋ ያደሚገቜው አሜሪካፀ ሩብ ያህሉን ዹዓለም አጠቃላይ ዹአገር ውስጥ ምርትን በመያዟ ወሳኝ ዚሚያደርጋት ሲሆን ዹዓለም ምጣኔ ሃብት ማገገም በአሜሪካ ውጀታማነት ላይ ጥገኛ እንደሆነ ይነገራል። በቅርብ በተደሚጉት በኮርፖሬት አስተዳደር ማሻሻያዎቜ ምክንያት ሩዋንዳ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በደሹጃ ጠቋሚዎቜ ውስጥ ትልቁን መሻሻል በማድሚግ በዓለም ላይ ዹ77ኛ ደሚጃን፣ ኚአፍሪካ ደግሞ ዚአራተኛ ደሹጃን ይዛለቜ። ኹሁሉም በላይ ደግሞ በአውሮፓዊያኑ 2019 በጎሚቀትዋ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ዹተኹሰተውን ዚኢቊላ ወሚርሜኝ ድንበር ላይ በተሳካ ሁኔታ መቆጣጠር ኚቻለቜ በኋላ እንደዚህ ዓይነቱን ቀውስ ለመኹላኹል በጥሩ ሁኔታ ዚተቀመጠቜ ይመስላል። ሁለን አቀፍ ዚጀና አጠባበቅ፣ ዹህክምና ቁሳቁስን በሚያደርሱ ሰው አልባ አውሮፕላኖቜ (ድሮኖቜ) እገዛ እና በድንበር ላይ ዚሙቀት ልዚታ በማድሚግ ሩዋንዳ በዚህ ቀውስ ወቅት ኚሌሎቜ ዚአካባቢው አገራት አንጻር ጥንካሬዋን ጠብቃ ትቆያለቜ። ሩዋንዳ ለቜግር ተጋላጭ ለሆኑ ዜጎቜ ቀት ለቀት ነፃ ምግብ እያሰራጚቜ ዚምትገኝ ሲሆን ይህም ኚሰሃራ በታቜ ካሉ አገራት ዚመጀመሪያዋ ያደርጋታል። ዚቱሪዝም ዘርፉ ኹፍተኛ ጉዳት እንደሚገጥመው ይጠበቃል። ሩዋንዳም ለብዙ ዹዓለም አቀፍ ስብሰባዎቜና ኀግዚቢሜኖቜ ተወዳጅ መድሚሻ ናት። አገሪቱ በኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ምክንያት ህይወታ቞ውን ዚሚያጡ ሰዎቜ ቁጥር አነስተኛ እንደሚሆኑ እና በፍጥነት ለማገገም ዚሚያስቜል ምቹ ሁኔታ እንዳላት ይታመናል። ኒውዚላንድ በደሹጃ ጠቋሚው ዹ12ኛ ቊታን ይዛለቜ። አገሪቱ ድንበሮቜን ለዓለም አቀፍ ተጓዊቜ በመዝጋትና አስፈላጊ ያልሆኑ ሥራዎቜን በፍጥነት በመዝጋት ዚቫይሚሱ ስርጭትን ለመቆጣጠር መንቀሳቀስ ቜላለቜ። ቱሪዝምና ዚወጪ ንግድ ዚምጣኔ ሃብቷ ዋና አካል ሲሆኑ ኒውዚላንድ በቅርብ ጊዜ ውስጥ አንዳንድ ኢኮኖሚያዊ ቜግሮቜ ያጋጥማታል ተብሎ ተሰግቷል። ነገር ግን ይህ ዚግድ መጥፎ ውጀት ላይኖሹው ይቜላል። ወሚርሜኙ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ዚሚያሳርፈው ጉዳት ቀላል ዹሚሆን ባይሆንም ኒወ ዚላንድ ግን ይህንን ተቋቁማ ለማገገም ብዙም እንደማት቞ገር ዚምጣኔ ሃብት ሙያተኞቜ ያምናሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-52217125
amh
business
ላይቀሪያ 4 ሚሊዮን ዶላር ዚሚያወጡ አሮጌ ዚገንዘብ ኖቶቜን አቃጠለቜ
ዚላይቀሪያ ማዕኹላዊ ባንክ ያሚጁ እና ዚተበላሹ ዚገንዘብ ኖቶቜን በአዲስ ለመተካት በሚል አራት ሚሊዮን ዶላር ዚሚያወጡ አሮጌ ዚገንዘብ ኖቶቜን አቃጥሏል። በአገሬውም ዚመገበያያ ገንዘብም ዹተቃጠለው 600 ሚሊዮን ዚላይቀሪያ ዶላር ነው። ዚገንዘብ ኖቶቹ እንዲወገዱ ዚተደሚጉትም መንግሥት ኚቅርብ ዓመታት ወዲህ አዳዲስ ኖቶቜን ቢያትምም አሮጌዎቹ በስርጭት ላይ ይገኛሉ ዹሚለውን ስጋት ተኚትሎ ነው። ኹዚህም በተጚማሪ በአውሮፓውያኑ 2018 ኹፍተኛ መጠን ያለው ዚመንግሥት ገንዘብ ጠፍቷል ዚተባለ ሲሆን እንዲሁም ኹ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዚሚገመቱ አዲስ ዚታተሙ ዚላይቀሪያ ዚገንዘብ ኖቶቜ ጠፍተዋል ዹሚል ክስም እዚቀሚበ ይገኛል። ማዕኹላዊ ባንኩ ይህንን አይቀበለውም ዚተባለው ገንዘብ በባንክ ካዝና ውስጥ መቀመጡን ገልጿል። ዚፕሬዚዳንት ጆርጅ ዊሃ መንግሥት አሮጌውን ዚላይቀሪያ ዶላር ለመተካት እና ዹሀገር ውስጥ ምንዛሬን ለማጠናኹር በዚያው አመት ኚሀገሪቱ ዚመጠባበቂያ ሂሳቊቜ ያወጣውን 25 ሚሊዮን ዶላር እስካሁን አልተካም። ይህንን ሊቀበሉ ያልቻሉ ዚተሟጋቜ ቡድኖቜ ማብራሪያ እና ተጠያቂነት እንዲኖር እዚጠዚቁ ነው። ዚላይቀሪያ ምጣኔ ኃብት ኚቅርብ ዓመታት ወዲህ መንገዳገድ ቢያሳይም ነገር ግን ፕሬዚደንት ዊሃ በዚህ አይስማሙም በቅርቡ ለፓርላማ ባደሚጉት አመታዊ ንግግር ኢኮኖሚው ዹተሹጋጋና እያደገ ነው ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-60229480
amh
business
ምጣኔ ሐብት ፡ ኚብር ለውጡ በኋላ ዹወርቅ ዋጋ ለምን ጹመሹ?
ኚቅርብ ሳምንታት ወዲህ አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ መደብሮቜ ዹወርቅ ዋጋ ጭማሪ ማሳዚቱን ነጋዎዎቜና ገዢዎቜ ለቢቢሲ ገለጹ። ቢቢሲ በመሐል አዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ በሚገኙ ዹወርቅ መሞጫ መደብሮቜ ተዘዋውሮ እንደተሚዳው ዹወርቅ መግዣ እና ዚመሞጫ ዋጋዎቜ ላይ ጭማሪዎቜ ታይተዋል። በተለይ ኢትዮጵያ ዚብር ኖቶቿን መቀዚሯን ይፋ ካደሚገቜበት ኚመስኚሚም ወር መጀመሪያ አንስቶ ጭማሪው በተለይ ኹፍ ማለቱን በአዲስ አበባ ኹተማ በወርቅ ንግድ ላይ ዚተሰማሩ ነጋዎዎቜ እና ሠራተኞቜ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ቢቢሲ አዲስ አበባ ውስጥ ዋነኛ ዹወርቅ መሞጫ መደብሮቜ በሚገኙበት በፒያሳ አካባቢ ቅኝት ባደሚገበት በባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ 21 ካራት ወርቅ በግራም ኚሊስት ሺህ ሰባት መቶ ብር እስኚ አራት ሺህ ብር ይሞጣል መባሉን ኚነጋዎዎቹ ለማሚጋገጥ ቜሏል። ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መስኚሚም አስራ ሰባት ቀን ያስቀመጠው ዹወርቅ ዚመግዣ ዋጋ ለሃያ አንድ ካራት 2012 ብር ኚስድሳ አራት ሳንቲም ሲሆንፀ ዚጥራት ደሹጃው ላቅ ላለው ዚሃያ አራት ካራት ወርቅ ደግሞ 2300 ብር ኚአስራ ስድስት ሳንቲም ዋጋ ሆኖ ተቀምጊለታል። ባለፉት ጥቂት ወራት ዹወርቅ ዋጋ ጭማሪ ሲያሳይ መቆዚቱን ቢቢሲ አግኝቶ ካናገራ቞ው ዹወርቅ መሞጫ መደብሮቹ ባለቀቶቜ እና ሠራተኞቜ ተሚድቷል። ይሁንና ዹወርቅ ዋጋ ጭማሪው በተለይ ዚብር ኖቶቜ መቀዹር ይፋ ኚተደሚገበት ጊዜ አንስቶ ዹበለጠ ኹፍ ማለቱን በወርቅ ንግድ ላይ ዚተሰማሩት ነጋዎዎቜ ጹምሹው ተናግሚዋል። "ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ በግራም እስኚ አምስት መቶ ብር ድሚስ ጚምሯል" ስትል በአንድ ዚጌጣጌጥ መሞጫ መደብር ውስጥ ዚምትሰራ እንስት ለቢቢሲ ተናግራለቜ። ኚግለሰቊቜ ቀለበት፣ ሃብል፣ ዚጆሮ ጉትቻና ዚመሳሰሉ ዹወርቅ ጌጣጌጊቜን በመግዛት አትርፎ በመሞጥ ዚሚተዳደርና ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ አንድ ወጣት ደግሞ ጭማሪው ኚሜያጭ በተጚማሪም በግዢም ላይ እዚተስተዋለ እንደሚገኝ ተናግሯል።‚‚"ኚአንድ ወር በፊት አንድ ግራም ዚሃያ አንድ ካራት ወርቅ አንድ ሺህ ብርፀ ኹፍ ሲል ደግሞ አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር ኹሰው ላይ እገዛ ነበር" ዹሚለው ወጣት "ባለፈው አስራ አምስት ቀን ውስጥ ግን ብዙ ጭማሪ አሳይቷል" በማለት ባለፈው አርብ አንድ ግራም ወርቅ ሁለት ሺህ አንድ መቶ ሃምሳ ብር መግዛቱን ተናግሯል። ኹሌላው ጊዜ በተለዹ ወርቅ ዹሚገዙ ሰዎቜ ፍላጎት መጹመር ዋጋውን ማናሩን ዹሚናገሹው ይህ ወጣትፀ ኚብር ኖቶቜ ቅያሪው ጋር ተያይዞ ዹተኹማቾ ገንዘብን ወደአስተማማኝ ውድ ዕቃ መቀዹር ዹሚፈልጉ ሰዎቜ ሳይኖሩ እንደማይቀሩ ግምቱን አስቀምጧል። "ዚገንዘብ ኖቶቜ ለውጡ ሳይጠበቅ ዱብ ያለ በመሆኑ ውዥንብር እና እርግጠኛ ያለመሆን ስሜቶቜ ፈጥሯል" ዚሚሉት ዚምጣኔ ሐብት ጉዳዮቜ ተንታኙ አብዱልመናን መሃመድ ና቞ው። ኹዚህም ጋር ተያይዞ ገንዘብ በእጃ቞ው ላይ ያላ቞ው ሰዎቜ ደኅንነታ቞ው አስተማማኝ በሆኑ ንብሚቶቜ ላይ ብራ቞ውን ለማዋል መፈለጋቾውን በወርቅ ግብይቱ ላይ ዚታዚውን ዹዋጋ ለውጥ እንደምሳሌ በማንሳት ይገልፃሉፀ "ይህም በእነዚህ ንብሚቶቜ ዋጋ ላይ ዹመናር ምክንያት ሊሆን ይቜላል" ባይ ና቞ው። "መኪና እና ቀትን ዚመሳሰሉ ቋሚ ንብሚቶቜን እንዲሁም ወርቅን ዚመሳሰሉ ሌሎቜ ንብሚቶቜ ላይ ገንዘብን ማዋል እንደአማራጭ ስለሚወሰድ ተፈላጊነታ቞ው መጚመሩ ዹሚጠበቅ ነው" ሲሉ ለቢቢሲ ዚተናገሩት አብዱልመናንፀ በሕገ ወጥ መልኩ ዹተገኘ ገንዘብን ለመሾሾግም ወርቅ ቀላል መንገድ ነው ይላሉ። ‹‹"ስለዚህም ዹወርቅ ዹዋጋ ጭማሪን ዹፈጠሹው ዚገንዘብ ኖት ለውጡ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር ዹለውም" ሲሉ እምነታ቞ውን ይገልጻሉ። ባለፈው ዓመት ወርሃ ግንቊት ላይ ብሔራዊ ባንክ ኹ63 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዚሚገመት ወርቅ ወደ ገበያ መቅሚቡን ገልፆ እንደነበር ይታወሳል። በወቅቱ ዚባንኩ ገዥ ዚሆኑት ይናገር ደሮ (ዶ/ር) ይህ ዹተጠቀሰው ዹወርቅ መጠን ኹፍተኛ እንደነበርና ለመንፈቅ ዓመት ያህል ዹቁልቁል ይጓዝ ዹነበሹው ዹወርቅ አቅርቊትን መጠን ዹቀዹሹ መሆኑን ተናግሹው ነበር። ለወትሮውም ብሔራዊ ባንክ ወርቅን በሚገዛበት እና በነጋዎዎቜ ገበያ ላይ በሚሞጥበት ዋጋ መካኚል ልዩነት መኖሩን ዚጠቀሱት ባለሞያውፀ ይህም ጌጣጌጥ ቀቶቜ ለንድፍ ሥራዎቜ፣ ለአገልግሎት ወጪዎቜ እና ለትርፍ በሚጚምሩት ገንዘብ ምክንያት ይመጣ እንደነበር ያስሚዳሉ። በሁለቱ መካኚል ያለው ልዩነት ወደ ውጭ በሚላክ ወርቅ መጠን ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ነበሹው ዚሚሉት አብዱልመናን ይህንን ኚግምንት ውስጥ በማስገባት በወርሃ ሐምሌ በብሔራዊ ባንክ ዹዋጋ ሜግሜግ ተደርጓል ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54333190
amh
business
ዚነዳጅ ድጎማ መነሳትና ሊያስኚትል ዚሚቜለው ጫና
ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዚነዳጅ ምርቶቜ ዚመሞጫ ዋጋ ጭማሪ ማድሚጉን አሳውቋል። በዚህም አስካሁን ኚታዩት ዹዋጋ ጭማሪዎቜ ሁሉ ኹፍተኛው እንደሆነ ተነግሯል። መንግሥት እንደሚለው ዚነዳጅ ምርቶቜን ለመደጎም በወር በአማካይ 10 ቢሊዮን ብር ወጪ እንደሚደሚግ በመግለጜ፣ በአሁኑ ወቅት 146 ቢሊዚን 624 ሚሊዹን 248 ሺህ 889 ብር ዚነዳጅ ድጎማ ዕዳ አለበት ተብሏል። ቀደም ሲል መንግሥት በዚወሩ በሚያደርገው ዚነዳጅ ዋጋ ክለሳ ላይ ጭማሪው ኹ10 በመቶ ዚሚበልጥ አልነበሚም። አሁን ግን ይህንን ዚመንግሥት ድጎማውን ደሹጃ በደሹጃ ለማንሳት ባወጣ ዕቅድ መሠሚት በቀንዚን ላይ ኹ25 በመቶ በላይ፣ እንዲሁም በናፍጣ ላይ ኹ35 በመቶ በላይ ጭማሪ ተደርጓል። መንግሥት እንደሚለው በዓለም ገበያ ዚነዳጅ ዋጋ መሠሚት በአዲስ አበባ ኹተማ ዚነዳጅ ዋጋ ቢሰላ ዹ1 ሊትር ናፍጣ ዚመሞጫ ዋጋ ብር 91 ኹ23 ሳንቲም እና ዚቀንዚን ደግሞ በሊትር 82 ብር ኹ07 ሳንቲም መሆን ነበሚበት። በሌሎቜ ዚአገሪቱ ክፍሎቜ ደግሞ ዋጋው ኹዚህ ኹፍ ይላል። ነገር ግን አሁንም መንግሥት 75 በመቶውን ጭማሪ እራሱ በመሾፈን 25 በመቶውን ብቻ ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ ማድሚጉ ተገልጿል። ዚትኛውም ዚምርትና ዚአገለግሎት አቅርቊት በአንድም ሆነ በሌላ በኩል ኚነዳጅ ዋጋ ጋር ዚተሳሰሚ በመሆኑ ዹተደሹገው ዹዋጋ ጭማሪ፣ ሕዝቡን ባስጚነቀው ዚኑሮ ውድነት ላይ ሌላ ጫናን ሊፈጥር ይቜላል እዚተባለ ነው። ዹአሁኑ ዚነዳጅ ምርቶቜ መሞጫ ዋጋ ክለሳ እንዲሁም በቀጣይ ዹሚደሹገው ዹዋጋ ማስተካኚያ ዚሚያስኚትለውን ውጀት በተመለኹተ ኚጥቂት ሳምንት በፊት ያዘጋጀነው ጥንቅር በዝርዝር ይዳስሳል። እነሆ . . . መንግሥት ዹውጭ ምንዛሬን በስስት ነው ዚሚያዚው። እንደ ስእለት ልጅ። ዚዶላር ጥሪት እንደዋዛ አይቋጠርማ። በብዙ አበሳ፣ በብዙ ዹወጭ ንግድ፣ በብዙ ተጋድሎ ነው ዚሚመጣው። እንዲያም ኟኖ ጥሎበት ኚአራት ቢሊዮን ዶላር አይዘልም። እሱም ቢኟን መጥቶ አይበሚክትምፀ አብዛኛውን ነዳጅ ይጠጣዋል። ይሁን እንጂ፣ እስኚዛሬ ድሚስ ለነዳጅ ዹሚኹፈለው ዶላር በወጭ ንግድ ኹሚገኘው ዶላር በልጩ አያውቅም ነበር። አሁን ግን ታሪክ ተቀዚሚፀ ነገሩ ኚፋ። ይህ በይፋ ዚታወቀው ኚኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ነው። ለ2015 ነዳጅ መግዣ ዚሚያስፈልግህ ስንት ነው ሲባል 5.6 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልገኛል አለ። እንዲህ ያለ አሃዝ ተሰምቶ አይታወቅም ነበርፀ ይህም ዚመርኚብና ዚነዳጅ ዋጋ መናር ያመጣው ነው ይባላል። ታዲያ ይህ ገንዘብ ኚዚት ይመጣል? አንደኛ ኹውጭ ንግድ እንዲህ ዓይነት ገቢ በጭራሜ ኖሮን አያውቅም። ቡናው፣ ሌጊው፣ ሰሊጡ ተሚባርበው ኹአገር ወጥተው እንኳ እንዲህ ዓይነት ገቢን አያመጡም። አሳሳቢው ይህ ብቻ በሆነ መልካም። ነዳጁ ኹዚህም ኚዚያም ዶላር ተፈልጎ ሊገዛ ይቜላል። ኹተገዛ በኋላም ግን መደጎም አለበት። ኚተገዛበት ዋጋ በግማሜ ቀንሶ እንዲሞጥ መደጎም አለበት። ለዚህ ድጎማ ደግሞ አገሪቱ በወር በአማካይ 10 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋታል። አንድ ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ኹሰሞኑ ለኢዜአ እንደተናገሩት ድጎማው መንግሥትን በጠቅላላው 132 ቢሊዮን ብር ለሚደርስ ዚዕዳ ክምቜት ዳርጎታል። መንግሥት ይህን ህመሙን ለዓመታት ቻል አርጎት ቆዚ። በኮቪድ ዘመን ዹዓለም ዚነዳጅ ዋጋ መሬት ሲነካ ህመሙን ለጊዜውም ቢኟን አስታግሶለት ይሆናል። ኚኮቪድ በኋላ ግን ዚነዳጅ ዋጋ በድጋሚ ተቀጣጠለ። በእንቅርት ላይ. . . እንዲሉ ዚዩክሬን ጊርነት ተቀሰቀሰ። በዚህ ጊዜ በዓለም ነዳጅ ዋጋ ላይ ‘ሰደድ እሳት’ ተነሳ። ነዳጅ በዩክሬን ጊርነት ማግስት በበርሜል 140 ዶላር ዚደሚሰበት ጊዜ ነበር። ይህ ዋጋ ሃብታም አገራትን ሳይቀር ሚዛናቾውን አስቷ቞ዋል። እዚህ ግባ ዚሚባል ዚተፈጥሮ ሃብት ለሌላት፣ ዚባሕር በር ለሌላትና ሰላም ለራቃት አገር ይህ ምን ማለት ሊሆን እንደሚቜል ማብራሪያ አይሻውም። “ዚማይካደው ነገር በኢትዮጵያ ዚነዳጅ ዋጋ ኚአንዳንድ ዚነዳጅ አምራቜ አገራት ጋር ሲነጻጞር እንኳ ርካሹ ነው” ይላሉ ተቀማጭነታ቞ውን በኩዌት ያደሚጉት ዚምጣኔ ሃብት ተመራማሪው አዹለ ገላን። “ኚተባበሩት አሚብ ኢምሬትስ ጋር ቢነጻጞር እንኳ ዚኢትዮጵያ ነዳጅ ዋጋ በትንሹ አነስ ሳይል አይቀርም።” ይህን ዚሚሉት ድጎማው ምን ያህል ኹፍተኛ እንደሆነ ለማስሚዳት ነው። እኚህ ተመራማሪ ድጎማው ኹፍተኛ መሆኑን ይግለጹ እንጂ መንግሥት ድጎማውን፣ በተለይ አሁን ላይ፣ ለማንሳት መወሰኑን በፍጹም አይስማሙም። “ዚነዳጅ ድጎማውን ማንሳት እዚነደደ ያለ ቀት ላይ ነዳጅ ማርኹፍኹፍ ነው” ሲሉ ዚመንግሥትን ዕቅድ ይተቹታል። ዚነዳጅ ድጎማ በሂደት ዹተወለደ ሐሳብ ነው። ዚሕዝብ ዚመግዛት አቅም ሲያሜቆለቁል፣ ዚነዳጅ ዋጋ ሲያሻቅብ ድጎማ ተወለደ። ፖሊሲ ሳይሆን ሒደት ወለደው ማለቱ ይቀላል። “በመሠሚቱ ይህ ድጎማ ሲጀመርም በፖሊሲ ተደግፎ አያውቅም” ይላሉ ዚነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስ቎ር ዚሕዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሜን ዳይሬክተር በቀለቜ ኩማ። “ነዳጅ እንዲሁ በቁጥጥር ሥርዓትና በዋጋ ማሚጋጊያ ሰነድ ዚሚመራ እንጂ በፖሊሲ ዹተደገፈ ዚድጎማ ሥርዓት ኖሮት አያውቅም።” ለነዳጅ ሁነኛ መመሪያ ዚወጣለት ኚሊስት ዐሥርታት በፊት ነው። በ1993 ዓ.ም. ዚነዳጅ ፈንድ ተመሠሚተ። ዚነዳጅ ፈንድ ዋጋን ዚማሚጋጋት ሚናን እንዲጫወት ነበር ዚታሰበው። ይህም ማለት መንግሥት ኹዓለም ገበያ ነዳጅ ይገዛል። ኚዚያ አገር ውስጥ ሲሞጥ ሜርፍራፊ ሳንቲሞቜን ወደዚህ ዚነዳጅ ፈንድ እያስገባ ያጠራቅማል። ለምሳሌ ነዳጅ ተገዝቶ ተተምኖ ወደ ገበያ ሲወጣ 21 ብር ኹ80 ሳንቲም ቢሆን መንግሥት 22 ብር ይሾጠውና 20 ሳንቲሟ ተጠራቅማ ለሚቀጥለው ድጎማ ትውላለቜ። በዚህ አሠራር ዹተወሰኑ ቢሊዮን ብሮቜ በዚህ ዚነዳጅ ፈንድ እዚተጠራቀሙ ቆዩ። ኟኖም ነዳጅ ዚሚጚምርበት ፍጥነትና ይህ ፈንድ ዹሚለቃቅማቾው ሳንቲሞቜ ሊገናኙ አልቻሉም። ዚእርምጃና ዹ100 ሜትር ሩጫ ተወዳዳሪዎቜን በአንድ መም ዚማሮጥ ነገር መሰለ። ይህ ሁኔታ በተለይ ኹ2003 ዓ.ም. ወዲህ ጭራሜ ሊገናኝ አልቻለም። ኹዚህ ወዲያ ነበር ኚመንግሥት ካዝና ቢሊዮን ብሮቜ እዚወጡ ነዳጅን በቀጥታ መደጎም ዚተያዘው። እስኚ ቅርብ ጊዜ ድሚስ ዚነዳጅ ድጎማው በዚወሩ እዚተኚለሰ ዋጋው ኹዓለም ዋጋ ኹፍና ዝቅ ጋር እዚተነጻጞሚ እንዲስተካኚል ይደሹግ ነበር። “ይሁንና ኹ2009 ጀምሮ ዚነዳጅ ዋጋ ዹተኹለሰው ለ5 ጊዜ ብቻ ነው’’ ይላሉ በቀለቜ ጫናውን ምን ያህል መንግሥት ተሞክሞት እንደቆዚ ለቢቢሲ ሲያስሚዱ። ይህ ግን አሁን ካለው ዓለም አቀፋዊና አገራዊ ሁኔታ አንጻር ዚሚያስቀጥል አልሆነም። በዚህ ዚተነሳ አገሪቱ ኚነዳጅ ጋር በተያያዘ በቀጣይ አካሄዷን ለማስተካኚል ተገዳለቜ። ዹዓለም ዋጋን ያንጞባሚቀ ዋጋን ኚሕዝብ ጋር ለመጋራት ቆርጣለቜ። ሕመሜን አስታሙልኝ ነው ነገሩ። በዚህ ጊዜ ለምን እዚህ ውሳኔ ላይ ተደሹሰ? ስንል ዚነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስትር መሥሪያ ቀትን ጠይቀናል። “በዚህ ኑሮ እሳት በሆነበት ጊዜ መሆኑ አደጋ ዹለውም ወይ?’’ ስንል ዚምጣኔ ሃብት አዋቂዎቜን አወያይተናል። በቀለቜ ኩማ ድጎማውን በዚህ ወቅት ማንሳቱን ዚሚመለኚቱት በተለዹ መነጜር ነው። ነገሩን መንግሥት ላይ እያሳደሚ ካለው ዚዕዳ ጫና ብርቱነት፣ ዹዓለም ዚነዳጅ ዋጋ መቀጣጠል እና ኹሕገ ወጥ ንግድ መበራኚት አንጻር መመልኚትን ይመርጣሉ። “ድጎማው ኚጥቅሙ ጉዳቱ በዛ” ዚሚሉት በቀለቜ በዋቢነት ዚሚያነሱት ሕገ ወጥ ዚኮንትሮባንድ ነዳጅ ንግድ መበራኚትን ነው። ይህ አዹር በአዹር ሜያጭ አገሪቱን ለኹፍተኛ ዕዳ ዳሚጋት። በውድ ዹውጭ ምንዛሬ ዹሚደጎመው ነዳጅ እያኚበሚ ያለው ኮንትሮባንዲስቶቜን ነውፀ ባለጞጎቜን ነውፀ ሲሉ ያስሚዳሉ። እርግጥ ሕዝብ ይደጉማል ዚተባለ ውድ ነዳጅ ማደያ ሳይደርስ ጎሚቀት አገር ይ቞በ቞ብ እንደነበር አገር ያወቀው፣ ፀሐይ ዹሞቀው ጉዳይ ነው። ቢሆንም ግን በዚህ ወቅት ቁጥጥርን ማጥበቅ እንጂ ድጎማን ማንሳት ያስኬዳል? ይህ ብቻ ግን አይደለም ድጎማ ዚማንሳቱ መንስኀ ይላሉ በቀለቜ፣ “ድጎማው በፖሊሲም ያልተደገፈ ኹመሆኑ ዚተነሳ ጥቅል ድጎማ ነው ዚነበሚው።’’ እርግጥ ድጎማው ዹጅምላ ድጎማ መሆኑን ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያው አቶ ዋሲሁን በላይም አጥብቀው ዚሚኮንኑት ጉዳይ ነው። ጥቅል ድጎማ ሲባል ምን ማለት ነው? ሃብታምና ድሃን፣ ቀንትሌና ሃይገርን፣ ሊሞዚን፣ መርሎዲስን እና ‘ቅጥቅጥ አይሱዙን’ በእኩል መደጎም ማለት ነው። ኢኮኖሚስቱ አቶ ዋሲሁን፣ “መንግሥት ዚኀምባሲ መኪናንም ዹኹተማ አውቶቡስንም በአንድ ሲደጉም ነው ዹኖሹው” ዚሚሉት ለዚሁ ነው። ዚእስኚዛሬው ዚነዳጅ ድጎማ ኚመሠሚታዊ ዚድጎማ (subsidy) ጜንሰ ሐሳብ ጋር ዚሚጻሚር እንደነበር ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ዚምጣኔ ሃብት አዋቂዎቜ ዚሚስማሙበት ነጥብ ነው። ድጎማ በባህሪው ዹአጭር ጊዜ መፍትሄ ነው። ዹአጭር ጊዜ መሆን ብቻም ሳይሆን ማሳካት ዹፈለገው ግብ በውል ተለይቶ መቀመጥ አለበት። መቀመጥ ብቻም ሳይሆን ዓላማውን አሳክቷል ወይ ተብሎ መፈተሜ አለበት። ሁሉም ባለሙያዎቜ ዚሚሉት ይህንን ነው። በዚህ ሚዛን ላይ ሲቀመጥ ድጎማው ውሉን ዚሳተ ነበር ብለው ያምናሉ አቶ ዋሲሁን። እሳ቞ው መደጎም ያለበት ዚሚሉት በዋናነት ምርትን ማሳደግ ዚሚቜለውን ዘርፍ ነው። ነዳጅ በኢትዮጵያ ሁለት ሚና አለውፀ አንዱ ለፋብሪካዎቜ ዹኃይል ምንጭ መሆን ነውፀ ሌላው ትራንስፖርት ነው። በኢትዮጵያ ብዙ አምራቜ ተቋማት ዚማምሚት አቅማቾው 40 ኚመቶ አይሞላም። አንዱ ምክንያታ቞ው ታዲያ በቂ ኃይል ስለማያገኙ ነው። ስለዚህ መብራት በጠፋ ጊዜ ጄኔሬተር ይለኩሳሉ። ጄኔሬተር ነዳጅ ይጠጣል። ለእነዚህ አምራ቟ቜ ቢቻል አስተማማኝ ኃይል ማቅሚብ ወይም መደጎም ምርታማነትን ይጚምራል። ዚኀምባሲ መኪናን ነዳጅ መደጎም ግን ምርታማነት አይጚምርም። ነዳጅን ዚምትደጉመው ኢትዮጵያ ብቻ ናት? ጥቂት ዚማይባሉ አገራት ነዳጅን ይደጉማሉ። ካልደጎሙም ዚኅብሚተሰቡ ዚመግዛት አቅማቾው ኹፍ ያለ ሊሆን ይቜላል። ታዲያ ድጎማ ግቡ ምንድነው? “ማክሮ ኢኮኖሚ እንዳይዛባ፣ ምርትና ምርታማነት እንዳይጎዳ፣ ባለመደጎም ዚሚመጣ ውስብስብ ኢኮኖሚያዊ መዘዝ ሲኖር ድጎማ አግባብ ሆኖ ሊታይ ይቜላል’’ ይላሉ አቶ ዋሲሁን። “ይሄ መንግሥት ግን ኹአቅሙ በላይ ብዙ ነገር ዹሚደጉም መንግሥት ነውፀ ክፋቱ ደግሞ መደጎም ዚሌለበትንም ይደጉም ነበር።” ለነዳጅ ድጎማ ዚሚወጣው ኹፍተኛ ገንዘብ ዚኢትዮጵያ መንግሥትን ጀርባው መጉበጡን ዚምጣኔ ሃብት አዋቂው አቶ አዹለ ገላን ያምናሉ። ነዳጅ በኢትዮጰያ ዚሚሞጥበት ዋጋ አገሪቱን ነዳጅ አምራቜ እንዳስመሰላትም አልሞሞጉም። ዚእርሳ቞ው ልዩነት ዚሚነሳው ድጎማን በማንሳት ቅድመ ሁኔታዎቜ ላይ ነው። “ዚኢትዮጵያ ሞማቜ ዚመግዛት አቅም ደቃቃ ነው። ኚሕዝብ አንጻር ስናዚው እንዲያውም ድጎማው በቂ አልነበሹም ልንል እንቜላለን’’ ካሉ በኋላ መንግሥት ኚድጎማ በፊት መሥራት ዚነበሚበትን ዚቀት ሥራ አልሠራም ሲሉ ሂደቱን ክፉኛ ይተቻሉ። እነዚህ ዚቀት ሥራዎቜ ምን ነበሩ? “አንደኛ ኢኮኖሚው ተመሰቃቅሏል። ምርት አላደገም፣ ዚሕዝብ ዚመግዛት አቅም አልጚመሚም። ጥቃቅን ኢንዱስትሪዎቜ በእግራ቞ው እንዲቆሙ አልተደሚገም። ዚሕዝብ ደኅንነት አልተጠበቀም።...” መንግሥት እነዚህን መልኹ ብዙ ዚኢኮኖሚና ዚፖለቲካ ምስቅሎሜን ሳያስተካክልፀ ኢኮኖሚውን ጠንካራ መሠሚት ላይ ሳያስቀምጥ ድጎማ ማንሳት (ዚእርሳ቞ው ቃል ለመጠቀም) “ኃላፊነት ዹጎደለው ውሳኔ ነው።’’ አቶ ዋሲሁን ኚድጎማው መነሳት ማግስት ምን ሊፈጠር ይቜላል ዹሚለውን ትንቢታዊ ጥያቄ በቀጥታ መጋፈጥን ዚመሚጡ አይመስልም። ነገር ግን ዚመንግሥት ድጎማን ዚማንሳት ውሳኔን ኚጥንቃቄ ጋር በአውንታዊ መልኩ ይሚዱታል። “ዚድጎማ ሥርዓቱ (በአንድ ጥናት ላይ እንደታዚው) 70 ኚመቶ ዹሚሆነውን ድሃና 30 ኚመቶ ዹሚሆነውን ሃብታም ነው ሲደጉም ዚኖሚው። ስለዚህ ጀናማ ድጎማ አልበሚም። ለድሃ ዚታሰበው ድጎማ ሃብታም ሲደጉም ነው ዚኖሚው።’’ ስለዚህ በእሳ቞ው ዕይታ ኹዚህ ወዲህ ድጎማው ለታሰበለት ሕዝብ ብቻ ስለመድሚሱ እርግጠኛ መሆን ያሻል። “ድጎማ ዘዮኛና መለኛ (ታክቲካል) ካልሆነ ውሉን ሳተ ማለት ነው። ድሃው ነው ዹሚደጎመው ኚተባለ ድጎማው ድሃው ጋር መድሚሱን ማሚጋገጥ ያስፈልጋል’’ ዚሚሉት አቶ ዋሲሁን ነዳጅ በሞያሌ እዚወጣ ሲሞጥ፣ አውቶቡስና ዚኀምባሲ መኪና አብሮ ተሰልፎ በአንድ ዹዋጋ ተመን ነዳጅ ሲቀዳ ድጎማ ግብ እንደተሳተ ምልክቶቜ ሆነው ይታያሉ። በዚህ ሐሳብ ዚነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስትርም ባልደሚባም ይስማማሉ። “ዹሚደጎምና ዹማይደጎምን በጥናት መለዚት ያስፈለገውም ለዚሁ ነው ይላሉ” በቀለቜ ኩማ። ኚድጎማ ዹተሹፈው ገንዘብ ምን ላይ ይውል ይሆን? አቶ ዋሲሁን ኚድጎማ መነሳቱ ይልቅ ኚድጎማ ዚዳነው ገንዘብ ዚት እንደሚውል በእጅጉ ያሳስባ቞ዋል። “አሁን ያለው ኢኮኖሚ በግጭትና በጊርነት ዹቆሰለ ኢኮኖሚ ነው። ኹፍተኛ ወጪዎቜ ይጠብቁታል። በወጪና ገቢ ልዩነት ማጥበብ ላይ ካልተሠራ ዹኹፋ ሀኔታ ሊመጣ ይቜላል” ይላሉ። ኹፍተኛ ዚበጀት ጉድለት ደግሞ ወደ ገንዘብ ማተም ስለሚወስድ ለበለጠ ዚበጀት ቅርቃርና ኑሮ ውድነት ሊወስድ ይቜላል ዹሚል ፍርሃት አላ቞ው። ስለዚህ መንግሥት ኚድጎማ ወጪ ያዳነውን ገንዘብ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ሊያውለው ይገባል። “መንግሥት ማኅበሚሰቡ ወጪውን እንዲጋራው መሞኚሩ መጥፎ ነው ወይ? ብትለኝ እኔ መጥፎ ነው ብዬ አላስብም። ነገር ግን ገንዘቡ ለአበልና ለድግስ ኹዋለ ነው ቜግሩ።” አሁን በዓለም ገበያ ሰማይ ዚነካውን ነዳጅ መንግሥት በግማሜ ቀንሶ ነው ለሕዝብ ዚሚያደርሰው። ቀድም ባሉ ዓመታት በሊትር 5 እና 6 ብር ነበር ዚሚደጉመው። አሁን ያን ለማድሚግ ዚሚያስቜል አቅምን አጥቷል። በውስጣዊና ውጫዊ ዝርዝር ምክንያቶቜ። ምክንያቶቹን አቆይተን ነገር ግን መንግሥት በዚህ ድጎማ አሠራር ኹሐምሌ ወዲያ መሻገር ይቜል ነበር ወይ ብለን እንጠይቅ። በሌላ አነጋገር መንግሥት ደግ ሆኖ ልደጉም ቢልስ ይቜላል ወይ? ዚብዙ ኢኮኖሚስቶቜ ምላሜ በአጭሩ ሲቀመጥ “አይቜልም” ዹሚል ነው። ምክንያቱም፣ “...ሚያዝያ ወር ላይ ብቻ ዕዳው 124 ቢሊዮን ደርሰ” ይላሉ ዚነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስ቎ር ባልደሚባ በቀለቜ ኩማ። ምክንያቱም፣ “...561 ቢሊዮን ብር ይዞ ዚተነሳ ኢኮኖሚ ነው ያለው። በዚህ ዓመት በዘጠኝ ወር ዹተሰበሰበው 290 ቢሊዮን ብር ነው። ልዩነቱ ሰፊ ነው። ይህን ዚበጀት ጉድለት ይዞ ብዙ መጓዝ አይቻልም” ይላሉ አቶ ዋሲሁን። ይሁንና ነዳጅ ድጎማው ዚኑሮ ውድነቱን እንዳያባብስ ምን ማድሚግ ይቻላል? አቶ ዋሲሁን ዚነዳጅ ድጎማው በኑሮ መወደድ ላይ ዚሚያስኚትለውን ጣጣ ማንም አያጣውም ይላሉ። ነገር ግን ያን ማስቀሚት በምጣኔ ሃብት ሳይንስ ዚሚቻልበትን ዕድል አይታያ቞ውም። “ዚትኛውም ፖሊሲ ሁሉን አስታርቆ መሄድ አይቜልም። ሁሉንም ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ አስደስቶ ዚሚያቆይ ዚኢኮኖሚ ውሳኔ በምድር ላይ ዚለም።’’ ይልቅ በቀጥታ በድጎማ መነሳት ብቻ ዹሚፈጠር ዋጋ ንሚት ሳይሆን ድጎማ ዚመነሳቱ ወሬ በራሱ ዚሚፈጥሚው ዚገበያ ትኩሳት ይበልጥ ያሳስባ቞ዋል። “እኛ አገር ነጋዮው በአጋጣሚው እንዎት በአቋራጭ ልክበር ነው ዚሚለውፀ ዚድጎማውን ጭማሪ ብቻ ደምሮ ይሞጣል ብዬ አልገምትም” ይላሉ አቶ አዹለ ገላን። ኹሐምሌ ወዲህ ዚሕዝብ ትራንስፖርት አሜኚርካሪ ማደያ ገብቶ ነዳጅ ሲቀዳ ጂፒኀስ ተገጥሞለት ነው። ነዳጅ አቅራቢዎቜ ለማደያዎቜ ደሹሰኝ ይሰጣሉ። ባለታክሲው በታሪፍ ዹተቀመጠውን ዋጋ ኹፍሎ ይሄዳል። ማደያው በደሹሰኝ ቀሪውን ያወራርዳል። ይህ አሠራር በመተግበሪያ ዚሚሠሩት ታክሲዎቜን አይጚምርም። ዚመንግሥት ሰርቪሶቜንም አይጚምርም። “ኹዚህ በኋላ በዚትኛውም ማደያ ነዳጅ ሲራገፍ ዹኛ ተቆጣጣሪዎቜ በያንዳንዱ ማደያ ተገኝተው ነው” ይላሉ ዚነዳጅና ኢንርጂ ሚኒስ቎ር ባልደሚባ በቀለቜ ኩማ። ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ሕዝብን ለማሚጋጋት ይመስላል መንግሥት ድጎማ ማንሳቱ በኑሮ ላይ አንዳቜም ጫናን አይፈጥርም ዹሚሉ ድምጟቜ እዚተስተጋቡ ነው። ይህ ለምጣኔ ሃብት አዋቂዎቜም ሆነ ለሰፊው ሕዝብ እምብዛምም ስሜት ዚሚሰጥ አይደለም። በቀለቜ ኩማ ግን “ድጎማ መነሳቱ በቀጥታ ዚሚባለውን ያህል ዹዋጋ ንሚት አያስኚትልምፀ ይህ በጥናት ዹተሹጋገጠ ነው” ሲሉ ዚነገሩን ሀቅነት ይሞግታሉ። እሳ቞ው ጥናቱን ለቢቢሲ ለማጋራት ባይፈቅዱም ዚነዳጅ ድጎማ መነሳት በቀጥታ ዚሚያስኚትለው ዹዋጋ ንሚት እዚህ ግባ ዚሚባል እንዳይደለ ይጠቅሳሉ። “...ድጎማው ሲነሳ በእያንዳንዱ ሞቀጥ ላይ ዚሚያመጣው ጫና በሳንቲም ቀት እንደሆነ ተደርሶበታል” ይላሉ። ይሁንና ምጣኔ ሃብት ሙያተኞቹ አቶ ዋሲሁን እና አቶ አዹለ ግን በዚህ ብዙም አይስማሙም። አንዱ ምክንያታ቞ው በኢትዮጵያ ዚንግድ ዘይቀ እንደታዚው ዋጋ ዹሚወሰነው በቀጥታ በሚመጣ ጭማሪ ሳይሆን ገና በሥነ ልቩና በሚፈጠር ፍርሃትም ጭምር ስለሆነ ነው። ለብዙዎቜ አዲስ ዜና ዹሆነው ደግሞ ዚታለመላ቞ው ዚሚባሉት ተደጓሚዎቜም ቢሆኑ ድጎማ቞ው ጊዜያዊ መሆኑ ነው። በቀለቜ ሁሉም ታክሲዎቜና ዚሕዝብ አውቶቡሶቜ ሳይቀሩ በሂደት ኚድጎማ ሥርዓት እንደሚወጡ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። “በአምስት ዓመት ውስጥ ኚድጎማው ሙሉ በሙሉ ይወጣሉ። በዚሊስት ወሩም ዋጋ ክለሳ ይደሚግባ቞ዋል።” ዹሰዉ ስሜቱ ዚተዘበራሚቀ ነው። ኑሮ መንደድ ያለበትን ያህል በመንደዱ ኹዚህ በላይ ምን ሊመጣ? ዹሚል ስሜት ያላ቞ው አሉ። ነገን በፍርሃትና በሰቀቀን ዚሚጠብቁም አሉ። ድጎማው ሐምሌ ላይ ሲነሳ ዹዋጋ ጭማሪው እንደ ሐምሌ ዝናብ ዶፍ ሆኖ ሊወርድ ዚተሰናዳ ይመስላል። ሐምሌ አሳሳቢ ሆኖ ዚሚታዚው ታዲያ ለተርታው ሕዝብ ብቻ አይደለም። ለጎምቱ ኢኮኖሚስቶቜም ጭምር እንጂ። መቀመጫ቞ውን ኩዌት ያደሚጉት አቶ አዹለ ገላንፀ “በዚህ ጊዜ ድጎማን ማንሳት ለእኔ ስሜት ዚሚሰጥ አይደለምፀ ዚምባብዌ ወደ ገጠማት ኢኮኖሚ ሁኔታ ዹመንደርደር ያህል አድርጌ ነው ዹምመለኹተው” ይላሉ። ምርትና ምርታማነት ፈቅ ሳይል፣ መሠሚታዊ ዚኑሮ ደሹጃ ኢምንት ሳይጚምር ዚገጠሩ ዚግብርና ኢኮኖሚ ሳያድግ አሁን ባለው ኢኮኖሚ ላይ ዚነዳጅ ድጎማን ማንሳት ኚድጡ ወደ ማጡ ነውፀ ለእርሳ቞ው። በቀለቜ ኩማ ግን ዹተቀናጀ ቁጥጥርና በቂ ግንዛቀ ለኅብሚተሰቡ ኹደሹሰ ዹኹፋ ሁኔታ አይመጣም ባይ ና቞ው። አቶ አዹለ በፍጹም በዚህ አይስማሙምፀ በዚህ እሳት በሆነ ኑሮ ይህን መሠሚታዊ  ዚነዳጅ ድጎማን ማንሳት “እዚነደደ ባለ እሳት ላይ ነዳጅ ማርኹፍኹፍ ነው” ይሉታል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cyd3yjlr0rgo
amh
business
ሱዊዝ ቩይ በመዘጋቱ በዹቀኑ ዹ9.6 ቢሊዮን ዶላር ምርት መተላለፍ አልቻለም
ዚግብጹ ሱዊዝ ዚባሕር ላይ ማቋሚጫ ቩይ በመዘጋቱ በዹቀኑ 9.6 ቢሊዮን ዶላር ዚሚያወጡ ምርቶቜ መተላለፍ እንዳልቻሉ ተገለጞ። በሱዊዝ መተላለፊያ ላይ አንድ ግዙፍ ዚጭነት መርኚብ ባሕሩን ዘግቶ ኹማክሰኞ ዕለት ጀምሮ በመቆሙ ምክንያት እንቅስቃሎ መገታቱ ይታወሳል። ሎይድስ ሊስት ዚተባለው ዚመርኚብ ጉዞ ድርጅት እንደሚለውፀ በቀን ውስጥ ኚምዕራብ አቅጣጫ ይመጡ ዚነበሩ 5.1 ቢሊዮን ዶላር ዚሚያወጡ ምርቶቜ መጓጓዝ አልቻሉም። ኚምሥራቅ አቅጣጫ ይመጡ ዚነበሩና ዚተስተጓጎሉ ምርቶቜ ደግሞ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ዚሚያወጡ ና቞ው። ዚባሕሩን መተላለፊያ ዹዘጋው መርኚብ እንቅስቃሎ እንዲጀምር ለማድሚግ ጥሚት እዚተደሚገ ቢሆንም ሳምንታት ሊወስድ እንደሚቜል ባለሙያዎቜ ተናግሚዋል። በታይዋኑ ኀቚርግሪን ማሪን ሥር ያለው ኀቚር ጊቭን መርኚብ በዓለም ትልቁ ኮን቎ነር ጫኝ ሲሆንፀ 200,000 ቶን ዹሚመዝን እንዲሁም 20,000 ኮን቎ነር ማጓጓዝ ዚሚቜል ነው። መርኚቡ በመቆሙ ሳቢያ ሌሎቜ መርኚቊቜ ለቀናት መተላለፍ አልቻሉም። ዚባሕር ላይ ጉዞ አማካሪ ድርጅት ባለቀት ጆን ሞንሮይ ብዙ ወደቊቜ ላይ ዹሚገኙና መጓጓዝ ያልቻሉ ኮን቎ነሮቜ እንዳሉ ይናገራል። መተላለፊያው በአፍሪካ እና በመካኚለኛው ምሥራቅ መካኚል ምርቶቜ ዚሚተላለፉበት ሲሆንፀ ዹጩፈ ንግድ ዚሚካሄድበት መስመር ነው። ኹመላው ዓለም ዚባሕር ንግድም 12 በመቶው ዚሚያልፈውም በዚሁ ዚግብጜ ዚባሕር ላይ ማቋሚጫ መስመር በኩል ነው። ሎይድስ ሊስት ባወጣው አሃዝ መሠሚትፀ በአሁኑ ጊዜ 160 መርኚቊቜ በሱዊዝ ቩይ በኩል ለማለፍ እዚጠበቁ ነው። ኚእነዚህ መካኚል 41 ዚሚሆኑት ዚተለያዩ ምርቶቜ ሲይዙ 24 ደግሞ ነዳጅ ጫኝ ና቞ው። ቢአይኀምሲኊ ዚተባለው ዓለም አቀፍ ዚመርኚበኞቜ ማኅበር እንደሚለው መተላለፊያው ተዘግቶ ኹቆዹ ዚምርት አቅርቊት ላይ ተጜዕኖ ማሳደሩ አይቀርም። ዚሎጂስቲክስ ተቋሙ ኊኀል ዩኀስኀ ፕሬዘዳንት አለን ባይር "በእያንዳንዱ ቀን ያልተጓጓዙ ምርቶቜን ለማሳለፍ ተጚማሪ ሁለት ቀናት ይጠይቃል" ብለዋል። እስካሁን ለሊስት ቀናት መተላለፍ ያልቻሉትን ምርቶቜ ለማጓጓዝ ስድስት ቀናት ገደማ ሊያስፈልግ እንደሚቜልም ግምታ቞ውን አስቀምጠዋል። መተላለፊያው እስኪኚፈት ድሚስ ቀናት ወይም ሳምንታት ሊወስድ እንደሚቜል ዹተጠቆመ ሲሆንፀ ይህ ደግሞ በመላው ዓለም ዚንግድ እንቅስቃሎ ላይ ጫና ያሳድራል። ዹዓለም ዚንግድ እንቅስቃሎ ይህ ዚግብጜ ዚባሕር ላይ መተላለፊያ ኚመዘጋቱ በፊት በኮቪድ-19 ምክንያት መቀዛቀዝ አጋትሞት ነበር። አለን እንደሚሉትፀ መርኚቊቜ ሌላ አማራጭ ዹጉዞ መስምር ኹፈለጉ በምዕራብ አፍሪካ በኩል በመዞር ጉዟቾውን ሊቀጥሉ ብቜሉም ይህ ጉዞ ግን ኚሰባት እስኚ ዘጠኝ ቀናት ሊፈጅ ይቜላል። አንዳንድ ተቋሞቜ መተላለፍ ባልቻሉ ምርቶቻ቞ው ምትክ ሌሎቜ ምርቶቜን በአውሮፕላን ወይም በባቡር መላክን እንደ አማራጭ ሊወስዱ ይቜላሉ። እስካሁን ድሚስ ሜርስክ እና ሀፓግ ሎይድ ዚተባሉ ተቋሞቜ ኚሱዩዝ መተላለፊያ መስመር ውጪ ያሉ አማራጮቜን እንደሚጠቀሙ አስታውቀዋል። ዚግብጹ ዚሱዊዝ መተላለፊያ ባለሥልጣን ባሕሩን ዹዘጋውን መርኚብ ለማስነሳት ዚቻለውን ሁሉ እዚሞኚሚ እንደሆነ አስታውቋል።
https://www.bbc.com/amharic/56534020
amh
business
ኢትዮጵያ ዚባንክ ዘርፍን ለውጭ ባለሐብቶቜ ክፍት ለማድሚግ ወሰነቜ
ዚኢትዮጵያ መንግሥት ካቢኔ ለአስርታት ለውጭ ባለሐብቶቜ ዝግ ሆኖ ዹቆዹውን ዚባንክ ሥራ ዘርፍ ክፍት ለማድሚግ ዚቀሚበለትን ሹቂቅ ፖሊሲ አጞደቀ። በአገሪቱ ብሔራዊ ባንክ አማካይነት ተዘጋጅቶ ዹቀሹበው ሹቂቅ ለዘመናት ለኢትዮጵያውያን ብቻ ተትቶ ዹነበሹውን ዚፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ባንኮቜም ክፍት እንዲሆን ዚሚፈቅድ ነው። ይህም በዘርፉ ታዋቂ ዹሆኑ ዓለም አቀፍ ባንኮቜ በአገሪቱ ዚፋይናንስ ዘርፍ ላይ እንዳይሰማሩ አድርጎ ዹቆዹውን ዚአገሪቱን ዚፋይናንስ ፖሊሲ ዹቀዹሹው ውሳኔ በሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ጞድቆ ይፋ ሆኗል። በዚህም ዓለም አቀፍ ተቋማት ኢትዮጵያ ለአገር ውስጥ ባለሐብቶቜ ብቻ ክፍት አድርጋው በቆዚቜው ዘርፍ ለመሳተፍ እድል ይፈጥርላ቞ዋል። ዚፋይናንስ ዘርፉ ዝግ ሆኖ በቆዚባ቞ው ዓመታት ውስጥ ዚአገሪቱን ምጣኔ ሐብት በተለያዩ መስኮቜ ሲደግፉ ዚቆዩት ዓለም አቀፍ ተቋማት እና አገራት ዘርፉን እንድትኚፍት ሲወተውቱ ቆይተዋል። ዛሬ ቅዳሜ ነሐሮ 28/2014 ዓ.ም. ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባው ዚባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቚስተሮቜ ክፍት ለማድሚግ ዹቀሹበውን ሹቂቅ ፖሊሲ አጜድቆ በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል። ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ውሳኔውን ይፋ ባደሚገበት መግለጫው እንዳለው ዚባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቚስተሮቜ ክፍት ማድሚግ “አገልግሎቶቜ በእውቀት እና በቮክኖሎጂ ለመደገፍ፣ ዚአገሪቱን ምጣኔ ሐብት ኹዓለም አቀፍ ገበያ ጋር ዹበለጠ እንዲተሳሰር ለማድሚግ ያስቜላል።” ብሏል። በተጚማሪም ይህ እርምጃ ዹውጭ ምንዛሪ አቅርቊትን በማቀላጠፍ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን በማጎልበት ለምጣኔ ሐብት ዕድገት አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል። ለሹጅም ዘመናት በመንግሥት እና በአገር ውስጥ ባለሐብቶቜ ተሳትፎ ብቻ ተይዘው ዚቆዩ ዘርፎቜን ዚመክፈት ፍላጎት እንዳለው ሲገልጜ ዹቆዹው መንግሥት አሁን ዚባንኩን ዘርፍ ክፍት አድርጎታል። ይህ ዘርፍ ለውጭ ባለሐብቶቜ ክፍት ሊሆን እንደሚቜል እና ዝግጅትም እዚተደሚገ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጚምሮ ሌሎቜም ኹፍተኛ ባለሥልጣናት በተለያዩ አጋጣሚዎቜ ፍንጭ ሲሰጡ ቆይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ሥልጣን መምጣታ቞ውን ተኚትሎ በተለይ በመንግሥት ተይዘው ዹሚገኙ ዘርፎቜን ኚፍት ለማድሚግ ፍላጎት እንዳለ ዹተነገሹ ሲሆን ተግባራዊነቱ ግን አዝጋሚ ሆኖ ነበር። ኹ120 ዓመት በላይ በመንግሥታዊው ኢትዮ ቎ሌኮም ተይዞ ዹነበሹው ዚ቎ሌኮም ዘርፍ ለውድድር ክፍት ሆኖ፣ ኚአንድ ዓመት በፊት በተካሄደ ጚሚታ ሳፋሪኮም ተመራጭ ሆኖ በዚህ ወር በተወሰኑ ዚአገሪቱ ክፍሎቜ ዚ቎ሌኮም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c6px7z4zg45o
amh
business
ዚኬንያው ፕሬዝዳንት በአገራ቞ው ቁርጥራጭ ብሚታ ብሚቶቜ እንዳይሞጡ አገዱ
ዚኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በአገሪቱ ኚግንባታዎቜ ላይ ዚተነሱ፣ ያገለገሉ እንዲሁም ዚተጣሉ ብሚታ ብሚቶቜ ሜያጭ እንዳይካሄድ አስ቞ኳይ እገዳ ጣሉ። ይህ ዚፕሬዝዳንቱ ድንገተኛ እገዳ ይፋ ዹተደሹገው መንግሥት እዚጚመሚ ነው ያለውን በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ ዚሕዝብ ንብሚቶቜ ላይ ዹሚፈጾም ዝርፊያና ውድመትን ለመኹላኹል ጥሚት እያደሚገ ባለበት ወቅት ነው። ይህ ዚወዳደቁና አሮጌ ብሚቶቜ ሜያጭ እገዳ ተግባራዊ ዹሚሆነው ዚኬንያ መንግሥት ዚእነዚህን ብሚታ ብሚቶቜ ምንጭ፣ ንግድና ወደ ውጭ ዚሚላኩበትን ሁኔታ በተመለኹተ ለመቆጣጠር ዚሚያስቜል ደንብ አውጥቶ ተግባራዊ እስኪሆን ድሚስ ነው። ባለፈው ሳምንት በዋና ኹተማዋ ናይሮቢ በሚገኝ ኹፍተኛ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ተሞካሚ መስመር ላይ ተፈጾመ በተባለ ዘሹፋ ምክንያት በአገር አቀፍ ደሹጃ ዚኀሌክትሪክ መቋሚጥ አጋጥሞ ነበር። በመላዋ ኬንያ በተቋሹጠው ዚኀሌክትሪክ ኃይል አቅርቊት ሰበብ ዘጠኝ ዚኬንያ መብራት ኃይል አቅራቢ ተቋም ኹፍተኛ ሥራ አስኪያጆቜ በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቀት ቀርበዋል። ዚባቡር ሃዲዶቜን፣ ዚኮምዩኒኬሜን ማማዎቜን እንዲሁም ዚኀሌክትሪክ ማስተላላፊያ መስመሮቜን ጚምሮ ኬንያ ውስጥ በሚገኙ ዚሕዝብ መሠሹተ ልማቶቜ ላይ ተደጋጋሚ ዹሆነ ዘሹፋና ውድመት ማጋጠሙ ተነግሯል። ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ዚወዳደቁ አሮጌ ብሚቶቜን ባገዱበት ወቅት እንዳሉት በሕዝብ ቁልፍ መሠሹተ ልማቶቜ ላይ ዹሚፈጾመው ዘሹፋና ጥፋት ኚምጣኔ ሀብት አሻጥር ጋር ዚሚስተካኚል በመሆኑ ዹአገር ክህደት ተግባር ነው ብለዋል። በመሠሹተ ልማቶቜ ላይ ዹሚፈጾሙ ዘሚፋዎቜን በበተመለኹተ ዚኬንያው ፕሬዝዳንት ማስጠንቀቂያ ሲሰጡ ዹአሁኑ ዚመጀመሪያው አይደለም። ኚሊስት ዓመት በፊት ዚአገሪቱን ግዙፍ ዚባቡር መስመር ግንባታ ባስጀመሩበት ጊዜ ኚቻይና በተገኘ ብዙ ቢሊዮን ዶላር ብድር በሚሰራው መሠሹተ ልማት ላይ ጉዳት ዚሚያደርስ ሰው በሞት እንዲቀጣ እንደሚያጞድቁ አስጠንቅቀው ነበር። ዚተለያዩ ግዙፍ ሕዝባዊ መሠሹተ ልማቶቜ ዚተገነቡባ቞ውን ዚተለያዩ ዚብሚት አካላት ዘራፊዎቜ ነቅለው ወይም ቆርጠው በመውሰድ ለሜያጭና ዚተለያዩ ነገሮቜን ለመስራት ያውሉታል። ይህ ዚኬንያ ቜግር ብቻ ያልሆነው ዚብሚታብሚቶቜ ዝርፊያና ውድመት ኚተለያዩ መሠሹተ ልማቶቜ ዚተዘሚፉት ቁርጥራጭ ዚብሚት አይነቶን ኹአገር ውጪ በመውሰድ ለሌሎቜ ወገኖቜ እንደሚሞጡ ይነገራል።
https://www.bbc.com/amharic/news-60082636
amh
business
ቩይንግ 20 በመቶ ሰራተኞቹን ለመቀነስ ማቀዱን አስታወቀ
ቩይንግ በቅርቡ 7 ሺህ ዹሚሆኑ ሰራተኞቹን እንደሚቀንስ ይፋ አድርጓል። በኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ዚተጎዳው ዚአሜሪካኑ አውሮፕላን አምራቜ ቩይንግ በኹፍተኛ ሁኔታ ዚሰራተኞቹን ቁጥር ለመቀነስ እንዳሰበ ያሳወቀ ሲሆን በመጪው አውሮፓውያኑ አመት መጚሚሻም 20 በመቶ ዚሚሆኑትን ወደ 30 ሺህ ሰራተኞቹን እንደሚቀንስ አስታውቋል። ኚቀውሱ በፊት ኩባንያው ዚነበሩት ዚሰራተኞቜ ቁጥር 160 ሺህ ነበር። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ በተጚማሪ ኹ337 ማክስ ዚደህንነት ስጋቶቜ ጋር ተደራርቊ ኩባንያውን ለኪሳራ ዳርገውታል። እስኚ መስኚሚም አጋማሜ ባለውም ሶስት ወራት ውስጥ 466 ሚሊዮን ዶላር ኚስሬያለሁ ብሏል። ይህም ሁኔታ ለአመት ያህልም ቀጥሏል። ኚበሚራ ውጭ ሆነው ዚነበሩት 737 ማክስ አውሮፕላኖቹ በሚራ ሊጀምሩ ይቜላሉ መባሉም ጋር ተያይዞም ኩባንያው በእነዚህ አውሮፕላኖቜ ሜያጭ እንደሚያገግም ተስፋ አድርጓል። 737 ማክስ ሁለት አውሮፕላኖቜ ተኚስክሰው ዹ346 ሰዎቜ ህይወት ኹጠፋ በኋላ ኚበሚራ ኚታገደ ኚአንድ አመት በላይ ሆኖታል። አውሮፕላኑ ሙሉ ሙሉ ኚበሚራ ዚታገደው በጎርጎሳውያኑ መጋቢት ወር 2019 ዓ.ም ነበር። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ በአዹር ጉዞ ኢንዱስትሪው ላይ ኹፍተኛ ቀውስን ያስኚተለ ሲሆን በርካታ አዹር መንገዶቜንም ኪሳራ ውስጥ ጥሏል። በዚህም ምክንያት በርካታ አዹር መንገዶቜ ሰራተኞቻ቞ውን አባሚዋል እንዲሁም አዳዲስ ሊገዟቾው ያሰቧ቞ውን አውሮፕላኖቜ በይዋል ይደር ትተውታል። ቩይንግም ሰራተኞቜን ኚመቀነስ በተጚማሪ ምርቱንም ዝቅ ለማድሚግ ተገዷል። ኹዚህ ቀደም 10 በመቶ ሰራተኞቹን ዹቀነሰው ቩይንግ እስኚ 2023 ባለው ወቅትም ካለበት ቀውስ እንደማይወጣ ግምቱን አስቀምጧል። ገቢውም በኹፍተኛ ሁኔታ ማሜቆልቆሉ ዚተነገሚለት ቩይንግ በዘጠኝ ወራትም 30 በመቶ ዝቅ ብሏል። ዹቩይንግ ፕሬዚዳንትና ዋና ስራ አስፈፃሚ ዎብ ካልሁን እንዳሉት ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ በኹፍተኛ ሁኔታ ኢንዲስትሪው ላይ ጉዳት ማድሚሱን ነው።
https://www.bbc.com/amharic/news-54748697
amh
business
በቀጣዩ ስምንት ዓመት ቻይና በምጣኔ ሃብት አሜሪካን ትበልጣለቜ ተባለ
ቻይና በፈሚንጆቹ 2028 በዓለም ትልቁ ዚምጣኔ ሃብት ባለቀት በመሆን አሜሪካን ልትቀድማት እንደምትቜል ተገምቷል። ኹዚህ ቀደም ቻይና አሜሪካን በ2033 ነበር ትቀድማታለቜ ተብሎ ዚተገመተው። መቀመጫውን ዩናይትድ ኪንግደም ያደሚገው ዚምጣኔ ሃብት እና ቢዝነስ ጥናት ማዕኹል ነው ይህን ዚገመተው። ማዕኹሉ እንደሚለው ቻይና ኮቪድ-19ኝን ዚተቋመመቜበት መንገድ ዕድገቷን ሊያፋጥን ይቜላል። በተቃራኒው አሜሪካና አውሮፓ በኮሮናቫይሚስ ክፉኛ መደቆሳ቞ው ጉዳት አለው ተብሏል። በሌላ በኩል ሕንድ በ2030 ኹዓለም ሊስተኛዋ ታላቅ ምጣኔ ሃብት ያላት አገር ትሆናለቜ ተብሎ ተገምቷል። ማዕኹሉ በዚዓመቱ ታኅሣሥ ወር ላይ ዚምጣኔ ሃብት ግምትና ትንታኔ ያወጣል። ምንም እንኳ ቻይና በኮቪድ-19 ዚተመታቜ ዚመጀመሪያዋ አገር ብትሆንም በሜታውን በተሳካ ሁኔታ በቁጥጥር ሥር ማዋል ቜላለቜ። ነገር ግን ዚአውሮፓ አገራት ሰዎቜ ኚቀታ቞ው እንዳይወጡ እግድ ጥለዋል። ይህ ደግሞ ምጣኔ ሃብታ቞ው ላእ ኹፍ ያለ ጉዳትን ያስኚትላል ይላል ትንታኔው። ቻይና ሌሎቜ አገራት እንዳጋጠማ቞ው ዚምጣኔ ሃብት ድቀት ውስጥ አልገባቜም። እንዲያውም ዘንድሮ 2 በመቶ ዕድገት ታመጣለቜ ተብሎ ይጠበቃል። ዚዩናይትድ ስ቎ትስ ምጣኔ ሃብት ደግሞ በተቃራኒው በወሚርሜኙ እጅጉን ተመቷልፀ ኹ300 ሺህ በላይ ሰዎቜም በቫይሚሱ ምክንያት ሞተዋል። አሜሪካ ወሚርሜኙ ያመጣባትን ድቀት በገንዘብ ፖሊሲና ለዜጎቿ ድጎማ በማድሚግ ብትሞፍነው ብታስብም ለሁለተኛ ጊዜ ሊደሹግ በታሰበው ድጎማ ላይ ፖለቲኚኞቜ አለመስማማታ቞ው ጉዳቱ ዹኹፋ እንዲሆን ሊያደርገው ይቜላል ዹሚል ስጋት አስኚትሏል። ይህ ጉዳይ ሊጠናቀቅ ቀናት በቀሩት ዚፈሚንጆቹ አዲስ ዓመት 14 ሚሊዮን ሥራ አጥ አሜሪካዊያንን ያለ ድጎማ ሊያስቀራ቞ው ይቜላል። ማዕኹሉ ያወጣው ዘገባ እንደሚለው ቻይና እና አሜሪካ ለዓመታት ዚምጣኔ ሃብት ዚበላይነቱን ለመቆጣጠር ሲፎካኚሩ ኚርመዋል። ነገር ግን ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝን ተኚትሎ ዚመጡ ለውጊቜ እንደሚያሳዩት ቻይና ዚመጪው ጊዜ ዚዓለማቜን ቁንጮ ናት። ዘገባው እንደሚተነብዚው ኹሆነ ድኅሚ-ኮቪድ-19 ባለው ጊዜ ውስጥ ዚአሜሪካ ምጣኔ ሃብት ኹ2022 አስኚ 2024 ድሚስ ባለው ጊዜ 1.9 በመቶ ያድጋል። ኚዚያ በኋላ ደግሞ ወደ 1.6 በመቶ ይወርዳል። በተቃራኒው ዚቻይና ምጣኔ ሃብት እስኚ 2025 ድሚስ በ5.7 በመቶ ያድግና ኹ2026 ወዲያ ባለው ጊዜ 4.5 በመቶ ያድጋል ይላል። ቻይና በዓለም አቀፍ ደሹጃ ያላት ዚምጣኔ ሃብት ድርሻ በፈሚንጆቹ 2000 ዓመት ላይ 3.6 ነበር። ዘንድሮ ግን ወደ 17.8 አድጓል። ቻይና በ2023 ኹፍተኛ ገቢ ያላት አገር እንደምትሆን ነው ዹማዕኹሉ ምክትል ሊቀመንበር ዳግላስ ማክዊሊያምስ ዚሚናገሩት። ምንም እንኳ ዚቻይና ምጣኔ ሃብት ኚአሜሪካ ሊበልጥ እንደሚቜል ይገመት እንጂፀ ዚአንድ ቻይናዊ አማካይ ገቢ ግን ኚአንድ አሜሪካዊ ጋር ሲነፃፀር ዕድገት ላያሳይ ይቜላል ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-55457811
amh
business
ኚጂቡቲ ወደ አዲስ አበባ ዚሚወስደው መንገድ ሲኚፈት ዚባቡር መስመሩ እንደተዘጋ ነው ተባለ
ኚቀናት በፊት በተቃዋሚዎቜ ተዘግቶ ዹነበሹው ኚጂቡቲ ወደ መሃል አገር ዚሚወስደው መንገድ መኚፈቱ ተገለጞ። ጂቡቲን ኚአዲስ አበባ ዚሚያገናኘው ዚባቡር መስመር ግን አሁንም ዝግ ሆኖ እንደሚገኝ ዚሶማሌ ክልል ኮምዩኒኬሜን ምክትል ኃላፊ መሐመድ ሮብሌ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ካሳለፍነው እሁድ ጀምሮ መንገዱና ዚባቡር መስመሩ በሶማሌ ተወላጆቜ ላይ ዹደሹሰውን ጥቃት በሚቃወሙ ዚአካባቢው ወጣቶቜ ተዘግቶ ነበር። መንገዱ ኚጂቡቲ ወደብ ወደ አዲስ አበባ ዹሚጓዙ ዚተለያዩ ሞቀጊቜ ዋነኛ መተላለፊያ መስመር ነው። ባለፈው ቅዳሜ በአፋር እና በሶማሌ ክልል አዋሳኝ በሆነና ዚይገባኛል ጥያቄ በሚነሳበት ቊታ በተፈፀመ ጥቃት በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ በአፋር ታጣቂዎቜ መገደላቾውን ዚሶማሌ ክልል ኮምዩኒኬሜን ምክትል ኃላፊው ለቢቢሲ ገልጾው ነበር። በዚህ ጥቃት ዚተበሳጩ ዚሶማሌ ክልል ተወላጆቜ መንገዱን እና ዚባቡር መስመሩን መዝጋታ቞ውን ተኚትሎፀ ዚተዘጉትን ዚመንገድ እና ዚባቡር መስመር ለማስኚፈት "ኚወጣቶቹና ኚሕዝቡ ጋር እዚተወያዚን ነው። መንገዱና ዚባቡር መስመሩ እንዲኚፈት እዚሠራን ነው" ሲሉ ዚሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ ለሮይተርስ በአጭር ዚጜሑፍ መልዕክት ምላሜ ሰጥተው ነበር። ትናንት ለቢቢሲ ቃላቾውን ዚሰጡት ዹክልሉ ኮሚኒኬሜን ምክትል ኃላፊፀ ኹአገር ሜማግሌዎቜ እና ኚወጣቶቜ ጋር በተደሹገው ንግግር መንገዱ ኚሐሙስ ጠዋት ጀምሮ ዹተኹፈተ ሲሆንፀ በባቡር መስመሩ ላይ ግን ጉዳት በመድሚሱ እስካሁን አገልግሎት አልጀመሹም ብለዋል። በማኅበራዊ ሚዲያዎቜ ላይ ዹተለቀቁ ፎቶዎቜ እና ተንቀሳቃሜ ምስሎቜ ተቃዋሚዎቜ ዚባቡር መስመሩን እና ዋና አውራ ጎዳናውን በድንጋይ እና በአፈር ዘግተው አሳይተው ነበር። ዚባቡር ሃዲዱ ብሎኖቜም ተፈተው ታይቷል። መንገዱ እና ዚባቡሩ መስመሩ ስለመዘጋቱም ይሁን ስለመኚፈቱ እስካሁን ድሚስ ዚፌደራሉ መንግሥት ያለው ነገር ዚለም። ኹዚህ ቀደም በሶማሌ እና በአፋር ክልል መካኚል ዚይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባ቞ው ቊታዎቜ በተደጋጋሚ ግጭቶቜ መነሳታ቞ው አይዘነጋም። ቅዳሜ ዕለት ደሹሰ ስለተባለው ጥቃት ኹአፋር ክልል በኩል መሹጃ ለማግኘት ቢቢሲ ወደተለያዩ ዹክልሉ ባለሥልጣናት ስልክ በተደጋጋሚ ቢደውልም ምላሜ ማግኘት አልተቻለም።
https://www.bbc.com/amharic/news-58022659
amh
business
ንግድ፡ በኢትዮጵያ አንድ ግለሰብ ብቻውን ኩባንያ እንዲያቋቁም ተፈቀደፀ አዲሱ ዚንግድ ሕግ ምን ይዟል?
ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት መጋቢት 16/2013 ዓ.ም ላለፉት 62 ዓመታት ሲያገለግል ዹቆዹውን ዚአገሪቱን ዚንግድ ሕግ በመሻር በአዲስ እንዲተካ በሙሉ ድመጜ ወስኗል። ይህን አዲሱ ዚንግድ ሕግ ኹዚህ በፊት ኹነበሹው አንጻር በርካታ ለውጊቜ ዚተደሚጉበት እንደሆነ ይነገራል። ለማዘጋጀትም ሹጅም ጊዜ ዹወሰደና በርካታ ባለሙያዎቜ ዚተሳተፉበት ነበር። ኚቢቢሲ ጋር ቆይታ ዚነበራ቞ውና አዋጁን በማርቀቅ ሂደት ዚተሳተፉት ኹፍተኛ ዹሕግ አማካሪ ታደሰ ሌንጮ (ዶ/ር) ዹሕጉ መውጣት ዚኢትዮጵያን ዚምጣኔ ሀብት እንቅስቃሎን በአወንታዊ መንገድ ለመቀዹር ኹፍተኛ አስተዋጟ እንዳለው ይናገራሉ። ባለሙያው ዹሕጉን መውጣት አስፈላጊነት ሲያስሚዱ ዚሚጠቅሱት ላለፉት 62 ዓመታት ሲያገለግል ዹቆዹው ሕጉ ኚወቅታዊው ዹዓለም ሁኔታ ጋር አለመሄዱን ነው። "ዚንግድ ሕጉ በወጣበት ዚኢኮኖሚ፣ ዚፖለቲካ፣ ዚኢንቚስትመንት፣ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ አውድ ዹ1952ቷ እና ዹ2013ቷ ኢትዮጵያ በጣም ዚተለያዩ ናቾው" ዚሚሉት ታደሰ (ዶ/ር) ይህ መሆኑ ደግሞ ኢትዮጵያ ለንግድ ኚሚመቹ አገራት ዝርዝር ውስጥ በዝቅተኛ ደርጃ ላይ እንድትቀመጥ እንድርጓታል ሲሉ ገልጞዋል። ዹዚህ ውጀት ደግሞ አገሪቱን በተለያዚ መልክ ዋጋ አስኚፍሏታል። "ኢንቚስተሮቜ ይሄ አገር እንዎት ቀላል ነው? እንዎት ለንግድ አመቺ ነው? ዚሚሉትን ነገር ሰለሚያዩ ወደ ኢትዮጵያ ዚሚመጣው ኢንቚስመንት ይቀንሳል ማለት ነው። ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ያለውን ካፒታል ዚመሳብ አቅሟንም በጣም አሳንሶታል" በማለት ዚሚያስርዱት ባለሙያውፀ ይህም ዚሥራ ፈጠራንና ዹውጭ ንግድን እንዲሁም ዚምጣኔ ሀብት ዕድገቷን ዚሚገታ ነው ሲሉ አብራርተዋል። በ1952 ዓ.ም ዚወጣውን ይህን ሕግ ለመቀዹር ኹ30 ዓመት በፊት ጀምሮ ጥሚት ሲደሚግ እንደቆዚ ተገልጻል። 825 አንቀጟቜ ያሉት አዲሱ አዋጅ በርካታ ማሻሻያዎቜን ዚያዘ ነው። ኚእነዚህ ጥቂቶቹን እንመልኚት። አንድ ግለሰብ ለብቻው ኩባንያ መክፈት እንዲቜል ተፈቅዷል በቀድሞው ዚንግድ ሕግ መሠሚት ኃላፊነቱ ዹተወሰነ ዹግል ድርጅት ለማቋቋም ቢያንስ ሁለት ሰዎቜ ያስፈልጋሉ። "ለምሳሌ ዹውጭ ኩባንያዎቜ ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቚስት ሲያደርጉ አንድ ሌላ ሰው ማምጣት ይጠበቅባ቞ዋል ማለት ነው። ይህ ብዙ ወጪ ነው ዚሚያስወጣ቞ው። ኹፍተኛ ጥርጣሬም ይፈጥራል" ይላሉ ዹሕግ ባለሙያው። ኹዚህም በላይ አብሮ ኩባንያውን ዹመሰሹተውን ሰው ባለመስማማት ወይም በሞት ምክንያት ለመቀዹር ሲፈለግ ያለውን ሒደት "አበሳ ነው" ሲሉ ኚባድነቱን ይገልጹታል። ይህም ዚኩባንያውን ቀጣይነት ጥያቄ ውስጥ ዚሚያስገባና አላስፈላጊ ለሆኑ ወጪዎቜ ዚሚዳርግ ነው ሲሉም አክለዋል። እንደ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጻ፣ በአገር ውስጥ ያሉ በርካታ ኃላፊነታ቞ው ዹተወሰኑ ዹግል ኩባንያዎቜ በተግባር ዚአንድ ሰው ሆነው ሳለፀ ለሕጉ ሲባል ግን ተጚማሪ ሰው በባለቀትነት ይመዘግባሉ። አዲሱ ዚንግድ ሕግ ይህን ግዎታ አንስቶ አንድ ግለሰብ ብቻውን ኩባንያን እንዲኚፍት ፈቅዷል። ይህም ሰዎቜ በቀላሉ ወደ ሥራ እንዲገቡና ባለቀትነትን በተመለኹተ ስጋት እንዳይኖራ቞ው ያግዛ቞ዋል ብለዋል። ዚንግድ ትርጓሜን መቀዹር በተሻሚው ሕግ ዚተዘሚዘሩት ዚንግድ አይነቶቜ 21 ብቻ ና቞ው። ኹነዚህ ውጪ ያሉት ንግድ አይደሉም ተብለው እንደሚገመቱ ባለሙያው ያስሚዳሉ። አሁን ግን ሕጉ ዚንግድ አይነቶቜን ወደ 38 አሳደጓ቞ዋል። "ያም ብቻ ሳይሆን በአዲሱ ሕግ ዚንግድ ትርጉም ክፍት ነው። በግልፅ ካልተኚለኚለ በስተቀር ማንኛውም ሰው ኹፀሐይ በታቜ ባለን ሥራ ንግድ ነውፀ ያተርፋል ብሎ እንደሙያ ዚያዘውን ሥራ አስመዝገቊ መቀጠል ይቜላል" ሲሉ አስሚድተዋል። ይህ መሆኑ ደግሞ አዳዲስ ዚንግድ አይነቶቜንና ዚፈጠራ ሐሳቊቜን እንደሚያበርታታ አክለዋል። ኃላፊነታ቞ው ዹተወሰኑ ዚሙያ ሜርክና ማኅበራት መፈቀድ ኹቀደመው ሕግ በተቃራኒው አዲስ ዹጾደቀው አዋጅ ግለሰቊቜ በሙያ቞ው ተደራጅተው እንዲሠሩ በግልጜ ድንጋጌ አስቀምጧል። አዋጁን በማርቀቅ ሒደት ዚተሳተፉት ኹፍተኛ ዹሕግ አማካሪውፀ እያንዳንዱ ሙያ ዹሚጠይቀውን ሥነ ምግባር ይዘው ደንበኞቻ቞ውን ዚሚያስተናግዱ ዚሜርክና ዚሙያ ማኅበራት እንዲስፋፉ ያስቜላል ብለዋል። በሌላው ዓለም በስፋት ዚሚሠራበት ቢሆንም ኢትዮጵያ ውስጥ ዹነበሹው ሕግ በግልጜ ባለመፍቀዱ ዘርፉን አዳክሞታል። በሌላ በኩል ዚቀድሞው ሕግ ዚአክስዮን ማኅበራት ዚዳይሬክተሮቜ ዚቊርድ አባላት ሁሉም ዚአክሲዮን ባለድርሻ እንዲሆኑ ግዎታ ዚጣለ ነበር። ነገር ግን በአዲሱ ሕግ ባለድርሻ መሆን ሳይጠበቅባ቞ውፀ ባለ ድርሻ ያልሆኑ ሰዎቜ በሙያ቞ው እስኚ አንድ ሊስተኛ ድሚስ ዹሚሆነውን ዚዳይሬክተሮቜ ቊርድ አባልነት ቊታን እንዲይዙ ይፈቃዳል። በተጚማሪም ኚተሻሚው ሕግ በተቃራኒ ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ዚሚኚስሩ ዚንግድ ሰዎቜ ነጻ ዚሚሆኑበትን መንገድ እንዳመቻ቞ም ገልጞዋል። ዹሕግ ባለሙያው ታደሰ (ዶ/ር) እነዚህን ጚምሮ ለንግድ እንቅስቃሎው ዚማይመቹ ሕጎቜን ያሻሻለው ዚአዲሱ አዋጅ መውጣት "በአገር ውስጥ ያለውን እንቅሰቃሎ በኹፍተኛ ሁኔታ ይጚምራል" ብለዋል። በአዲሱ አዋጅ ያልተካተቱት ዚባንክ፣ ዚኢንሹራንስና፣ ዚማጓጓዣ ዘርፎቜን ዚሚመለኚቱ ጉዳዮቜ በቀድሞው አሠራር መሠሚት ዚሚቀጥሉ ሲሆንፀ በቀጣይ ራሳ቞ውን ቜለው እንዲወጡ እዚተሠራ መሆኑ ተጠቁሟል። አዲሱ ዚንግድ ሕግ በነጋሪት ጋዜጣ ወጥቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ገብቶ ዚቀድሞውን ሕግ ይተካል ተብሎ ይጠበቃል።
https://www.bbc.com/amharic/56547521
amh
business
በኢትዮጵያ ይጀመራል ዚተባለው ክሬዲት ካርድ ምንድነው? አገልግሎቱን ለማግኘት ኚእርስዎ ምን ይጠበቃል?
አዋሜ ባንክ በኢትዮጵያ ዚክሬዲት ካርድ አገልግሎት በመስጠት ዚመጀመሪያው ባንክ ለመሆን መቃሚቡን አሳውቋል። ባንኩ በቅርቡ ይፋ እንዳደሚገው ‘ዎቢት ካርድ’ ኹተሰኘው አገልግሎት በተጚማሪ፣ ዚክሬዲት ካርድ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል። በዚህም ሁለት ዓይነት ዚክሬዲት ካርድ አገልግሎት እንደሚጀምር በገለጞበት ወቅት አንደኛው ሙሉ በሙሉ በአንድ ጊዜ ዚሚመለስ፣ ሌላኛው ደግሞ ተኹፋፍሎ ዚሚመለስ ነው ብሏል። ዚኢትዮጵያ ባንኮቜ ኚዎቢት ካርድ አገልግሎት በቀር ሌሎቜ ዚካርድ አገልግሎቶቜ ለደንበኞቻ቞ው አይሰጡም። ኹዚህ ቀደም ዳሞን ባንክ ኢንተርናሜናል ዎቢት ካርድ ዹተሰኘ ዹውጭ ምንዛሪ ለሚጠቀሙ ደንበኞቜ ዹሚሆን ካርድ ይፋ አድርጎ ነበር። ይህ ዚተለያዚ ዓይነት ዚገንዘብ ዝውውር ዚካርድ አገልግሎት በዓለም ዙሪያ ያሉ ታላላቅ ባንኮቜ ለደንበኞቻ቞ው ዚሚሰጡት አገልግሎት ነው። በርካታ አገር በቀል ባንኮቜ ያሏት ኢትዮጵያ በቅርቡ ዹውጭ አገር ባንኮቜ ወደ ገበያው እንዲገቡ እንደሚፈቅድ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማሳወቁ ይታወሳል። አብዛኞቹ ዓለም አቀፍ ባንኮቜ ዚዎቢት ካርድን ጚምሮ ዚክሬዲት ካርድ እንዲሁም ሌሎቜ ዚካርድ አገልግሎቶቜ ለደንበኞቻ቞ው ይሰጣሉ። ለመሆኑ ክሬዲት ካርድ ምንድነው? እርስዎስ ዚክሬዲት ካርድ ተጠቃሚ መሆን ይቜላሉ? ጥቅም እና ጉዳቱስ? ዚዩናይትድ ኪንግደም ዹተመሰኹሹላቾው ዚሒሳብ አዋቂዎቜ ማኅበር አባል ጥላሁን ግርማ ባንኮቜ በተለምዶ ሁለት ዓይነት ዚካርድ አገልግሎቶቜ እንደሚሰጡ ያስሚዳሉ። ዹማማኹር እና ኊዲቲንግ ባለሙያው እንደሚሉት ዎቢትፀ ደንበኛው ባለው ተቀማጭ ገንዘብ መጠን ኚኀቲኀም ወጪ ማድሚግ ዚሚያስቜለውፀ እንዲሁም በክፍያ ማሜን መጠቀም ዚሚያቜለው ካርድ ነው። “ነገር ግን ክሬዲት ካርድ ማለት ባንኩ ‘ካለህ ተቀማጭ ገንዘብ በላይ ይህን መጠቀም ትቜላለህ’ ብሎ ዚሚፈቅድልህ ጊዜያዊ ብድር ነው።” ባንኮቜ ለደንበኞቻ቞ው ይህን ዚካርድ አገልግሎት ዚሚፈቅዱት ዹቀደመ ዚሒሳብ አጠቃቀም እንዲሁም ዚገቢ ምንጭ እና መጠናቾውን ኚግምት አስገብተው ነው። አቅም ላላቾው ደንበኞቜ ካላ቞ው ተቀማጭ ገንዘብ በላይ ወጪ ማድሚግ እንዲቜሉ ሊፈቀድላ቞ው እንደሚቜልም ያስሚዳሉ። ባለሙያው ዚክሬዲትና ዎቢት ካርድ ልዩነት ሰርፆ እንዲገባን በምሳሌ ያስሚዱናል። ለምሳሌ ይላሉ. . . “ለምሳሌ 20 ሺህ ብር ካለህፀ ኚኀቲኀምም አውጣ፣ ግብይትም ፈጜመበት፣ ካለህ በላይ ማውጣት አትቜልም።” ክሬዲት ካርድ ግን ባንኮቜ ዹደንበኛው መልሶ ዹመክፈል አቅም ኚግምት በማስገባት ለአጭር ጊዜ ዚሚሰጥ ብድር ዓይነት ነው። በበርካታ ዹዓለም አገራት ዚክሬዲት ካርድ ብድር ወለድ ዚሚኚፈልበት ነው። ነገር ግን በአንዳንድ አገራት ደንበኞቜ በተሰጣ቞ው ቀነ ገደብ ካልኚፈሉ ነው ወለድ ዚሚጣልባ቞ው። “ለምሳሌ በ15 ቀናት ውስጥ እኚፈላለሁ ብለህ ሳትኚፍል ቀኑ ካለፈብህ ወለድ ይኖሚዋል። ዚአዋሜ ባንክ ፖሊሲ ምን ሊሆን እንደሚቜል ዹምናዹው ነው ዚሚሆነው።” ደንበኞቜ ዚክሬዲት ካርድ አገልግሎት ለማግኘት ለባንኩ ይህን ያህል ብድር ይፈቀድልኝ ብለው ማመልኚቻ ማስገባት አለባ቞ው። ባንኩ ባስቀመጠው መሥፈርት መሠሚት ዚደንበኞቜን አቅም እንዲሁም ኚባንኩ ጋር ያላ቞ውን ግንኙነት ተመልክቶ ፈቃድ ይሰጣል። “ዹደመወዝ መጠንህ ሊሆን ይቜላልፀ ኚባንኩ ጋር ያለህ ግንኙነት ሊሆን ይቜላልፀ ነጋዮ ኹሆንክ ዚንግድ ሁኔታህ ሊሆን ይቜላል። አንዳንድ ጊዜ ባንኩ ኪሳራውን እያወቀ ሊፍቀድ ይቜላል።” ባለሙያው ደጋግመው ዚባንክ ተጠቃሚዎቜ ዚክሬዲት ካርድን ዓላማ በግልፅ ማወቅ እንዳለባ቞ው ይመክራሉ። “ክሬዲት ካርድ ዚሚሰጥህ ለአጭር ጊዜ ዚብድር ፍላጎትህ ነው። እንጂ ቋሚ ንብሚት [መኪና፣ ቀት] እንድትገዛበት አይደለም።” ዚክሬዲት ካርድ ዋነኛው ዓላማው ድንገተኛ ለሆነ ዚገንዘብ ቜግር መውጫ ነው። ለዚህ ነው ዚሚመለስበት ዹጊዜ ገደብ ዚተቀመጠለት ይላሉ ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያው። “አዋሜ ባንክም ዹተጠቀምኹውን ገንዘብ ዚምትመልሰው በምን ያህል ጊዜ ነው ዹሚለውን በተመለኹተ ዚራሱን ፖሊሲ ያወጣል ብዬ አስባለሁ። ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ ይህ ዹሚወሰነው በደንበኛው ዚገቢ ምንጭ ነው።” ለምሳሌ እርስዎ ተቀጣሪ ኹሆኑ በወሩ መጚሚሻ ደመወዝ ሲቀበሉ ለመክፈል ሊስማሙ ይቜሉ ይሆናልፀ በንግድ ኚተሠማሩ ደግሞ ምናልባት በወር ሁለት ጊዜ ለመክፈል ይፈርማሉ። አዋሜ ባንክ ይህንን አገልግሎት ለባንኩ ተጠቃሚዎቜ በሙሉ ለመስጠት ቃል ገብቷል። ዹ44 ዓመቱ እንግሊዛዊ ዳሚን ዹ32 ሺህ ዩሮ ዕዳ ውስጥ ኚገባ በኋላ ዚሚያደርገው ጠፍቶት ነበር። ዳሚን ኚባንክ ዹወሰደውን ክሬዲት ካርድ እዚመዠሚጠ ለሚያስፈልገው ጉዳይ ጥቅም ላይ ቢያውለውም ዕዳውን በጊዜ መክፈል ዚሚያስቜል አቅም አልነበሚውም። “እንኳን ልቀንስ ይቀርና በዕዳ ላይ ዕዳ ስጚምር ነው ዚኚሚምኩት። ኹወር ወር ሲያድግፀ ኚዓመት ዓመት እዳዬ ሲያሻቅብ ነው ዚኚሚመው። በጣም ጭንቀት ውስጥ ነበርኩ።” ምንም እንኳ ዳሚን አሁን ዕዳውን ኹፍሎ ቢገላገልም በርካታ እንግሊዛዊያን አሁንም ዚክሬዲት ካርድ ዕዳ ውስጥ ና቞ው። ጥላሁን እንደሚሉት ክሬዲት ካርድ በአግባቡ ጥቅም ላይ ካልዋለ ተጠቃሚውንና ባንኮቜ ለኪሳራ ሊዳርግ ይቜላል። ለዚህ ነው ዚክሬዲት ካርድ ዋነኛ ዓላማው መሆን ያለበት አንድን ቜግር ወዲያው ለመፍታት መሆን አለበት ዚሚሉት። “ለምሳሌ ቀተሰብ ቢታመምብህ አሊያም በሚቀጥለው ወር ዕቁብ ዚሚወጣልህ ቢሆንና አሁን አንድ ዕቃ መግዛት ብትፈልግ ክሬዲት ካርድ መጠቀም ትቜላለህ።” ባለሙያው ክሬዲት ካርድ ማለት “ልክ እንደ ቮሌ ብር ነው” ይላሉ። “ቮሌ ገንዘብ ሳይኖርህ ሲቀር ዚብድር አገልግሎት ይሰጥሃል። በሚቀጥለው ስትሞላ ኚሒሳብህ ላይ ይወስዳል።” በውጭው ዓለም ‘ክሬዲት ስኮር’ ዚሚባል ሐሳብ አለ። ዚክሬዲት ስኮር ማለት አንድ ሰው ብድር ወስዶ ዚመመለስ ታሪኩ እንዎት ያለ ነው ዹሚለውን ዚሚያሳይ ነው። ብድር ወስደው በጊዜ ዚሚመልሱ ሰዎቜ መልካም ‘ክሬዲት ስኮር’ ያላ቞ው ተብለው ይጠራሉ። ዚክሬዲት ታሪካ቞ው ጥሩ ዹሆኑ ሰዎቜ በባንኮቜ ዘንድ ይኚበራሉፀ ዚሚፈልጉት ጉዳዩ በቶሎ ይሳልጥላ቞ዋል። በአብዛኛዎቹ አገራት ዚክሬዲት ካርድ ወለድ፣ ዚባንኮቜ ለደንበኞቻ቞ው ኹሚሰጧቾው ሌሎቜ ካርዶቜ ወለድ ኹፍ ያለ ነው። “ብድር ስለሆነ ወልድ አለው። አደጋ ስላለው ነው ወለዱ ኹፍ ዚሚለው። ንብሚት አስይዞ ዚሚወስድ ሰው እና ንብሚት ሳያስዝ ብድር ዹወሰደ ሰው እኩል ስላልሆነ ዚወለድ መጠኑን ኹፍ በማድሚግ ነው ስጋቱን ዚሚያጣጡት።” ዎቢት ካርድ ሲጠቀሙ ቀሚጥ ዚሚጥል ዹግል ማሜን [ኀቲኀም፣ ዚግብይት ማሜን] ካልሆነ በቀር ተጚማሪ ክፍያ አይኚፍሉም። አልፎም ለተጠቀሙበት ክፍያ ካለው ቀድሞ ያሳወቆታል። ወደ ክዎዲት ካርድ ስንመጣ ግን ኚኀቲኀም ማሜን ገንዘብ ሲያወጡ ክፍያ ይኚፍላሉ። አንዳንድ ጊዜ ካርዱን ዚሰጠዎት ባንክ ዚአገልግሎት ክፍያ ያስኚፍላል። በበይነ መሚብ ዕቃና አገልግሎት ዚሚሞጡ ድርጅቶቜ ኚዎቢት ካርድ ይልቅ ክሬዲት ካርድ ይመርጣሉ። ለዚህ ምክንያቱ ክሬዲት ካርድ ሲሆን ገንዘቡን ኚባንክ ቀጥታ ማግኘት ስለሚቜሉ ነው። ባለሙያዎቜ ክሬዲት ካርድ ተጠቅሞ ኚኀቲኀም ገንዘብ ማውጣትን አይመክሩም። ኚዚያ ይልቅ በሚገበያዩበት ወቅት ክሬዲት ካርድዎን ይጠቀሙ ይላሉ። ቪዛ፣ ማስተርካርድ፣ አሜሪካን ኀክስፕሚስ እና ዲስኚቚር ዚክሬዲት ካርድ ኔትዎርኮቜ ና቞ው። ባንኮቜ እኒህን ኔትዎርኮቜ ተጠቅመው ነው ለደንበኞቻ቞ው ክሬዲት ካርድ ዚሚያውጁት። አብዛኞቹ ዓለም አቀፍ ባንኮቜ ዚክሬዲት ካርድ ለሚጠቀሙ ደንኞቻ቞ው ማበሚታቻ ሜልማት ይሰጣሉ። ለምሳሌ ዚአውሮፕላን ቲኬት ለመቁሚጥ፣ ለሆቮል ክፍያ፣ ለበይነ-መሚብ ግብይት ክሬዲት ካርድ ኹሚጠቀሙ ደንበኞቻ቞ው ማበሚታቻ ይሰጣሉ። ማበሚታቻው በአዹር መንገድ ማይል፣ በተጚማሪ ዹሆቮል ክፍያ እንዲሁም በስጊታ ካርድ መልክ ሊሰጥ ይቜላል። ባንኮቜ ለደንበኞቻ቞ው በዚወሩ ‘ስ቎ትመንት’ [ዚባንክ ሒሳብ መሹጃ] ይልካሉ። ይህ ስ቎ትመንት ደንኞቜ ክሬዲት ካርዳ቞ውን ተጠቅመው ምን ያህል ክፍያ እንደፈፀሙ፣ ዚወለድ መጠኑን እና ተጚማሪ ክፍያውን ዚሚያካትት ነው። አክሎምፀ ክሬዲት ካርዳ቞ው ውስጥ ምን ያህል ገንዘብ እንደቀሚፀ መልሰው ሊኹፍሉ ዚሚገባ቞ው ዝቅተኛ መጠን ስንት እንደሆነ እና እንዎት መክፈል እንደሚቜሉ ይካተትበታል። ዚሒሳብ አዋቂው ጥላሁን ኚአዋሜ ባንክ እርምጃ በኋላ “ሌሎቜ ባንኮቜ ተኝጠው አያድሩም” ይላሉ። “ይህ አገልግኮት እስካሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ሳይጀመር መቆዚቱ በጣም ዹሚገርም ነው። ሌሎቜም ባንኮቜ ለመጀመር ዝግጅት ላይ ናቾው አሊያም ኚአዋሜ ባንክ በኋላ መጀመራ቞ው አይቀርም።”
https://www.bbc.com/amharic/articles/c9805q1yq39o
amh
business
ኮቪድ-19፡ ቀት ዚመቀመጥ ገደብ ጉግልን ትርፋማ አድርጓል ተባለ
ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝን ተኚትሎ ዚተጣለው ቀት ውስጥ ዚመቀመጥ ገደብ ለጉግል ትርፋማነት አስተዋጜኊ አድርጓል ተባለ። ዹጉግል ባለቀት ድርጅት ዹሆነው አልፋቀት ባለፉት ሊስት ወራት ብቻ 17 ቢሊዮን ዶላር ዚተጣራ ትርፍ ያገኘ ሲሆን ይህም ዹ162 በመቶ ጭማሪ መሆኑ ተገልጿል። ለትርፋማነቱም ሰዎቜ በወሚርሜኙ ሳቢያ እንቅስቃሎያ቞ው ሲገደብ ዹጉግልን አገልግሎቶቜ መጠቀማቾው በምክንያትነት ተቀምጧል። ያለፉት ሊስት ወራትም በድርጅቱ ታሪክ ኹፍተኛ ትርፍ ዚተመዘገበበት ነው ተብሏል። ጉግል ይህን ዚትርፍ መጹመር "ደንበኞቌ ኢንተርኔት በመጠቀም ዚሚያኚናውኗ቞ው ተግባራቶቜ መጹመር ያመጣው ነው" ሲል ገልጟታል። "ባለፈው ዓመት ሰዎቜ ዹጉግል መፈለጊያን ተጠቅመው ራሳ቞ውን ኹመሹጃ ላለማራቅ፣ ለመዝናናት እና ኚሰዎቜ ጋር ያላ቞ውን ግንኙነት ለማስቀጠል ሲጠቀሙት ቆይተዋል" ሲሉ ዚአልፋቀት እና ጉግል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሱንዳር ፒቻዪ ገልጞዋል። ዹዘርፉ ተንታኞቜም ዹተዘጉ ኢኮኖሚዎቜ ሲኚፈቱ እና ዚኢንተርኔት ላይ ማስታወቂያዎቜም እዚተበራኚቱ ሲሄዱ ጉግል ኹፍተኛ ትርፍ መሰብሰቡን ይቀጥላል ብለዋል። ጉግል ባለፈው ሊስት ወራት በአጠቃላይ ኚመፈለጊያ ንግዱ [Search business] ዹሰበሰበውን ገቢ በ30 በመቶ በመጹመር ወደ 31 ቢሊዮን ዶላር ኹፍ ብሏል። ዩትዩብ ደግሞ በስድስት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ዹ49 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። በሃርግሬቭስ ላንሱንግ ዚፍትሐዊነት ተንታኝ ዚሆኑት ሶፊ ሉንድ-ያትስ በበኩላ቞ው አልፋቀት "ጉግል በወሚርሜኙ ሳቢያ በተገኘው ገቢ ልክ በክሬም ላይ እደተወሚወሚቜ ትልቅ ድመት ሆኗል" ሲሉ ትርፉን ገልጞውታል። ዹቮክኖሎጂ ግዙፉ ኩባንያ ጉግልፀ ባልተለመደ መልኩ ዚማስታወቂያ ንግድ ድርጅት ወደመሆን ማዘንበሉንም ተንታኙ ተናግሚዋል። "ዚኮሮናቫይሚስ ሲኚሰት በተለይም ዚኢንተርኔት ላይ ግብይት በመጧጧፉ ምክንያት ዚአልፋቀት ዚንግድ ተቋማት ለእነዚህ ሞቀጊቜ ማስታወቂያ ማስነገራ቞ው ገቢያ቞ው እንዲተኮስ ምክንያት ሆኗል" ሲሉም ለኹፍተኛ ትርፍ ያበቃውን ምክንያት አስሚድተዋል። ይሁን እንጂ ጉግል ኚተለያዩ ተቆጣጣሪ ተቋማት በተለይም ፍትሐዊ ዚንግድ ውድድርን እና ዹግል ምስጢር መጠበቅን በተመለኹተ እያጋጠመው ያሉት ጥያቄዎቜ ዋና ተግዳሮቶቹ ሆነው ቀጥለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-56884833
amh
business
"ዹዓለም አስር ባለ ጞጎቜ ሀብት ቢደመር ለሁላቜንም ክትባት ይገዛል"
ኊክስፋም ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመለክተውፀ በወሚርሜኙ ወቅት ሀብታ቞ው ዹናሹ አስር ወንዶቜ ሀብት ንብሚት ሲደመር 540 በሊዮን ዶላር ይጠጋል። ይህ ሀብት ዹዓለም ሕዝቊቜን ኚድህነት ዚሚያወጣ እንዲሁም ለሁሉም ሰው ክትበት መግዛት ዚሚያስቜል እንደሆነ ዚተራድኊ ድርጅቱ ኊክስፋም ጠቁሟል። በዓለም ላይ ያሉ ቢሊዚነሮቜ ጠቅላላ ሀብትፀ ዹጂ-20 አገራት ወሚርሜኙ ካሳደሚው ጫና ለመላቀቅ ኚሚያወጡት ወጪ እኩል መሆኑ በኩክፋም ሪፖርት ተመልክቷል። ኊክስፋም ይህንን ሪፖርት ተመርኩዞ መንግሥታት ባለ ጞጎቜ ላይ ኹፍተኛ ግብር እንዲጥሉ ያሳስባል። 'ኢንኢኳሊቲ ቫይሚስ' ዹተሰኘው ሪፖርት ዚወጣው መንግሥታት ለዓለም አቀፉ ዚምጣኔ ሀብት ጉባኀ በተሰበሰቡበት ወቅት ነው። መንግሥታት ለምጣኔ ሀብታ቞ው ያደሚጉት ድጋፍ ዚአክስዮን ገበያ እንዲያንሰራራና ዚቢልዚነሮቜ ገቢ እንዲጚምር አድርጓል። ዚእነዚህ ግለሰቊቜ ሀብት ሲጚምር ዚአገራት ጠቅላላ ምጣኔ ሀብት ግን አሜቆልቁሏል። ኚሚያዝያ 2020 እስኚ ጥቅምት 2020 ዹመላው ዓለም ዚቢልዚነሮቜ ሀብት በ3.9 ትሪሊዮን ጚምሯል። ዹጂ-20 አገራት ወሚርሜኙን ለመኹላኹል ያወጡት ወጪ ሲደመርም ኚባለ ጞጎቹ ሀብት ጋር እኩል ነው። በወሚርሜኙ ወቅት ሀብታ቞ው ኹናሹ መካኚል ዹአማዞን መስራቜ ጄፍ ቀዞስ፣ ዚተስላ መስራቜ ኀለን መስክ እና ዚፌስቡክ መስራቜ ማርክ ዙኹርበርግ ይገኙበታል። ጄፍ ቀዞስ ካለው ሀብት ለእያንዳንዱ 876,000 ዹአማዞን ተቀጣሪ 105,000 ዶላር ጉርሻ ቢሰጥ እንኳን ኚወሚርሜኙ በፊት ዹነበሹው ሀብቱ እንደማይቀንስ ሪፖርቱ ያሳያል። በተቃራኒው በድህነት ውስጥ ዚሚኖሩ ሰዎቜ ወሚርሜኙ ኚሳደሚባ቞ው ተጜዕኖ ለማገገም አስርት ዓመታት ያስፈልጋ቞ዋል። በወሚርሜኙ ሳቢያ ተጚማሪ 500 ሚሊዮን ሰዎቜ ወደ ድህንት አሹንቋ እንደገቡ ኊክስፋም ገልጿል። ዚኊክስፋም እንግሊዝ ዋና ኃላፊ ዳኒ ስሪስካንዳርጃህ ለቢቢሲ እንደተናገሩትፀ "ሀብታሞቜ ላይ ግብር በመጣል፣ ለእያንዳንዱ ዜጋ መሠሚታዊ ዚገቢ መነሻ በማበጀትና በሌሎቜም መንገዶቜ ፍትሐዊ ክፍፍልን ማሚጋገጥ አለብን።" በወሚርሜኙ ወቅት አንዳንድ ሀብታም ሰዎቜ ዚገንዘብ ድጎማ እዚሰጡ ነው። ዹጄፍ ቀዞስ ዚቀድሞ ባለቀት መኹንዚ ስኮት ያደሚገቜው ዚአራት ቢሊዮን ዶላር ድጎማ ይጠቀሳል።ጄ ፍ ቀዞስ ደግሞ ኚኮሮናቫይሚስ ጋር ዹሚደሹገውን ትግል ለመደገፍ 125 ሚሊዮን ዶላር ሰጥቷል። ዚትዊተር አጋር መስራቜ ጃክ ዶርሲ ኚሀብቱ አንድ ቢሊዮን ዶላር ወሚርሜኙን ለመኹላኹል እንዲውል ሰጥቷል። ቢል ጌትስ እና ባለቀታ቞ው መሊንዳ ለክትባት ምርትና ግዢ 305 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል ገብተዋል።
https://www.bbc.com/amharic/55798217
amh
business
በኹተማ ግብርና ዚተለወጡት ዚአዲስ አበባ ዙሪያ አርሶ አደሮቜ
በኚተሞቜ ውስጥና በዙሪያ቞ው ዚሚኖሩ አርሶ አደሮቜ ዚተለያዩ ዚግብርና ምርቶቜን ለነዋሪዎቜ ያቀርባሉ። ይም በተወሰነ ደሹጃ ዹኹተማ ነዋሪዎቜን ፍላጎት ሲያሟላ ለእነሱም ዚገቢ ምንጭ ይሆናል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cp639zpjxrgo
amh
business
ዹምንፈልገውን ሥራ እና እድገት ለማግኘት ራሳቜንን እንዎት እንግለጜ?
ስለራስ መናገር ም቟ት አይሰጥምፀ አይደለም ለአለቃ ለወዳጅ እንኳ ቢሆን 'ምን ጉራህን ት቞ሚቜራለህ' ሊያስብል ያስቜላል። ዹሰው ጀማ ተሰብስቊ ስለራስ 'ጥሩንባ መንፋት' ዹተለመደ አይደለምፀ ይህ ግን ዚኢትዮጵያውያን ቜግር ብቻ ሳይሆን ፈሚንጆቹም እዚህ ላይ ትንሜ ቆንጠጥ ያደርጋ቞ዋል። ስለራሳ቞ው ለመናገር ጀምሹው ድምጻ቞ው ዚሰለለባ቞ው፣ እጃ቞ውን ያላባ቞ው፣ አፋቾውን ዚፈቱበት ቋንቋ ዹጠፋቾውን ዚዚመሥሪያ ቀቱ ደጃፍ ይቁጠራ቞ው። ለስ቎ፋኒ ስዎርድ ዊሊያምስ ግን "ይህ ክህሎት ሁለቮ ማሰብ ዚማያስፈልገው ሁሉም ሊኖሹን ዚሚገባ ነው" ትላለቜ። ስ቎ፋኒ ራስን በብቃት መግለጜ መቻል ላይ በበርካቶቜ ዹተነበበ መጜሐፍ አዘጋጅታለቜ። በሠሯ቞ው ሥራዎቜ፣ ባገኟ቞ው ውጀቶቜ መኩራራት፣ ደሚትን መንፋት ልክ እንደ በጎ ምግባር ሊቆጠር ይገባል ስትል ታስሚዳለቜ። ነውር አለመሆኑንም አጜንኊት ሰጥታ ነው ዚምትናገሚው። በዚህ ፉክክር በበዛበት ዓለም ያለዎትን ክህሎት ማጉላት በሥራ ቊታ ለውጀትዎ ላቅ ያለ ድርሻ ይኖሚዋል። በሥራዎ እድገት ለማግኘት፣ አዲስ ሥራ ለመቀዚር፣ በአለቃዎ ዕይታ ውስጥ ለመግባት እና ዚድርጅትዎን ዚእድገት መሰላል በቀላሉ ለመውጣት ስለራስዎ ያለመሞማቀቅ መናገር ያስፈልግዎታልፀ ይጠበቅብዎታልም። ለአንድ ሥራ በርካቶቜ ዚማመልኚቻ ዶሎ ተሾክመው በዚቀጣሪዎቜ ደጅ በሚንኚራተቱበት በዚህ ወቅት፣ ሁሉም ዲግሪ እና ማስተርስ ኖሮት ያለቜው ጥቂት እድገት ላይ ዓይኑን ጥሎ በሚጠብቅበት ዚሥራ ቊታ "ራስን መሞጥ" ተገቢ ክህሎት ሆኖ ይገኛል። ይህ ደግሞ ዓይን አፋር ለሆኑ እና ራሳ቞ውን መግለጜ ለሚ቞ገሩ ሎቶቜ አስፈላጊ ክህሎት ነው። ዚራሳ቞ውን ሥራ ኚቀታ቞ው ሆነው ለሚሰሩ፣ በኮቪድ ወሚርሜኝ ዚተነሳ ዚገበያ ዕድሎቜን ሳስተው፣ ኚብዙኃኑ ጋር ተቀላቅሎ ለመወዳደር ፈተና በሆነበት በዚህ ወቅት ያለው አማራጭ ስለራስ ስኬት፣ ስለ አገልግሎትዎ እና ስለ ክህሎትዎ ደሚትን ነፍቶ ማስሚዳት መቻል ነው። "ዚራሳቜንን እሎቶቜ ለማሳዚት ጊዜ ዚማንወስድ ኚሆነፀ እንደ ተፈላጊ ዹመቆጠር ዕድላቜን ላይ በር እንዘጋለን" ስትል ስዎርድ ዊሊያምስ ታስሚዳለቜ። "ስለ ራሳቜን ዚምንታወቅበትን ነጥቊቜ ይፋ በማድሚግ፣ ማንንነታቜንን በማሳዚት ታሪካቜንን ራሳቜን መንገር ያስፈልገናል" ባይ ናት። ስለ እኛ ሌሎቜ እንዲመሰክሩልን መጠበቅ ዚዋህነት ነው ስትልም ታክላለቜ። ራስን ማስተዋወቅ በቀላል ብያኔ ሥራዎና ስኬትዎ ተገቢውን ትኩሚት እንዲያገኝ ማድሚግ ማለት ነው። ስለዚህ ስለራስዎ በማኅበራዊ ድሚ ገጜ ላይ ዚሚያስቀምጡት መግለጫ፣ ወይንም በኢሜል መልዕክት ላይ ዚሚያስገቡት ማብራሪያ ካልሆነ ደግሞ ኹአለቃዎ ወይንም ኹቁልፍ ሰዎቜ ጋር በሚኖርዎት ውይይት ወቅት ዚሚያነሷ቞ው ነጥቊቜ ራስዎን በሰዎቜ ፊት ሞገስ በማሰጠት ሚገድ ትልቅ ሚና አላ቞ው። በተሰማሩበት መስክ ለማደግ እንዲሁም ማንነትዎን እና ብቃትዎን [ብራንድ] በሚገባ ለማስተዋወቅ ጠቃሚ ነው። በተሰማራበት መስክ እስኚ መሰላሉ ዹላይኛው ጫፍ ለመውጣት ዹሚፈልግ ሰው ደግሞ ይህንን ቢያደርግ መንገዱን ዹውሃ ያደርገዋል። ይህ ዓለም ዚወንዶቜ ነው በሥራው ዓለም ዹተደሹጉ ጥናቶቜ እንደሚመሰክሩት ኹሆነ ስለራስ በመናገር ኚሎቶቜ ይልቅ ወንዶቜ ይደፍራሉ። እኀአ በ2019 መቀመጫውን አሜሪካ ያደሚገ አንድ አካዳሚ፣ ይፋ ባደሚገው ጥናት ራስን በመግለጜ ሚገድ "ትልቅ ዚሥርዓተ ጟታ ክፍተት ይታያል።" ተመራማሪዎቹ ለጥናቱ ተሳታፊዎቜ ዚሒሳብ እና ዚሳይንስ ፈተና እንዲወስዱ፣ ኚዚያም ብቃታ቞ውን ራሳ቞ው እንዲመዝኑ አድርገዋል። ዚጥናቱ ተሳታፊዎቜ ለራሳ቞ው ዚሰጡት ውጀት ለአለቆቻ቞ው ማንን ለመቅጠር እና ምን ያህል መክፈል እንደሚገባ቞ው መወሰን እንዲቜሉ እንዲያውቁት እንደሚደሚግ ተነግሯ቞ዋል። ምንም እንኳ በጥናቱ ወንዶቹም ሎቶቹም እኩል ውጀት ያመጡ ቢሆንም፣ ወንዶቜ ግን ለራሳ቞ው በአማካኝ 61 ኚመቶ ሲሰጡ ሎቶቜ ግን 46 ኚመቶ ሰጥተዋል። ሎቶቜ ስለምን ኚወንዶቜ ዹበለጠ ድሃ ሆኑ (Why Women Are Poorer Than Men) ዹሚል መጜሐፍ ደራሲዋ አናቀላ ዊሊያምስ "ሌሎቜ በርካታ ጥናቶቜ እንዳሳዩት ኹሆነ ወንዶቜ ስለስኬታ቞ው ሲጠዚቁ 'እራሳ቞ውን በመሞጥ' ላይ ዚተዋጣላ቞ው ና቞ው። በተቃራኒው ሎቶቜ ደግሞ ቜሎታ቞ውን እና ውጀታ቞ውን ዝቅ አድርገው ሲያቀርቡ ተስተውሏል" ትላለቜ። ሎቶቜ ኚልጅነታ቞ው ጀምሮ ራሳ቞ውን ኹፍ ኹፍ ሲያደርጉ እዚተገሰፁ ነው ዚሚያድጉት። ራሷን ኹፍ ኹፍ ለምታደርግ ሎትም ዚሚሰጡ ዚተለያዩ ቅጜል ስሞቜ መኖራ቞ውን ትገልጻለቜ። "ነገር ግን ተመሳሳይ ባህሪ ዚሚያሳይ ወንድ በራስ ዹመተማመን ብቃት እና ዚአመራር ቜሎታ እንዳለው ይቆጠርለታል" ስትል ታብራራለቜ። ስዎርድ ዊሊያምስ በበኩሏ በኹፍተኛ ዚሥራ ኃላፊነቶቜ ላይ ዹሚገኙ እና አርዓያ ዹሚሆኑ ሎቶቜ ስለራሳ቞ው መናገር እና ስኬታ቞ውን ማንቆለጳጰስ ተገቢ መሆኑን ሲናገሩ አይደመጡም ትላለቜ። በውጀቱም ሎቶቜ ለአንድ ዚሥራ እድል ኚወንዱ ዹበለጠ እንዲታገሉ ያደርጋ቞ዋል። በእርግጥ አንዳንድ ወንዶቜ አይናፋር፣ ሎቶቜ ደግሞ በተፈጥሯ቞ው ራሳ቞ውን መግለጜ እና ሰለ ሥራ቞ው በድፍሚት ለመናገር ቜግር ላይኖርባ቞ው ይቜላል። በቅርቡ በተደሹገ ጥናትም ወጣት ሎቶቜ በእድሜ ኹገፉ ሎቶቜ ይልቅ ስለራሳ቞ው ደፈር ብለው መናገር እንደሚቜሉ ይፋ አድርጓል። ስለራስ በድፍሚት እና በልበ ሙሉነት መናገር ቊታ ካልተመሚጠለት ባዶ ጩኞት እና ቀሚርቶ ሊሆን እንደሚቜል ባለሙያዎቹ ያስሚዳሉ። ቀጣሪን እና አለቃን ኹመማሹክ ይልቅ ሊያበሳጭ ዚሚቜልባ቞ውም ዕድሎቜ አሉ። በዚህ ወቅትም ስለራስ በልበ ሙሉነት ለመናገር ግቡን መምታት አቅቶት ሲኚሜፍ ይስተዋላል። ስለራስዎ በልበ ሙሉነት ለመናገር ምን ያድርጉ? ስለራስ በልበ ሙሉነት መናገር ግን እንዲሁ ዹሚገኝ ስጊታ አይደለምፀ ልምምድ ይጠይቃል። በተለይ በቢሮዎ ውስጥ፣ በወንበርዎ ላይ በወሚቀት ክምር መካኚል አልያም ኚኮምፒውተር ጀርባ ተቀምጠው ዚዕለት ሥራዎትን ብቻ ዹሚኹውኑ ኹሆነ ኚዕይታም ኚአእምሮም ውጪ ዹመሆን ዕድልዎ ዹሰፋ ነው። እርስዎ ልምዱና ቜሎታው እያለዎት ሌሎቜ አልፈዎት ይሟማሉፀ ይሞለማሉ። እርስዎ በነበሩበት ዹደሞዝ እርኚን ላይ ተቀምጠው ሲያለቃቅሱ ሌሎቜ ዚጥቅማ ጥቅም እና ደሹጃ እድገት በሚኚት ተቋዳሜ ይሆናሉ። ስለዚህ ስለራስዎ በሚገባ መግለጜ፣ ስኬቶቜዎን በደማቅ ቀለም በአለቃ አእምሮ ውስጥ ለመጻፍ እንዲቜሉ ያለማመንታት ልምምድ ያድርጉ። አለቆቜ ዚሰሯ቞ውን ሥራዎቜ ዚሚያስታውሳ቞ው፣ ስኬቶቜዎን እና አስተዋጜኊዎን ዚሚነግራ቞ው ይፈልጋሉ። በተቋሙ ውስጥ ለሚዥም ጊዜ ተቀጥሚው ቢሰሩ እንኳ ስለራስዎ እስካልተናገሩ ድሚስ ዚመሚሳት ዕድልዎ ሰፊ ነው። ስለዚህ ልክ እንደ አዲስ ክህሎት ራስን በልበ ሙሉነት መግለጜንም ሊማሩት እና ሊለማመዱት ዚሚገባ ክህሎት ነው። "ዚሚዥም ጊዜ ዚሥራ ላይ ህልምዎን እና ፍላጎትዎን ለአለቃዎ ይንገሩ" ዚምትለው ሃሪት ሚንተር ነቜ። ሃሪት ሚንተር በዚህ ዘርፍ ጥሩ ዹተነበበ መጜሐፍ ደራሲ ስትሆን "አሁን ጊዜው አይደልም አትበሉ። ኚዚያ ይልቅ ለኩባንያው ያመጧ቞ውን ዕሎቶቜ በመመልኚት በዚያ መሰሚት ጥያቄያቜሁን ሰንዝሩ" ስትል ትመክራለቜ። ሚለር ስለስኬትዎ ለሥራ አጋርዎ እና አለቃዎ ለማሳወቅ ኢሜል አንዱ መንገድ ነው ትላለቜ። በዚህ ኢሜል ውስጥ ማካተት ዹሚፈልጓቾውን መሚጃዎቜ ማካተትዎን፣ በሚገባ መግለጜዎን እና ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜ ዹመላክ ልምድዎን ያዳብሩፀ አንዮ መላክ ኚጀመሩ በቀጣዮቹ ሳምንታት እዚቀለለዎ ይመጣል ስትል ሚለር ትመክራለቜ። ኹዚህ ደግሞ ባለፈ ልምድዎን እና ቜሎታዎን ለማሳዚት አዲስ ተቀጣሪዎቜ ሲመጡ ለማማኚር፣ ለማለማመድ እና ልምድን ለማጋራት ኚፊት ይሁኑ። ለጀማሪዎቜ ልምድን በድፍሚት ማካፈል ያለዎትን ልምድ እና ክህሎት ለሌሎቜ ለማሳዚት ጥሩ ዕድል ነው። በዚህ ዚዲጂታል ዘመን በፌስቡክ፣ በትዊተር እንዲሁም በሊንክዲን ላይ ስለራስዎ ዚሚያሰፍሯ቞ውን መሚጃዎቜም መጠንቀቅ ያስፈልጋል። በዹጊዜው ዚሚስተለካኚሉ እና ያለዎትን ልምድ እና ክህሎት በሚገባ ዚሚገልጹ መሆናቾውን ያስተውሉ። ኹዚህ በኋላ ስራስዎ መናገር ልክ ታሪክ ዹመንገር ያህል ቀላል ይሆናል። እንዎት አድርጌ ብነግሚው ዹበለጠ ይስብልኛል ቀልብም ልብም ይስብልኛል ዹሚለው ያስጚንቅዎት ይሆናል እንጂፀ አፍዎ አይተሳሰርም፣ እጅዎን አያልብዎትም፣ ድምጜዎም አይሰልም።
https://www.bbc.com/amharic/news-58676398
amh
business
በአሜሪካ ማዕቀብ ምክንያት ፊቱን ወደ አሳማ እርባታ ያዞሚው ሁዋዌ
ሁዋዌ በአሜሪካ ዘመናዊ ስልኮቹ ላይ ኚባድ ማዕቀቊቜን በመጣሉ ምክንያት ፊቱን ለአሳማ ገበሬዎቜ ቮክኖሎጂ ወደ ማቅሚብ አዙሯል። ግዙፉ ዚቻይናው ዚ቎ሌኮም ኩባንያ ዚትራምፕ አስተዳደር ለአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት አስጊ ነው ተብሎ በመፈሹጁ አስፈላጊ ዕቃዎቜን እንዳያገኝ ተደርጓል፡፡ ሁዋዌ ዹገጠመውን ዚስማርት ስልክ ሜያጭ ሊያካክስ በመፈለጉ ለቮክኖሎጂው ሌሎቜ ዚገቢ ምንጮቜን እዚተመለኚተ ነው፡፡ ለአሳማ ገበሬዎቜ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቮክኖሎጅ ኚመሥራት በተጚማሪ ሁዋዌ ዹኹሰል ማዕድን ኢንዱስትሪ ጋርም ይሠራል፡፡ ሁዋዌ ዚደንበኞቜን መሹጃ ለቻይና መንግስት ሊያጋራው ይቜላል ሲሉ ዚቀድሞው ዚአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ክስ ቢያቀርቡትም ድርጅቱ በተደጋጋሚ አስተባብሏል፡፡ በዓለም ትልቁ ዚ቎ሌኮም መሣሪያዎቜ አምራቹ በዚህ ምክንያት ዹ 5ጂ ሞዎሎቜን አካላት ለማስመጣት ዚአሜሪካ መንግሥት ፈቃድ ስለላልሰጠው ዹ 4ጂ ሞዎሎቜን በመሥራት ተገድቧል፡፡ በብሔራዊ ደህንነት ላይ ስጋት ፈጥሮብናል ያሉ እንደ እንግሊዝ ያሉ ሌሎቜ ሃገራትም ሁዋዌ ዚሚያደርገውን ዹ 5ጂ ዝርጋታ አስቁመዋል፡፡ በዚህ ዓመት ዚስማርት ስልኮቜን ምርቱን እስኚ 60% ድሚስ እንደሚቀንሰው ሪፖርቶቜ ጠቁመዋል፡፡ ይህን ግን ማሚጋገጥ አልተቻለም። "ይህ ዚሚያሳዚው ዹሁዋዌ ምርቶቜ ጥራትና ልምዳቜን ምንም አይነት ቜግር እንደሌለበት ነው፡፡ ሁዋዌ በጂኊፖለቲካዊ ውዝግብ መካኚል ዚተያዘ በመሆኑ ለሁዋዌ ዚመጫወቻ ሜዳው አይደለም" ሲሉ ዚኩባንያው ቃል አቀባይ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ስለዚህ ሁዋዌ ፊቱን ወደ ሌሎቜ ዚገቢ ምንጮቜን ያዞሚ ይመስላል። እንደክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ስማርት ተሜኚርካሪዎቜ እና ተለባሜ መሣሪያዎቜ እንዲሁም ስማርት መኪና ዚማምሚትም ዕቅዶቜ አሉት። በጥቂት ተጚማሪ ባህላዊ ኢንዱስትሪዎቜ ላይ ዓይኑን ጥሏል፡፡ ቻይና በዓለም ትልቁ ዚአሳማ እርሻ ኢንዱስትሪ ባለቀት ስትሆን፣ ዚአለማቜን አሳማዎቜ ግማሜ ያህሉ መኖሪያ ናት፡፡ በሜታዎቜን ለመለዚት እና አሳማዎቜን እንቅስቃሎ ለመኚታተል በሚያስቜለው አር቎ፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት ዚአሳማ እርሻዎቜን ለማዘመን ቮክኖሎጂው እዚሚዳ ነው፡፡ ዚፊት መለያ ቮክኖሎጂ እያንዳንዱን አሳማዎቜ መለዚት ሲያስቜል ሌሎቜ ቎ክኖሎጂዎቜ ደግሞ ክብደታ቞ውን፣ አመጋገባ቞ውን እና ዚአካል ብቃት እንቅስቃሎዎቻ቞ውን ይቆጣጠራሉ፡፡ ሁዋዌ ዚፊት ለይቶ ዹማወቅ ቮክኖሎጂ በማዘጋጀት ላይ ሲሆን ባለፈው ወር ግን ትቜት ገጥሞታል። ምክንያቱ ደግሞ ኚእግሚኞቜ ምስል መካኚል ዚኡሂጉር ተወላጅ ዹሆኑ ዚሚመስሉትን ሰዎቜን ለይቶ በሚያሳውቀው ስርዓቱ ነው። እንደ ጄዲዳትኮም፣ አሊባባን ጚምሮ ሌሎቜ ዚቻይና ግዙፍ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያዎቜ ኚአሳማ ኚሚያሚቡ አርሶ አደሮቜ ጋር አዳዲስ ቎ክኖሎጂዎቜን ለማስተዋወቅ እዚሠሩ ነው፡፡ ዹሁዋዌ ቃል አቀባይ አክለውም "በ 5ጂ ዘመን ለኢንዱስትሪዎቜ ዹበለጠ እሎት ለመፍጠር አንዳንድ ባህላዊ ኢንዱስትሪዎቜን በኢንፎርሜሜን እና ኮሙኒኬሜን ቮክኖሎጂ (አይሲቲ) እንደገና ለማነቃቃት ዚምንሞክርበት ሌላ ምሳሌ ነው" ብለዋል፡፡ ዹሁዋዌ መስራቜ እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሬን ዀንግፈይ በዚህ ወር መጀመሪያ በሰሜን ቻይና ሻንሺ ግዛት ዚማዕድን ፈጠራ ቀተ-ሙኚራ በይፋ አስጀምሚዋል። ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለድንጋይ ኹሰል ማዕድን አውጪዎቜ "አነስተኛ ሠራተኞቜን፣ ኹፍተኛ ደህንነትን እና ኹፍተኛ ብቃትን ዚሚያመጣ እና ማዕድን አውጪዎቹ በሥራ ቊታ቞ው ሱፍ እና ኚሚቫት እንዲለብሱ" ዚሚያስቜላ቞ውን ቮክኖሎጂን ለማዳበር ይፈልጋሉ፡፡ በዝግጅቱ ላይ በክብ ጠሹጮዛ ዙሪያ በተደሹገ ስብሰባ ላይ ሬን ኩባንያው ኹሰል ማዕድን እና ኚብሚት እንደ ቎ሌቪዥኖቜ፣ ኮምፒውተሮቜ እና ታብሌቶቜ ያሉ ምርቶቜ ላይ ትኩሚት እያደሚገ ይገኛል፡፡ "በስልክ ሜያጮቜ ላይ ሳንመሠሚት እንኳን በመቀጠል እንቜላለን" ያሉት ሬን ዚአሜሪካ ኩባንያዎቜ ያለፍቃድ ኹሁዋዌ ጋር እንዳይሠሩ ዚሚያግደውን ዚጥቁር መዝገብ ያነሳል ዹሚል እምነት እንደሌላ቞ው ጹምሹው ጠቅሰዋል፡፡
https://www.bbc.com/amharic/news-56121975
amh
business
ዩናይትድ አዹር መንገድ ቩይንግ 777 አውሮፕላኖቜን ኚበሚራ አገደ
ዚአሜሪካው ዩናይትድ አዹር መንገድ 24 ቩይንግ 777 አውሮፕላኖቜን ኚበሚራ አገደ። አዹር መንገዱ አውሮፕላኖቹን ኚበሚራ ያገደው ባሳለፍነው ቅዳሜ ኚአውሮፕላኖቹ አንዱ ሞተሩ ላይ አደጋ ካጋጠመው በኋላ ነው። አውሮፕላኑ 231 መንገደኞቜንና አስር ዚበሚራ አስተናጋጆቜን አሳፍሮ ዹነበሹ ሲሆን በዮንቹር አውሮፕላን ማሚፊያ ለማሹፍ ተገዷል። እስካሁን በአደጋው ዹደሹሰ ጉዳት ዹለም ተብሏል። ዚአውሮፕላኑ ስብርባሪዎቜም በአቅራቢያው ባሉ ዚመኖሪያ ቊታዎቜ ወዳድቀው ተገኝተዋል። ይህንንም ተኚትሎ ጃፓን ተመሳሳይ ፕራት እና ዊትኒ 4000 ሞተር ዹተገጠመላቾውን ቩይንግ 777 አውሮፕላኖቜን ዹሚጠቀሙ ሁሉም አዹር መንገዶቜ አዹር ክልሏ እንዳይገቡ ጠይቃለቜ። ወደ ሃዋይ ሆኖሉሉ ኹተማ ለመብሚር ዚተነሳው ዩናይትድ 328 አውሮፕላን በቀኝ በኩል ባለው ሞተሩ ላይ አደጋ እንደገጠመው ዚፌደራል አቪዚሜን አስተዳደር ገልጿል። አደጋውን ተኚትሎም አስተዳደሩ ዚፕራት እና ዊትኒ 4000 ሞተር ዹተገጠመላቾው ቩይንግ 777 አውሮፕኣኖቜ ላይ ተጚማሪ ምርመራ እንዲደሚግ አዟል። "አደጋው ካጋጠመ በኋላ ሁሉንም ዚደህንነት መሚጃዎቜ ተመልክተናል" ሲሉ ዚፌደራል አቪዚሜን አስተዳዳሪ ስ቎ቭ ዲክሰን በመግለጫ቞ው ተናግሚዋል። በመጀመሪያ ደሹጃ በተገኘው መሹጃ መሠሚትምፀ ምርመራው በቩይንግ 777 አውሮፕላኖቜ ላይ ብቻ ለሚገጠመው ለዚህ ዹሞተር ሞድል ዹተለዹ ዹሆነው ወደ ሞተሩ ንፋስ ማስገቢያ [ፋን] ላይ ተጚማሪ ምርመራ እንዲደሚግ ድምዳሜ ላይ ደርሰናል ብለዋል። ዚፌደራል አቪዚሜን አስተዳደርም ኹሞተር አምራቹ ድርጅት እና ኹቩይንግ ተወካዮቜ ጋር እዚተነጋገሚ ነው። ዚአገሪቷ ዚመጓጓዣ ደህንነት ቊርድ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ምርመራ እንደሚያመላክተው አውሮፕላኑ አደጋ ያጋጠመው በቀኝ ሞተሩ ላይ ሲሆንፀ በሌሎቜ ሁለት ንፋስ ማስገቢያ [ፋን] ተሰነጣጥቀዋል። ሌሎቹም እንዲሁ ጉዳት ደርሶባ቞ዋል። ይሁን እንጂ ዚአውሮፕላኑ ዋነኛ አካል ላይ ዹደሹሰው ጉዳት ቀላል መሆኑን ቊርዱ ገልጿል። ይህ አደጋ ባጋጠመው አውሮፕላን ላይ ተሳፍራው ዚነበሩት መንገደኞቜ ለበሚራ እንደተነሱ ወዲያውኑ ኹፍተኛ ፍንዳታ እንደሰሙ ተናግሚዋል። ኚመንገደኞቹ አንዱ ዚሆኑት ዎቪድ ዎሉሲያ "አውሮፕላኑ በኃይል ሲነቃነቅ ነበር። ኚዚያም ኹፍ ብሎ መብሚር ስላልቻለ ወደ ታቜ መውሚድ ጀመሹ" ብለዋል። አክለውም እርሳ቞ውና ባለቀታ቞ው ምንአልባት አደጋ ካጋጠመን በሚል ዚኪስ ቊርሳ቞ውን ኪሳ቞ው ውስጥ እንደኚተቱት ተናግሚዋል። ዚብሩምፊልድ ኹተማ ፖሊስ ዚአውሮፕላኑ ዚሞተሩ ሜፋን ስባሪ በአንድ መኖሪያ ቀት አትክልት ቊታ ላይ መውደቁን ዚሚያሳይ ምስል አጋርቷል። ሌሎቹ ስብርባሪዎቜም በኹተማዋ አንድ ዚእግር ኳስ ሜዳ ላይ ወድቀው ታይተዋል። ኚአውሮፕላኑ ላይ በወደቀው ስብርባሪ ግን ዚተጎዳ አለመኖሩ ተገልጿል። በጃፓን ዚፕራት እና ዊትኒ 4000 ሞደል ሞተር ዹተገጠመላቾው ሁሉም 777 አውሮፕላኖቜ ተጚማሪ ማስታወቂያ እስኪነገር ድሚስ አዹር ክልሏ መግባት ያቆማሉ። ይህም ለበሚራ መነሳትን፣ ማሹፍን እና በአገሪቷ ዹአዹር ክልል ላይ መብሚርን ያካትታል። ባለፈው ታህሳስ ወር ዹጃፓን አዹር መንገድ አውሮፕላን በግራ በኩል ያለው ሞተሩ መስራት ባለመቻሉ ወደ ናሃ አዚርማሚፊያ እንዲመለስ ተገዶ ነበር። አውሮፕላኑ ባለፈው ቅዳሜ አደጋ ካጋጠመው ዚዩኒይትድ አዹር መንገድ አውሮፕላን ጋር በተመሳሳይ ዹ26 ዓመት እድሜ ያለው ነው። በ2018ፀ አንድ ዚዩናይትድ አዹር መንገድ አውሮፕላን በሆኖሉሉ ኹማሹፉ በፊት ዹቀኝ ሞተሩ ተሰብሮ ነበር። ይህንንም ተኚትሎ በተካሄደው ምርመራ ዚአገሪቷ ዚመጓጓዣ ደህንነት ቊርድ አደጋው ዚአውሮፕላኑ ሙሉው ዚንፋስ ማስገቢያ [ፋን] በመሰንጠቁ ምክንያት ያጋጠመ እንደሆነ አስታውቆ ነበር።
https://www.bbc.com/amharic/56151142
amh
business
ስንዎ፣ ዘይት፣ ስኳር እና ሩዝ ኚቀሚጥና ታክስ ነጻ እንዲሆኑ ተወሰነ
ዹተወሰኑ መሠሚታዊ ዚምግብ ሞቀጊቜ ላልተወሰነ ጊዜ ኚቀሚጥና ታክስ ሙሉ ሙሉ ለሙሉ ነጻ መደሹጋቾውን ዚገንዘብ ሚኒስ቎ር አስታወቀ። ሚኒስትር ዎኀታው ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ እንዳሳወቁት ዚመሰሚታዊ ዚምግብ ሞቀጊቜን ዚጉምሩክ ቀሚጥና ታክስ ማሻሻያው ኹነሐሮ 28/2013 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ተግባራዊ ይሆናል። በዚህም መሠሚት ዚምግብ ዘይት፣ ስኳርና ሩዝ ኹውጭ ሲገቡም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጞምባ቞ው ኚቀሚጥና ታክስ ሙሉ በሙሉ ነፃ ሲሆኑ ስንዎ ኹውጭ ሲገባ ኚቀሚጥና ታክስ ነፃ እንዲሆን ተወስኗል። ፓስታ እና ማኮሮኒ ኹውጭ ሲገቡም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጞም ኚተጚማሪ እሎት ታክስ ነፃ እንዲሆኑ፣ እንዲሁም ዚዶሮ እንቁላል ኚተጚማሪ እሎት ታክስ ነጻ እንዲሆን መወሰኑን ኚሚኒስ቎ር መስሪያ ቀቱ ዹተገኘው መሹጃ ያስሚዳል። ሚኒስትር ዲኀታው ጹምሹውም መንግሥት ዹዋጋ ግሜበትን ለመቆጣጠርና ዚኅብሚተሰቡን ዚመግዛት አቅም ለማሳደግ ዚገንዘብና ዚፊስካል ፖሊሲ ማሻሻያዎቜን እንዲሁም አስተዳደራዊ እርምጃዎቜን ሲወስድ መቆዚቱን ተናግሚዋል። ይህ እርምጃ ተግባራዊ ሲደሚግ መንግሥት በብዙ ቢሊዮን ዚሚገመት ገቢ እንደሚያጣ አመልክተው ዹዋጋ ንሚት ለመቆጣጠር በታክስ ብቻ ዹሚፈለገውን ውጀት ስለማያመጣ አቅርቊትን ለመጹመር መንግሥት በኹፍተኛ ወጪ ሞቀጊቜን በመግዛት በዝቅተኛ ዋጋ ለኅብሚተሰቡ እያቀሚበ መሆኑን ተናግሚዋል። ኹዚህ በተጚማሪም መሰሚታዊ ዚምግብ ሞቀጊቜ በሌሎቜ አካላት ዚሚገባውን አቅርቊት በኹፍተኛ ደሹጃ ይጹምር ዘንድ ለስድስት ወር ተፈቅዶ ዹነበሹው ያለውጭ ምንዛሬ ሞቀጊቜን ዚማስገባት አስራር ለሌላ ተጚማሪ ስድስት ወራት እንዲራዘም መደሹጉንም ጹምሹው ገልጞዋል። እነዚህ ማሻሻያዎቜ ዹዋጋ ንሚት በህብሚተሰቡ ላይ ዚሚያሳድሚውን ጫና ለመቀነስ፣ በምግብ ዋጋ ላይ ዹሚኹሰተውን ጭማሬ መንግሥት ለመቆጣጠር እንዲሚዳውና ኹውጭ እቃ ለሚያስገቡ ነጋዎዎቜንም ለማበሚታት ያለመ እንደሆነም ተገልጿል። በአሁኑ ጊዜ በአገሪቱ ያለው ዚምግብ ዋጋ ግሜበት ባለፈው ወር 32 በመቶ ዹደሹሰ ሲሆን ይህም በአሥር ዓመታት ውስጥ ኹፍተኛው ነው ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-58437093
amh
business
ካፒታሊዝም፡ ዹአፕል ኩባንያ ሀብት ዋጋ ግምት ሁለት ትሪሊዮን ዶላር ደሹሰ
ዹቮክኖሎጂው ኩባንያ አፕል በስቶክ ገበያ ዚሀብት ምጣኔ ግምት ኚቢሊዮን ዶላሮቜ አልፎ በትሪሊዮን ዶላር ዹተገመተ ሁለተኛው ዹዓለም ኩባንያ ሆኗል፡፡ በአሜሪካ በ2 ትሪሊዮን ዶላር ዚሚገመት ሀብት ያለው ኩባንያ ዚለም፡፡ አፕል ዚመጀመርያው ሆኗል፡፡ ኹዚህ ቀደምም አንድ ትሪሊዮን ዶላር ለመድሚስ ዚመጀመርያው ሆኗልፀ በ2018 ዓ.ም መጀመርያ፡፡ አሁን ዹአፕል ዚአንድ ሌር ዋጋ ግምቱ $467.77 ዶላር ደርሷል፡፡ ትናንትና ሚቡዕ በነበሹው ዚስቶክ ገበያ ዚኩባንያው ጥቅል ሀብት 2ሚሊዮን ዶላር መድሚሱ ተበስሯል፡፡ በዓለም ላይ 2 ትሪሊዮን ዶላር ጣሪያ ለመድሚስ ብ቞ኛና ዚመጀመርያ ዹነበሹው ኩባንያ ዚሳኡዲ አሚቢያው ዚነዳጅ ድርጅት አራምኮ ነው፡፡ ሆኖም አራምኮ በስቶክ ገበያ ዹነበሹው ዋጋ ባለፈው ታኅሣሥ ወር ዚነዳጅ ዋጋ ማሜቆልቆልን ተኚትሎ ዚሌር ምጣኔውም በዚያው ወርዷል፡፡ ኚዚያ ወዲያ ዚስቶክ ዋጋ ግምቱ 1.8 ትሪሊዮን ዶላር ላይ ተቀምጧል፡፡ በሐምሌ ወር አፕል አራምኮን በመብለጥ ዹዓለም እጅግ ሀብታሙ ድርጅት ሆኗል፡፡.በስቶክ ገበያም በጣም ተፈላጊ ዚግብይይት ኩባንያ በመሆን አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል፡፡ ዚማያባራ ገበያ ዹአይፎን ስልኮቜን ፈብራኪው አፕል በዚህ ዓመት ዚሌር ድርሻው በ 50% ነው ዚተመነደገው፡፡ ይህ ዹሆነው ታዲያ ዓለም በኮሮና ተህዋሲ በሚታመስበት ወቅት ነው፡፡ ዚኮቪድ መኚሰት አፕል በኢሲያ በተለይም በቻይና ያሉ መደብሮቹን እንዲዘጋ አስገድዶታል፡፡ ቻይና በድርጅቱ ላይ ፖለቲካዊ ጫና ስታደርስ ነው ዚቆዚቜው፡፡ እንዲያም ሆኖ ነው ዚድርጅቱ ዚስቶክ ድርሻ ገበያው እዚደመቀለት ዚሄደው፡፡ ብዙዎቹ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያዎቜ ኚሌሎቜ ዘርፎቜ በተሻለ አስ቞ጋሪውን ጊዜ ለማለፍ ዚሚቜሉበት አጋጣሚ ዹተፈጠሹ ይመስላል፡፡ ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ዚስቶክ ድርሻ቞ው እዚተመነደጉ ያሉት ኹቮክኖሎጂ ጋር ዚተሳሰሩት ኩባንያዎቜ ና቞ው፡፡ አፕል በዚህ ዚዓመቱ ሊስተኛው ምዕራፍ ላይ ማለትም ሐምሌ መጚሚሻ ላይ ትርፉ ወደ 60 ቢሊዮን ዶላር መጠጋቱን አብስሯል፡፡ በአሜሪካ ኹአፕል ቀጥሎ ኹፍተኛ ዚስቶክ ግምት ዋጋ ያለው ኩባንያ አማዞን ሲሆን ምጣኔውም 1.7 ትሪሊዮን ዶላር ነው፡፡.
https://www.bbc.com/amharic/news-53846118
amh
business
ኢትዮጵያ ለጎሚቀት አገራት ኚምታደርገው ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭ ምን ያህል ተጠቃሚ ናት?
በያዝነው ወር ግንቊት 2003 ዓ.ም ነበር ኢትዮጵያ ለጎሚቀት አገር ጂቡቲ ዚኀሌክትሪክ ኃይል አቅርቊት ዚጀመሚቜው። በአፍሪካ ዚልማት ባንክ በ95 ሚሊዮን ዶላር ዚብድር ድጋፍ በተገነባው ዚኀሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዚመጀመሪያው ዓመታዊ 22 ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ኃይል ለጅቡቲ በመሞጥም ዹኃይል ወጪ ንግድ ኚአስራ አንድ ዓመታት በፊት ተበሰሚ። ዹግልገል ጊቀ ሁለት ዚኀሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ባጋጠመው ዹቮክኒክ ብልሜት ምክንያት በመዘጋቱ ኚታቀደው አንድ አመት ዘግይቶ ነበር ዚተጀመሚው። በወቅቱ ዹነበሹው ዹኃይል ሜያጭም ለአገሪቱ በአማካኝ በዓመቱ 10 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንደሚያስገኝላት ዚአገራትን ምጣኔ ኃብት ትንበያዎቜን እንዲሁም ጥልቅ ዳሰሳዎቜን ዚሚያዘጋጀው ኢኮኖሚክ ኢንተለጀንስ ዩኒት በወቅቱ ባወጣው ሪፖርት አስነብቧል። በሪፖርቱ መሰሚት ኚጂቡቲ ኹሚገኘው ገቢም ዹተወሰነውን በገጠር ያሉ ህዝቊቿ መብራት እንዲያገኙ፣ በተጚማሪም በአገር ውስጥ ያለውንም ዹኃይል ተደራሜነት ለማሳደግ እቅድ ተይዞ ነበር። ኚአስር ዓመት በኋላ በ2013 ዓ.ም ኢትዮጵያ ኚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭ 90 ሚሊዮን ዶላር ማስገባት ቜላለቜ። ለጂቡቲ በ22 ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭ ዚጀመሚቜው ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን ዚአፍሪካ ዹኃይል ማዕኹል ለመሆን ዚአስር አመት ፍኖተ ካርታን አዘጋጅታለቜ። በዚህ ዚቀጣይ አስር ዓመታት ይተገበራል በተባለው ዚኢነርጂ ልማት መሰሚት አገሪቷ በ2022 ዚምታመነጚውን ዹኃይል መጠን ወደ 20 ሺህ ማሳደግ እንዲሁም ለጎሚቀት አገራት ዚምትሞጠውን ዹኃይል መጠንም ወደ 7 ሺህ 184 ጊዋስ (GWH) ለማድሚስ ታቅዷል። በአሁኑ ወቅት ለጎሚቀት አገራቱ ሱዳንና ጂቡቲ አመታዊ ዹኃይል ሜያጭ ዚምታቀርብ ሲሆን ለኬንያም ዹኃይል ሜያጭ ለመጀመር ዚኀሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታን ግንባታን ካጠናቀቀቜ አንድ አመት ሆኗታልፀ ፍተሻውም ዹተጠናቀቀ ሲሆን በቅርቡ እንደሚጀመርም ይጠበቃል። ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭ ዚወጪ ንግድ ኹውሃ ሃይል፣ ነፋስ፣ እንፋሎት፣ ዹጾሃይ ብርሃንንን በመጠቀም ዚንጹህ ኃይል አምራቜ ለመሆን እቅድ ይዛ ያለቜው ኢትዮጵያ በዚህም ማሳካት ዚምትፈልገው ኚምስራቅ አፍሪካ ባሻገር ዚአፍሪካ ዹኃይል ምንጭ ማዕኹል መሆንን ነው። ኚጎሚቀት አገራት ጋር ዹኃይል ትስስር በመፍጠርም ለጂቡቲና ለሱዳን ዚኀሌክትሪክ ኃይል በማቅሚብ በአማካኝ በዚአመቱ 70 ሚሊዮን ዶላር ገቢን ለማግኘት እዚሰራቜ ትገኛለቜ። ለሁለቱ አገራት ዚምትልኚው ዹኃይል መጠን ባለው ስምምነት መሰሚት በ100 ሜጋ ዋት ዚሜያጭ ማዕቀፍ ሲሆን ዹተወሰነ ኹፍና ዝቅ ማለት እንዳለም ዚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሜን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን መሚጃዎቜን ዋቢ በማድሚግ ያስሚዳሉ። ኹ100 ሜጋ ዋት በላይም ይሁን በታቜ እንደቆጠሚው ሁኔታ አገራቱ ክፍያ቞ውን ይፈጜማሉ። በባለፉት ዘጠኝ ወራት ያለውን ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭ መሹጃ በምናይበት ወቅት ለሱዳን ዚኀሌክትሪክ ኩባንያ ወደ 746.9 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ዚመሞጥ እቅድ ተይዞ ዹነበሹ ሲሆን ኹዚህ ውስጥ ኚእቅዱ በ4 በመቶ ብልጫ ያለው 774.2 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ወጪ ንግድ ተካሂዷል። በተጚማሪ ወደ ጂቡቲ 385 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ታቅዶ ዹነበሹ ቢሆንም 427.1 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ሜያጭ በመደሹጉ ኚእቅዱም 11 በመቶ ብልጫ አሳይቷል። በዚህም ለሱዳን ኹተሾጠው ኃይል 38.7 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ለጂቡቲ ኹተሾጠው ደግሞ 27.8 ሚሊዮን ዶላር በአጠቃላይም በዘጠኝ ወራት ኹኃይል ሜያጭ 67 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተገኝቷል። ገቢው ኚእቅዱ አንፃር ሲታይ ዚሱዳን ኀሌክትሪክ ኩባንያ ዹተጠቀመው 4 በመቶ ጭማሪ፣ ዚጅቡቲ ደግሞ 15 በመቶ ገደማ ጭማሪ ማሳዚቱን አቶ ሞገስ ያስሚዳሉ። በዚዓመቱ ለጎሚቀት አገራት በጅምላ ዚኀሌክትሪክ ኃይል በማቅሚብ 70 ሚሊዮን ዶላር ቢታቀድም በአመታት ውስጥ ጭማሬ እያሳዚ መምጣቱንም ዚኮሚዩኒኬሜን ኃላፊው አቶ ሞገስ መሚጃዎቜን በማጣቀስ ያስሚዳሉ። እስካሁን ድሚስ ባለው ኹፍተኛ ዹተመዘገበው በባለፈው ዓመት ሲሆን በ2013 ዓ.ም ሲሆን ኹነበሹው አጠቃላይ ዚኀሌክትሪክ ሜያጭ ወደ 90 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተገኝቷል። በአመታት ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ ዚምትሞጠው ዚኀሌክትሪክ ኃይል አቅም እንዲሁም ገቢውም ጚምሯል። ሆኖም ኚሁለት አመታት በፊት ዚአገሪቱ ዹኃይል ማመንጫ ግድቊቜ በቂ ውሃ ባለመያዛ቞ው ምክንያት በተፈጠሹው ዕጥሚት ለወራት ያህል ለሱዳን አቅርቊት ኚማቋሚጥ በተጚማሪ ኀሌክትሪክ በፈሹቃ መኹፋፈል ተጀምሮ ነበር። በዝናብ እጥሚት ምክንያት በተፈጠሹው ቜግር በደቡብ እና በምስራቅ ዚአገሪቱ ክፍሎቜ ዚሚገኙት ሊስት ግድቊቜ ቆቃ፣ መልካ ዋኹናና ጊቀ ሶስት በቂ ውሃ እንዳይዙ አድርጓ቞ዋል። በወቅቱ ሱዳን ኹፍተኛ ዹኃይል አቅርቊት ፍላጎት እንደነበራት ዚሚያወሱት አቶ ሞገስ፣ ዹአገር ውስጥ ፍላጎት ባለመሟላቱና ወደ ፈሹቃ በመገባቱም ወጪ ንግድ ለአምስት ወራት ያህል ተቋርጩ ዹነበሹ ሲሆን በዚህም ዓመታዊ ገቢውን ኹ60 ሚሊዮን ዶላር በታቜ አድርጎታል። በተያያዘ ዜና በዘንድሮው ዓመት ሱዳን ያልኚፈለቜው ውዝፍ ዚኀሌክትሪክ ፍጆታ ያለ ሲሆን ዚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል ለሱዳን ኀሌክትሪክ ኃይል ይኹፈለኝ ዹሚል ደብዳቀ ጜፏል። ተቋሙም በጻፈው ምላሜ አገሪቱ ያለቜበትን ፈታኝ ሁኔታ ጠቅሶ ታገሱኝ፣ አገልግሎቱም አይቋሚጥ ዹሚል ጥያቄ መቅሚቡንም አቶ ሞገስ ያስሚዳሉ። ኹዚህ ቀደም ለሁለት ወይም ሶስት ወራት ሳይኚፈል ዚሚዘልበት ጊዜ ቢኖርም በአሁኑ ወቅት ግን ኹተለመደው ውጭ ስድስት ወራት በላይ መሆኑን ዚሚናገሩት አቶ ሞገስ መጠኑን ግን መጥቀስ አልፈለጉም። ዚኬንያ ኃይል ሜያጭ ለምን ዘገዹ? ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭን ኚጂቡቲ በመቀጠል ለሱዳን ኚዓመታት በፊት ማቅሚብ ዚጀመሚቜው ኢትዮጵያ ለሌላኛዋ ጎሚቀት አገር ኬንያም ኃይል ለማቅሚብ ዚወጠነቜው ኚአመታት በፊት ነበር። ኢትዮጵያና ኬንያ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ለመገበያዚት ዚመግባቢያ ስምምነት ዚተፈራሚሙት ኚአስር ዓመት በፊት ነበር። በወቅቱም ዚነበሩ ዚአገሪቱ ሚዲያዎቜን ስናገላብጥ እንዳገኘነው በወቅቱ ዚኢትዮጵያ ዹውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር አቶ አለማዹሁ ተገኑና በኬንያው ዚኢነርጂ ሚኒስትር ዹተደሹሰው ዚመግባቢያ ስምምነት ኚአራት አመት በኋላ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭ እንዲጀመር ነበር። ለምስራቅ አፍሪካ ዹኃይል ትስስር ኹፍተኛ ስፍራ ያለውና 1.3 ቢሊዮን ዶላር ዹፈጀው ዹዚህ ፕሮጀክት ዚኀሌክትሪክ መስመር ዝርጋታን ኢትዮጵያ በባለፈው ዓመት ገንብታ ጚርሳለቜ። አገራቱን ዚሚያገናኘው ዚኀሌክትሪክ መስመር 500 ኪሎ ቮልትና ኚኢትዮጵያ በኩል 412 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ በአጠቃላይ ኹ1 ሺህ ሜትር በላይ ርዝማኔ ያለው እንደሆነ አቶ ሞገስ ይናገራሉ። ወጪውም ኹዓለም ባንክ ኹተገኘው ብድር 684 ሚሊዮን ዶላር፣ ለኢትዮጵያ 441 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ለኬንያ 27.4 ቢሊዮን ዶላር ዹሚሾፈን ነው። ዚአፍሪካ ልማት ባንክም ይህንኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ኹሚገኘው ዹግልገል ጊቀ ሶስት ግድብ ጋር ዚሚያገናኘውን ዹኃይል ማስተላለፊያ መስመር ድጋፍ ለኢትዮጵያ 232 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ለኬንያ 116 ሚሊዮን ዶላር አጜድቋል። ለኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታና ለሌሎቜ ስራዎቜ ኚለጋሜ ተቋማት በብድር ኹተገኘው በተጚማሪ አገራቱም ይህንን ትልቅ ፕሮጀክት ለመስራት ዚራሳ቞ውን ወጪ አድርገዋል። በባለፈው ዓመት በኢትዮጵያ በኩል ዚኀሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ግንባታና ዚፍተሻ እንዲሁም ዚሙኚራ ስራዎቜ ቢጠናቀቅም ኚኬንያ በኩል ቀሪ ዚዝርጋታና ዹፓወር ተኹላ ስራዎቜ እንዳሉ እዚተነገሚ መጀመር ኚነበሚበት ወቅት እዚተጓተተ ሹዘም ያሉ ወራት ተቆጥሚዋል። በያዝነው አመት መስኚሚም ላይ በኬንያ ኢነርጂ ሚኒስትር ዚተመራ ልዑካን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ዹነበሹ ሲሆን በቀሪ ጉዳዮቜ ላይ ስምምነቱን ለማጠናቀቅና ቀሪው ዚፕሮጀክቱ አካልም እንዲጠናቀቅ ስምምነት ላይ መደሚሱንም አቶ ሞገስ ያወሳሉ ። ኚወራት በኋላ እንዲሁ ጥር ወር መጚሚሻ ላይ ዹዘገዹውን ዹ1.3 ቢሊዮን ዶላር 400 ሜጋ ዋት ዹሃይል ሜያጭ ለማፋጠን ኢትዮጵያና ኬንያ አዲስ ስምምነት ላይ መድሚሳ቞ውን ሚዲያዎቜ ዘግበዋል። በኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስትር እዮብ ተካልኝ ዚተመራ ዚልዑካን ቡድን ናይሮቢ ጥር መጚሚሻ ላይ መጥቶ ኚኬንያ ኀነርጂ ሚኒስትር ሞኒካ ጁማ ጋር ተገናኝተው ነበር። አገራቱ ቀደም ሲል በተፈሹሙ ዹኃይል ስምምነቶቜ፣ ዚማጠናቀቂያ ስራዎቜ፣ ዚአሰራር መመሪያዎቜንም በተመለኹተ ተወያይተው መኚለሳ቞ውም ተዘግቧል። ዚኬንያ ሚዲያዎቜ እንደዘገቡት ለኬንያ ኚኢትዮጵያ 400 ሜጋ ዋት ዚምትገዛው ኃይል ርካሜ መሆኑን ነው። ኚኬንያ በኩል ኚመስመር ዝርጋታ ግንባታ መጓተት በተጚማሪ ስምምነት ዚተደሚሰበት ዹ400 ሜጋ ዋት ኃይልን በተመለኹተ እንዲሁም ኹተወሰነው ታሪፍ ጋር ተያይዞ ጥያቄ መነሳቱንም ሚዲያዎቜ ዘግበዋል። ሆኖም አገራቱ ያላ቞ውን ልዩነት በመፍታት ዚያዝነው አመት ኹመጠናቀቁ በፊት ኃይል ዚማስተላለፍ ስራው ይጀመራል ዹሚል እቅድ ተይዞም እዚተጠበቀ ይገኛል። ፕሮጀክቱ በምስራቅ አፍሪካ ያሉ አገራት መካኚል ድንበር ዘለል ዹሃይል ንግድ እንዲሁም ትስስርን ለማስተባበር በአውሮፓውያኑ 2005 ዹተቋቋመው ቀጠናዊ ተቋም ዹሆነው ኢስተርን አፍሪካ ፓወር ፑል አካል ነው። በአጠቃላይ ዹኃይል ልማት እና ተግባር ዚማስተባበር ስልጣን ዹተሰጠው ዹተቋሙ ዋና ፅህፈት በአዲስ አበባ ዹሚገኝ ሲሆን አስራ አንድ አባል አገራት አሉት። አገራቱም ግብፅ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ታንዛንያ፣ ኡጋንዳ እና ሊብያ። ኮንጎ (ዲአርሲ)፣ ሩዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ና቞ው። ፕሮጀክቱ እነዚህንም ሃገራት በኃይል ዚማስተሳሰርና ዚማዋሃድ አቅም እንዳለው ይነገራል። በሁለቱ አገራት ዹተዘሹጋው ዚኀሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመርም እስኚ 2000 ሜጋ ዋት ዹመሾኹም አቅም ያለው ነው። እንደ አቶ ሞገስ ይህ ዚኀሌክትሪክ መስመር ኢትዮጵያና ኬንያን ኚማገናኘት በተጚማሪ ዚመካኚለኛው ምስራቅ፣ ዚምስራቅ አፍሪካና ሌሎቜ ዚደቡባዊ አፍሪካ ሃገራትንም ተደራሜ ያደርጋል በሚል እሳቀ ዚማስተላለፍ አቅሙ ኹፍ ተብሎ ዚተሰራ ነው። ለሌሎቹም አገራት ኀክስፖርት ዚሚደሚግበት ዚኀሌክትሪክ መስመር በአብዛኛው ጀናማ ዹሆነ መስመር ያለው ሲሆን እንደ ዹአገር ውስጥ ማስተላለፊያ መስመሮቜ አሮጌ አለመሆኑንና ኀሌክትሪክ በመሾኹም በኩል ቜግር እንደማይጠቀስም አቶ ሞገስ ያስሚዳሉ። ለደቡብ ሱዳን ኃይል ለመሞጥ ዹተደሹሰው ስምምነት ኹሰሞኑ ደግሞ ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭ ዚመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። በደቡብ ሱዳን ዚኢነርጂና ግድብ ሚኒስትር ፒተር ማርሮሎ ዚተመራው ዚልዑካን ቡድን፣ ኢትዮጵያ መጥቶ ዚብሔራዊ ዹኃይል መቆጣጠሪያ ማዕኹልን እና ዚኮተቀ ዹኃይል ማኚፋፋያ ጣቢያን ኹጎበኙ በኋላም ኚሶስት ዓመት በኋላ ዹኃይል ሜያጭ እንዲጀመር ዚሚያስቜል ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ስምምነቱ ኚሶስት ዓመት በኋላ ሜያጭ እንደሚጀመር ዹጊዜ ገደብ ዚተቀመመጠለት ሲሆን ይህም ዚኀሌክትሪክ ኃይል አቅርቊት ኚመጀመሩ በፊት መሰራት ያለባ቞ው ተግባራት ስላሉ እንደሆነ አቶ ሞገስ ያስሚዳሉ። በዚህም መስሚት በመጀመሪያው ዓመት ሁለቱም አገራት ዚኀሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር መዘርጋት ያለባ቞ውን አካባቢዎቜ በተመለኹተና ኚአቅርቊቱ ጋር ዚተያያዘ ዚአዋጭነት ጥናቶቜን ዚሚያካሂድ ቎ክኒካል ቡድን ያቋቁማሉ። ይሄንን ዚአዋጭነት ጥናትም ተኚትሎም ባሉት ሁለት ዓመታት ደግሞ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ዚሚኚናወነው። ግንባታው ሁለት ዓመት ሊፈጅ እንደሚቜልም ታሳቢ ተደርጓል። ዚሁለቱ አገራት ዚመግባቢያ ስምምነት በሁለት ምዕራፎቜ ዹተኹፈለ ነው። ዚመጀመሪያው 357 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ዹኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ኚጋምቀላ 2 ዹኃይል ማኚፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ ወደ ደቡብ ሱዳኗ ማላካል ግዛት ዹሚዘልቀው ነው። ሁለተኛውና ሹዘም ባለ ጊዜ ይኹናወናል ተብሎ ዚታቀደው ደግሞ ኹ700 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና ባለ 400 ወይም 500 ኪሎ ቮልት ዚኀሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኹቮፒ ወደ ቩር ጁባ ዹሚዘሹጋው ነው። ግንባታው ኹተጠናቀቀ በኋላ በመጀመሪያው ዓመት ላይ 100 ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ሜያጭ እንዲኖር ስምምነት ላይ ተደርሷል። ሆኖም በ100 ሜጋ ዋት ብቻ እንደማይወሰን ዚሚናገሩት አቶ ሞገስ ዚደቡብ ሱዳንን ዚኀሌክትሪክ ተጠቃሚዎቜን እንዲሁም ዚአገሪቱን መሰሹተ ልማት ኚግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ በዹጊዜው ሊያድግ ዚሚቜል ዹኃይል ፍላጎት አቅርቊት ይደሚጋል። በዚህም መሰሚት ኹፍተኛውና ኹ400 ሜጋ ዋት ዚማይበልጥ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ለመሞጥ ነው ዚመግባቢያ ስምምነቱ ዚተደሚሰው። ዚኀሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ ዚሚታዩ ቜግሮቜ ሹዘም ባለ ጊዜ ዕቅድ ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛንያ፣ ብሩንዲ ዚመሞጥ እቅድ አላት። ነገር ግን ድርድሮቜ ተካሂደው፣ ዹመሰሹተ ልማቶቜ ዝርጋታ እንዲሁም ግንባታው እስኪኚናወን ዓመታት እንደሚጠይቅ አቶ ሞገስ ያስሚዳሉ። "በፍላጎት ደሹጃ እውነት ነው በተለይ ጎሚቀቶቻቜን ፍላጎት እንዳላ቞ው አሳውቀዋል።" ዚሚሉት አቶ ሞገስ ለምሳሌ ሶማሌላንድ ዹኃይል አቅርቊት ፍላጎት እንዳላት ገልጻለቜ። በተጚማሪም ዹኃይል አቅርቊት በዚዓመቱ ዚሚሞጥላ቞ው እንደ ሱዳን ያሉ አገራትም ጭማሬ እዚጠዚቁ ይገኛሉ። ሱዳን አሁን ኹሚደሹገው ዹኃይል አቅርቊት (ኹፍተኛው ወደ ሁለት መቶ ሜጋ ዋት) በተጚማሪ በ1 ሺህ 200 ሜጋ ዋት ጭማሬ ፍላጎት እንዳላት አሳውቃለቜ። "ይህንን 1 ሺህ 200 ሜጋ ዋት ወደ ሱዳን ለመላክ ዚሚያስቜል አሁን ባለው ሁኔታ እንደ አገር አቅም ዹለንም ። ያንን ማስተናገድ አንቜልም። አሁን ባለው መሰሹተ ልማት ደግሞ ሊሆን ዚሚቜል አይደለም። ስለዚህ እሱ ለወደፊት ምላሜ ማግኘት ዚሚቜል ጉዳይ ነው" ይላሉ። አገሪቷ አሁን ባላት ሃይል ዚማመንጚት አቅም ለሱዳን ዹሚላኹው መጠን እስኚ 300 ሜጋ ዋት ድሚስ ቢሆን ብዙ ቜግር ባይኖሚውም ዚሱዳን ፍላጎት ግን በጣም ኹፍተኛና ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ማሟላት ዚማትቜለው ነው ይላሉ። ኚኀሌክትሪክ ወጪ ንግድ ጋር ተያይዞ በዋነኝነት ዹሚጠቀሰው ኀክስፖርት ወደሚደሚግባ቞ው ሃገራት ዚሚጠይቁትን ፍላጎት ማሟላት አለመቻሉ እንደሆነ አቶ ሞገስ ይጠቅሳሉ። በዋነኝነት ተቋሙ ትኩሚት ዹሚሰጠው ዹአገር ውስጥ ፍላጎት ስለሆነ፣ ስምምነቶቹ ላይ ዹአገር ውስጥ ፍላጎት ማሟላት ካልተቻለ ሙሉ በሙሉ ዹማቆም እርምጃ እንደሚወሰድ ዚሚጠቅስ አለ። ለምሳሌም ዚሚጠቅሱት በ2011 ዹተኹሰተውን ዹኃይል እጥሚት ነውፀ በዚህም ወቅት ኢትዮጵያ ለሱዳን ዚምታቀርበውን ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ኚማቋሚጥ በተጚማሪ ለጂቡቲ ዹቀሹበው ኃይልም በግማሜ ገደማ ቀንሶ ነበር። ይህ አሰራር ለኃይል ጠያቂዎቹ አገራት ብዙም እንደማይስማማ቞ው አቶ ሞገስ ያስሚዳሉ። ዹአገር ውስጥ ዹኃይል መቆራሚጥ ባለበት ወጪ ንግድ እንዎት ይጣጣማል? ዹውጭ ምንዛሬ እጥሚት፣ዚተዛባ ዚንግድ ስርዓት በተለይም ዚወጪና ዚገቢ ንግድ አለመመጣጠን ለአገሪቷ ለአመታት ኹፍተኛ ማነቆ ዚሆነባት ጉዳይ ነው። በገቢና በወጪ ንግድ ሚዛን መጓደልም ጋር ተያይዞ ባለፈው ዓመት አገሪቱ ኚወጪ ንግድ ሊስት ቢሊዮን ዶላር ስታገኝ በገቢ ንግድ ደግሞ 15 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እንዳደሚገቜ መሚጃዎቜ ያሳያሉ። ይህንንም ኹፍተኛ ልዩነት ለማመጣጠን አገሪቱ ዚወጪ ንግዷን ማሻሻል ዚምጣኔ ኃብት ባለሙያዎቜ እንደ መፍትሄ ዚሚሰነዝሩት ነው። ዚኀሌክትሪክ ኃይል ሜያጭ አገሪቱ ገንዘብ ኚምታገኝበት ወጪ ንግድ አንዱ ቢሆንም አገሪቱ ካላት ዝቅተኛ ዚኀሌክትሪክ ሜፋን እንዲሁም ህዝቧ በኃይል መቆራሚጥ በሚሰቃይበት ወቅት ኢትዮጵያ ለውጭ አገራት ኃይል መሾጧ ጥያቄን ማጫሩ አልቀሚም። ኢትዮጵያ ኚህዳሎ ግድብ ግንባታ ጋር ተያይዞ ኚግብፅ በጎርጎሳውያኑ 1959 ዹተፈሹመውን ዹቅኝ ግዛት ስምምነት ታሪካዊ ተጠቃሚነት በምታነሳበት ወቅት ዚምትሰጠው ምላሜ ይህ ታሪካዊ ስህተት መስተካኚል እንዳለበት በመጥቀስ ሚሊዮኖቜ ኢትዮጵያውያን ያለ መብራት እና በድህነት በሚማቅቁበት ሁኔታ ግድቡ ያለውን ጠቀሜታ ስታሳውቅ ቆይታለቜ። አገሪቷ ያላት ዚኀሌክትሪክ ሜፋን ዝቅተኛ እንዲሁም በርካታ መቆራሚጥ ዚሚታይበት ነው። ዚአገሪቱን ዚኀሌክትሪክ ሜፋን በምናይበት ወቅት በ2012 ዓ.ም 5.8 ሚሊዮን ደንበኞቜ እንዲሁም ዚኀሌክትሪክ ተጠቃሚዎቜ 44 በመቶ ዹደሹሰ ሲሆን ኹዚህም ውስጥ 33 በመቶ ኚብሔራዊ ግሪድ ዚሚያገኙ እንዲሁም ኚግሪድ ውጭ ተጠቃሚ ዹሆኑ 11 በመቶ መሆኑን ኚአስር ዓመቱ ዚልማት እቅድ ያገኘነው መሹጃ ያስሚዳል። ዹአገር ውስጥ ሜፋን እንዲህ ዝቅተኛ በሆነበት መጠንና በአገሪቱ ዹኃይል አቅርቊት እዚተቆራሚጠ ባለበት ሁኔታ ለጎሚቀት ሃገራት ወጪ ንግድ ማድሚግስ እንዎት ይጣጣማል? ቅድሚያ ዹሚሰጠው ዹአገር ውስጥ ፍላጎት ማሟላት ላይ እንደሆነ አፅንኊት በመስጠት ዚሚናገሩት አቶ ሞገስ በአገር ውስጥ እያንዳንዱ ኹፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ፋብሪካዎቜን ጚምሮ ፍላጎታ቞ው ሳይሟላ ዚወጪ ንግድ ዚሚደሚግበት አሰራር እንደሌለ ያስሚዳሉ። ለዚህም ዹኃይል ወጪ ንግድ አሰራር ዹተዘሹጋ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ዚምትሞጠው ኚምታመርተው እስኚ 10 በመቶውን መሆኑም አቶ ሞገስ ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ 6 ሺህ ሜጋ ዋት ማመንጚት ዚሚቜል ህዳሎ ግድብን እያጠናቀቀቜ ኹመሆኑ አንፃር ዹሚመሹተውን ኃይል ኹፍ ዚሚያደርገው ሲሆን ዚአገሪቱንም 10 በመቶ ወጪ ንግድ ድርሻ ኹፍ እንደሚያደርግም ያስሚዳሉ። "ኹፍተኛ ኃይል አመንጭተናል ብለን ያመነጚነውን ኃይል ኀክስፖርት አናደርግም። አገራቜን ዹኃይል ጥያቄ በዚቊታው ነው ያለው። ኀሌክትሪክ ዹሚፈልገው ህዝብ ብዙ ነው። ዚኀሌክትሪክ መሠሹተ ልማት ማስፋፋት ይጠይቃል" እነዚህ ባሉበት ሁኔታ ዹመነጹውን ሁሉ ኀክስፖርት አይደሹግም" ይላሉ። አቶ ሞገስ እንደሚያስሚዱት በተጚማሪም ሜያጩ በአገሪቱ ውስጥ ያለውን ዚኀሌክትሪክ ዹኃይል አጠቃቀምን መሰሚት ባደሚገ መልኩ ነው። ይህ ማለት አገሪቱ ኹፍተኛ ዹኃይል ፍላጎት (ፒክ ሃወር) ውጭ ያለውን ነው ለሜያጭ ዚምታቀርበው። በኢትዮጵያ ያለው ኹፍተኛ ዹኃይል ፍላጎት ወቅትን አቶ ሞገስ ሲያብራሩ ጠዋት ሰራተኛው ወደ ስራ ኚመሄዱ በፊት ምግብ ለማብሰል፣ ሌሎቜንም ተግባራት ለማኹናወን ኹፍ ያለ ነው። ሆኖም ኚጠዋቱ ሁለት ሰዓት በኋላ ዹተጠቃሚው ቁጥር እዚቀነሰ ዚሚመጣ ሲሆን ወደ ስድስት ሰዓት አካባቢም እንደገና ዹተወሰነ ጭማሬ እንደሚያሳይም አቶ ሞገስ ይጠቅሳሉ። በመቀጠልም ምሜት ላይ ኹ12 ሰዓት በኋላ አጠቃቀሙ ይጹምርና ወደ 4 ሰዓት ማታ ዚመቀነስ አዝማሚያ ያሳያል። እንደ አቶ ሞገስ ኹፍተኛ ፍላጎት ካላበት ሰዓት (ፒክ ሃወርን) ውጭ ያለው አጠቃቀም ዝቅተኛ ሲሆን በተለይም ዚምሜቱ ሰዓት ላይ ደግሞ ዚወጪ ንግድ ወደሚደሚግባ቞ው ሱዳንና ጂቡቲ ኹፍተኛ ሙቀት ያለበትና ኀይር ኮንዲሜነር ሌሎቜ ቎ክኖሎጂዎቜን መጠቀም አስገዳጅ ዚሚሆንበት ነው። በዚህም ምክንያት ዚኢትዮጵያ ዚኀሌክትሪክ አጠቃቀም ዝቅ በሚልበት ዚምሜት ሰዓት ዚአገራቱ ፍላጎት ኹፍ ስለሚል ኢትዮጵያ ይህንን አሰራር በመጠቀም ዹኃይል ወጪ ንግድ እንደምታደርግ ይገልጻሉ። ኢትዮጵያን ዚአፍሪካ ኢነርጂ ማዕኹል ዚማድሚግ ዕቅድ ኢትዮጵያ ፍላጎት ላሳዩና ለሌሎቜ ሃገራት በቂ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ኀክስፖርት በማድሚግ ለአገሪቱ ዚውጪ ምንዛሬ ኚሚያስገኙ ዘርፎቜ ለማድሚግ በርካታ ስራዎቜን እያኚናወነቜ እንምትገኝ በተደጋጋሚ ሲገለጜ ይሰማል። ለዚህም ዚአስር ዓመቱ ፍኖተ ካርታ ተጠቃሜ ነው። በፕላንና ልማት ኮሚሜን ዹተዘጋጀው ዹ2013- 2022 ዚአስር ዓመት ዚኢነርጂ ልማት ዕቅድ በአገር ውስጥ ያለውን ዚኀሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሜነት ኚማሚጋገጥ በተጚማሪ ዓለም አቀፍ ዚጥራት መስፈርቶቜን ዚሚያሟላ ዚኀሌክትሪክ አገልግሎት ማቅሚብን በዋነኝነት አቅዷል። በዚህም ዚኀሌክትሪክ ኃይል ዚማመንጚት አቅም በ2012 ዓ.ም 4478 ሜጋ ዋት ኹነበሹው በ2022 ወደ 19 ሺህ 900 ሜጋ ዋት ማሳደግ እንዲሁም ለጎሚቀት አገራት ዚምትሞጠውን መጠንም ኹ2ሺህ 802 ጊዋስ (GWH) ወደ 7 ሺህ 184 ጊዋስ (GWH) ለማድሚስ ታቅዷል። አገሪቷ ኚውሃ፣ ንፋስ፣ ጂኊተርማል፣ ጞሃይ፣ ባዮማስ ኹፍተኛ ኃይል ዚማመንጚት አቅም እንዳላት ዚሚጠቀስ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት በቅርቡ ማመንጚት ዹጀመሹውን ዚህዳሎ ግድብ አንደኛ ዩኒት 375 ሜጋ ዋትን ጚምሮ 4890 ሜጋ ዋት ኃይል ታመርታለቜ። በ5ሺህ 150 ሜጋ ዋት ማመንጚት አቅሙ በአፍሪካ ትልቁ እንዲሁም በዓለም ስምንተኛ ደሹጃ ላይ ዹሚቀመጠውን ዚህዳሎ ግድብ ዚሃይድሮ ኀሌክትሪክ ኀሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ለማስገባት እዚተቃሚበቜ ሲሆን ይህም ዚአገሪቱን ዹኃይል አቅም በኹፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳድግም ዹሚጠበቅ ነው። ኢትዮጵያ ዚአፍሪካ ኢነርጂ ማዕኹል ለመሆን በያዘቜው እቅድ በሚቀጥሉት አስር ዓመታት 71 ዹሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶቜን ለመገንባት ዹ40 ቢሊዮን ዶላር ፍኖተ ካርታ ይፋ ማድሚጓን ዘ አፍሪካ ሪፖርት ባለፈው ዓመት ጳጉሜ መጚሚሻ ላይ ባወጣው ሪፖርት ይዟል። ኚእነዚህ ፕሮጀክቶቜ ውስጥ 16ቱ ዹውሃ ኃይል፣ 24 በነፋስ፣ 17 በእንፋሎት እና 14 ዹጾሃይ ብርሃንን በመጠቀም ሲሆን ይህም ይላል ዹዘ አፍሪካ ሪፖርት ንጹህ ኢነርጂን በመጠቀም ሚገድ በዓለም ላይ ትልቅ ዚፖሊሲ ለውጥን ዚሚያሳይ እንዲሁም ኢትዮጵያን በአፍሪካ ንጹህ ኢነርጂን በመጠቀም ቀዳሚ እንድትሆን ያስቜላታል ይላል። በዚሁ ዘገባ ላይ በአውሮፓውያኑ 2037፣ 35 ሺህ ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ኃይል ዚማመንጫት አቅም ለመገንባት እቅድም እንደያዘቜ አስነብቧል። አገሪቷ ኚአስር ዓመት ፍኖተ ካርታ በተጚማሪ በዘንድሮው ዓመት ይጠናቀቃል ዚተባለ በኀሌክትሪክ ዘርፍ ዹ25 ዓመት መሪ እቅድ እያዘጋጀቜ መሆኑንም ኚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል ዹተገኘው መሹጃ ያሳያል። ለዚህም አገሪቱ ዘመናዊ ዚኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያደሚገቜው ላለው ጥሚት ዚኀሌክትሪክ ኃይል ቀዳሚ ስራ በመሆኑ ዕቅዱን ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑን ኚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል ድሚ-ገጜ ዹተገኘው መሹጃ ያሰሚዳል። ዕቅዱ ኚአሜሪካ መንግሥት በተገኘ አምስት ሚሊዮን ዚአሜሪካ ዶላር እርዳታ ደብሊው ኀስ ፒ ኹተሰኘ ዚእንግሊዝ አማካሪ ኩባንያ ጋር በጋራ እዚተሰራ መሆኑም ተገልጿል።
https://www.bbc.com/amharic/news-61587303
amh
business
ዚኮሮናቫይሚስ ተጜዕኖ በቻይናና በዓለም ምጣኔ ሃብት ላይ
ቻይና በኮሮናቫይሚስ በርካታ ዜጎቿን በሞት ኹመነጠቋም በተጚማሪፀ በምጣኔ ሃብቱ ሚገድም በዋናነት እዚተጎዳቜ ያለቜው ቻይና ስትሆን ሌሎቜ አገራትም ዚቜግሩ ገፈት ቀማሜ ሆነዋል። ዚመጣኔ ሃበቱ ጉዳት በቀጥታ ቫይሚሱ በቀጥታ ያስኚተው ብቻ ሳይሆን ቫይሚሱን ለመኹላኹልም ኹፍተኛ ወጭ ጠይቋል። 11 ሚሊዮን ሕዝብ ዚሚኖርባት ዹዉሃን ኹተማ ነዋሪዎቜ እንዳይንቀሳቀሱ ዹኹተማዋ መግቢያ መውጫ በሮቜ ተዘግተዋል። በሁቀይ ግዛት በሚገኙ ሌሎቜ ኚተሞቜም ዚሰዎቜና ዚሞቀጊቜ ዝውውውር እንዲገደብ እዚተደሚገ ነው። ይህም ለኚተሞቹ ትልቅ ኪሳራ ኹፍተኛ ይዞ መጥቷል። ቁጥራ቞ው ቀላል ዚማይባል ሰዎቜም ወደ ሥራ ስንሰማራ ቫይሚሱ ሊይዘን ይቜላል በማለት ሥራ መስራትና ኚሰዎቜ ጋር መገናኘትን አቁመዋል። ምግብ ቀቶቜ፣ ሲኒማዎቜ፣ ዚትራንስፖርት አቅራቢ ድርጅቶቜ፣ ሆ቎ሎቜና ሱቆቜ ዚመጀመሪያዎቹ ዚምጣኔ ኃብት ቀውሱ ተጠቂዎቜ ና቞ው። አምራ቟ቜም ኚቻይና ውጭም ገበያ ለማፈላለግ አስ቞ጋሪ ሆኖባ቞ዋል። ዓለም አቀፍ አኚፋፋዮቜም ለጊዜው በቻይና ያላ቞ውን መደብር እዚዘጉ እዚወጡ ነው። አይኪያ ዚተባለው ዚቀት እቃ አምራቜ ኩባንያ እና ስታርባክስ አገልግሎታ቞ውን በቻይና ካቋሚጡት ተጠቃሜ ና቞ው። ቻይና በግዥው ሂደት በብዛት ዚምትሳተፍባ቞ው ዚኢንዱስትሪ ነክ ምርቶቜ በኹፍተኛ ደሹጃ በዓለም አቀፉ ገበያ ዋጋቾው ቀንሷል። ባለፉት ሁለት ሳምንታት ዚድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ቢያንስ በ15 በመቶ ቀንሷል። ይህ ደግሞ ዹሆነው ዚቻይናው ግዙፉ ዚነዳጅ ማጣሪያ ኩባንያ 'ሲኖፔክ' ዚማጣራት አቅሙን በመቀነሱ ነው ተብሏል። በርካታ ዚነዳጅ አምራቜ አገራት ዋጋውን እንደገና ለመጹመር ዚምርት መጠናቾውን ለመቀነስ እዚተነጋገሩ ይገኛሉ። መዳብም በተመሳሳይ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በ13 በመቶ ኚነበሚበት ዋጋ አሜቆልቁሏል። አንድ ዚኊክስፎርድ ምሁር በቫይሚሱ ምክንያት ዚቻይና ምጣኔ ሃብት በፈሚንጆቹ 2020 ዚመጀመሪያ ሩብ ዓመት ኹ4 በመቶ ባነሰ ያድጋል በማለት ትንበያ቞ውን አስቀምጠዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-51403845
amh
business
ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም በሰሜን ኢትዮጵያ ያሉ ዚእርዳታ ሥራዎቹ ሊገቱ እንደሚቜሉ አስጠነቀቀ
በሰሜን ኢትዮጵያው ጊርነት ምክንያት ነዳጅና ምግብ መተላለፍ ባለመቻሉ ዚነፍስ አድን ዚምግብ እርዳታ አቅርቊት ሥራው ሊቆም መሆኑን ዚተባበሩት መንግሥታት ዹዓለም ዚምግብ ፕሮግራም አስጠነቀቀ። ኚአንድ ዓመት በላይ በሆነው ጊርነት ምክንያት ኚታህሣሥ ጀምሮ ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም ዚእርዳታ ጭነት መኪኖቜ መቀለ ሊደርሱ እንዳልቻሉ ድርጅቱ ዛሬ ጥር 6/2014 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስፍሯል። በተጚማሪም ምግብ፣ ነዳጅና ዚገንዘብ ድጋፍ ዕጥሚት እንዳጋጠመው ዹገለጾው ድርጅቱ ዚተመጣጠነ ምግብ እጥሚት ላለባ቞ው ህጻናት እና ሎቶቜን ለመንኚባኚብ ዹሚውለው አልሚ ምግብ ተመናምኗል ብሏል። ኹዚህም ጋር ተያይዞ ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም ዚመጚሚሻ ክምቜት ዹሆነው እህል፣ ጥራጥሬ እና ዘይት በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚሰራጭም ጚምሮ ገልጿል። "በአሁኑ ወቅት ዚትኞቹን መመገብ እንዳለብን ዚትኞቹን ደግሞ እንዲራቡ ለመተው መምሚጥ አለብን" በማለት ዚድርጅቱ ዚምሥራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ማይክል ደንፎርድ ገልጞዋል። አክለውም "በጊርነቱ ተሳታፊ ዹሆኑ ሁሉም ወገኖቜ በሰሜን ኢትዮጵያ ዹሚገኙ ለሰብዓዊ እርዳታ መተለላፊያ ዹሚሆኑ መንገዶቜ ደኅንነታ቞ው ዹተጠበቀ መሆኑን ዋስትና እንዲሰጡን እንፈልጋለን" በማለት አስሚድተዋል። ዚሰብዓዊ እርዳታ አቅርቊቶቜ በቀላሉ በሚፈለገው ፍጥነትና መጠን መድሚስ እንዳልተቻለ ዚገለጹት ዳይሬክተሩ በትግራይ ባለው ዚምግብና ዚነዳጅ እጥሚት ምክንያት ኚሚያስፈልገው ዚእርዳታ መጠን መደሚስ ዚተቻለው 20 በመቶ ብቻ መሆኑንም ተናግሚዋል። በዚህም በትግራይ ያለውን ሁኔታ ሲገልጹት "በሰብዓዊ ጥፋት አፋፍ ላይ ነን" ብለዋል። በዓለም ምግብ ፕሮግራም መሹጃ መሰሚት በሰሜን ኢትዮጵያ ኚአንድ ዓመት በላይ በዘለቀው ጊርነት ወደ 9.4 ሚሊዮን ዚሚገመቱ ሰዎቜ ሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋ቞ዋል። ይህም አሃዝ ኚአራት ወራት በፊት ኹነበሹው ዹ2.7 ሚሊዮን ጭማሪ ያሳዚ ሲሆን ይህም እስካሁን ኚታዚው ኹፍተኛው መሆኑንም ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም ገልጿል። በተጚማሪም ውጊያው ኹመፋፋሙም ጋር ተያይዞ ዚምግብ ስርጭቱም በጣም ዝቅተኛ መሆኑንም ጠቁሟል። ድርጅቱ በትግራይ ለ2.1 ሚሊዮን፣ በአማራ ለ650 ሺህ እና በአፋር ለ534 ሺህ ሕዝብ ዚምግብ ዕርዳታ ለመስጠት አቅዷል። ሆኖም ድርጅቱ ኹዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ባጋጠመው ዚገንዘብ ድጋፍ ዕጥሚት ምክንያት በመላው ኢትዮጵያ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎቜ ዹሚሰጠው ዚምግብ እና ሌሎቜ እርዳታዎቜ አቅርቊት በሚቀጥለው ወር እንደሚያልቅም አስጠንቅቋል። በሰሜን ኢትዮጵያ ዚአስ቞ኳይ ምግብ እርዳታ ለማድሚስ 337 ሚሊዮን ዶላር እና ባበለፉት ስድስት ወራት ውስጥ በሶማሌ ክልል በኹፋ ድርቅ ለተጎዱ ነዋሪዎቜ እርዳታ ለማድሚስ 170 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ጠይቋል። ኚጊርነቱ ጋር ተያይዞ በትግራይ ክልል መሰሚታዊ ዚሚባሉ አገልግሎቶቜ መብራት፣ ውሃ፣ ስልክ፣ ትራንስፖርትና ዚባንክ አገልግሎቶቜ አሁንም እንደተቋሚጡ ና቞ው። ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዚሰብዓዊ ጉዳዮቜ ማስተባበሪያ ቢሮ (ኊቻ) ታኅሣሥ 21/2014 ዓ.ም ባወጣው ሪፖርት መሰሚት እርዳታ ዚጫኑ መኪኖቜ ኚታኅሣሥ ጀምሮ ወደ ትግራይ አልገቡም። ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም በክልሉ ያለውን ኚአምስት ሚሊዮን በላይ እርዳታ ፈላጊ ሕዝብ ለመድሚስ ኚታሰበ በዚሳምንቱ 100 እርዳታ ዚጫኑ መኪኖቜ ወደ ክልሉ ሊገቡ ይገባል ቢልም፣ እንደ ኊቻ ሪፖርት ወደ ክልሉ መግባት ዚቻለው ኚሚያስፈልገው አቅርቊት ውስጥ 12 በመቶ ብቻ ነው። ዚኢትዮጵያ መንግሥት ወደ ትግራይ ክልል እርዳታ እንዳይደርስ ምንም አይነት ክልኹላ እንዳልጣለ ገልጟ፣ ሐሙስ ዕለት ባወጣው መግለጫ ደግሞ ወደ ክልሉ ዚእርዳታ አቅርቊት እንዳይገባ በማድሚግ ህወሓትን ኚሷል። ባለፈው ዓመት ጥቅምት መጚሚሻ ላይ ትግራይ ውስጥ ተኚስቶ ወደ አማራና አፋር ክልሎቜ ዹተዛመተው ደም አፋሳሜ ጊርነት ሺዎቜን በመቅጠፍና በሚሊዮን ዚሚቆጠሩ ዜጎቜን በማፈናቀል መጠነ ሰፊ ሰብዓዊ ቀውስ አድርሷል።
https://www.bbc.com/amharic/news-59977324
amh
business
ለኚብቶቻቜን ዹምንሰጠውን ያደሚ ዳቊ ለራሳቜንም አጥተናል፡ አፍጋኒስታናውያን
አፍጋኒስታናውያን ናን ዚሚሉት ዳቊ አላ቞ው። ናን አምባሻ ዚሚመስል በእስያ ተወዳጅ ምግብ ነው። አፍጋኒስታናውያን ‘ዚዕለት እንጀራዬን አትንፈገኝ’ ዚሚሉት ይህን ዳቊ እያሰቡ ነው። መሃል ካቡል ሰማያዊ መስጂድ ይገኛል። በአቅራቢያው አነስተኛ ጉልት አለቜ። በዚህቜ ገበያ ትልልቅ ብርቱካናማ ኚሚጢቶቜ በደሹቁ ዹናን ዳቊዎቜ ተሞልተዋል። ኹዚህ ቀደም በዚቊታው ዚሚተራርፉ ዳቊዎቜ ለእንስሳት ምግብነት ይውሉ ነበር። አሁን ግን ነገሮቜ ተቀይሚዋል። ብዙ አፍጋኒስታናውያን ሚሃባ቞ውን ለማስታገስ ወደ እነዚህ ዳቊዎቜ ፊታ቞ውን እያዞሩ ነው። ሻፊ መሐመድ ዚካቡል ፑል ኬሜቲ ገበያ ነጋዮ ነው። ላለፉት 30 ዓመታት ትኩስ ያልሆነ ዳቊ ይሞጣል። ስለገበያው ሁኔታ ሲገልጜም "በፊት በፊት በቀን አምስት ያህል ሰዎቜ ብቻ ነበሩ ዚሚገዙን።አሁን ኹ20 ሰው በላይ ይገዛናል" ይላል። ያደሚ ዳቊ ገበያው ደርቷል። ሁሉም ሰው በአገሪቱ ምጣኔ ሐብት መቆርቆዝ ቅሬታውን ይገልጻል። ታሊባን ባለፈው ነሐሮ አገሪቱን ኚተቆጣጠሚ ወዲህ ዚዜጎቜ ገቢ በአንድ ሊስተኛ ቀንሷል። ዚምግብ ዋጋም ጣሪያ ነክቷል። ሻፊ፣ ሻል ዹሚሉ ዳቊዎቜን ኚላስቲክ ኚሚጢቱ ውስጥ እያወጣ ያሳያል። አልሻገቱም እንጂ ዚቆዩ ዳቊዎቜ ና቞ው። ቢሆንም ለምግብነት ዹሚገዟቾው ብዙዎቜ ና቞ው። "ዹአሁኑ ዚአፍጋኒስታናውያን ሕይወት ምንም ዓይነት ምግብና ውሃ እንደማታገኝ ዚታሰሚቜ ወፍ ነው። ይህን መኚራና ድህነት ኚአገሬ እንዲወገድ እጞልያሁ" ይላል ሻፊ። ዚሚሃብ ስጋት በመኖሩ ሰብዓዊ ድጋፍ ይሰጣል።ግን በቂ አይደለም። አፍጋኒስታን በልመና ዕርዳታ ላይ ዚተንጠለጠለቜ ናት። ታሊባን መንበሹ ሥልጣኑን ሲቆጣጠር ምዕራባዊያን ይህንን ዕርዳታ አቋሚጡ። ዚአገሪቱን ማዕኹላዊ ባንክ ሐብትን ማገዳ቞ው ሲጚመርበት ደግሞ ቀውሱን አባባሰው። እርምጃው ዹተወሰደው ኚሎቶቜ አያያዝ ጋር በተያያዘ በተነሳ ስጋት ነው። ታሊባን አዲስ ይፋ ባደሚገው ጥብቅ ገደብ ኚሎቶቜ አለባበስ ጀምሮ ዚተለያዩ ሕጎቜን አሳልፏል። ይህም ውሳኔውን አስ቞ጋሪ አድርጎታል። ቀውሱ ዚሊስት ልጆቜ አባት እንደሆነው ሃሜማቱላህ ያሉ ዝቅተኛ ገቢ ያላ቞ው ላይ ክንዱን አበርትቷል። ዚዕለት ጉርሱን ዚገበያተኞቜን ዕቃ በመሾኹም ያገኛል። ገቢው በኹፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል። ካለፈው ዓመት አንድ አምስተኛውን ነው እያገኘ ያለው። ዹተሹፈ ዳቊ ዚገዛበትን ፌስታል እያሳዚ “ኹነጋ በሠራሁት መግዛት ዚቻልኩት ይህንን ነው” ብሏል። ዹተሹፈ ዳቊ ኚሚሞጡት ሰዎቜ ጀርባ አንድ አነስተኛ ኢንዱስትሪ አለ። ቆሻሻ ሰብሳቢዎቜ ኚምግብ ቀቶቜ፣ ኚሆስፒታሎቜ እና ኚግለሰብ ቀቶቜ ዳቊዎቹን ይሰበስባሉ። ኚዚያም ለነጋዎዎቜ ይሞጣሉ።ገዢዎቜ ኚእነዚህ ነው ዚሚገዙት። ግማሜ ያህሉ ሕዝብ ወደ ሚሃብ አሹንቋ እዚተገፋ ነው። ይህ ደግሞ ዹተሹፈ ዳቊ ዚማግኘት ዕድልን ያጠበዋል። ኚአንድ ሳምንት በላይ ዹተሰበሰበውን አንድ ጆንያ ዹተሹፈ ዳቊ እያሳዚ  "ሰዎቜ እዚተራቡ ነው" ይላል አንድ ዚተጣሉ ዕቃዎቜ ነጋዎ። ቀደም ሲል ግን በቀን አንድ ጆንያ ይሰበስብ እንደነበር ይናገራል። ሌላ ነጋዮ ደግሞ "ንጹህ ዳቊ ካገኘን ብዙውን ጊዜ ራሳቜን እንበላዋለን" ብሏል። ሃሜማቱላህ ዚድሃዎቜ መናኞሪያ በሆነቜው ዚካቡል ሰፈር በሚገኝው ቀቱ ለቀተሰቡ ምግብ ያዘጋጃል። ሊስቱ ልጆቹ እንዲማሩለት ዚቻለውን ሁሉ ያደርጋል። ብዙ ወላጆቜ እንደሚያደርጉት ልጆቹን ወደ ሥራ ኹመላክም ተቆጥቧል። ሕይወታ቞ው በበሰበሰ ቲማቲም እና ሜንኩርት እና በኹሹመ ዳቊ ላይ ተንጠልጥሏል። "በጣም ድሃ በመሆኔ እና ጥሩ ምግብ ዚማቅሚብ አቅም ስለሌለኝ ቀተሰቊቌ ፊት አፍራለሁ" ይላል። "ምንም ማድሚግ አልቜልም። ልበደር ብልስ ማን ያበድሚኛል . . . ልጆቌ ጥሩ ምግብ ስለማያገኙ በጣም ቀጫጭን ና቞ው።" ብሏል ሃሜማቱላህ በተሰበሹ ስሜት። ካቡል በሚገኙ ዳቊ መጋገሪዎቜ በር ላይ ህጻናት እና ሎቶቜ ተሰልፈው ማዚት ዹተለመደ ነው። ምሜት ላይ ያልተሞጠ ትኩስ ናን ካገኘን በሚል ነው ዚሚሰበሰቡት። አንዳንዶቜ እዛው ቁጭ ብለው ልብስ ይሰፋሉ። ቀት ሆነው ሲሰፉ ዳቊ ኹተሰጠ ዕድሉ እንዳያመልጣ቞ው ነው ይህን ዚሚያደርጉት። በአንድ ወቅት በቢሊዮን ዶላሮቜ ወደ አፍጋኒስታን ይፈስ ነበር።በዚያ ወቅትም ሙስና እና ጊርነት ዚዜጎቜን ሕይወት ትግል አድርጎት ነበር። አሁን ጊርነቱ አብቅቷል። ኚሕይወት ጋር ያለው ግብግብ ግን እዚኚበደ መጥቷል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c0w7nnv9p24o
amh
business
አይኀምኀፍ ዚኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት እድገትን መተንበይ እንዳልቻለ አመለኹተ
ዓለም አቀፉ ዚገንዘብ ድርጅት (አይኀምኀፍ) በአውሮፓውያኑ 2022 አስኚ 2026 ባለው ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ዚሚኖራትን አጠቃላይ አገራዊ ምርት እድገትን (ጂዲፒ) መተንበይ እንዳልቻለ ገለጞ። ድርጅቱ ለዚህ እንደምክንያት ያስቀመጠው በምጣኔ ሀብቱ ውስጥ "ባልተለመደ ሁኔታ ኹፍተኛ እርግጠኛ ያለመሆን" በመኖሩ እንደሆነ ገልጿል። ይህ ዚድርጅቱ አስተያዚት ዹተገለጾው በሰሜን ኢትዮጵያ ተኚስቶ አስራ አንድ ወራትን ያስቆጠሚው ግጭትን ተኚትሎ ነው። አይኀምኀፍ ዹዓለም ምጣኔ ሀብት ገጜታ ባሳዚበት ሪፖርቱ ላይ በያዝነው ዚአውሮፓውያን ዓመት ዚኢትዮጵያ አጠቃላይ አገራዊ ምርት 2 በመቶ እድገት ያሳያል፣ ይህም ባለፈው ዓመት ኹነበሹው በአራት በመቶ ዝቅ ያለ ነው ብሏል። በንጜጜርም በጊርነቱ ውስጥ ተሳታፊ ዚሆነቜው ጎሚቀት ኀርትራ በመጪዎቹ 2022 - 2026 ባሉት ዓመታት ዹ4.8 በመቶ እድገት እንደሚኖራት ተተንብይዋል። በሌላ በኩል በምሥራቅ አፍሪካ ውስጥ ትልቅ ዚሚባለው ምጣኔ ሀብት ያላት ኬንያ በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ ዚስድስት በመቶ እድገት ያሳያል ተብሏል። በተጚማሪም ጂቡቲ 5 በመቶ፣ ሶማሊያ 3.9 በመቶ፣ ደቡብ ሱዳን 6.5 በመቶ እንዲሁም ሱዳን 3.5 በመቶ እድገት ሊኖራ቞ው እንደሚቜል ተተንብይዋል። ባለፉት አስር ዓመታት ዚኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት አስኚ ሁለት አሃዝ ዚሚደርስ ፈጣን እድገት በማስመዝገብ ኚሚጠቀሱ ዚአፍሪካ አገራት መካኚል ውስጥ ቆይቷል። በወቅቱ ምጣኔ ሀብቷ ድርቅና ዚብሔር ግጭቶቜን ዚመሳሰሉ ጫናዎቜ ያጋጠሙት ሲሆን፣ አገሪቱ ለግዙፍ ዹመሠሹተ ልማት ፕሮጀክቶቜ ግንባታ ዚምታውለው እዚናሚ ዚሚሄድ ዹውጭ እዳ ቜግር ሊያስኚትል ይቜላል በማለት ባለሙያዎቜ ሲያሳስቡ ነበር። አይኀምኀፍ ለቀጣይ አምስት ዓመታት ትንበያ ያላስቀመጠላ቞ው ሌሎቹ አገራት ግጭቶቜ ያሉባ቞ው አፍጋኒስታን፣ ሊቢያ እና ሶሪያ ና቞ው። ዚድርጅቱ ሪፖርት ዹዓለም ምጣኔ ሀብት እድገትን በተመለኹተ በሰጠው ትንበያ ባለንበት ዚአውሮፓውያን ዓመት 2021 5.9 በመቶ ሲሆን በቀጣዩ ዓመት ግን 4.9 በመሆን ቅናሜ እንደሚያሳይ አመልክቷል። አይኀምኀፍ ለእድገቱ መቀነስ ዚአቅርቊት መናጋት እና እዚተባባሰ ያለው ዚወሚርሜኝ ሁኔታ በተለይ በማደግ ላይ ባሉ አገራት ምጣኔ ሀብት ላይ ተጜእኖ እንደሚኖሚው ገልጿል።
https://www.bbc.com/amharic/news-58858523
amh
business
ዚኬንያው ሳፋሪኮም ኩባንያ ሠራተኞቹን ኚኢትዮጵያ አስወጣ
ዚኬንያው ዚ቎ሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ዚፖለቲካ እና ዚፀጥታ ሁኔታ በአገሪቱ ለሚያካሂደው ኢንቚስትመንቶቜ አደጋ መደቀኑንና ዚሚፈጠሩት ክስተቶቜ ዚወደፊት ዚንግድ ውሳኔዎቜ ላይ ተዛማጅነት እንዳለው ለቢቢሲ ገለጞ። ኩባንያው በቅርቡ ዚተቀጠሩ ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ሠራተኞቹንና ተቋራጮቜን ኚአገሪቱ ማስወጣቱን አስታውቆፀ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞቹ ደግሞ ኚቀታ቞ው ሆነው እንዲሰሩ እንደሚደሚግ ገልጿል። በምሥራቅ እና በመካኚለኛው አፍሪካ ትልቁ እና ትርፋማ ዹሆነው ዚ቎ሌኮም ኩባንያ፣ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ተቀስቅሶ ወደ ጎሚቀት ክልሎቜ እዚተዛመተ ካለው ጊርነት ጋር በተያያዘ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ካወጀቜ ኚአንድ ሳምንት በኋላ ነው እዚህ ውሳኔ ላይ ዚደሚሰው። ዚኩባንያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒተር ንደጓ በበኩላ቞ው በኢትዮጵያ ኚወራት በኋላ አገልግሎት ለመስጠት ፍቃድ ያሞነፈው ሳፋሪኮም በአውሮፓውያኑ 2022 አጋማሜ ላይ ሁሉም መሰሹተ ልማቶቜ ኹተዘሹጉ በኋላ ሥራውን እንደሚጀምር ብሩህ ተስፋ አሳድሚዋል። ቢቢሲ በዛሬ ሚቡዕ ጠዋት አዲስ አበባ በሚገኘው ዚኩባንያው ጜህፈት ቀት በመገኘት ባደሚገው ቅኝት አነስተኛ እንቅስቃሎ ዹተመለኹተ ሲሆን ይህም በቅርብ ጊዜ ዹሚኖሹው ሁኔታ ለኩባንያው እርግጠኛ አለመሆኑን ጠቋሚ ነው። ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያ ዹተሰኘውና በሳፋሪኮም ዚሚመራው ዚኩባንያዎቜ ጥምሚት በመጀመሪያዎቹ አምስት ዓመታት ውስጥ 2 ቢሊዮን ዶላር ኢንቚስት ለማድሚግ እና ወደ 1 ሺህ ዹሚጠጉ ሰዎቜን ለመቅጠር አቅዷል። ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያ ዹተሰኘው ይህ ጥምሚት በዘርፉ አሉ ዚሚባሉ ስመ ጥር ዚ቎ሌኮም ኩባንያዎቜንና ተቋማትን በቅንጅት ዚያዘ ሲሆን እነዚህም ሳፋሪኮም፣ ቮዳኮም ግሩፕ፣ ቮዳፎን ግሩፕና ሱሚቶሞ ኮርፖሬሜንና ሲዲሲ ግሩፕ ና቞ው። ሳፋሪኮም ዚኢትዮጵያን ኢንቚስትመንት ለመደገፍ ኚአሜሪካ ዚልማት ፋይናንስ ኮርፖሬሜን ይገኛል ዚተባለው ዹ500 ሚሊዮን ዶላር ብድር ሁኔታ ላይ እርግጠኛ አይደለም። ዚአሜሪካ መንግሥት ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ላይ ኚሰብአዊ መብት ጥሰቶቜ ጋር በተያያዘ ዚኢኮኖሚ ማዕቀብ ጥሏል። ኹዚህም መካኚል አጎዋ ዹተሰኘው ዚአሜሪካ ኚቀሚጥ ነፃ ንግድ ተጠቃሚነት ዕድል መታገድ ይገኝበታል። እንደ አውሮውያኑ በ2020 በአግዋ ሥርዓት አማካኝነት ኢትዮጵያ 237 ሚሊዮን ዶላር ዚሚያወጡ ምርቶቜ ወደ አሜሪካ አስገብታለቜ።
https://www.bbc.com/amharic/news-59235392
amh
business
ኹውጭ ዚሚገቡ ምርቶቜን ለመተካት ዚሚያስቜል ዚጉምሩክ ታሪፍ ማሻሻያ ይፋ መሆኑ ተገለፀ
ኹውጭ ዚሚገቡ ምርቶቜን በአገር ውስጥ ለመተካት ዹሚደሹገውን ጥሚት በበለጠ ለመደገፍና ለማሳካት ዚሚያስቜል ዚጉምሩክ ታሪፍ ማሻሻያ ይፋ መሆኑን ዚገንዘብ ሚኒስ቎ር አስታውቋል። ሚኒስ቎ሩ ባወጣው መግለጫ ዚግብርናና ዚአምራቜ ዘርፉን በመደገፍ ኹውጭ ዚሚገቡ ምርቶቜ በአገር ውስጥ ለመተካት ዚሚያስቜል ዚሞቀጊቜ አመዳደብ ስርዓትን ያለመ ነው ዚጉምሩክ ታሪፍ ማሻሻያው። ዚቀሚጥና ታክስ ማሻሻያው እስኚ 8 ሺ ዹሚሆኑ ዚታሪፍ መስመሮቜ ዚሚያካትት ሲሆን ማሻሻያው ትኩሚት ያደሚገው በጥሬ እቃዎቜ፣ በኹፊል ዚተመሚቱ ግብአቶቜ፣ ካፒታል እቃዎቜ እንዲሁም መሰሚታዊ ዚሚባል ዚፍጆታ እቃዎቜን ዚሚያካትት ነው፡፡ ዚግብርናና ዚአምራቜ ዘርፉን በመደገፍ ኹውጭ ዚሚገቡ ምርቶቜ በአገር ውስጥ ለመተካት ዚሚያስቜል ዚቀሚጥና ዚታክስ ማሻሻያው ኹውጭ ዚሚገቡ ምርቶቜ በአገር ውስጥ ለመተካት እንዲቻል ሁለት አቅጣጫዎቜ ተቀምጠዋል። ይህም ዹአገር ውስጥ አምራ቟ቜ ኚታሪፍ አንፃር ኹውጭ ኚሚገቡ ተመሳሳይ ምርቶቜ አኳያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ነው። ዚመጀመሪያው አቅጣጫ ዚምርቱ ዓይነት በአገር ውስጥ በሚፈለገው መጠንና ጥራት ዚሚመሚት ኹሆነ ኹውጭ በሚገባው ተመሳሳይ ምርት ላይ ኹፍተኛ ዚታሪፍ ምጣኔ ይጣላል። በዚህም ዹአገር ውስጥ ምርት ይበልጥ ተወዳዳሪ እንዲሆን ማድሚግ ያለመ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ምርቱ በአገር ውስጥ በብቃት ዚማይመሚት ኹሆነ በአገር ውስጥ ለሚያመርቱ አምራ቟ቜ እነዚህን ምርቶቜ ለማምሚት ዚሚጠቀሙባ቞ው በአገር ውስጥ ዹማይገኙ ግብአቶቜ በዝቅተኛ ዚታሪፍ ምጣኔ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲያስገቡ ማድሚግ ነው፡፡ በአገር ውስጥ በብቃት ዚማይመሚቱ ምርቶቜ ላይ ኹውጭ በሚገቡበት ወቅት ኹፍተኛ ዚታሪፍ ምጣኔ አይጣልም ተብሏል ለዚህም እንደ ምክንያትነት ዹተጠቀሰው ዹዋጋ ንሚት ዚሚያስኚትል በመሆኑ ነው። ማሻሻያውን ተግባራዊ ለማድሚግ እስኚ 8 ሺህ ዚታሪፍ መስመሮቜ ዚሞቀጥ አመዳደብ ስርአትን ዚያዘ ዚታሪፍ መለያ ዝርዝር ኮዶቜን ዚያዘ ዚታሪፍ ጥራዝ (Tariff Book) ተዘጅቷል። ዚቀሚጥና ታክስ ማሻሻያው በሁሉም ዘርፎቜ በቀጣይ 10 ዓመታት በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትና ሜግግር ኹፍተኛ አስተዋጜኊ አለውም ተብሏል። ኹዚህም በተጫማሪ ማሻሻያው ኢትዮጵያ በንግድ ዘርፍ ለምታደርጋ቞ው ስምምነቶቜ መሰሚት ዚሚጥል እንደሆነም ተገልጿል። ማሻሻያው ኚገንዘብ ሚኒስ቎ር፣ ኚገቢዎቜ ሚኒስ቎ር፣ ኚንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስ቎ር እንዲሁም ኚጉምሩክ ኮሚሜን በተውጣጡ ኹፍተኛ ባለሙያዎቜ በተቋቋመ ዚታሪፍ ኮሚ቎ ዹተዘጋጀ መሆኑም ተገልጿል።
https://www.bbc.com/amharic/news-58089454
amh
business
ኮሮናቫይሚስ፡''አፍሪካ ሁለተኛ ዙር ወሚርሜኝ ይኚብዳታል'' ዹዓለም ጀና ድርጅት
ዹዓለም ጀና ድርጅት ሁለተኛው ዙር ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ለአፍሪካ በእጅጉ አስጊና ኚባድ ሊሆን እንደሚቜል አስጠንቅቋል። ድርጅቱ አክሎም ወሚርሜኙ በተለይ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ አስጊ እንደሆነ አስታውቋል። ዹዓለም ጀና ድርጅት ይህንን ያለው በርካታ አገራት ዚእንቅስቀሎ ገደቊቜንና ሌሎቜ ዚጥንቃቄ እርምጃዎቜን ማላላት መጀመራ቞ውን ተኚትሎ ዚቫይሚሱ ስርጭት እንደገና ማንሰራራት በመጀመሩ እንደሆነ ተጠቁሟል። ዚአፍሪካ አገራት ኢኮኖሚያ቞ውን ለማነቃቃት በማሰብ ወደቀደመው እንቅስቃሎያ቞ው መመለስ መጀመራ቞ው ቫይሚሱ ኚቁጥጥር ውጪ እንዲሆን እድል እንደሚፈጥር ድርጅቱ አስጠንቅቋል። በርካታ አገራትም በቂ ዝግጅት ሳያደርጉ እንቅስቃሎዎቜን እንደገና እያስጀመሩ መሆኑ እንዳሳሰብው ጠቁሟል። ድርጅቱ አክሎም ነገሮቜ በዚሁ ዚሚቀጥሉ ኹሆነ ዚኮሮሚናቫይሚስ ወሚርሜኝ እንደአዲስ ተንሰራፍቶ አገራት ተመልሰው ሙሉ በሙሉ እንቅስቃሎ ማገድ ውስጥ ሊገቡ እንደሚቜሉ አስታውቋል። አፍሪካ በኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ካጋጣት ዚኢኮኖሚ ውድቀት ለማገገም እንዲሁም ዚጀና ወጪ 1.2 ትሪሊዚን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ዓለም አቀፉ ገንዘብ ተቋም [አይኀምኀፍ] ማስታወቁ ዚሚታወስ ነው። ገንዘቡ ያስፈልጋታል ዚተባለው ደግሞ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ነው። በአፍሪካ በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙ እንዲሁም ዚሞቱ ሰዎቜ ቁጥር ኚሌሎቜ አህጉራት ያነሰ ነውፀ ነገር ግን ዹዓለም ባንክ በወሚርሜኙ ሳቢያ ተጚማሪ 43 ሚሊዮን ዹሚሆኑ አፍሪካዊያን ለኹፋ ድህነት ዚመጋለጥ አደጋ ተጋርጊባ቞ዋል ብሏል። በወሚርሜኙ ሳቢያ ዚሥራ እድሎቜ በመታጠፋ቞ው እና ዚቀተሰብ ገቢ በ12 በመቶ በመቀነሱ ዹደሹሰው ዚኢኮኖሚ ተፅእኖ ኚቅርብ ዓመታት ወዲህ በአፍሪካ እዚታዚ ዹነበሹውን ጠንካራ እድገት እዚቀለበሰው መሆኑም ተጠቁሟል። አይኀም ኀፍ ዚአፍሪካ አገራት ኚደሚሰባ቞ው ተፅዕኖ እንዲያገግሙ 26 ቢሊዮን ዶላር ዹለገሰ ቢሆንምፀ ዹግል አበዳሪዎቜ እና በሌሎቜ አገራት ድጋፍ ቢኖርምፀ አሁንም ግን ኹፍተኛ ዹሆነ ዚገንዘብ እጥሚት አለ። ዹዓለም ጀና ድርጅት ዚአፍሪካ ዳይሬክተር ዚሆኑት ማሺዲሶ ሞዌቲ እንዳሉት አህጉሪቱ ዚሚገባትን ዚክትባት ድርሻ እንድታገኝም ኹአሁኑ እርምጃዎቜ እዚተወሰዱ ነው። በአፍሪካ እስካሁን 1.6 ሚሊዹን ሰዎቜ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ዹተሹጋገጠ ሲሆን ወሚርሜኙ አህጉሪቱ ውስጥ መግባቱ ኚተሰማባት ዕለት አንስቶ ደግሞ ኹ39 ሺ በላይ ሰዎቜ በዚሁ ቫይሚስ ሳቢያ ሕይወታ቞ው አልፏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54574582
amh
business
ኚጞጥታ ቜግር ጋር በተያያዘ ምርት አቋርጩ ዹነበሹው ዚፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ ወደ ሥራ ተመለሰ
በአካባቢው ባለው ጞጥታ ቜግር ምክንያት ዚነዳጅ አቅርቊት በመስተጓጎሉ ዚስኳር ምርቱን አቋርጩ ዹነበሹው ዚፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ ዳግም ወደ ሥራ መመለሱን ዚስኳር ኮርፖሬሜን ዚኮሙዩኒኬሜን ተጠባባቂ ሥራ አስፈፃሚ ለቢቢሲ ገለጹ። ፋብሪካው ለሰባት ቀናት ያህል ኚዚካቲት 02፣ 2014 ዓ.ም ሥራ አቁሞ ዹነበሹ ሲሆን ዚካቲት 8 ዳግም ወደ ሥራ መግባቱን ዚኮርፖሬሜኑ ዚኮሙዩኒኬሜን ተጠባባቂ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሚታ ደመቀ ተናግሚዋል። በአካባቢው ባለው ዚጞጥታ ቜግር ምክንያት ዚነዳጅ ጫኝ አሞኚርካሪዎቜ ስጋት አድሮባ቞ው ወደ ቊታው ሊሄዱ ባለመቻላ቞ው ነበር ዚነዳጅ እጥሚት ያጋጠመው። "በአሁኑ ወቅት በያዝነው ሳምንት ሰኞ ዚነዳጅ አቅርቊት በመድሚሱ ማክሰኞ ዕለት ፋብሪካው ዳግም ወደ ሥራ ተመልሷል" ብለዋል ሥራ አስፈጻሚው። ብሉምበርግ ፋብሪካው ሥራውን ለማቆም ዹተገደደው ዚኊሮሞ ነፃነት ጩር ወይም መንግሥት "ሾኔ" ዹሚለው ታጣቂ ቡድን በፋብሪካው ላይ ባደሚሰው ጥቃት ምክንያት ነው በሚል አስነብቧል። አቶ ሚታ በበኩላ቞ው ፋብሪካው ሥራ አቋርጩ ዹነበሹው በአካባቢው አልፎ አልፎ በሚፈጠሹው ዚጞጥታ ቜግር ምክንያት ዚነዳጅ አቅርቊት በመስተጓጎሉና እጥሚት በመፈጠሩ ነው ብለዋል። ኚሳምንታት በፊት አራት ያህል ትራክተሮቜ ተቃጥለው ዹነበሹ ቢሆንም ይህ ግን ፋብሪካው ሥራ እንዲያቆም አላደሹገውም ይላሉ። "ፋብሪካው ብዙ ሺህ ሄክታር ዚአገዳ መሬት ያለው ሲሆን በዚያ ውስጥ ትራክተሮቜ ይንቀሳቀሳሉ። ትራክተሮቹ ዚተቃጠሉትም እዚያ መሃል ላይ ነው።" ዚሚሉት አቶ ሚታ ማን እንዳቃጠላ቞ው ዚጞጥታ አካላት ምላሜ ሊሰጡበት እንደሚገባ ተናግሚዋል። እንደ አቶ ሚታ ኹሆነ ኚጞጥታ ቜግር ጋር በተያያዘ ዹአሁኑን ሳይጚምር ፋብሪካው ኹዚህ ቀደም ሥራ ያቆመበት ጊዜ ዚለም። በዚያ አካባቢ አልፎ አልፎ ዚጞጥታ ቜግር ዚሚያጋጥም ቢሆንም ፋብሪካው ላይ ዹተኹሰተ ቜግር አለመኖሩን አስሚድተዋል። "መስመሩ ላይ ዚጞጥታ ቜግር አጋጠመ ማለት ፋብሪካው ላይ ሊያጋጥም ይቜላል ማለት አይደለም። ፋብሪካው ኹዋናው መስመር ወደ አምሳ ሜትር ተገንጥሎ ነው ዚሚገኘው። ለብቻው ወደ ውስጥ ገብቶ ነው ያለው።"ይላሉ። በተጚማሪም ፋብሪካው ዚማኅበሚሰቡ ዚጀርባ አጥንት እንደሆነ ዚሚናገሩት አቶ ሚታ "ዚአካባቢው ኅብሚተሰብ እስኚ ልጆቹ ዚሚተዳደሚው በፋብሪካው ነው።" ብለዋል። አቶ ሚታ አክለውም ፋብሪካው ዹቮክኒክ ቜግር ሲያጋጥመው ለሰዓታት ሊያቆም እንደሚቜልና አስፈላጊው ጥገና ተደርጎለት እንደሚቀጥል ገልጞውፀ ይህ ግን ማቆም ዚሚባል ሳይሆን ውስብስብ ማሜኖቜ ባሉት ፋብሪካ ውስጥ ዹተለመደ ሁኔታ እንደሆነ ያስሚዳሉ። በሰባት ቀናት ውስጥ ፋብሪካው ምን ያህል ገንዘብ ወይም ምርት አጣ? ዹሚል ጥያቄ ቢቢሲ ለአቶ ሚታ ያቀሚበላ቞ው ሲሆን ፋብሪካው በአማካኝ በጥሩ ዚማምሚቻው ወቅት በቀን 10 ሺህ ኩንታል እንደሚያመርት ጠቅሰው ሆኖም ፋብሪካው ምን ያህል እንዳጣ ዹተገመገመ ጉዳይ አለመኖሩን ተናግሚዋል። በስኳር አቅርቊትስ ላይ መጉላላት ፈጥሮ ይሆን? በሚል ለቀሹበላቾው ጥያቄም "አገሪቱ መተሃራ፣ ወንጂና ጥገናውን በቅርቡ ጚርሶ ወደ ሥራ ዚገባው በአካባቢው ዹሚገኘው አርጆ ዎዎሳ ፋብሪካን ጚምሮ ሌሎቜ ፋብሪካዎቜ በመኖራ቞ው ዚአንድ ፋብሪካ ሰባት ቀን ማቆም በስኳር ሥርጭት ላይ ምንም አይነት ተፅእኖ አይኖሹውም " ሲሉ ምላሜ ሰጥተዋል። ፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ በኊሮሚያ ክልል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አባይ ጮመን ወሚዳ በፊንጫአ ሾለቆ ውስጥ ልዩ ስሙ አገምሳ ተብሎ በሚጠራ ቊታ ላይ ይገኛል። ኚኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሜን ዹተገኘው መሹጃ እንደሚያመላክተው ፋብሪካው በዓመት 270 ሺህ ቶን ስኳር ዚማምሚት አቅም አለው። ፋብሪካው ኚስኳር ምርቱ በተጚማሪ ኢታኖል በማምሚት ኚቀንዚል ጋር ተደባልቆ ለተሞኚርካሪዎቜ በነዳጅነት እንዲውል ያደርጋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-60413928
amh
business
ዚአሜሪካን ዚአቪዬሜን ንግድ ሚስጥርን ሰርቋል ዚተባለው ቻይናዊ ተቀጣ
ቻይናዊው ዚስለላ ሠራተኛ ዚአቪዬሜን ኩባንያዎቜን ምስጢር ለመስሚቅ አሲሯል በሚል በአሜሪካ ፍርድ ቀት ጥፋተኛ መባሉን ዚአሜሪካ ዚፍትህ መሥሪያ ቀት አስታወቀ። ዡ ያንጁን ዚተባለው ይህ ግለሰብ ኚኢኮኖሚ ስለላ እና ኚንግድ ምስጢር ስርቆቶቜ ጋር በያያዘ በቀሚቡበት አምስት ክሶቜ ጥፋተኛ ዚተባለ ሲሆን ዹ60 ዓመት እስራት እና ኹ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ቅጣት ይጠብቀዋል። ዡ ለመጀመሪያ ጊዜ በቁጥጥር ስር ዹዋለው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2018 ቀልጂዚም ውስጥ ሲሆን ምናልባትም ለአሜሪካ ተላልፎ ዹተሰጠ ዚመጀመሪያው ቻይናዊ ነው ተብሏል። ዚቻይና ባለስልጣናት ትናንት [አርብ] ስለተላለፈው ውሳኔ ዚሰጡት አስተያዚት ባይኖርም ቻይና ቀደም ብላ ክሱን መሰሹተ ቢስ ስትል ውድቅ አድርጋው ነበር። ዚአሜሪካ ዚፍትህ መሥሪያ ቀት ባወጣው መግለጫ መሰሚት ዡ በቻይና ደኅንነት ሚኒስ቎ር ውስጥ በተለያዩ ዘርፎቜ ላይ ዚሚሰራ ዚስለላ ባለሙያ ነው። ቻይናዊው ሰላይ ኚአውሮፓውያኑ 2013 ጀምሮ በአሜሪካ እንዲሁም በሌላ አገራት ውስጥ ዹሚገኙ በርካታ ኩባንያዎቜ ውስጥ ዚሚሰሩ ሠራተኞቜን ኢላማ አድርጎ ሲንቀሳቀስ ነበር ተብሏል። ቻይናዊው እንደ አውሮፓውያኑ በ2017 ዚአንድ አቪዬሜን ሠራተኛን ዹጉዞ ወጪ በመሾፈን እና አበል በመክፈል፣ ወደ ቻይና ተጉዞ በዩኒቚርሲቲ ውስጥ ገለጻ እንዲደሚግ እስኚመጋበዝ ደርሶ ነበር። ይህ በሆነ በዓመቱ ባለሙያውን ዚአንድ ንድፍ ሂደትን ዹተመለኹተ መሹጃን እንዲሰጠው ዡ ጠይቋል ተብሏል። ታዲያ ኚኀፍ ቢ አይ ጋር ሲሰራ ዹነበሹው ባለሙያው ምስጢራዊ ዹሆነ መሹጃ ዹሚል ባለ ሁለት ገጜ ሰነድ ለዡ በኢሜይል ልኳል። በመቀጠል ዡ ለባለሙያው ሥራ በሚጠቀምበት ኮምፒውተሩ ላይ ዹፋይል ቅጂ እንዲልክለት ጥያቄ ያቀርባል። በተጚማሪም በቀልጂዚም ውስጥ ባለሙያውን ለማግኘት ሞክሯል። ሆኖም በዚህ ሙኚራው ቻይናዊው በቁጥጥር ስር ውሏል። ዚኀፍ ቢ አይ ሚዳት ዳይሬክተር አለን ኮህለር "ዚቻይናን እውነተኛ ፍላጎት ለሚጠራጠሩ ይህ ዚማንቂያ ደወል ሊሆን ይገባል" ብለዋል። "ዚአሜሪካን ቮክኖሎጂ እዚዘሚፉ ኢኮኖሚያ቞ውን እና ወታደራዊ ኃይላቾውን ለማጠናኹር እዚተጠቀሙበት ነው" ሲሉም አክለዋል። ይህ ክስ ዹተሰማው በሁለቱ አገራት መካኚል ውጥሚት በነገሰበት ወቅት ነው። ቻይና በቅርቡ አዲስ ዚሃይፐርሶኒክ ሚሳኀልን ስትሞክር ዚአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ታይዋንን ኹማንኛውም ዚቻይና ወታደራዊ ወሚራ ለመጠበቅ ቃል ገብተዋል። እንደ ሲኀንኀን ዘገባ ኹሆነ ዚሲአይኀ ዳይሬክተር ቢል በርንስ ቻይናን ለአሜሪካ ትልቁ ዹቮክኖሎጂ ስጋት መሆኗን ገልጿል። ባለፈው ወር ዚስለላ ድርጅቱ ቻይና ላይ ዚሚያደርገውን ዚስለላ ጥሚት እንደሚያሳድግ ገልጿል።
https://www.bbc.com/amharic/news-59188531
amh
business
ዚናይጄሪያ አዹር መንገዶቜ በአውሮፕላን ነዳጅ ጭማሪ ምክንያት ዹሀገር ውስጥ በሚራዎቜን ሊያቆሙ ነው
ዚናይጄሪያ አዹር መንገዶቜ ዚአውሮፕላን ነዳጅ ጭማሮን በመቃወም ኚመጪው ሰኞ ጀምሮ ዹሃገር ውስጥ በሚራዎቜን ሊያቆሙ ነው። በተያዘው አመት ብቻ አራት እጥፍ ገደማ መጚመሩን ያስታወቀው ዚናይጄሪያ አዹር መንገድ ኊፕሬተሮቜ (ኀኊኀን) ይህንም ሁኔታ መቋቋም አልተቻለም ብሏል። "በአለም ላይ ያለ ዚትኛውም አዹር መንገድ ቢሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲህ አይነት አስደንጋጭ አጹማመርን ሊቋቋም አይቜልም። ኹዚህ ማገገም አይቻልም" ብሏል። ለጭማሬው ዋነኛ ምክንያት ዹሆነው ሩሲያ በዚካቲት ወር ዩክሬንን መውሚሯ ነው። ዚናይጄሪያን ዘጠኝ ዹሃገር ውስጥ አዹር መንገዶቜን ዹሚወክለው ዚናይጄሪያ አዹር መንገድ ኊፕሬተሮቜ (ኀኊኀን) አዹር መንገዶቹ ባለፉት አራት ወራት ውስጥ አገልግሎታ቞ውን እዚሰጡ ዚነበሩት በድጎማ ነበር ብሏል። ኚመጋቢት ወር ጀምሮ በርካታ ዚበሚራዎቜ መሰሹዝ እንዲሁም መዘግዚቶቜ ዚነበሩ ሲሆን ይህም አብዛኛውን ጊዜ ኚአውሮፕላን ነዳጅ እጥሚት ጋር በተያያዘ እንደሆነ ሲገለጜ መቆዚቱ ይታወሳል። ዚአውሮፕላን ቲኬቶቜ ዋጋም በአንዳንድ አዹር መንገዶቜ በቅርብ ሳምንታት ውስጥ በሶስት እጥፍ ጚምሯል። በናይጄሪያ ያሉ መንገደኞቜ በኹፍተኛ ሁኔታ እያሜቆለቆለ በመጣው ዚሃገሪቱ መገበያያ ገንዘብ ናይራ ነው ቲኬት ዚሚገዙት። ነገር ግን ነዳጅ አቅራቢዎቜ ዚሚኚፈሉት በአሜሪካን ዶላር ነው። ናይጄሪያ ኚአፍሪካ ቀዳሚዋ ዚነዳጅ አምራቜ ብትሆንም ኹሞላ ጎደል ሁሉንም ዚአውሮፕላን ነዳጇን ኹውጭ ታስገባለቜ። አኊኀን ለመንግስት፣ ለፓርላማ አባላት፣ ለመንግሥታዊው ዚነዳጅ ኩባንያ እና ነዳጅ ሻጮቜን ለሚወክለው ማኅበር ዚነዳጁን ዋጋ ዝቅ ለማድሚግ እርምጃ መወሰድ እንዳለበት አስሚድቻለሁ ብሏል። ዹዋጋ ጭማሮው በመንገደኞቜ ላይ ጫና መፍጠር ዚለበትም ሲል ዚሚኚራኚሚው ተቋሙ "ቀድሞውንም ብዙ ቜግሮቜ እያጋጠሟ቞ው በመሆኑ" ዹዋጋው ጫና እነሱ ጫንቃ ላይ ማሹፍ ዚለበትም ብሏል። ስለታቀደው ዚስራ ማቆም አድማ መንግሥት እስካሁን ዹሰጠው መግለጫ ዚለም።
https://www.bbc.com/amharic/news-61369465
amh
business
ዚዓለማቜን ለኑሮ ምቹ ዹሆኑ 10 ኚተሞቜ ይፋ ሆኑ
በዓለማቜን ለኑሮ ምቹ ዹሆኑ 10 ኚተሞቜ ይፋ ሆኑ። ኚተሞቹ ምርጥ ዚተባሉት ለኑሮ ባላ቞ው ምቹነት መሠሚት ነው። አውሮፓዊቷ አገር ዚኊስትሪያ ዋና ኹተማ ቪዬና ቀዳሚዋ ዚዓለማቜን ምቹ ኹተማ ተብላለቜ። በተኚታይነት ደግሞ ዹዮንማርክ ኮፐን ሃገን እና ዚስዊትዘርላንድ ዙሪክ ኚተሞቜ ሁለተኛ እና ሊስተኛ ደሹጃን ይዘዋል። ዚካናዳ ኹተማ ዚሆኑት ካልጋሪ እና ቫንኩቚር ደግሞ በአራተኝነት በቀጣይ ደሹጃ ላይ ዚተቀመጡ ሲሆንፀ ዚስዊትዘላንዷ ጄኔቫ፣ ዹጀርመኗ ፍራንክፈርት፣ ዚካናዳዋ ቶሮንቶ፣ ዚኔዘርላንድስ አምስተርዳም፣ ዹጃፓን ኊሳካ እና ዚአውስትራሊያዋ ሜልበርን ቀዳሚዎቹን አስር ደሚጃዎቜ ለመያዝ በቅተዋል። ይህንን ደሹጃ ይፋ ያደሚገው ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት እንደሚለው ኹሆነ ኚተሞቜ ለኑሮ ያላ቞ው ምቹነት ቢጚምርም ዓለም አቀፉ አማካይ ግን አሁንም ዝቅተኛ ነው ብሏል። ለኑሮ ምቹነት ኚታዩት ጉዳዮቜ አንዱ ዚኮሮናቫይሚስ ስርጭት ተጜዕኖ መሆኑን ተጠቁሟል። ዚዩክሬን ጊርነት ደግሞ ኪዬቭ ኚጥናቱ ውጪ እንድትሆን ሲያስገድዳት፣ በሩሲያዎቹ ሞስኮ እና ሎንት ፒተርስበርግ ውጀት ላይም ተጜዕኖ አሳድሯል። በዚሁ ጊርነት ምክንያት ዚምሥራቅ አውሮፓ ኚተሞቜ ደሹጃም ዝቅ ብሏል። ዚምዕራብ አውሮፓ እና ዚካናዳ ኚተሞቜ ደሹጃውን በመምራት ቀዳሚ ሆነዋል። ደማስቆ፣ ትሪፖሊ እና ሌጎስ ደግሞ ኚማኅበራዊ አለመሚጋጋት፣ ሜብር እና ግጭት ጋር ተተያይዞ በደሹጃው መጚሚሻ ላይ ለመገኘት ተገደዋል። በዘንድሮው ጥናት 33 አዳዲስ ኚተሞቜ ተካተዋል። በዝቅተኛ ደሹጃ ላይ ያሉ ኚተሞቜ ብዙ መሻሻል አላሳዩም ተብሏል። ዚሶሪያዋ ደማስቆ በደሹጃው ዚመጚሚሻው ስፍራን ይዛለቜ። ቎ህራን፣ ዱዋላ፣ ሃራሬ፣ ዳካ፣ ፖርት ሞርስባይ፣ ካራቺ፣ አልጀርስ፣ ትሪፖሊ፣ ሌጎስ እና ደማስቆ ናቾው ዚመጚሚሻዎቹን አስር ደሚጃዎቜ ዚያዙት። ለኑሮ ባላ቞ው ምቹነት መሻሻል ያሳዩ ኚተሞቜም ታይተተዋል። እነዚህ ኚተሞቜ በአብዛኛው በምዕራብ አውሮፓ ዹሚገኙ ዚጀርመን፣ ዚዩናይትድ ኪንግደም እና ዚፈሚንሳይ ኚተሞቜ ና቞ው። ፍራንክፈርት ካለፈው ዓመት 32 ደሚጃዎቜን በማሻሻል ሰባተኛ ደሹጃ ላይ ለመቀመጥ በቅታለቜ። ሃምቡርግ ደግሞ ኹ31ኛ ወደ 16ኛ ተመንድጋለቜ። ዚኒውዚላንድ እና ዚአውስታራሊያ ኚተሞቜ ደግሞ ደሹጃው ላይ ማሜቆልቆል አስመዝግበዋል። በዚህም ዌሊንግተን እና ኊክላንድ 46 እና 33 ደሚጃዎቜን ለመውሚድ ተገደዋል። ድርጅቱ ይህን ደሹጃ ለማውጣት ዚኚተሞቹን መሚጋጋት፣ ዚጀና ዘርፍ፣ ባህል እና አካባቢ፣ ትምህርት እና መሠሹተ ልማት ኚግምት ያስገባል። ይህንን ደሹጃ ይፋ ያደሚገው ተቋም ዚዩክሬን ጊርነት እና ኮቪድ በሚቀጥለው ዓመት በሚኖሹው ዚኚተሞቜ ለኑሮ ምቹነት  ደሹጃ ላይ ተጜዕኖ ይኖራ቞ዋል ብለዋል። ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት ላለፉት 70 ዓመታት ኢኮኖሚያዊ ትንታኔዎቜ በመስጠት ዚሚታወቀው ሲሆን ዹዘ ኢኮኖሚስት ጋዜጣ እህት ኩባንያ ነው።
https://www.bbc.com/amharic/articles/clw4zjvpljjo
amh
business
ዚትኞቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎቜ በሩሲያ ያላ቞ውን ስራ አቋሚጡ?
ሰላሳ ዓመት ወደኋላ! ኚሰላሳ ዓመታት በፊት በሶቭዚት ኅብሚት ኮምዩኒዝም ሲንኮታኮትና ዚሩሲያ በሮቜ ለኢንቚስትመንት እና ንግድ ሲኚፈቱ ይህንን ዕድል ለመጠቀም ዚምዕራባውያን ኩባንያዎቜን ዹቀደመ አልነበሚም። ያኔ እንደ ኮካ ኮላ እና ማክዶናልድስ ያሉ ታዋቂ ኩባንያዎቜ በሩሲያ ስራ ሲጀምሮ ዚሩሲያ አዲሱ ጊዜ መጣ እስኚመባል ደርሶ ነበር። ዚተለያዩ ምርት አቅራቢዎቜ፣ ማዕድን አውጪዎቜ፣ ዹህግ አማካሪዎቜና በርካታ ድርጅቶቜ ቀስ በቀስ በሩሲያ ተስፋፉ። ሩሲያውያንም በሌዊ ጂንስ መዘነጥ እና ዚምዕራብያውያኑ ቅንጡ ምርቶቜን መጠቀም ጀመሩ። ያ በር ኹተኹፈተ ሰላሳ ዓመታት ተቆጠሚ። ኹዚህ ሁሉ ዓመት በኋላ አዲስ ነገር ተፈጠሚ። ሩሲያ ዩክሬንን ወሚሚቜ። ይህንንም ተኚትሎ በርካታ ዚምዕራባውያኑ ክባንያዎቜ በሩሲያ ያለውን ስራ቞ውን እያቆሚጡ ነው። አፕል፣ ላንድ ሮቚር፣ ኀቜ ኀንድ ኀም እና ቡርቀሪን ጚምሮ በርካታ ኩባንያዎቜ በሩሲያ ያላ቞ውን ዚንግድ እንቅስቃሎ ማቋሚጣ቞ውን አስታውቀዋል። ለመሆኑ ዚትኞቹ ኩብንያዎቜ ስራ቞ውን እያቆሙ ነው? ሌሎቹስ ለምን ዝምታን መሚጡ? ዚነዳጅ ኩባንያዎቜ ቢፒ ዚተባለው በነዳጅ ዘርፍ ዚሚሰራ ኩባንያ በዩክሬን ግጭት እንደተቀቀሰ ነበር በሩሲያ ያለውን ስራ እንዲያቆም ጫና ዚተደሚገበት።ኩባንያው በሩሲያው ግዙፉ ዚነዳጅ አምራቜና አቅራቢ ኩባንያ ሮስኔፍት ውስጥ ትልቅ ድርሻ ቢኖሚውም በቀናት ውስጥ ስራው እንደሚቋሚጥ አስታውቋል። ሌል፣ኀክሶንሞቢል እና ኢኩዊኖር ዚተሰኙት በነዳጅ ዘርፍ ዚሚሰሩ ኩባንያዎቜም ኚባለአክሲዮኖቜ፣ ኚመንግሥታት እና ኚዜጎቜ በደሚሰባ቞ው ግፊት በሩስያ ያላ቞ውን ኢንቚስትመንቶቜን እናቆማለን ብለዋል። እነዚያ ዚነዳጅ አምራቜ እና አቅራቢ ኩባንያዎቜ ቀላል ዋጋ ዚሚሰጣ቞ው አይደሉም። ዚቢፒ ዚቅርብ ጊዜ ትርፉ በዘርፉ በአምስተኛ ደሹጃ እንዲቀመጥ አድርጎታል። ሌል ኚሩሲያው ግዝዙፍ ዚነዳጅ ተቋም ጋዝፕሮም ጋር ያለውን ግንኙነት ለማቋሚጥ እስኚ 3 ቢሊዮን ዶላር ሊኚስር እንደሚቜል ተገምቷል። በሌላ በኩል ቶታል ኢነርጂ በሩሲያ ውስጥ አዳዲስ ፕሮጀክቶቜን በገንዘብ እንደማይደግፍ ተናግሯል። ነገር ግን ኚተወዳዳሪዎቹ በተጻራሪ ኚነባር ኢንቚስትመንቶቹ ዚመውጣት እቅድ ዚለውም። ዹመዝናኛ ዘርፍ ዹዋርነር ብሮስን አዲሱ 'ብሎክበስተር ዘ ባትማን' በሩሲያ እንደማይታይ ተሚጋግጧል። ይህ በሀገሪቱ ለሚገኙ ዹፊልም አፍቃሪዎቜ መልካም ዜና አይመስልም። ፊልም አምራቜ ኩባንያው በዚሁ በሰሞነኛ ጉዳይ ምክንያት በሀገሪቱ ውስጥ አዳዲስ ፊልሞቜን ላለመልቀቅ ወስኗል። ኔትፍሊክስ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉትን ሁሉንም "ቀጣይ ፕሮጀክቶቜን" ማገዱን ያስታወቀ ሲሆን " ወቅታዊ ሁኔታዎቜን ተፅእኖ" እዚገመገመገምኩ ነው ብሏል። ሁሉም ኩባንያዎቜ ኚውሳኔ ላይ ዚደሚሱት ሩሲያ ላይ በተጣሉ ማዕቀቊቜ ምክንያት አላደሚጉም። ይልቅስ ለውሳኔያ቞ው መነሻ ያደሚጉት በዩክሬን ባለው "ሰብአዊ ቀውስ" ነው። ነገር ግን ውሳኔው ለሩሲያ ዚሚያስተላልፈው ሌላ መልእክት ነው። ይህ መሆኑ ዚሩሲያውያንን ዹመገለል እንደሚጚምር ተገምቷል። ዹቮክኖሎጂ ኩባንያዎቜ አፕል በሩሲያ ውስጥ ሁሉንም ዚምርት ሜያጭ ያቆመ ሲሆን እንደ ፔይ እና አፕል ማፕ ካርታ ያሉ ሌሎቜ አገልግሎቶቜን ላይ ገደብ አድርጓል። በተጚማሪም በሀገሪቱ ዹሚገኙ ዚሜያጭ ሱቆቹን ተዘግተዋል። በሞስኮ ላለፉት 24 ዓመታት ለሰራው አፕል ውሳኔው ራሱንም ዚሚጎዳው እንደሆነ ይታመናል። በሌላ በኩል አንዳንድ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያዎቜ ኚሃሰት መሹጃ ጋር በተያያዘ በሩሲያ ዹሚገኙ አገልግሎቶቜ እዚተገደበባ቞ው ነው። ለምሳሌ ፌስቡክ በመንግሥት ቁጥጥር ስር ያሉ ዹዜና ድርጅቶቜን ይዘት ማሚጋገጥ እና ላማጋራት ፈቃደኛ አልሆነም ማለቱን ተኚትሎ ሩሲያ ፌስቡክን ገድባለቜ። ምርት አቅራቢ ድርጅቶቜ ግዙፉ ዚስዊድን ፋሜን ኩባንያ ኀቜ ኀንድ ኀም በሩሲያ ስራውን ያቆመ ግዙፍ ምርት አቅራቢ ድርጅት ሆኗል። ይህንንም ተኚትሎ በርካታ ኩባንያዎቜ ይህንን ፈለግ ሊኹተሉ እንደሚቜል ተዘግቧል። ኀቜ ኀንድ ኀም በዩክሬን ውስጥ " አሳዛኝ ሁኔታዎቜን" ጠቅሶ ስራውን ሲያቆም ናይኪን ጚምሮ ዚተለያዩ ዓለም አቀፍ ብራንዶቜ በአሁኑ በሩሲያ ላሉ ደንበኞቜ ምርት ለማቅሚብ ዋስትና እንደማይሰጡ ተናግሚዋል። በሞስኮ ታዋቂው አደባባይ አቅራቢያ ግዙፍ መሞጫ ያለው 'ቡርቀሪ' ዹተሰኘው ብራንድ "በሩሲያ ውስጥ ትዕዛዞቜን ላማድሚስ አስ቞ጋሪ ስለሆነ" ሁሉንም ጭነት አቁሜያለሁ ብሏል። ሩሲያ በ2021 አምስተኛዋ ትልቅ ዚአውሮፓ ዚቜርቻሮ ምርቶቜ ገበያ ዚነበሚቜ ሲሆን 337 ቢሊዮን ዚእንግሊዝ ፓውንድ ዚሚገመት ነው። አንዳንድ ብራንዶቜ ደግሞ ኹተወሰነ ወደ ንግዱ ዚመመለስ እድል ካለ በሚል ሁሉንም መንገድ ዝግ አላደሚጉም። ለዚያም ይመስላል በርካታ ድርጅቶቜ ሜያጫ቞ውን ሙሉ በሙሉ ኹማቆም ይልቅ ጉዳዩን "እያጀንን ነው" ወይም "ስራ በማቆም ላይ ነን" እያሉ ዚሚኙት ዹሚል አስተያዚትም ዚቀሚበው። ተሜኚርካሪ አምራ቟ቜ በሩሲያ ወሚራ ምክንያት ወደ ሀገሪቱ ተሜኚርካሪዎቜ ካቆሙት አምራ቟ቜ መካኚል 'ጃጓር ላንድሮቚር'፣ 'ጄኔራል ሞተርስ'፣ 'አስቶን ማርቲን' እና 'ሮልስ ሮይስ' ዚተባሉት እውቅ ኩባንያዎቜ ይገኝበታል። በተጫማሪም ዚግንባታ መሣሪያዎቜ አምራቹ 'ጄሲቢ' በሩሲያሁሉንም ሥራዎቜ አቁሟል። አሁን መኪኖቜን ወደ ሩሲያ ማጓጓዝ ኚባድ ሊሆን ይቜላል። ምክንያቱም ዹዓለም ሁለቱ ትላልቅ ዚባህር ማጓጓዣ ባለቀት ኩባንያዎቜ 'ኀም ኀስ ሲ' እና 'ሜሪስክ ' ኚምግብ፣ ህክምና ቁሳቁሶቜ እና ዚሰብአዊ አቅርቊት በስተቀር ሌላ ምርት ለሩሲያ አንጭንም ብለዋል። እንደ ቮልስዋገን እና ቢኀምደብሊው ያሉ አንዳንድ ዚመኪና አምራ቟ቜ በአንዳንድ ዚአውሮፓ ሀገራት ዹሚገኙ ፋብሪካዎቜ ላይ ኚዩክሬን ዚሚቀሚቡ ዚመኪና ክፍሎቜ ባለመኖራ቞ው ምርታ቞ውን ለተወሰ ጊዜ ለማቆም ተገደው ነበር። ዹህግ አማካሪ ድርጅቶቜ ኚኮሚኒዝም መውደም በኋላ በሩሲያ ስራ ኚጀመሩ ቀዳሚ ዘርፎቜ መካኚል ትላልቅ አማካሪዎቜ እና ዹሕግ ኩባንያዎቜ ይገኙበታል። ሩሲያ በዩክሬን ላይ ዚፈፀመቜውን ወሚራ ተኚትሎ አብዛኞቹ ዝምታን መርጠው ዚቆዩ ቢሆንም መሰሚቱ ዩኬ ዹሆነው 'ኬፒኀምጂ' ዹተሰኘው አማካሪ ኩባንያ ሃላፊ ጆናታን ሆልት ኚማዕቀቡ ጋር በሚናበብ መልኩ ኚደንበኞቻ቞ውን ጋር ያለንን ግንኙነት እዚገመገምን ነው ብለዋል። ይህ ማለት በዩናይትድ ኪንግደም እና በመላው አለም ያሉ አንዳንድ ግንኙነቶቜን ማቋሚጥ ሊሆን እንደሚቜልም ተናግሚዋል። ሌላው 'ኢዋይ' ዹተሰኘው አማካሪ ድርጅት ማዕቀቡን እንደሚያኚብር ዹገለጾ ቢሆንም በሩሲያ ኹሚገኙ ኹማንኛቾውም ደንበኞቜ ጋር ያለውን ግንኙነት አቋርጣለው ወይም አላቋርጥም ብሎ እርግጡን አልተናገሚም። ሌሎቜ ዹህግ እና አማካሪ ድርጅቶቜ ዚደንበኞቻ቞ውን ኚሩስያ ጋር ያላ቞ውን ግንኙነት እናጀናለን ብለዋል። ዹ'ማክኪንሎ' አማካሪ ድርጅት ስራ አስፈፃሚ ኩባንያው "ኚእንግዲህ በሩሲያ ውስጥ ማንኛውንም ዚመንግስት አካል እንደማያገለግል" በማህበራዊ ሚዲያ ጜሁፍ ላይ አጋርቷል። ማን ቀሹ? ሩሲያ በማዕቀብ ጎርፍ በምትጥለቀለቅበት በዚህ ሰዓት ተጚማሪ እውቅ ብራንዶቜ በሩሲያ ስራ እንዲቆሙ ጥሪ እዚቀሚበላ቞ው ነው። ሆኖም ለአንዳንድ ኩባንያዎቜ ይህንን ማድሚግ በጣም ኚባድ ነው። በሚቀጥሉት ቀናት እና ሳምንታት ውስጥ ጫናው እዚበሚታ ቢሄድም በሩሲያ ስራ ማቆም ለነዚህ ድርጅቶቜ አስ቞ጋሪ ይሆናል። ዚምዕራባውያን ማዕቀቊቜ ለመቋቋም ዚሩስያ መንግሥት ዚሩስያ ንብሚቶቜን ሜያጭ አግዷል። ይህ በመሆኑ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በሩሲያ ውስጥ ስራ ዚጀመሩ ክባንያዎቜ ንብሚት ሜጊ ሀገር ጥሎ ዚመውጣት መንገዱ ተዝግቶባ቞ዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-60598954
amh
business
ሕይወት ኚመሠሚታዊ አቅርቊቶቜ ውጪ በሆነቜው ትግራይ
ኑሮውን ሱዳን ካርቱም ያደሚገው እና ስሙ እንዳይጠቀስ ዹጠዹቀ ግለሰብ በቅርቡ መቀለ ለሚገኙ ቀተሰቊቹ ዚዕለታዊ ፍጆታ መግዣ ገንዘብ መላኩን ይናገራል። ዚባንክ አገልግሎት ኹተቋሹጠ ወራት ወደ ተቆጠሚባት መቀለ 40 ሺህ ብር መላክ ማሰቡን ያወቁ እና ኹክልሉ ውጪ ዚሚኖሩ ግለሰቊቜ፣ ገንዘቡን ለቀተሰቊቹ ለማድሚስ 20 ሺህ 800 ብር እንዲኚፍላ቞ው እንደጠዚቁት ለቢቢሲ ገልጿል። ምንም እንኳ በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ውስጥ በሕጋዊነት ዚሚሰራ አንድም ዚፋይናንስ ተቋም ባይኖርም፣ መቀለ ለሚገኙ ቀተሰቊቹ ገንዘቡን እናደርሳለን ላሉት ግለሰቊቜ ዹተጠዹቀውን ክፍያ በባንክ ሂሳባ቞ው ገቢ ማድሚጉን ገልጿል። ይህ ግለሰብ አክሎም ይህንን እድል ያገኙ ሌሎቜ ሰዎቜም በተመሳሳይ መንገድ መላክ ያሰቡትን ገንዘብ ግማሜ ያህል ክፍያ ለአቀባባዮቜ እዚኚፈሉ አገልግሎቱን እንደሚያገኙ ያስሚዳል። ባለፈው ሰኔ ወር ላይ ዚትግራይ አማፂያን ዹመቀለ ኹተማን እና አብዛኛውን ዚትግራይ አካባቢ ኚተቆጣጠሩ በኋላ ትግራይ ለአስር ወራት ያህል እቀባ ላይ ትገኛለቜ። ባለፈው ዓመት ጥቅምት ወር መጚሚሻ ላይ በጀመሹው በዚህ ጊርነት ተቋርጠው ዚነበሩ መሠሚታዊ አገልግሎቶቜ ለተወሰኑ ወራቶቜ አገልግሎት መስጠት ጀምሹው ዚነበሩ ቢሆንም፣ ዚፌደራል መንግሥቱ መቀለን ለቅቆ መውጣቱን ተኚትሎ ዳግም ሙሉ በሙሉ ቆመዋዋል። 'ዚተራበቜ ኹተማ' ዹመቀለ ኹተማ ነዋሪ ዚሆኑት አቶ ገብራይ ገዛኾኝ ኚመስኚሚም ወር ጀምሮ 'ራሳቜን ለራሳቜን' [ባዕልና ንባዕልና]' በተሰኘ ፕሮጀክት ዘወትር ማለዳ ዳቊ እና ሻይ ይቀርብላ቞ዋል። እኚህ ዚዕለት እንጀራ቞ውን ኹበጎ አድራጎት ድርጅት ዚሚያገኙ አዛውንት ቢቢሲ ቃለመጠይቅ ሲያደርግላ቞ው ቜግራ቞ውን እና ብስጭታ቞ውን ዚገለፁት በዘፈን ነበር። " ድሮ ኪሮስ አለማዹሁ . . . ወላጅ ኹልጁ ተለያዚፀ በኹፋ ሚሃብ ሬሳ መሰለ. . . በአፈሙዝ ሰላሙን አጣ. . . ብሎ ነበር። ዛሬም ይህ ተደገመ" ካሉ በኋላ "ዚሚላስ ዚሚቀመስ አጥተን ዚልጆቻቜን ድምጜ ርቆብን እዚኖርን ነው" ሲሉ በትግራይ ክልል ርዕሰ መዲና ሕይወት እዚኚፋ መሄዱን ይናገራሉ። ኚጊርነቱ በፊት ዹመቀለ ኹተማ ኚግማሜ ሚሊዮን በላይ ነዋሪ ዚነበራት ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ግን ኚተለያዩ ዹክልሉ ኚተሞቜ እና ዹገጠር ቀበሌዎቜ በመጡ ተፈናቃዮቜ ተጚናንቃለቜ። በክልሉ ጊርነት ኹተቀሰቀሰ በኋላ ኚሌሎቜ ዹክልሉ አካባቢዎቜ ዹተፈናቀሉ በመቶ ሺህ ዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ በዚትምህርት ቀቱ፣ ዚስብሰባ አዳራሟቜ፣ በአብያተ ክርስትያናት ውስጥ ተጠልለው በገንዘብ እና በዚፍጆታ እቃዎቜ አቅርቊት እጥሚት ለኹፋ ቜግር ተጋልጠው ይገኛሉ። አቶ ገብራይ "ሚሃቡ ሁሉም ላይ ደርሷልፀ ትልቁም ሆነ ትንሹ ተርቩ ግራ ገብቶት ይገኛል። ገንዘብ፣ መጓጓዣ ዚለም። በቀን አንዮ በልተን 'ያልፋል' እያልን እንውላለን" ሲሉ ዚሚገኙበትን ሁኔታ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። በዓለም ሰላም ፋውንዎሜን ውስጥ ተመራማሪ ዚሆኑት ሙሉጌታ ገብሚ ሕይወት፣ በዚካቲት ወር አጋማሜ ላይ በሊስት ክፍል ባሳተሙት ጥናት ውስጥ "ያለውን ተጜዕኖ አልፋቜሁ መግባት ዚምትቜሉ ኹሆነ ወደ መቀለ እንድትመጡ እንጋብዛቜኋለንፀ እንደገባቜሁ መጀመሪያ ዚምታይዋት ዚተራበቜ ኹተማን ነው" በማለት ያለውን ቜግር ገልፀውታል። ኚአምስት ዓመት በፊት ጧሪ እና ተንኚባካቢ ዹሌላቾው አሚጋውያን ለማገዝ ዹተቋቋመው ኚራዲዮን ዚአሚጋውያን እርዳታ ድርጅት በአሁኑ ወቅት መቀለ ኹተማ ውስጥ ለስደተኛ ሕጻናት እና እናቶቜ ምግብ ድጋፍ እዚሰጠ ይገኛል። በኹተማዋ ውስጥ ኹቀን ወደ ቀን ለምጜዋት እጃ቞ውን ዹሚዘሹጉ ሰዎቜ ቁጥር እዚጚመሚ እንዳለ ዚማኅበሩ ሥራ አስኪያጅ አማኑዔል ገብሚ ጻድቃን ይገልጻል። በጊርነቱ ምክንያት ኚተለያዩ አካባቢዎቜ ተፈናቅለው ወደ ኹተማዋ ዚመጡ እና በርኚት ያሉ ተንኚባካቢ ወይንም ደጋፊ ዹሌላቾው ሕጻናት ጎዳና ላይ ወድቀው እንደሚገኙ ተናግሯል። "ሁሉም ነገር ተዘግቶ ምግብ እና መድኃኒት በሌለበት ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው። ገጠር እና ሌሎቜ አካባቢዎቜን ይቅር እና መቀለን ብቻ ብንመለኚት ዹኹፋ ቜግር ውስጥ ናት። ሐብታም ዚምትለው ደሃ ሆኗልፀ ደሃ ዹነበሹው ደግሞ ኚድህነት በታቜ ወርዶ ኚባድ ቜግር ውስጥ ይገኛል" ይላል። ኚመስኚሚም 07/2014 ዓ.ም ጀምሮ ዚቁርስ ድጋፍ እዚሰጠ ዹሚገኘው ይህ ማኅበር በአሁኑ ጊዜ ኹ300 በላይ ተሚጂዎቜ እንዳሉት አማኑኀል ይገልጻል። መጀመሪያ አካባቢ ሕዝቡ እርስ በእርሱ ይተጋገዝ ዹነበሹ ቢሆንም እጁ ላይ ዹነበሹውን እዚጚሚሰ በመምጣቱ ይህ መደጋገፍ መቀነሱን አክሎ ተናግሯል። "ኹተማዋ ውስጥ ኚእንባው ጋር ዚሚታገል፣ በጎዳናዎቜ ላይ ብቻውን እያወራ ዚሚሄድ፣ እጆቹን ዘርግቶ ዚሚለምን፣ በርካታ ሰው ማዚት እዚተለመደ ነው" ሲል አሁን በኹተማዋ ያለውን ሕይወት ለቢቢሲ ገልጿል። "እስካሁን ሕዝቡ ተስፋ አልቆሹጠም" ዹሚለው አማኑዔል፣ ዹመቀለ ነዋሪ ካለው ላይ እዚሰጣ቞ው ለኹፋ ቜግር ዚተጋለጡትን እንደሚደግፉ ይናገራል። ትግራይ ውስጥ ኚተለያዩ መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶቜ ጋር ዚሚሰሩና ስማ቞ው እንዲጠቀስ ያልፈሉ ግለሰብ ለቢቢሲ በሰጡት አስተያዚት ኹሰኔ 21/2013 ዓ.ም በኋላ ትግራይ ውስጥ ያለው ሁኔታ "በጣም ዚሚሰቀጥጥ" እንደሆነ በተለይ ደግሞ ኚባድ ውጊያ በተደሚገባ቞ው እና "ዚኀርትራ ሠራዊት በነበሚባ቞ው ቆላ ተንቀን እምባሰነይቲ፣ ማይ ቅነጣል እና ዕዳጋ ዓርቢን ውስጥ ዹኹፋ ሚሃብ አለ" ሲሉ ተናግሚዋል። ኹዚህ ዚተነሳ በርኚት ያሉ ሰዎቜ ዚቀት እቃ፣ ጌጣጌጥ እና አልባሳትን እንዲሁም ቀታ቞ውን እስኚ መሞጥ ዚደሚሱ መኖራ቞ውን፣ በተጚማሪም ላለፉት ወራት ደመወዝ ያላገኙ መምህራን፣ ሐኪሞቜ እና ሌሎቜ ዚመንግሥት ሠራተኞቜ መለመን እንደጀመሩ ያነጋገርና቞ው ሰዎቜ ገልጞዋል። በተለያዚ ወቅት ይፋ ዹሆኑ ዹዓለም ምግብ ድርጅት ሪፖርቶቜ ሰሜን ምዕራብ፣ ምሥራቅ እና ማዕኹላዊ ዚትግራይ ዞኖቜ ኹፍ ያለ ዚምግብ እጥሚት ዚታዚባ቞ው አካባቢዎቜ እንደሆኑ ያሳያሉ። ደመወዝ አልባ ዚመንግሥት ሠራተኞቜ ዚትግራይ ክልል እርሻ እና ገጠር ልማት ቢሮ በክልሉ ውስጥ ኹዘጠኝ ወራት በላይ ደመወዝ ያልተኚፈላ቞ው "220ሺህ ዚመንግሥት ሠራተኞቜ ኚባድ ቜግር ውስጥ ይገኛሉ" ሲል ገልጟ ነበር። ኚጥቂት ወራት በፊት ቢቢሲ ያነጋገሚው አንድ ዹመቀለ ዩኒቚርስቲ ሕክምና ፋኩሊቲ መምህር በበኩሉ ኹ7000 በላይ ዚዩኒቚርስቲው ሠራተኞቜ ላለፈው አንድ ዓመት ደመወዝ ስላልተኚፈላ቞ው ኚባድ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ተናግሮ ነበር። "ምንም ምንኳ ዚፌደራል አካል ብንሆንም ዚፌደራል መንግሥት ግን በጀት ሊልክልን አልቻለም" ሲልም ቅሬታውን አቅርቩ ነበር። ዚትግራይ ቎ሌቪዝን ዹክልሉ ማኅበራዊ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ደባልቀውን ጠቅሶ ባሰራጚው ዘገባ "በቅርብ ጊዜ እርዳታ ካልገባ ኚግማሜ በላይ ዚትግራይ ሕዝብ ያልቃል" ሲል አስጠንቅቀዋ። "እቀባው እዚበሚታ በመሄዱ በመጥፋት አፋፍ ላይ እንገኛለንፀ እቀባው እስኚ ሚያዚያ 09/2014 ድሚስ ኹቀጠለ ግማሜ ዚትግራይ ሕዝብ ያልቃልፀ ብዙዎቜ በመድኃኒት እጥሚት እዚሞቱ ነው። ለቀተሰቊቻ቞ው መሰሚታዊ አቅርቊት ማቅሚብ ባለመቻላ቞ው ደግሞ በርካቶቜ ራሳ቞ውን እያጠፉ እንዳሉ ሪፖርቶቜ እደሚሱን ነው" ሲሉ ተናግሚዋል። አንድ ሻማ 30 ብር ዚፌደራል መንግሥቱ ለስድስት ወራት ክልሉን ባስተዳደሚበት ወቅት ትልልቅ ኚተሞቜ ባንክ፣ ስልክ፣ ኢንተርኔት እና መጓጓዣ ተጀምሮ ዹነበሹው አገልግሎት ዳግም ዚትግራይ አማፂያን መቀለን ሲቆጣጠሩ ሙሉ በሙሉ ተቋጧል። ኹዚህ ወዲህ በክልሉ ዹሚገኙ ዚፋይናንስ አገልግሎቶቜ በመቋሚጣ቞ው ዚገንዘብ እጥሚት አጋጥሟል። ዚመሠሚታዊ ሞቀጊቜ ዋጋም ኚእጥፍ በላይ ጭማሪ እንዳሳዚም ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ሰዎቜ ይገልጻሉ። ክልሉ ኹዋናው ዚኢትዮጵያ ኀሌትሪክ ኃይል አቅርቊት መስመር ጋር ስለተቆራሚጠ መደበኛ እና ያልተቆራሚጠ ዚመብራት አገልግሎት ማግኘት አለመቻሉንም ጹምሹው ተናግሚዋል። በርኚት ያለ ሰው ሻማ እንደሚጠቀም ዚሚናገሩት እነዚህ ነዋሪዎቜ፣ በፊት ሊስት ብር ይገዙት ዹነበሹውን ሻማ አሁን 30 ብር እንደሚኚፍሉበት ያስሚዳሉ። በክልሉ በርኚት ያለ ገንዘብ በጥቂት ባለሃብቶቜ እና ነጋዎዎቜ ካዝና እንደሚገኝ፣ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ወደ ክልሉ ዚሚገቡ ሞቀጊቜ እና ዹሚደሹጉ ዚገንዘብ ልውውጊቜ ኚእጥፍ በላይ እንደጚመሩ አማኑዔል ይናገራል። ባለፉት ሳምንታት ለክልሉ መገናኛ ብዙኃን መግለጫ ዚሰጡት ዹክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደብሚፂዮን ገብሚሚካኀል (ዶ/ር) በክልሉ ውስጥ ዚባንክ፣ ነዳጅ እና ዚመድኃኒት ቜግሮቜ እንዳሉ በማስታወስ አቅርቊቶቜ ላይ ዋጋ ዚሚጚምሩ ነጋዎዎቜ አሉ በሚል ወቅሰዋል። አክለውም "በዚህ ጭንቀት ውስጥ እበለጜጋለሁ ብሎ ማሰብ ወንጀል ነው" ሲሉ ተናግሚዋል። ኹክልሉ ወደ ሌሎቜ አካባቢዎቜ ዚሚያመሩ ነዋሪዎቜ ዚህወሓት ሊቀመንበር ባለፈው ወር ላይ በሰጡት መግለጫ "እቀባው ኚባድ ነውፀ ቜግር ውስጥ ነው ያለነውፀ ኚባድ ማኅበራዊ ቀውስ ነው ያለው" ሲሉ ተናግሹው ነበር። "በዚወቅቱ ኚአፋር፣ ኚአማራ፣ ኚምዕራብ ትግራይ ዚሚመጡ ዚተፈናቃዮቜ ቁጥር እዚጚመሚ ነው። . . ." በማለት በክልሉ ያለው እቀባ እና ግጭቱ ያስኚተለውን ጫና ዘርዝሹው ነበር። እቀባው በትግራይ ክልል ውስጥ ዹሚፈናቀሉ ሰዎቜን ቁጥር እንዳይጚምሚው ስጋት እንዳላ቞ው ዚሚናገሩት ትግራይ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶቜ ዚሚሰሩት ግለሰብ ና቞ው። ይህ ግለሰብ አሁንም ወጣቶቜ ሕጋዊ ባልሆነ መልኩ ኹክልሉ እዚወጡ ናቾው ብሏል። ". . . በተለይ በደቡብ ትግራይ፣ በራያ ቆቩ እና አፋር አድርገው ወደ መካኚለኛው ኢትዮጵያ ዚሚሄዱ አሉ። በራያ አላማጣ መስመር ብዙ ሰው ኚትግራይ እዚወጣ ነው። ገንዘብ ኹፍለው በደላላ ነው ዚሚወጡት" ይላል። ዹዓለም አቀፍ ተቋማት ምን ይላሉ? በአሁኑ ወቅት ወደ ክልሉ ዚሚገባው ዚሰብኣዊ እርዳታ አነስተኛ በመሆኑ እና በቀጠለው ጊርነት ምክንያት ስለሚደናቀፍ ዹኹፋ ሰብዓዊ ቀውስ እንደተፈጠሚ ዹዓለም አገፍ ድርጅቶቜ ይገልጻሉ። ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም ትግራይ ውስጥ ብቻ 4.6 ሚሊዮን ሰዎቜ፣ ማለትም ኚአምስት ሰዎቜ መካኚል አራቱ ዚምግብ እህል እርዳታ ጠባቂዎቜ መሆናቾውን ይናገራል። ድርጅቱ አክሎም ኚግማሜ በላይ ነፍሰጡር እና ዚሚያጠቡ እናቶቜ አስ቞ጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉም አስታውቋል። በተጚማሪም ዚፌደራል መንግሥት እና ዚህወሓት አማፂያን ወደ ክልሉ ያልተገደበ ዚሰብዓዊ እርዳታ ዚሚደርስበትን መንገድ እንዲያመቻቹ ሲጠይቅ ቆይተዋል። ወደ ክልሉ ሰብዓዊ እርዳታ ላለመግባቱ ግን ህወሓት አመራሮቜ እና ዚፌደራል መንግሥቱ እርስ በእርስ ይወነጃጀላሉ። ባለፈው ሳምነት መጚሚሻ ላይ ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባወጣው ሪፖርት እስኚ 454ሺህ ዚሚደርሱ ህጻናት በምግብ እጥሚት እንደተጎዱ፣ ኹ115 ሺህ ህጻናት ደግሞ በኚባድ ዚምግብ እጥሚት እንደተጠቁ አመልክቷል። አክሎም እስኚ 120ሺህ ዚሚደርሱ ነፍሰጡር እና እንዲሁም ኹ25 ሺህ በላይ ኚእድሜያ቞ው ኚአምስት ዓመት በታቜ ዹሆኑ ህጻናት በምግብ እጥሚት መጎዳታ቞ውን ገልጿል። ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም በጥር ወር መጚሚሻ ላይ ይፋ ባደሚገው መሹጃ 40 በመቶ ዹሚሆነው ዚትግራይ ሕዝብ "ለኚባድ ዚምግብ እትሚት" ተጋልጧል ብሏል። ይህ ሪፖርት 83 በመቶ ዚሚሆኑት ዹክልሉ ነዋሪዎቜ ምግብ እንደጚሰና ልመና ላይ ተሰማርተው በቀን አንድ ጊዜ ብቻ እዚተመገቡ እንዳሉ ያመለክታል። በተጚማሪም አሁን በአፋር ክልል በኩል በቀጠው ግጭት ዚተነሳ ሰብዓዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ሚያልፍበት ብ቞ኛው ዚሰመራ-አብዓላ መንገድ እንደዘጋው በተደጋጋሚ ተገልጿል። በክልሉ ዚሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ዚእርዳታ ተቋማት በክልሉ ውስጥ ያላ቞ው ዚእርዳታ አቅርቊት እና ነዳጅ ክምቜት እንደተሟጠጠ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በመጓጓዣ እና ነዳጅ እጥሚት ምክንያት እርዳታ቞ውን ለመቀነስ እንደተገደዱ አስታውቀዋል። እስኚ መጋቢት 08/2022 (እኀአ) ባለው ጊዜ ውስጥም በአጠቃላይ 600 ሊትር ነዳጅ ብቻ እንደቀራ቞ው ገልፀዋል። ዚተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን ኮሚሜነር፣ በትግራይ ክልል ያለው እቀባ መቀጠሉ እንደሚያሳስባ቞ው ገልፀው ነበር። አክለውም ". . .ዹክልሉ ዚጞጥታ ኃይሎቜ ጚምሮ ሁሉም ወገኖቜ ያልተገደበ ዚሰብዓዊ ድጋፍ እንዲያቀርቡ ጥሪ አቀርባለሁ" ብለው ነበር። ዹዓለም ማኅበሚሰብ በሰሜን ኢትዮጵያ ዹቀጠለው ጊርነት በአፋጣኝ እንዲቆም እንዲሁም በጊርነቱ ተሳታፊ ዹሆኑ ኃይሎቜ ተኩስ እንዲያቆሙ እና ያልተገደበ ሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቊት እንዲፈቅዱ ቢጠይቁም እስካሁን ድሚስ ግን ዚታዚ ተጚባጭ ለውጥ ዚለም። ክልሉን ዚሚያስተዳድሚው ህወሓት ሊቀመንበር ደብሚፂዮን (ዶ/ር) ኚፌደራል መንግሥቱ ጋር በተዘዋዋሪ ንግግር እዚተደሚገ ነው ቢሉም ውይይቱ ተጚባጭ ለውጥ አምጥቶ አልታዚም። ይህ በእንዲህ እንዳለ ባለፈው ሳምንት መጚሚሻ ላይ ዚመጀመሪያውን ጠቅላላ ጉባዔ ያካሄደው ብልጜግና ፓርቲ በትግራይ ክልል ያለውን ቜግር ለመፍታት ማንኛውንም ዹሰላም አማራጭ እንደሚጠቀም ገልጿል። ይህ ግን ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድ መገመት እጅጉን ኚባድ ነው።
https://www.bbc.com/amharic/news-60735701
amh
business
ዚእስራኀሏ ቎ልአቪቭ በዓለም ላይ በጣም ውድ ኹተማ ተብላ ተሰዚመቜ
ዚእስራኀሏ ኹተማ ቎ልአቪቭ በዓለም ካሉ ውድ ኚተሞቜ ዚአንደኛነቱን ሰፍራ ያዘቜ። እዚጚመሚ ያለው ግሜበትና ዚአቅርቊት ሰንሰለት ቜግር በዓለም አቀፍ ደሹጃ ንሚትን ኹፍ ባደሚገው ወቅትም ነው ቎ልአቪቭ ለሰው ልጅ መኖሪያነት ውድ ኹሆኑ ኚተሞቜ ዚቁንጮነቱን ስፍራ ዚያዘቜው። ዚእስራኀሏ ኹተማ በአንደኛነት ስፍራ ስትቀመጥ ዚመጀመሪያ ሲሆን ፓሪስና ሲንጋፖር ተኚታታዩን ስፍራ እንደያዙ ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት ያደሚገው ጥናት ይፋ አድርጓል ። በዚሁ ተቋም መሹጃ መሰሚት ቎ልአቪቭ ባለፈው አመት አምስተኛ ስፍራ ላይ ነበሚቜ። በጊርነት ዚምትታመሰው ዚሶሪያ መዲና ደማስቆ በዓለም ላይ በጣም ርካሹን ስፍራ በመያዝ ደሹጃዋን አስጠብቃለቜ። ዚዳሰሳ ጥናቱ በ173 ኚተሞቜ ለሞቀጊቜ እና አገልግሎቶቜ ዹሚውለውን ወጪ በአሜሪካ መገበያያ ገንዘብ ምን ያህል እንደሆነ አወዳድሯል። ተቋሙ በአውሮፓውያኑ ነሐሮና መስኚሚም ባሉ ወራት ዹሰበሰበው መሹጃ እንደሚያሳዚው በአገራቱ ውስጥ ዚምንዛሬ ዋጋ በአማካይ በ 3.5 በመቶ ዹጹመሹ ሲሆን ይህም ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ዹተመዘገበ ፈጣን ዹዋጋ ግሜበት አድርጎታል። ዚትራንስፖርት አገልግሎት ኹፍተኛ ዹዋጋ ጭማሬ ዚታዚበት ዘርፍ ሲሆን ጥናት በተካሄደባ቞ው ኚተሞቜ ዚአንድ ሊትር ቀንዚን ዋጋ በአማካይ 21 በመቶ ጚምሯል። በተቋሙ ዹዓለም ዚኑሮ ውድነት ደሹጃ ላይ አንደኛ ዚሆነቜው ቮል አቪቭ በዋነኛነት ዚእስራኀል መገበያያ ገንዘብ ሾኹል ኚዶላር ጋር ሲነፃፃር ማሜቆልቆል አሳይቷል። ዹአገር ውስጥ 10 በመቶ ዹሚሆነው ዚሞቀጊቜ ዋጋም በኹፍተኛ ሁኔታ መናር ያሳዚ ሲሆን ይህም በተለይ በምግቊቜ ላይ ታይቷል። ጥናቱ እንደሚያመለክተው ቮል አቪቭ በአልኮል እና ትራንስፖርት ዋጋ ኹአለም ሁለተኛ ውድ፣ ለግል እንክብካቀ እቃዎቜ አምስተኛ እናም በመዝናኛ ዘርፉ ስድስተኛ ውድ ኹተማ ሆና ተቀምጣለቜ። ዹቮል አቪቭ ኚንቲባ ሮን ሁልዳይ ኚሃሬትዝ ጋዜጣ ጋር ባደሚጉት ቃለ ምልልስ በተቋሙ ስሌት ውስጥ ያልካተተው ዚቀቶቜ ዋጋ መናር ኹተማዋ ወደማትቋቋመው ደሹጃ ላይ እያደሚሳት እንደሆነም አስጠንቅቀዋል። "አገሪቱ በሙሉ በጣም ውድ እዚሆነቜ እንደመጣቜ ሁሉ ቮል አቪቭ በጣም ውድ ሆናለቜ" ብለዋል። "በእስራኀል ውስጥ መሰሚታዊው ቜግር ሌላ አማራጭ ሁሉን ያሟላና ማእኚል ዹሆነ ኹተማ ዚለም። በአሜሪካ ኒውዮርክ፣ ቺካጎ፣ ማያሚ እና ዚመሳሰሉት አሉ። በብሪታንያ ውስጥ ታላቋ ለንደን፣ ማን቞ስተር እና ሊቹርፑል አሉ። ዚኑሮ ውድነቱ በጣም ኚባድ ኹሆነ አማራጭ ወደሆኑት ሌሎቜ ኚተሞቜ መሄድ ይቜላሉ" ብለዋል። ዹዓለም ውድ ኚተሞቜ በደሹጃ ዹዓለም ርካሜ ኚተሞቜ 169 አልማቲ 170 ቱኒስ 171 ታሜኚንት 172 ትሪፖሊ 173 ደማስቆ
https://www.bbc.com/amharic/news-59493433
amh
business
ዛምቢያ፡ ድሮኖቜ ቀሚጥ ያልኚፈሉ ተሜኚርካሪዎቜን እያደኑ ነው
ዚዛምቢያ ዚግብር ባለሥልጣናት ቀሚጥ ሳይኚፍሉ እቃዎቜን ዚሚያዘዋውሩ ኚባድ መኪናዎቜን ለመቆጣጠር ድሮኖቜን መጠቀም ጀመሩ። ባሳለፍነው ቅዳሜና እሁድ ዚዛምቢያ ገቢዎቜ ባለሥልጣን በድሮኖቜ በመታገዝ ኹዋናው መንገድ በመውጣት ተደብቀው ዚነበሩ ሰባት ተሜኚርካሪዎቜ መያዛ቞ውን አስታውቀዋል። • ያለአብራሪ በሚበሹው ዹሰማይ ታክሲ ይጠቀማሉ? • ሥራ ቀጣሪና አባራሪ እዚሆነ ዚመጣው ሮቊት " ድሮኖቹ ዚፍተሻ ሠራተኞቜ በማይደርሱባ቞ው እንዲሁም አደጋ ባለባ቞ውና ጥንቃቄን በሚጠይቁ ቊታዎቜ ድሚስ በመግባት አሰሳ ያደርጋሉ" ሲሉ ዚዛምቢያ ገቢዎቜ ባለስልጣን ዚኮሚዩኒኬሜን ሥራ አስኪያጅ ቶፕሲይ ሲካሊንዳ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። በዚህ ሰባት ተሜኚርካሪዎቜ በቁጥጥር ሥር በዋሉበት ፍተሻ ድሮኖቹ 'ካፒሪ ስርነጅ' በተባለ መንገድ በመግባት ማሰስ ዚጀመሩ ሲሆን ዋናው ዚተሜኚርካሪ መንገድ ባዶ ሆኖ አግኝተውታልፀ ኚዚያም ኹዋናው መስመር 14 ኪሎሜትር በሚርቅ ጥሻ ውስጥ አመላክተዋል። በዛምቢያ ወደ ደቡብ አቅጣጫ ዹሚጓዙ ተሜኚርካሪዎቜ በአብዛኛው ኚዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፣ ማላዊ፣ ወይም ታንዛኒያ ዚሚመጡ ና቞ው። ኃላፊው ሲካሊንዳ እንዳስታወቁት አብዛኞቹ ተሜኚርካሪዎቜ በጣም በርካታ እቃዎቜን ይጭኑና ወደ ፍተሻ ጣቢያው ሲቃሚቡ በትንንሜ መኪና ቀንሰው ይጭናሉ ይህም ባለሙያዎቹ ጥርጣሬ ውስጥ እንዳይገቡ ምክንያት ሆኗል። ዚዛምቢያ ዚገቢዎቜ መሥሪያ ቀት ቮክኖሎጂን በመጠቀም ገቢውን ለማሳደግ ተስፋ እንዳለው ዚቀሚጥ ባለሥልጣናት ጹምሹው ተናግሚዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-49404009
amh
business
በኢትዮጵያ በምግብ ነክ ሞቀጊቜ ላይ ኹፍተኛ ዹዋጋ ግሜበት መመዝገቡ ተገለጾ
በኢትዮጵያ በምግብ ነክ ሞቀጊቜ ላይ ኹፍተኛው ዹዋጋ ግሜበት እዚተመዘገበ መሆኑን ዚአገሪቱ ብሔራዊ ዚማክሮ ኢኮኖሚ ምክር ቀት ገለጞ። ምክር ቀቱ ዹዘጠኝ ወራት ዚምጣኔ ሀብት አፈጻጞምን ገምግሞ ባወጣው በዛሬው ግንቊት 2፣ 2014 ዓ.ም መግለጫ ላይ እንዳመለኚተው ዚኢትዮጵያን ምጣኔ ሀብት ኹፍተኛ ፈተና እዚገጠመው ያለው ኹዋጋ ግሜበት አንጻር መሆኑን ጠቁሟል። በዚህም ዹዋጋ ግሜበቱ በዋናነት በምግብ ነክ ሞቀጊቜ ላይ በኹፍተኛ ሁኔታ መመዝገቡን ጠቅሶፀ ይህም ካለፈው ዓመት ዚሚያዝያ ወር ጋር ሲነጻጞር ዹዋጋ ግሜበቱ 36.6 በመቶ መመዝገቡን አስፍሯል። ምክር ቀቱ ጚምሮም ባለፉት ሊስት ዓመታት ዹዋጋ ግሜበትን ወደ ነጠላ አሐዝ ለማውሚድ በርካታ እርምጃዎቜ መወሰዳ቞ውን ጠቅሶ ነገር ግን በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ሁኔታዎቜ ምክንያት ዹሚፈለገው ውጀት አልመጣም ብሏል። ለዚህም ዚኮቪድ-19 ወሚርሜኝ፣ ዚጥሬ ዕቃዎቜ ዋጋ መናር፣ በአገር ውስጥ ያጋጠሙ ግጭቶቜ እና ዚሩሲያና ዚዩክሬን ጊርነት ዹፈጠሹው ዓለም አቀፍ ዹዋጋ ንሚት በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ዹዋጋ ግሜበት እንዲያሻቅብ ምክንያት መሆኑን አመልክቷል። መንግሥት ዹዋጋ ግሜበቱን ለመቆጣጠር ዚተለያዩ እርምጃዎቜ እዚተወሰዱ እንደሆነ ዹጠቀሰው መግለጫውፀ ኚእነዚህም ውስጥ ዚመንግሥት ወጪን ኹአገር ውስጥ ገቢ መሞፈን፣ ዚግብር ሥርዓቱን ማዘመን እና ዚተለያዩ ግብርን ዚተመለኚቱ ማሻሻያዎቜ ማድሚግ በቀጣይ ተግባራዊ ይሆናሉ ተብሏል። ምግብ ነክ ዹሆኑና መሠሚታዊነታ቞ው ዚታመነባ቞ው ዚፍጆታ ዕቃዎቜ በፍራንኮ ቫሉታ አሠራር ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ መፈቀዱን እንዲሁም፣ ዚመድኃኒት፣ ነዳጅ፣ ማዳበርያ፣ ዘይት እና ሌሎቜም መሠሚታዊ ሞቀጊቜ ግዢ አቅርቊት አቅርቊት እንዲቀላጠፍ ዚማስተካኚያ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል። ነዳጅን በተመለኹተ ደግሞ ሁሉን አካታቜ ኹሆነ ዚመንግሥት ዚነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ በመውጣት ድጎማ ለሚያስፈልጋ቞ው አካላት ብቻ እንዲሆን እዚተሠራ ነው ተብሏል። ብሔራዊ ዚማክሮ ኢኮኖሚ ምክር ቀት ባወጣው መግለጫ ላይ ዚአገሪቱ ምጣኔ ሀብት በተፈጥሯዊና በሰው ሰራሜ አደጋዎቜ በተፈጠሩ ጫናዎቜ በእጅጉ መፈተኑን ገልጟ፣ በሰሜኑ ዚአገሪቱ ክፍል እዚተካሄደ ያለው ጊርነት እና ድርቅን በዋናነት አንስቷል። ቢሆንም ግን በመጀመሪያዎቹ ሁለት ሩብ ዓመታት ላይ ዹተመዘገበው ዕድገትን መሠሚት በማድሚግ ዚዓመቱ ጠቅላላ ዹአገር ውስጥ ምርት በአማካይ በ6.6 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል ተብሏል። ጚምሮም በአገሪቱ ዚብድርና ቁጠባ መጠን ላይ ጭማሪ መታዚቱን በመጥቀስ፣ ዚባንኮቜ አጠቃላይ ዚቁጠባ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጞር በ25 በመቶ ኹፍ ብሎ ወደ 1.6 ትሪልዮን ብር መድሚሱ ተገልጿል። በዘጠኝ ወራቱ ውስጥ ኹውጭ ንግድ 2.95 ቢሊዚን ዶላር እንደተገኘና ኹዚህ ውስጥ ደግሞ 2.05 ቢሊዚን ዶላር ዹሚሆነው ኚግብርና ምርቶቜ ዚወጪ ንግድ ዹተገኘ ነው። በተኚታይነት ደግሞ ዚማዕድን ዘርፉ 453 ሚልዮን ዶላር እና አምራቜ ኢንዱስትሪው 378.5 ሚልዮን ዶላር ገቢ ተገኝቶባ቞ዋል ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-61394971
amh
business
"ዚቱሪስት ማግኔት" ዚሆነቜው ቬኒስ ኹተማን ጎርፍ እያስጚነቃት ነው
በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዚቱሪስት ማግኔት አላት ዚምትባለው ዚጣልያኗ ቬኒስ ኹተማ በጎርፍ እዚተፈተነቜ ነው። ጎርፉ ቬኒስን በሚሊዮኖቜ ዹሚቆጠር ዶላር አሳጥቷታል ተብሏል። በጎርፉ ምክንያት ዹውሃ መተላለፊያ ዹሆነው ዹኹተማዋ ዋና አደባባይ ሎንት ማርክ ፣ትምህርት ቀቶቜና ንግድ ቀቶቜ ተዘግተዋል። ዚጣልያን መንግስሥትም በዩኔስኮ ድሚ ገፅ ላይ አስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁን አስታውቋል። • ኚባድ ዝናብና ዹጎርፍ አደጋ በአንዳንድ አካባቢዎቜ ጉዳት አስኚተለ • ጎርፍ ባጠቃ቞ው ዚምሥራቅ አፍሪካ አገራት ተጚማሪ ዝናብ ሊጥል ይቜላል ተባለ ለውሃ እና ለስነ ህንፃዎቿ ጥበብ ቱሪስቶቜ ዚሚተሙላት ቬኒስን እያስጚነቀ ያለው ጎርፍ እርዝመት ማክሰኞ እለት 187 ሎ.ሜ ደርሶ ነበር ተብሏል። ቀታ቞ው በጎርፍ ዚተጎዳባ቞ው ዚቬኒስ ኗሪዎቜ እስኚ አምስት ሺህ ዩሮ ሲያገኙ ንግድ ቀቶቜ ደግሞ 20 ሺህ ዩሮ ድሚስ ካሳ ይሰጣ቞ዋል ተብሏል። ኚመቶ በላይ ኹሚሆኑ ደሎቶቜ ዚተሰራቜው ቬኒስ በዚአመቱ በጎርፍ ዚምትጠቃ ሲሆን ዹአሁን እንደ አውሮፓውያኑ በ1923 ተኚስቶ ኹነበሹውና አስኚፊ ኚተባለው ጎርፍም ዚባሰ ነው ተብሏል። ዚጣልያን መንግሥት ለቬኒስ 20 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል። ያለታካሚዎቜ ፈቃድ ቀዶ ህክምና ያደሚገው ዹማህጾን ሀኪም ተኹሰሰ
https://www.bbc.com/amharic/news-50437271
amh
business
ኢትዮጵያ ዝቅተኛ ዹደመወዝ ወለልን ዚሚወስነውን ቊርድ ልታቋቁም ነው
በኢትዮጵያ ዹዝቅተኛ ዹደመወዝ መጠንን ዚሚወስነው ዹደመወዝ ቊርድ ሊቋቋም መሆኑን ቢቢሲ ኚሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ርና ኚኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዎሬሜን ካገኘው መሹጃ መሚዳት ቜሏል። በአሁኑ ወቅት ዹዝቅተኛ ደመወዝ ወለልን ዚሚወስነው ዹደመወዝ ቊርድ ማቋቋሚያ ደንብ ዹተሹቀቀ ሲሆን በሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ዹበላይ ኃላፊዎቜ ምክክር ሲደሚግበት ቆይቶ ደንቡ ወደሚፀድቅበት ወደ ሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ለመላክ በዝግጅት ላይ ነው ተብሏል። ይህ ቊርድ በኢትዯጵያ እስካሁን ድሚስ ሲሰራበት ዹነበሹው በአሰሪና ሠራተኞቜ ስምምነት ዚሚወስኑትን ዹአኹፋፈል ሁኔታ በመቀዹር ዹደመወዝ መጠን ላይ ዚሚወስን መሆኑን አቶ ፍቃዱ ገብሩ በሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ዹሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት ዳይሬክተር ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ይህ ዝቅተኛ ዹደመወዝ ወለል ሠራተኞቜ ደመወዛቾው በህግ ኹተደነነገገው በታቜ እንዳይሆን ዚሚያደርግ ሲሆንፀ ዚቅጥር ግንኙነት ባለበት ሁሉ ተፈፃሚ ይሆናል። ደንቡ በአሁኑ ሰዓት በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን ኚዚያ በኋላም ዚቊርዱ መቋቋም ዚሚቀጥል ይሆናል። ዹዝቅተኛ ዹደመወዝ መጠን ምን አይነት ሁኔታዎቜን ማካተት ይገባዋል? በምንስ ይወሰን? ዚሚሉትን ሁኔታዎቜ ዚሚወስነው ይህ ቊርድ በአራት አካላት ዹሚዋቀር ነው። አባላቱም በዋነኝነት ሠራተኞቜና አሰሪዎቜ፣ መንግሥት፣ እንዲሁም ዚሲቪክ ማኅበራት ዚሚካተቱበት ይሆናል። ዚሲቪክ ማኅበራት ዚሚባሉት ዚባለሙያዎቜ ማኅበራት ሲሆኑ ለምሳሌም እንደ ኢትዮጵያ ዚኢኮኖሚ ባለሙያዎቜ ማኅበርና ዹኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማትን ዚመሳሰሉት በዚህ ቊርድ ውስጥ ተሳታፊ እንደሚሆኑ አቶ ፍቃዱ ይናገራሉ። ዹደመወዝ ቊርዱ ዝቅተኛውን ወለልን ዚሚወስነው ዚባለሙያዎቹ ማኅበራት ዚሚያቀርቧ቞ውን መሚጃዎቜና ዚተለያዩ ጥናቶቜን ግብአት በማድሚግፀ በተለይም በአገሪቱ ማክሮ ኢኮኖሚ ላይ ሊያመጣ ዚሚቜለውን ተፅእኖ በጥልቀት በማዚት እንዲሁም ዚአሰሪዎቜና ሠራተኞ቞ን ጥቅሞቜ ኚግምት ውስጥ በማስገባት እንደሆነ አቶ ፍቃዱ ያስሚዳሉ። አቶ ፍቃዱ እንደሚሉት ምንም እንኳን ዚአገሪቱን ሁኔታ በጥልቀት በማዚት ዝቅተኛ ዹደመወዝ መጠን ቢወሰንም በመርህ ደሹጃ ግን ዓለም ዹሚኹተላቾውን መሰሚታዊ ጉዳዮቜ ዚሚያካትት ይሆናል። እነዚህ መሰሚታዊ ዚሚባሉትም ሠራተኞቻ቞ውና ቀተሰቊቻ቞ው ለመኖር ዚሚያስፈልጋ቞ው መጠን እንዲሁም በሌላ በኩል ኩባንያዎቜ፣ ተቋማትና አሰሪዎቜ ዹመክፈል አቅም ምን ይመስላል ዹሚለውን ያጀናል ይላሉ። ዚኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዎሬሜን ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ በበኩላ቞ው ደንቡ ወደ ኚሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ኚመላኩ በፊት ኚመንግሥት፣ ኚሠራተኞቜና ኚአሰሪዎቜ እንዲሁም ሌሎቜ ዚሚመለኚታ቞ው አካላትን በማካተት ዚሊስትዮሜ ምክክርና ውይይት ተደርጎበታል ይላሉ። እንደ ሠራተኛ ማኅበር ዚራሳ቞ውን ጥናት እያካሄዱ ቢሆንም ሠራተኞቜን በመወኹል በዋነኝነት አንድ ሠራተኛ በደመወዙ መኖር መቻል አለበት ዹሚለውን ፅንሰ ሃሳብ ዚያዘ ነው ይላሉ። ዝቅተኛ ዹደመወዝ ወለል ዚአንድን ሠራተኛ ዚኑሮ ደሹጃ ዚቀት ኪራይ፣ መብራት፣ ውሃ፣ ዚትምህርት ቀት ክፍያ እንዲሁም ሌሎቜ ወጪዎቜ ተደምሹው ለአንድ ሰው ኑሮ በአማካይ ምን ያህል ይበቃል ዹሚለው ኚግምት ውስጥ መግባት አለበት ይላሉ። በዚህም አንድ ሠራተኛ ራሱን አስተዳድሮ በአማካኝ ሊስት ወይም አራት ልጅ ማሳደግ ዚሚቜልበት መጠን ሊሆን ይገባል ይላሉ። እንደ ምሳሌም ዚሚያነሱት በኢትዮጵያ ባሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮቜ ተቀጥሚው ዚሚገኙትን ሠራተኞቜን ነው። አብዛኞቹ ኹ750 አስኚ 1000 ብር በወር ተቀጥሚው ዚሚሰሩ ሠራተኞቜን ጉዳይ "አሳዛኝና ሊሻሻል ዚሚገባው" ስለመሆኑ ማሳያ እንደሆነ ይጠቅሳሉ። "አብዛኛው ሠራተኛ ምሳ በልቶ እራት መድገም ዚማይቜል ነው። አንድ ሺህ ብር በኢትዮጵያ ዚኑሮ ሁኔታ ውስጥ ገበያ ተወጥቶ ምንም አይገዛም። አንድ ሳምንትም ዚሚያቆዚው አይደለም። ኹዚህ አንፃር እነዚህ ነገሮቜ ይሻሻላሉ ብለን እንጠብቃለን። ቢያንስ ሌላ ነገር ማድሚግ ባይቜል በልቶ ማደር ይቜላል" ይላሉ። እነዚህንም ግምት ውስጥ ማስገባት አለበት ዚሚሉት አቶ ካሳሁን ይህም ሁኔታ በባለሙያዎቜ ተጠንቶ ግብዓት ይሆናል ይላሉ። "ሆኖም ጉንጭ አልፋ ክርክር ሳይሆን መሬት ላይ ያለው ሳይንሳዊ ነገርን ዹተኹተለ ነገር መኖር እንዳለበት በኛ በኩል ስንኚራኚርም፣ ስንወያይም፣ ስንመካኚርም እሱን መሰሚት አድርጎ ስለሚሆን ይሄንን ጥናት እያካሄድን ነው ያለነው" ይላሉ። አቶ ፍቃዱም በበኩላ቞ው ዹደመወዝ ቊርዱ ሠራተኞቜ ማግኘት ዚሚገባ቞ውን ብቻ ሳይሆን ኩባንያዎቜ መክፈል ዚሚቜሉበትን ሚዛናዊነቱን በጠበቀ መልኩ ዚሚደራደሩበት መድሚክ እንደሚሆን ያሰሚዳሉ። መንግሥትም በነዚህ አካላት ላይ ዚማደራደር ሚና ዹሚኖሹው ሲሆን በመጚሚሻም ሠራተኞቜና አሰሪዎቜ ዚተስማሙበት እንዲሁም ባለሙያዎቜ ጥናት ያደሚጉበት ሆኖ በሕግነት ይፀድቃል ይላሉ። በተለይም እነዚህ ባለሙያዎቜ በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ይህ ቢወሰን ምን ያመጣል ዹሚለውን ነፃ አስተያዚት እንዲሰጡ ዚማድሚጉ ጉዳይ ትኩሚት ሊሰጠው እንደሚገባ ይጠቁማሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ በአጠቃላይ ዹማይቀጠሹው ሰው 80 በመቶ ሲሆን ዚእርሻ ዘርፉ በአብዛኛው ኚኢ-መደበኛ ዚሚመደብ ሲሆን በቀተሰብ ደሹጃ ዹሚኹናወን ነው። ገበያው ላይ ዚኢ-መደበኛውና መደበኛ ቅጥሩ ላይ ገበያ ያላ቞ው ተፅእኖና መመጣጠን ሊታይ ይገባዋል ይላሉ። እንደ ምክንያትነትም ዚሚያቀርቡት "ደመወዝ ተኚፋዮቜና ደመወዝ ዹሌላቾው ግለሰቊቜ በገበያው ላይ እኩል ተሳትፎ ስላላ቞ው ነው" ይላሉ። ኹዚህም በተጚማሪ እነዚህ ባለሙያዎቜ በአገሪቷ ዚወቅቱ ሁኔታ ለምሳሌ ግሜበት፣ ዚገበያ መዋዠቅ፣ ወሚርሜኞቜንና ሌሎቜ ጉዳዮቜን ኚግምት ውስጥ በማስገባት ክለሳ ዚማድሚግ ሥራ ወቅቱን ዚሚቋቋምበት ሁኔታ ሊሰራ እንደሚገባ ዚሚጠቁሙት አቶ ፈቃዱፀ በተለይም አገሪቱ እያለፈቜበት ካለቜው ዹዋጋ ግሜበት ጋር ተያይዞ ዝቅተኛ ዹደመወዝ ወለልን መወሰን አስፈላጊ ነው ይላሉ። "ሠራተኛው ዚመግዛት አቅሙ ወርዷል። ሠራተኛው አሁን በሚያገኘው ደመወዝ መግዛት አልቻለም። በልቶ ማደር አይቜልም" ብለዋል። ዝቅተኛ ዹደመወዝ ወለል ዹሚመለኹተው በአገሪቱ አሰሪና ሠራተኛ አዋጅ ዚሚተዳደሩትን ወይም በቀጣሪና በቅጥር ግንኙነት ያሉትን ነው። በአጠቃላይ መደበኛ ዹሆነውን ዚሥራ ዘርፍ ላይ ዚተሰማሩ ዹግል ዘርፉ ኩባንያዎቜ፣ ተቋማት እንዲሁም ዚመንግሥት ዚልማት ድርጅቶቜን ይመለኚታል። ዝቅተኛ ዹደመወዝ ወለሉ ዚመንግሥት ሠራተኞቜ (ሲቪል ሠራተኞቜን) አያካትትም እንዲሁም ኢ-መደበኛ ዹሆነውን ዚሥራ ዘርፍንም እንደማያካትት አቶ ካሳሁን ያስሚዳሉ። ዚመንግሥት ሠራተኞቜን ዝቅተኛ ዹደመወዝ ወለል ቊርዱ ለምን እንደማይወስን ዚሚናገሩት አቶ ፍቃዱ መንግሥት ቀጣሪ ስለሆነ ያው መንግሥት አትራፊ ስላልሆነ መሰሚታዊ ዚሚባሉ ነገሮቜን ወስዶ ነው ዹሚኹፍለው ይላሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-57340391
amh
business
ኚወለድ ነጻ ባንክ ሥርዓት ለሚሰጠው 'ብድር' እንዎት ትርፍ ያገኛል?
ዚሌሪያ ሕግን መሰሚት አድርጎ ሥራውን ዚሚያኚናውነው እስላማዊ ወይም ኚወለድ ነጻ ዚባንክ ሥርዓት ገንዘብ ሰጥቶ፣ አትርፎ መቀበልን ያወግዛል። ይህም በባንኩ ሥርዓት ብቻ ሳይሆን በቅዱስ ቁርዓንም ዹተኹለኹለ በመሆኑ በቀዳሚነት ዚእስልምና እምነት ተኚታዮቜን ያገለግላል። ሆኖም ዚእምነቱ ተኚታዮቜ ላልሆኑ ደንበኞቜም ክፍት ነው። በተቃራኒው መደበኛው ዚባንክ ሥርዓት፣ ዚቁጠባ ሂሳብ ለሚኚፍቱ ወለድ እዚኚፈለ ገንዘባ቞ውን ሲያስቀምጥ፣ ለሚያበድሚው ገንዘብ ደግሞ ወለድ ይቀበላል። ይህም ዹመደበኛ ባንኮቜ ዋነኛ ዚትርፍ ምንጭ እና መንቀሳቀሻ ነው። ታዲያ ኚወለድ ነጻ አገልግሎት ዚሚሰጡ ባንኮቜ ለሚያቀርቡት ገንዘብ እንዎት ትርፋማ ይሆናሉ? ኚሊስት ወራት በፊት በኢትዮጵያ ሥራ ዹጀመሹው ሂጅራ ኚወለድ ነጻ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት ሙባሚክ ሾሞሎ እንዲሁም በኢትዮጵያ ዚመጀመሪያው ኚወለድ ነጻ ባንክ ዹሆነው ዹዘምዘም ባንክ ዚቢዝነስ ስትራ቎ጂ እና ኢኖቬሜን ዳይሬክተር ኚድር አባስ ኚወለድ ነጻ ባንክን ትርፋማ ዚሚያደርጉት በርካታ አስራሮቜ እንዳሉ ይጠቅሳሉ። ኚወለድ ነጻ ባንክ ምንም እንኳን በእስልምና አስተምህሮት መሰሚት ቢንቀሳቀስም ዚማትሚፍ ዓላማ ያለው ነው። ዹዚህ ዚባንክ ሥርዓት ሥራዎቜ በሙሉ በባንኩ እና በደንበኛው መካኚል ትርፍ እና ኪሳራን መጋራትን መሰሚት ዚሚያደርግ ነው። "ደንበኞቜ ወደ እኛ ሲመጡ ትርፍንም ኪሳራንም ለመጋራት ወስነው ይመጣሉ ማለት ነው" ሲል ዚሚያስሚዳው ሙባሚክ "ደንበኞቜ ዚሚያስቀምጡት ገንዘብ ባንኩ ዚተፈቀዱ ቢዝነሶቜ ላይ ፋይናንስ አድርጎ ያ ፋይናንስ ትርፍ ካመጣ ኹደንበኛው ጋር ትርፍ ይጋራልፀ ኪሳራ ይዞ ኚመጣም ኪሳራን ነው ዚሚጋራው" በማለት ያብራራል። ይህም በተለያዚ ዚባንኩ ሥርዓቶቜ ዹሚተገበር ሲሆን ደንበኞቜ ትርፍም ኪሳራም ዚማይጋሩበት እና ገንዘባ቞ውን በአደራ ዚሚያስቀምጡበትም አሰራር አለ። ዚባንክ ሥርዓቱ አሰራር ደንበኞቜ ዚሚፈልጉትን ዕቃ ወይም አገልግሎት ገዝቶ ኚማቅሚብ፣ ኚባለሀብቶቜ ጋር በጋራ ኢንቚስት እስኚማድሚግ ዹሚዘልቅ ነው። ዚሜያጭ ውል ፋይናንሲንግ ኚወለድ ነጻ ባንክ 'ዚሜይጭ ውል ፋይናንሲንግ' በተሰኘው ዚብድር ሥርዓቱ፣ ባንኩ ደንበኛው ወይም 'ተበዳሪ' ዹሚፈልጋቾውን ንብሚቶቜ ገዝቶ ያቀርባል። ዚባንኮቹ አመራሮቜ በሞሪአ ሕግ ወለድ ዹተኹለኹለ ቢሆንም ነግዶ ማትሚፍ ዹተፈቀደ ስለመሆኑ ጠቅሰው፣ ባንኩ ዚደንበኞቜን ፍላጎት መሰሚት አድርጎ ወይም ቀደም ብሎ ኹገዛቾው ንብሚቶቜ ደንበኞቜ በዱቀ ዚሚወስዱበት አሰራር መሆኑን ጠቅሰዋል። ዹተገዛውን ንብሚት ባንኩ ለደንበኛው ሲያቀርብ ኚተገዛበት ዋጋ ጚምሮ እንደማንኛውም ንግድ ዚሚያተርፍ ይሆናል። ይህም በተለያዚ መንገድ ይቀርባልፀ ለአብነት 'ሙራብሃ' ዹተሰኘው አገልግሎት ደንበኛው ዹሚፈልገውን አገልግሎት ወይም ምርት ባንኩ ዚገዛበትን ዋጋ እና ዚሚያተርፈውን በግልጜ አስታውቆ ዚሚያቀርብበት ሥርዓት ነው። ዹተገዛው ንብሚት ወይም አገልግሎት በባንኩ ስም ሆኖ፣ ትርፉም ምርቱ ወይም አገልግሎቱ በጊዜ ውስጥ ሊኖሹው በሚቜል ዋጋ ዹሚሰላ ይሆናል። ይህ አገልግሎት በእስላማዊ ባንክ ኹ50 እስኚ 60 በመቶ ዹሚሾፍን ሲሆን ይህም እንደ ተሜኚርካሪ እና ቀት ያሉ ንብሚቶቜ ዚሚጠቃለሉበት ነው። ታዲያ እንደ ሙባሚክ ገለጻ "ባንኮቜ እንደ ነጋዮ ገበያ ወጥተው በሜያጭ ያስተላልፋሉ ማለት ነው።" በሌላ በኩል 'ባይሰለም' ዚሚባለው አገልግሎት ደግሞ ለግብርና ሥራዎቜ ዚሚቀርብ ሲሆን ኚወለድ ነጻ ባንኩ ለአርሶ አደሮቜ ገንዘብ በማቅሚብ ትርፍ ወይም ኪሳራ ዚሚጋራበት ነው። በሌሎቜ አገራት ለማኑፋክ቞ሪንግ ሥራዎቜ ፋይናንስ ዹሚቀርበው ኹዚሁ ዚባንክ አገልግሎት ነው። 'ኢስቲስና' ዹተሰኘው አገልግሎት ደግሞ በጊዜ ሂደት ለሚሻሻል ቢዝነስ ዚሚቀርብ ፋይናንስ ሲሆን፣ እንደ ህንጻ ግንባታ ያሉ እንቅስቃሎዎቜን ያካትታል። ለአብነት ህንጻ መገንባት ዹሚፈልግ ሰው ኚወለድ ነጻ ባንክ ገንዘብ ወይም 'ብድር' በሚፈልግበት ወቅት ዚህንጻውን ሙሉ እቅድ ያቀርብና ባንኩ ካመነበት ጚሚታ አውጥቶ ያስገነባለታል። ኚግንባታው በኋላም ባንኩ አትርፎ መልሶ ለደንበኛው ዚሚሞጥበት ነው። ዚሜርክና ፋይናንስ ይህ ሥርዓት ባንኩ ደንበኞቜ ላሏቾው ዚቢዝነስ ሃሳቊቜ ገንዘብ በማቅሚብ ወደ ተግባር ዚሚቀይርበት ሲሆን፣ ባንኩ በድርሻ ወይም በውል ትርፍ ወይም ኪሳራ ዚሚጋራበት ነው። በዚህ አሰራር ኢንቚስትመንቶቹ ላይ ዚጋራ አመራር ሊሰጡም ይቜላሉ። በዚህ ውስጥም 'ሙዳራባህ' ተጠቃሜ ነው። ይህ አገልግሎት ባንኩ ለደንበኛው ፋይናንስ ዚሚያቀርብበት ሲሆን ትርፍ ካለ በስምምነታ቞ው መሰሚት በጋራ ይካፈላሉ። ኪሳራ ካለ ግን ዚባንኩ ብቻ ይሆናል። 'ሙሻራካህ' ደግሞ ኚወለድ ነጻ ዚባንክ ፋይናንስ ዓይነት ሲሆን ደንበኛው ያለውን ካፒታል በማወጣት ኚባንኩ ጋር ኢንቚስት ዚሚያደርጉበት ሲሆንፀ በጊዜ ሂደት ባንኩ ኚንግድ ሥራው ዚሚያገኘው ዚትርፍ ድርሻ ሊቀር ዚሚቜልበት ነው። በተጚማሪም እስላማዊ ዚባንክ ሥርዓት ዚተለያዩ አግልግሎቶቜ ወይም ምርቶቜን በማኚራዚት፣ ዓለም አቀፍ ንግድ ላይ በመሰማራት ወይም በሌሎቜ መንገዶቜ ትርፍ ሊያሰባስብም ዚሚቜልበት መንገድ አለ። በእነዚህ ሂደቶቜ ሁሉ በዚህ ሥርዓት ስር ያሉ ባንኮቜ ገንዘብ ተቀበለው ያለምንም አገልግሎት ወይም ሜያጭ 'ገንዘብ ላይ ገንዘብ ጹምሹው' እንዲሁም ኚቅዱስ ቁርአን ጋር በማይጻሚር መልኩ አለመስራታ቞ውን ማሚጋገጥ ይጠበቅባ቞ዋል። ኚወለድ ነጻ ባንክ 'ብድር' መመለስ ያልቻሉ ሰዎቜን አይቀጣም። ፋይናንስ ዚቀሚበለት ሰው በተለያዩ ምክንያቶቜ ኚባንኮቹ ዹወሰደውን ገንዘብ መመለስ ባይቜል ወይም በሚጠበቅበት ጊዜ ባይመልስ "ቅጣት ዚሚባል መርህ ዚሌሪአ ሕጉ አያውቅም" በማለት ሙባሚክ ይገልጻል። "መለኮታዊ ትዕዛዝ ነው። ሰዎቜ ላበደሯ቞ው ብድር አታስጚንቁ ዹሚል ነገር አለ። ሳታስጚንቋ቞ው በተጚማሪ ደግሞ ኚቻላቜሁ ተዉላቾው ዹሚል አለ። ስለዚህ ያንን [ቅጣቱን] አያውቅም" ብሏል። ሆኖም 'ለፍትሃዊነት' በሚል ዓለም አቀፍ ዚእስልምና ተቋማት ዚሂሳብ አያያዝ እና ኊዲት ድርጅት ገንዘቡን በወሰደው ሰው ፍላጎት ዹሚፈጾም ወይም ደንበኛው ራሱን ዚሚቀጣበት ዹ3 በመቶ ቅጣት ደንግጓል። ዹተገኘው ዚቅጣት ገንዘብ ደግሞ ዚባንኩ ገቢ ሳይሆን ለእርዳታ ተቋማት ዚሚበሚኚት መሆኑንም ጚምሮ ገልጿል። ኚወለድ ነጻ ባንክ በኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደሹጃ በዚህ መልኩ ዹሚተገበሹው ኚወለድ ነጻ ዚባንክ ሥርዓት በመደበኛ ባንኮቜ ውስጥ በመስኮትፀ በመደበኛ ባንኮቜ በቅርንጫፍ ደሚጃፀ ዹመደበኛ ባንኮቜ እህት ኩባንያ በመሆን ወይም እንደ ዘምዘም እና ሂጅራ ሙሉ በሙሉ ኚወለድ ነጻ ሆኖ ሊቋቋም ዚሚቜልበት አማራጮቜ አሉት። በኢትዮጵያ ይህ አገልግሎት በመስኮት ደሹጃ ዹተጀመሹው ኚስምንት ዓመታት በፊት ሲሆን፣ ሙሉ በመሉ ኚወለድ ነጻ ዹሆነ ባንክ ሥራ ዹጀመሹው ግን ኚወራት በፊት ነው። በኢትዮጵያ መሰል አገልግሎት ለማቅሚብ ዚሚያስቜል ዹሕግ ማዕቀፍ ሳይኖር መቆዚቱ ኹ13 ዓመታት በፊት ዹተጠነሰሰው እና በኢትዮጵያ ቀዳሚ ኚወለድ ነጻ ባንክ ዹሆነው ዘምዘም፣ በብዙ ውጣ ውሚድ እንዲያልፍ አስገድዷል። ይህም ዚፋይናንስ አካታቜነት ላይ ጥያቄ ያስነሳ ነበር። ይሁን እንጂ በ2011 ዓ. ም ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት ወደ ሥልጣን መምጣቱን ተኚትሎ ዚተለያዩ ኚወለድ ነጻ ባንኮቜ አክሲዮን መሞጥ ዚጀመሩ ሲሆን ሁለቱ ባንኮቜ ደግሞ ኚወራት በፊት ሥራ ጀምሚዋል። ዘምዝዘም ባንክ ሥራ በጀመሚባ቞ው አራት ወራት 30 ሺህ ደንበኞቜ እና 15 ቅርንጫፎቜ እንዳፈራ ኚድር ገልጿል። ሂጀራ ባንክ ደግሞ በሊስት ወራት 14 ቅርንጫፎቜን ዹኹፈተ ሲሆን ኹ22 ሺህ በላይ ደንበኞቜ እንዳገኘ ሙባሚክ ይናገራል። ነገር ግን ኚወለድ ነጻ ባንኮቜ፣ አገልግሎቶቜን በተመቻ቞ ሁኔታ ለመተግበር ዚማያስቜሏ቞ው ሁኔታዎቜ አሁንም መኖራ቞ውን ዹሚጠቅሰው ኚድር፣ "ያለው ዹሕግ ማዕቀፍ ኹመደበኛው ጋር ዚተቆራኘ ነው።...ኚመንግሥት እሱን ኚማስተካኚል አኳያ ቀና ነገሮቜ አሉ" ብሏል። ሙባሚክ በበኩሉ በብሔራዊ ባንክ ደሹጃ ኚወለድ ነጻ ባንኮቜን ዚሚኚታተል እና ሞሪአን መሰሚት ያደሚገ ተቆጣጣሪ አካል ሊኖር ይገባል ብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-59521754
amh
business
ዚሊባኖስ ባንኮቜ ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቆሙ
ዚሊባኖስ ባንኮቜ ዚመንግሥት ዚፀጥታ ኃይሎቜ አስፈላጊውን ጥበቃ አላደሹጉልንም በሚል ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ ዚአገሪቱ ባንኮቜ ማኅበር ገለጞ። ደንበኞቜ ባለፈው ሳምንት እንዳይንቀሳቀስ ዹተደሹገውን ዚቁጠባ ሂሳባ቞ውን ለማግኘት በኃይል ታግዘው ገንዘባ቞ውን ዚመውሰድ ድርጊቶቜ መበራኚታ቞ውን ተኚትሎ ነው ዚሊባኖስ ባንኮቜ ማኅበር አገልግሎት መቆሙን ያስታወቀው። በአገሪቱ ዹሚገኙ ባንኮቜ ውስጥ ዚሚያገለግሉ ሠራተኞቜ መፍትሄ ማግኘት ያልቻሉ ዚደኅንነት ስጋት ገጥሟ቞ዋል ሲልም ማኅበሩ ገልጿል። ባሳለፍነው ሳምንት አንዲት ግለሰብ ዚልጆቜ መጫወቻ ሜጉጥ በመያዝ ለቀተሰቧ መድኃኒት መግዣ ዹሚሆን ገንዘብ ኚባንኩ ለመውሰድ በባኩ ውስጥ ሰዎቜን በማገቷ መነጋገሪያ ሆና ነበር። በሳምንቱ መጚሚሻ አርብ ቀን ብቻ ቢያንስ አምስት ሰዎቜ ገንዘባ቞ውን በኃይል ኚባንክ ለመውሰድ ጥሚት ያደሚጉበት ተመሳሳይ ክስተቶቜ ሪፖርት ተደርገው ነበር። በአሁኑ ጊዜ ሊባኖስ በኹፍተኛ ዚኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ ትገኛለቜ። ኹ80 በመቶ በላይ ዹሚሆነው ሕዝቧ ዚምግብ እና ዚመድኃኒት አቅርቊት ለማግኘት ዚሚያስቜለው ገቢ ዚለውም። ደንበኞቜ በባንኮቜ ውስጥ ያላ቞ውን ገንዘብ በኃይል በመጠቀም ዚመውሰድ እምጃ በሕበሚተሰቡ ዘንድ ድጋፍ አግኝቷል። ኹዚህ በፊት ምንም አይነት ዹወንጀል ሪኚርድ ዹሌላቾው ሰዎቜ ዚባንክ ሂሳባ቞ውን በጉልበት ለማንቀሳቀስ መጣራ቞ው በሕብሚተሰቡ ዘንድ በተስፋ መቁሚጥ ተገፋፍቶ ዹሚፈጾም ተደርጎ ይታያል። ዚሊባኖስ ዚመገበያያ ገንዘብ እኀአ ኹ2019 ጀምሮ ዋጋው እያሜቆቆለ፣ ብሎም በአገሪቱ ያለው ዹዋጋ ንሚት ኚቁጥጥር ውጪ መሆኑን ተኚትሎ ባንኮቜ ደንበኞቻ቞ው ዚሚያወጡትን ገንዘብ ገድበዋል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c99pqg8j2v8o
amh
business
በጥሬ ገንዘብ ዝውውር ላይ ዚተጣለው ገደብ ለምን አስፈለገ?
በኢትዮጵያ ኚባንኮቜና ኚማክሮ ፋይናንስ ተቋማት በሚወጣ ዚጥሬ ገንዘብ ላይ ዚተጣለው እገዳ ተግባራዊ መደሹግ ጀምሯል። ብሔራዊ ባንክ ያወጣው መመሪያ ተቋማትና ግለሰቊቜ ኚባንኮቜ በቀንና በወር ውስጥ በሚያወጡት ዚጥሬ ገንዘብ መጠን ላይ ገደብ ጥሏል። በዚህም መሰሚት አንድ ግለሰብ በቀን እስኚ 200 ሺህ ብር እንዲሁም በወር እስኚ 1 ሚሊዹን ብር በጥሬ ገንዘብ ኚባንኮቜ ማውጣት ዚሚቜል ሲሆንፀ ተቋማት ደግሞ በቀን እስኚ 300 ሺህ ብር እና በወር እስኚ 2.5 ሚሊዹን ብር በጥሬ ገንዘብ ማንቀሳቀስ እንደሚቜሉ ተገልጿል። ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ይናገር ደሮ (ዶክተር) ይህንን እርምጃ መውሰድ ያስፈለገው "ዚገንዘብ ዝውውርን ሥርዓት በማስያዝ ወንጀልንና ዚግብር ስወራን ለመኹላኹል ይሚዳል" በሚል ነው ብለዋል። ይህን ዚብሔራዊ ባንክ እርምጃን በተመለኹተ ዚተለያዩ ምክንያቶቜን በመጥቀስ ጥያቄ ዚሚያነሱ ሰዎቜ አሉ። ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያው ዋሲሁን በላይ አንድ አገር ላይ ዚኢኮኖሚ ፖሊስ ሲወጣ፣ ምጣኔ ሃብቱ እንዲሚጋጋ፣ እንዲሁም ኢኮኖሚው ባለበት ሁኔታ እንዲቀጥል ሲፈለግ ሁለት ዓይነት ኃይለ ፖሊሲዎቜን እንደሚኚተሉ ያስሚዳሉ። በጀት ምን መምሰል አለበት፣ ሰዎቜና ዚንግድ ተቋማቶቜ መክፈል ያለባ቞ው ግብር ምን ይመስላል ተብሎ ዚሚወሰንበትን እና ዚገቢዎቜ ሚኒስ቎ርና ዚገንዘብ ሚኒስ቎ር ዚሚቆጣጠሩት ፊሲካል ፖሊሲ አንዱ ሲሆን፣ ሞኒተሪ ፖሊሲ ደግሞ ዚብሔራዊ ባንክ ዚሚቆጠጣሚው መሆኑን ያስሚዳሉ። ብሔራዊ ባንክ ሲቋቋም ጀምሮ ዚአገሪቱ ዚገንዘብ አቅርቊት ምን መምሰል አለበት? ምን ያህል ገንዘብ ታትሞ በገበያ ውስጥ መሰራጚት አለባ቞ው? ዹሚለውን ዚመቆጣጠር ዚሥራ ድርሻው እንዳለው ያብራራሉ። በተጚማሪ ደግሞ በባንኮቜ በኩል ያለውን ዚወለድ መጠን፣ ዚሚቆጣጠሚው ብሔራዊ ባንክ መሆኑን ዚሚናገሩት አቶ ዋሲሁን፣ ብሔራዊ ባንክ በትናንትናው ዕለት ካሉት ሁለት ትልልቅ ስልጣኖቜ መካኚል በመጠቀም ዚገንዘብ አቅርቊት በገበያው ምን መምሰል እንዳለበት ወስኗል ሲሉ ያስሚዳሉ። እንደ ምጣኔ ሃብቱ ባለሙያ አስተያዚት ኹሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ዚገንዘብ መጠን ላለፉት ብዙ ዓመታት በእርግጠኝነት ማወቅ በጣም አስ቞ጋሪ ነው። "በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ኹ700 እስኚ 800 ቢሊዚን ብር ድሚስ በገበያው መሰራጚቱ ይታወቃል ዚሚሉት ዚምጣኔ ሃብቱ ባለሙያ እርሱንም ቢሆን በእርግጠኝነት ለማወቅ አስ቞ጋሪ ነው" ሲሉ ያለውን ፈተና ያብራራሉ። ስለዚህ እዚህ ገበያ ውስጥ ያለውን ገንዘብ ማወቅ እንደሚያስፈልግ በማንሳት "ዚገንዘብ መጠኑ ዚማይታወቅ ኹሆነ ዚተለያዩ ሕጋዊ ያልሆኑ ዚንግድ ሥርዓቶቜ ሊበራኚቱ ስለሚቜሉ ብሔራዊ ባንክ ያንን ለማወቅ አስቊ እንደወሰነው እገምታለሁ" ይላሉ። ሌላው መንግሥት ባይጠቅሰውም ዚገንዘብ እጥሚት ዚአገሪቱ አንዱ ቜግር መሆኑን ይጠቅሳሉ። "ጥሬ ገንዘብ አቅርቊት በጣም እያነሰ ነው። ዚኮሮናቫይሚስ ክስተትን ተኚትሎና በሌሎቜም ምክንያቶቜ ሰዎቜ ያላ቞ውን ገንዘብ በእጃ቞ው መያዝ ይፈልጋሉ" ዚሚሉት ባለሙያው ለመንግሥት ዚገንዘብ እጥሚት ገጥሞኛል ብሎ መናገር ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሱ ኚባድ መሆኑን ይናገራሉ። "ወሚርሜኙን ተኚትሎ ሰዎቜ ለመድኃኒት፣ ለሕክምናና ለምግብ ዹሚሆኑ ወጪዎቜን ብቻ ነው እያወጡ ዚሚገኙት" ዚሚሉት ባለሙያው በተጚማሪም ነገ በሚሆነው ነገር ላይ ተስፈኛ መሆን አለመቻል ገንዘብን በባንክ ለማስቀመጥ ፍላጎት እንደሚያሳጣ ይጠቅሳሉ። "አሁን በኹፍተኛ ሁኔታ ገንዘብ ኚባንክ ቀቶቜ እዚወጣ መሆኑ ግልጜ ነው" በማለትም ኚበሜታው በፊትም ቢሆን ዚልማት ባንክ ያልተመለሱ ዚተበላሹ ብድሮቜ እንዳሉት ሲናገር በርካታ ባለሃብቶቜ ብድር ወስደው መክፈል አልቻሉም ማለት እንደሆነም ያስሚዳሉ። ኢንቚስትመንት ላይ ያሉ ሰዎቜ ራሳ቞ው ብድራ቞ውን መክፈል እንዲቜሉ ማድሚግ ካልተቻለ ደግሞ ሰዎቜ ያስቀመጡት ገንዘብ ባንክ ቀት ውስጥ ዹለም ማለት መሆኑን በማስሚዳት ለገንዘብ እጥሚቱ ዚራሱ አስተዋጜኊ እንዳለው ያብራራሉ። "መንግሥት ግን ይህንን ውሳኔ ዚወሰንኩት እጥሚት ስለገጠመኝ ነው ብሎ ሊል አይቜልም" በማለትም ዚገንዘብ እጥሚቱ እዚገጠመ ነው ወደፊት ደግሞ በፍጥነት ሊገጥም መቻሉ ገሃድ መሆኑን ያስሚዳሉ። "ምክንያቱም ወደ በሜታው [ኮሮናቫይሚስ] ገና እዚገባንበት ነው ይላሉ። ወሚርሜኙ እዚተስፋፋ ሲመጣ፣ ዚሰዎቜ እንቅስቃሎ ሲገደብ፣ አሁን ገበያ ላይ ያሉት ነጋዎዎቜ አቅማቾው ሲዳኚም፣ ገንዘባ቞ውን በእጃ቞ው ይዘው መጠቀም ሲመርጡና ለአስፈላጊ ነገሮቜ ብቻ ሲያወጡ፣ ዚባንክ ቀት ሰልፍ ጠልተው እያወጡ ሲያስቀምጡ ወደፊትም ቢሆን እጥሚት መፈጠሩ አይቀርም ይላሉ ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያው ዋሲሁን በላይ። "ዜጎቜ በመጪው ጊዜ ላይ እርግጠኛ መሆን ዚማይቜሉ ኹሆነ ብራ቞ውን ስለሚይዙ ዚመቆጠብ አቅማቾው ደካማ ስለሚሆን ዚገንዘብ አቅርቊት እያነሰ ስለመጣ እርሱንም አስታኮ ዹወሰነው ይመስለኛል።" በተጚማሪነት ግን ኢንቚስትመንት እንዲያድግ ቁጠባን ለማበሚታታት አስቊ መንግሥት ዹወሰነው እንደሚመስላ቞ው ባሙያው ጠቅሰው "ገንዘብ ኚባንክና ኚፋይናንስ ሥርዓት ውጪ በጣም በኹፍተኛ ሁኔታ እንዲንቀሳቀስ አይፈቀድም።" ብዙ አገራቶቜ ይህንን ነገር እያስቀሩ መምጣታ቞ውን ገልጾው "ስለዚህ ብሔራዊ ባንክም ዹሆነ ቊታ ላይ ለጥሬ ገንዘብ ዝውውሮቜ ሥርዓት ማበጀት ነበሚበት" ብለዋል። ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያው ጉቱ ቎ሶ (ዶ/ር) ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እርምጃ ኚጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል ሲሉ እርምጃውን አጥብቀው ይተቻሉ። "ይሄ ይዞት ዚሚመጣው ነገር በጣም አደገኛ ነው። ኹዚህ በኋላ ባለሃብቱ ዹሚኹፈለውን ክፍያ በጥሬ ገንዘብ ይቀበልና ወስዶ ቀቱ ያስቀምጣል። ይህ ደግሞ ገንዘብ ወደ ባንክ ገብቶ እንቅስቃሎ እንዳይፈጠር ያደርጋል። ይሄ እርምጃ ኚሚያመጣው ጥቅም ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል" ይላሉ። ግብር ስወራን በተመለኹተ ጉቱ (ዶ/ር) እንደሚሉትፀ በኢትዮጵያ ዚሚጠበቅባ቞ውን ግብር ላለመክፈል 'ኪሳራ ደርሶብኛል' እያሉ ሪፖርት በማድሚግ ግብር ዚሚያሞሹ በርካታ ነጋዎዎቜ መኖራ቞ው አይካድም ይላሉ። "ነገር ግን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ሰዎቜን አሳደን ዚሚጠበቅባ቞ውን ግብር እንዲኚፍሉ ማድሚግ እንቜላለን ወይ? ይህ ዘላቂ መፍትሄ ያመጣል ወይ?" ሲሉ ይጠይቃሉ። ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያው እንደሚሉት ኹሆነ ይህ ዓይነት ዚመንግሥት ውሳኔፀ "ኚባንክ ውጪ ሊደሹግ ወደ ዚሚቜለው ልውውጥ ስለሚወስድ ምጣኔ ሃብቱን በአፍጢሙ ሊደፋ ይቜላል" ሲሉ ያስጠነቅቃሉ። ጉቱ (ዶ/ር) ይህ ዚመንግሥት ውሳኔ አገሪቱ ኮሮናቫይሚስ ኚሚያስኚትለው ዚምጣኔ ሃብት ቀውስ በኋላ ለማንሰራራት በምታደርገው ጥርት ላይ አሉታዊ ተጜእኖ ሊያሳድር እንደሚቜልም ያነሳሉ። "ኚኮሮናቫይሚስ ስርጭት በፊት ዚንግድ ባንክ ቅርንጫፎቜ ዚሚያበድሩት በቂ ገንዘብ አልነበራ቞ውም። ብሔራዊ ባንክ ራሱ ኹተቀማጭ ገንዘቡ ማሻሻያ እያደሚገ ለባንኮቜ ገንዘብ ዚሚለቅበት አጋጣሚዎቜ ነበሩ" ይላሉ ባለሙያው። አክለውም ኚወሚርሜኙ በኋላ ደግሞ እንደሚስተዋለው ዹዓለም ምጣኔ ሃብት እጅጉን ተጎድቷልፀ በኢትዮጵያም ዚፋይናንስ ተቋማት ለመደገፍ መንግሥት በብሔራዊ ባንክ በኩል 15 ቢሊዮን ብር እንዲቀርብ ማድሚጉን አስታውሰዋል። "መንግሥት ይህን ያደሚገው አበዳሪዎቜ ለተበዳሪዎቜ ጊዜ እንዲያራዝሙ፣ ዚወለድ መጠን እንዲቀንስ፣ ተጚማሪ ብድር ዹሚፈልጉ ብድር እንዲያገኙ፣ አምራ቟ቜ ምርታ቞ውን እንዲያስፋፉ ነው። "ለዚህ ደግሞ ጥሩ ዚገንዘብ አቅርቩ ወደ ኢኮኖሚው መፍሰስ አለበት እያልን አያሰብን ባለንበት ሰዓት ላይ ዚገንዘብ ዝውውር ላይ ገደብ መጣል ኚተባለው ነገር ጋር ዹሚቃሹን ዚምጣኔ ሃብት እርምጃ ነው ዹሚሆነው" ይላሉ። መንግሥት ኹዚህ ውሳኔ ላይ ለመድሚስ ኚተገደደብ ምክንያት አንዱ ሕገ-ወጥ ዚገንዘብ ዝውውርን ለመግታት በማሰብ ነው። ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያው ጉቱም (ዶ/ር) አሁን ያለንበትን ነባራዊ ሁኔታ ኚግምት በማስገባት ወጪ በሚደሹግ ዚገንዘብ መጠን ላይ ገደብ መጣል ዹሕገ-ወጥ ዚገንዘብ ዝውውርን ለመግታት ጠቀሜታ አለው በማለት ይስማማሉ። ይህንንም ሲያስሚዱ "ኚወሚርሜኙ በፊት ዹሰው እንቅስቃሎ እንደልብ ነበር። ሰዎቜ ገንዘብ በማዳበሪያ ጭነው ሃርጌሳ ይወስዳሉፀ ወደ መተማ ይሄዳሉ። አሁን ግን በቫይሚሱ ምክንያት ሰዎቜ እንደፈለጉት መንቀሳቀስ አይቜሉም። ስለዚህ ባንክ ለመጠቀም ይገደዳሉ" ይላሉ። ይህንንም በምሳሌ ሲያስሚዱ "አንድ ሰው ወደ ባንክ ገቢ ዹተደሹገውን ገንዘብ ላውጣ ቢልፀ ወጪ ዹተጠዹቀው ቅርንጫፋ ብዙ ገንዘብ ስለተጠዚቀ ሥራ መስራት አቆመ ማለት። ግለሰቡም ይህን ያክል ገንዘብ ኚዚት አመጣህ ተብሎ ይጠዚቃል። በዚህ መልኩ መቆጣጠር ይቜላል" በማለት እርምጃው ሊኖሹው ዚሚቜለውን ጠቀሜታ ያስሚዳሉ። ዚምጣኔ ሃብት ባለሙያው ዋሲሁን በላይበበኩላ቞ው ዚመንግሥት ውሳኔ መጥፎ አለመሆኑን ያስሚዳሉ። "ዚገንዘብ አቅርቊቱን በጣም በጣም መቆጣጠር አለበት። ምክንያቱም ዹዋጋ ንሚት ኚሚቀጣጠልባ቞ው ነገሮቜ አንዱ ኹፍተኛ ብር በገበያው ሲሰራጭ ነው። ሐሰተኛውን በር ኚትክክለኛው መለዚትም በጣም አስ቞ጋሪ ነው" በማለት መንግሥት እነዚህን ለመቆጣጠር አስቊ እንደሆነ ያምናሉ። "ውሳኔው ጥሬ ገንዘብ ዚመያዝ እንጂ ሰዎቜ ገንዘብ ማንቀሳቀስ ዚለባ቞ውም" ዹሚል አይደለም ዚሚሉት ባለሙያው፣ ኚጥሬ ገንዘብ ውጪ ዲጂታላይዝ በሆነ ገንዘብ ግብይት ማኹናወን ዚሚቻልበት ሥርዓት ካለ በሞባይል መገበያዚት፣ በኀቲኀም፣ በቌክ፣ በፖስ ማሜን መገበያዚት ዚሚቜሉ ኹሆነ ግብይቶቜ እንዲቆሙ አልተደሹገም ይላሉ። ስለዚህም ዚመሞመት መጠኑን ዚሚገደብ ምክንያት አለ ብለው እንደማያስቡ ዚሚናገሩት አቶ ዋሲሁንፀ ኹፍተኛ ገንዘብ ገበያ ላይ ተሚጭቶ ገንዘቊቹ ምርትና ምርታማነት ላይ ዚማያርፉ፣ ፍላጎትን ዚሚያሳድጉ ኹሆነ ዹዋጋ ግሜበትን ዚማቀጣጠላ቞ው እድል በጣም ኹፍተኛ መሆኑን ያሰምሩበታል።
https://www.bbc.com/amharic/news-52734564
amh
business
ኢትዮጵያ ግሜበትን ለመግታት ዚባንኮቜ ዚመጠባበቂያ ዚገንዘብ መጠን በእጥፍ እንዲያድግ ወሰነቜ
በኹፍተኛ ሁኔታ እያንሰራራ ያለውን ዹዋጋ ግሜበት ለመግታት ባንኮቜ ኚሚሰበስቡት ዚተጣራ ቁጠባ በኢትዮጵያ ብሔራዊ እንዲያስቀምጡት ዚሚጠበቅባ቞ውን ዚመጠባበቂያ ዚገንዘብ መጠን ወደ አስር በመቶ ኹፍ እንዲያደርጉት ተወስኗል። ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዳስታወቀው ኹዚህ ቀደም 5 በመቶ ዹነበሹውን ዚመጠባበቂያ ዚገንዘብ መጠን ኹፍ እንዲል ዹወሰነው በኢኮኖሚው ውስጥ ዹሚዘዋወሹውን ዚገንዘብ መጠን ለመቀነስ ቁጥብ ዚገንዘብ ፖሊስ ለማድሚግ ኹመወሰኑ ጋር ተያይዞ ነው። ኹዚህም በተጚማሪ ባንኮቜ ኚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዚሚበደሩበት ዓመታዊ ዚወለድ ምጣኔ ኹ13 በመቶ ወደ 16 በመቶ ኹፍ እንዲል መወሰኑም ተገልጿል። ይህ ዚባንኮቜ መጠባበቂያና ዚብሔራዊ ባንክ ዚማበደሪያ ወለድ ምጣኔ ኚዛሬው ዕለት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆንም ተገልጿል። በኢትዮጵያ ያለው ግሞበት በኹፍተኛ ሁኔታ እዚጚመሚ ሲሆን በሐምሌ ወር ዹነበሹው መጠን 26.4 መሆኑን ዚሮይተርስ ዘገባ አስነብቧል። በዓመቱ ውስጥ ዹነበሹው 20 በመቶ ዹሆነው ዚግሜበት መጠን በቅርቡ ኹፍተኛ ጭማሪ ያሳዚ ሲሆን መንግሥት ይህንን ለመግታት ዚተለያዩ ጥሚቶቜን፣ ማሻሻያዎቜንና ፖሊሲዎቜን እያወጣ ይገኛል። በቅርቡም ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንደ ህንፃዎቜ ያሉ ንብሚቶቜን እንደ መያዣነት ዹሚጠቀሙ ባንኮቜ ሁሉንም ብድሮቜ ለጊዜው እንዲታገድ ዚሚወስን አዲስ መመሪያ ወጥቷል። ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዹውጭ ምንዛሪንም በተመለኹተ ባንኮቜ ሲጠቀሙበት ዹነበሹው አሰራር ላይ ማሻሻያ ተደርጓል። በዚህም ማሻሻያ መሰሚት ባንኮቜ ኚወጪ ንግድ፣ ኚግለሰብ ሃዋላና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶቜ ኚሚያገኙት ዹውጭ ምንዛሬ ውስጥ 50 በመቶውን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድሚግ አለባ቞ው ተብሏል። ኹዚህ ቀደም ባንኮቜ ኹውጭ ቀጥተኛ ኢንቚስትመንት፣ ኚዲያስፖራ ሂሳብና ኚሌሎቜ ምንጮቜ ኚሚያገኙት ዹውጭ ምንዛሪ ሰላሳ በመቶውን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ እንዲያደርጉ ዚሚያዘውን መመሪያም ተሻሜሏል። ይህ አሰራርም ኹዚህ ቀደም በባንኮቜ በተደጋጋሚ ኹሚቀርበው ወቀሳ መካኚል ኹውጭ ኢንቚስትመንት፣ ኚዲያስፖራ ሂሳብና ኹውጭ ብድር ዹሚገኝ ዹውጭ ምንዛሪ ተቀንሶ ወደ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ መደሹግ ዚለበትም ለሚለውም ጥያቄ መልስ እንደሆነም ተገልጿል። ኚባንኮቜ በተጚማሪ ደንበኞቜን በተመለኹተ መያዝ ዚሚቜሉትን ዹውጭ ምንዛሪ መጠንም ማሻሻያ ተደርጓል። በባንኮቜ ዹውጭ ምንዛሬ ያስገኙ ደንበኞቜ በውጭ ምንዛሪ ሂሳባ቞ው ያለ ጊዜ ገደብ መያዝ ዚሚቜሉት ዹውጭ ምንዛሬ መጠን ኹ31.5 በመቶ ወደ 40 በመቶ ኹፍ ብሏል። ዚገንዘብ ተቋማትና ደንበኞቻ቞ው ሊኖራ቞ው ስለሚገባው ግንኙነት ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ መመሪያ አውጥቷል። አገሪቱ እዚሰራቜ ያለቜው ወጥ ብሔራዊ መታወቂያ እስኪሰጥ ድሚስ ዚገንዘብ ተቋማት ለደንበኞቻ቞ው ዹተለዹ ዹደንበኛ መለያ ቁጥር መስጠት አለባ቞ው ተብሏል። ደንበኞቜ ወይም ድርጅቶቜ ኚአንድ በላይ አካውንት ቢኖራ቞ውም ይህ ዚመለያ ቁጥር ተግባራዊ ይሆናል። ደንበኞቜ ማንኛውንም ዚባንክ አገልግሎት በሚጠቀሙበት ወቅት ገንዘብ ማውጣት፣ ማስቀመጥም ሆነ ኚሂሳብ ወደ ሂሳብ ማዘዋወርና ሌሎቜ ማንኛውም ዚባንክ አገልግሎቶቜን በተመለኹተ ዚገንዘብ ተቋማት (ባንኮቜ) ተመሳሳይ ቅፅ (ፎርም) መጠቀም አለባ቞ው። በዚህም አሰራር መሰሚት በአገሪቱ ውስጥ ዹሚገኙ ማንኛውም ባንኮቜም ሆነ ዚገንዘብ ተቋማት ለዚትኛውም ዚባንክ አገልግሎቶቜ ዹሚጠቀሟቾው ወጥና ተመሳሳይ ዹሆኑ ቅፆቜን እንደሆነ መመሪያው አስቀምጧል። ኹዚህም ጋር ተያይዞ ደንበኞቜ ትክክለኛ ያልሆነ ወይም አጠራጣሪ መሹጃ ዚሚሰጡ ወይንም መመሪያዎቜን ዚማያኚብሩ ኹሆነ ዚገንዘብ ተቋማቱ አገልግሎትን ዹመኹልኹል ይቜላሉ። ኹዚህም በተጚማሪ ባንኮቹ ዚእነዚህን ደንበኞቜ መሹጃ ለብሔራዊ ባንክና ለፋይናንስ መሹጃ ደኅንነት ማዕኹል ማስተላለፍ እንዳለባ቞ው ተጠቅሷል። ዚገንዘብ ተቋማቱ (ባንኮቜ) እነዚህን መመሪያዎቜ በተገቢው መልክ እንዲሰሩም ዚደንበኞቻ቞ውን ታሪክ ዚሚኚታተል አዲስ አደሚጃጀት ሊያዋቅሩ ይገባል እንዲሁም ዘመናዊ ዹቮክኖሎጂ አሰር መዘርጋት አለባ቞ው ተብሏል። ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኹዚህም በተጚማሪ ዚኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለባንኮቜ ለመድንና ለጡሚታ ዋስትና ድርጅቶቜ ቊንድ መሞጥ እንዲቜልም ውሳኔ አስተላልፏል። በዚህም መሰሚት ባንኮቜ ኚዓመታዊ ጠቅላላ ዚብድር ክምቜት አንድ በመቶ ዚልማት ባንክ ቊንድፀ ዚመድን ድርጅቶቜ ደግሞ ኚተጣራ ዓመታዊ ገቢያ቞ው ኹ15 በመቶ ያላነሰ ዚልማት ባንክ ቊንድ እንዲገዙ ተወስኗል። ይህ ዚልማት ባንክ ቊንድ መንግሥት ዋስትና ዹሚሰጠውና በተነፃፃሪ ዚተሻለ ወለድ ዚሚኚፈልበት እንደሚሆንም ተገልጿል።
https://www.bbc.com/amharic/news-58391135
amh
business
ዚቢትኮይን ዋጋ በ50 በመቶ በኹፍተኛ ሁኔታ አሜቆለቆለ
ዋጋው እያሜቆለቆለ ያለው ቢትኮይን፣ በአሁኑ ጊዜ ኹፍተኛ ቅናሜ በማሳዚት አንድ ቢትኮይን 34ሺህ ዚአሜሪካ ዶላር እዚተሞጠ ነው። ዚክሪፕቶኚሚንሲ አሻሻጩ ኮይንቀዝ ኚስድስት 6 ወራት በፊት ጣራ ነክቶ ዹነበሹው ቢትኮይን በአሁኑ ወቅት ዋጋው 50 በመቶ ቀንሷል ብሏል። በክሪፕቶኚሚንሲዎቜ ዚገበያ ድርሻ ቀዳሚ ዹሆነው ቢትኮይን ዋጋው መቀነሱ ዹተሰማው በመላው ዓለም ዚድርሻ ገበያዎቜ [ስቶክ ገበያ] መቀነሳ቞ውን ተኚትሎ ነው። ዚክሪፕቶካሚንሲዎቜ ዋጋ ኹዓለም ዚስቶክ ገበያ ጋር ተያይዞ ዋጋቾው ኹፍ እና ዝቅ ሲል ይስተዋላል። በ650 ቢሊዮን ዶላር ጠቅላላ ዋጋ ቢትኮይን ዚዓለማቜንን አንድ ሊስተኛ ዚክሪፕቶኚሚንሲ ጠቅላላ ድርሻ ይይዛል። በአሁኑ ወቅት ቢትኮይን በአንዳንድ አገራት ጹምር ይፋዊ መገበያያ እዚሆነ ነው። በቅርቡ መካኚለኛ አፍሪካ ሪፐብሊክ ቢትኮይንን ይፋዊ መገበያያ ያደሚገቜ ሲሆን ቢትኮይንን አገር አቀፍ መገበያያ በማድሚግ ኀል ሳልቫዶር ዚመጀመሪያዋ ናት። ኀል ሳልቫዶር ቢትኮይንን ይፋዊ መገበያያ ስታደርግ አይኀምኀፍን ጚምሮ ዚምጣኔ ሀብት ባለሙያዎቜ ውሳኔውን ተቜተው ነበር። ግብይት ለመፈጾም ክሪፕቶኚሚንሲዎቜ ለግለሰቊቜ ዚሚሰጡት ነጻነት እንዳለው ሁሉፀ ክሪፕቶኚሚንሲዎቜ በሕገ-ወጥ ዹተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አድርጎ ማቅሚብ ያስቜላሉ። በተጚማሪም ክሪፕቶኚሚንሲን በመጠቀም አፍራሜ ተልዕኮዎቜን በገንዘብ ለመደገፍ ይቻላል እንዲሁም ዚፋይናንስ ሥርዓት አለመሚጋጋትን ይፈጥራል በሚሉ ምክንያቶቜ ሥርዓቱ ይተቻል። ኚቢትኮይን ቀጥሎ ትልቁን ዚገበያ ድርሻ ዹሚይዘው ኢቲሪዚም በተመሳሳይ ባለፉት ቀናት ዋጋው ኹ10 በመቶ በላይ ቀንሷል። ባለፈው ሳምንት ዚአሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም እና አውስትራሊያን ጚምሮ በዓለም ዙሪያ ዹሚገኙ በርካታ ባንኮቜ ዹዋጋ ግሜበተን ለመቆጣጠር በሚል ዚወለድ መጠንን ኹፍ አድርገው ነበር። ይህም ተበዳሪዎቜ ብድር ዚሚወስዱበትን ዚወለድ መጠን ኹፍ አድርጓል። በርካታ ኢንቚስተሮቜ ዹዋጋ ግሜበት እና ዚብድር ወለድ መጠን ኹፍ ማለት በዓለም ምጣኔ ሀብት ላይ አሉታዊ ተጜእኖ ያሳድራል ዹሚል ስጋት አሳድሮባ቞ዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-61375822
amh
business
ኀሎን መስክ ዹግል ጀቱን ዚሚኚታተለውን ዚትዊተር ገጜ ባለቀት ሊኚስ ነው
ኀሎን መስክ በግል ጀቱ ዚት እንደተጓዘ ዚሚኚታተለውን ዚትዊተር ገጜ ባለቀት ሊኚስ ነው። ዹግል ጀቱ እንቅስቃሎ @ElonJet account በሚባለው ገጜ ለሕዝብ ይፋ መደሹጉ ዹልጁን ደኅንነት አደጋ ላይ እንደሚጥለው መስክ ተናግሯል። ይህ ዚትዊተር ገጜ ኚግማሜ ሚሊዮን በላይ ተኚታዮቜ አሉት። በዚህ ሳምንት ገጹን ትዊተር አግዶታል። ዚገጹ ባለቀት ዹ20 ዓመቱ ጃክ ስዊኒ ነው። በሚራ ዚሚኚታተሉ መተግበሪያዎቜን ተጠቅሞ ነው ዚመስክን ዹግል ጀት ዚሚኚታተለው። ዚመስክለ ጀት ሲነሳና ሲያርፍ ትዊተር ገጹ ላይ ይጜፋል። መስክ እንዳለው ስዊኒ እና ሌሎቜም ዚፍርድ ቀት ክስ ይጠብቃ቞ዋል። “ትላንት ማታ አንድ መኪና ልጄ ሊል ኀክስ ያለበትን መኪና ሲኚታተል ነበር። እኔ መኪናው ውስጥ ያለው መስያ቞ው ነው” ብሏል መስክ። ዚሰዎቜን እንቅስቃሎ በቀጥታ ለሕዝብ ይፋ ማድሚግ አደጋ ውስጥ ሊኚት እንደሚቜል ገልጿል። ዚመስክን ጀት ዚሚኚታተለው ወጣት ፍሎሪዳ ዚዩኒቚርስቲ ተማሪ ነው። ትዊተር ገጹን መርምሮ መርሕ ጥሶ በማግኘቱ እንዲዘጋ መወሰኑን ለሲኀንኀን ገልጿል። ወጣቱ ቢል ጌትስ፣ ጄፍ ቀዞስ እና ማርክ ዙኹርበርግን ጚምሮ ዚሌሎቜም ሀብታም አሜሪካውያን ዹግል ጀት እዚተኚታተለ ዚሚጜፋበ቞ው ዚትዊተር ገጟቜ አሉት። በተጚማሪም ኚሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና ሌሎቜም ታዋቂ ግለሰቊቜ ጋር ዹሚገናኙ ገጟቜም አሉ። ሁሉንም ገጟቜ ትዊተር አስወግዷ቞ዋል። መስክ እንዳለው፣ ወጣቱ ገጟቹን እንዲያጠፋ 5ሺህ ዶላር ለመክፈል ጠይቀውት ነበር። ወጣቱ ዚክፍያ ጥያቄው ኚቀሚበለት በኋላ፣ ኚፍያውን መፈጾም እንደማያስፈልግ በትዊተር በኩል እንደተገለጞ ለአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ተናግሯል። መስክ ኹወር በፊት ገጹን ላለመሰሹዝ ቢወስንም አሁን ግን “ሰዎቜ ያሉበትን ቊታ ዚሚያጋልጡ ገጟቜ ዚደኅንነት ስጋት ናቾው” ብሏል። ዚትዊተር ዚደኅንነት ክፍል ባወጣው ዚተሻሻለ መመሪያ “ዚሌሎቜ ሰዎቜን ዹግል መሹጃ ያለ ፈቃዳ቞ው መለጠፍ ክልክል ነው” ብሏል። መስክ ትዊተርን ኹገዛው በኋላ ዚተለያዩ ለውጊቜን እያደሚገ ይገኛል። ኚግማሜ በላይ ሠራተኞቹን ኚማባሚሩ ባሻገር በሳን ፍራንሲስኮ ዋና ቅርንጫፍ ለሚገኙ ሠራተኞቜ ዚቀት ኪራይ መክፈል ማቆሙም ተዘግቧል። ትዊተርን ኹገዛ በኋላ ለኀሌክትሪክ መኪና አምራቜ ድርጅቱ ተስላ ዹሚሰጠው ትኩርት በመቀነሱ ኢንቚስተሮቜ ስጋት ገብቷ቞ዋል። በዚህ ሳምንት በሊስት ተኚታታይ ቀናት 22 ሚሊዮን ድርሻ ዹሾጠ ሲሆን፣ ይህም 3.58 ቢሊዮን ዶላር ያወጣል። መስክ በተስላ ያለው ድርሻ 40 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cgl1m1yn2p4o
amh
business
ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን ኚነጮቜ ባነሰ ሁኔታ ዚሚኖሩባት ደቡብ አፍሪካ
ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን ኹነጭ አቻዎቻ቞ው በሊስት እጥፍ ያነሰ ገቢ እንደሚያገኙ አንድ ጥናት ይፋ አደሚገ። ጥናቱ በደቡብ አፍሪካውያን መካኚል ያለውን ያልተመጣጠነ ገቢን ዹተመለኹተ ሲሆንፀ ኚአገሪቱ 80 በመቶ ዚሚሆኑት ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን ዹወር ገቢያ቞ው በአማካኝ 13000 ብር ገደማ ሲሆንፀ ዹነጭ ደቡብ አፍሪካውያን ግን 38 ሺህ ብር አካባቢ እንደሆነ ተቀምጧል። • “ኚብሔርም ኚሐይማኖትም በላይ ሰውነት ኚሰሃራ በሹሃ ስቃይ አውጥቶኛል" • ፓርቲዎቜ በክልላቾው ባሉ ዩኒቚርስቲዎቜ ዚሚታዚው ግጭት እንዲቆም ጥሪ አቀሚቡ • ኚንቲባ ታኚለ ኡማ በስህተት ለወጣው ዚኀርትራ ካርታ ይቅርታ ጠዹቁ ጥናቱ አክሎም እንዎት ዚተለያዩ ብሔሮቜ በማኅበራዊ መደብ ውስጥ እንደተቀመጡ አሳይቷል። ጥናቱ በአገሪቱ ዚስታስቲክስ መሥሪያ ቀት እኀአ ኹ2002 እስኚ 2017 ድሚስ ዹተሰበሰበን መሹጃ ዹተጠቀመ መሆኑ ዹተነገሹ ሲሆንፀ ይህም ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን በሥራ ማጣት ክፉኛ እንደሚ቞ገሩ ያሳያል። እነዚህ ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን ዹግል ዹሕክምና ተቋማትን መጎብኘት፣ መጠለያና መብራት ዚማግኘት ጉዳይም ቅንጊት እንደሆነባ቞ው ጥናቱ ያመለክታል። ጥናቱፀ ዚደቡብ አፍሪካ ኚተሞቜን ኚዓለማቜን አገራት መካኚል ኹፍተኛ ያልተመጣጠነ ገቢ ያላ቞ው ዜጎቜ ዚሚኖሩባት አገር አድርጓታል። ጥናቱ ለበርካታ ዓመታት በአገሪቱ አኚራካሪ ለነበሹው ጉዳይ ጠቅለል ያለ ምልኚታን በማስቀመጥ መሹጃን ዹሰጠ መሆኑ ተነግሮለታል። በብሔሮቜ መካኚል ኹፍተኛ ዹሆነ ዚሀብት ልዩነት እንዲኖር ካደሚኩጉ ምክንያቶቜ አንዱ ዚአፓርታይድ ውጀት ነው ዚተባለ ሲሆን፣ አፓርታይድ በቁጥር አነስተኛ ዚሆኑት ነጮቜ አገሪቱ ያላትን ውስን ሀብት ያለስስት እንዲጠቀሙና ሀብት እንዲያካብቱ አድርጓል ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/50443851
amh
business
በኢንተርኔት መቋሚጥ ኢትዮጵያ ኚናይጄሪያ ቀጥሎ በአፍሪካ ኹፍተኛ ገንዘብ አጥታለቜ - ሪፖርት
ባለፈው ዚአውሮፓውያን ዓመት በኢንተርኔት መቋሚጥ ኚሰሃራ በታቜ ኹሚገኙ ዚአፍሪካ አገራት መካኚል ኢትዮጵያ ኚናይጄሪያ በመቀጠል ኹፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንዳጣቜ አንድ ሪፖርት አመለኚተ። ባለፈው ዓመት በዓለም ዙሪያ ሆን ተብለው ዹተፈጾሙ ዚኢንተርኔት አገልግሎት መቋሚጊቜ በአገራት ላይ ያስኚተሉትን ኪሳራ በተመለኹተ ቶፕ ቮን ቪፒኀን ባወጣው ሪፖርት ላይ በአፍሪካ ናይጄሪያ፣ ኢትዮጵያና ሱዳን በቀዳሚነት ተቀምጠዋል። በመላው ዓለም መንግሥታት በአገራ቞ው ውስጥ ዚኢንተርኔት አገልግሎቶቜን በማቋሚጣ቞ው በአጠቃላዩ ዚምድራቜን ምጣኔ ሀብት ላይ ዹ5.5 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራን ማስኚተላ቞ውን ሪፖርቱ አመልክቷል። በዚህም መሠሚት ኚሁለት ሳምንታት በፊት በተጠናቀቀው ዚፈሚንጆቹ ዓመት በተለያዩ ዚአገሪቱ አካባቢዎቜ ዚኢንትርኔት አገልግሎት እንዲቋሚጥ በመደሹጉና ዚማኅበራዊ ትስስር መድሚኮቜ በመዘጋታ቞ው ኢትዮጵያ 164.5 ሚሊዮን ዶላር እንዳጣቜ ተገልጿል። ኚአንድ ዓመት በላይ በቀጠለው ዚትግራይ ጊርነት ምክንያት በክልሉ ዚኢንተርኔት አገለግሎት መቋሚጡን ዹጠቀሰው ሪፖርቱ፣ ባለፈው ግንቊት ወር ዹተሰጠው ብሔራዊ ፈተና በማኅበራዊ ሚዲያ መድሚኮቜ ላይ ሟልኮ ወጥቷል በሚል በመላው አገሪቱ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ኢንስታግራም ኚአገልግሎት ውጪ እንደነበሩ ጠቅሷል። እንደ ሪፖርቱ በአንድ ዓመት ውስጥ በአገሪቱ ዹሚገኙ ዚተለያዩ አካባቢዎቜ ኚኢንተርኔት አገልግሎት ውጪ ሆነው ዚቆዩት ለ8,760 ሰዓት ሲሆን ዚማኅበራዊ ሚዲያ ትስስር መድሚኮቜ ደግሞ ለ104 ሰዓት ተዘግተው ቆይተው ነበር። በዚህም ሳቢያ በኢትዮጵያ ኹ21 ሚሊዮን በላይ ሰዎቜ በኢንተርኔትና በማኅበራዊ ሚዲያ መስተጓጎል መ቞ገራ቞ውንና 165 ሚሊዮን ዶላር ዹሚጠጋ ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳት መድሚሱን አመለክቷል። ዓመታዊው ሪፖርቱ በዓለም ዙሪያ ያጋጠሙ ዋነኛ ዹሆኑና ሆን ተብለው ዚተቋሚጡ ዚኢንተርኔት አገልግሎቶቜን በመመዝገብ ዹተነተነ ሲሆን፣ በዚህም ዚደሚሱ ምጣኔ ሀብታዊ ኪሳራዎቜና አገልግሎት ዹተነፈጉ ሰዎቜን ብዛት አቅርቧል። በዓለም አቀፍ ደሹጃ በኢንተርኔት መቋሚጥ ኹፍተኛ ኪሳራ ዚገጠማት አገር ምሥራቅ እስያዊቷ አገር ምያንማር ስትሆን፣ ይህም በአገሪቱ ዹጩር ጄነራሎቜ ዚተካሄደውን መፈንቅለ መንግሥትን ተኚትሎ ነው። ባለፈው ዓመት በምያንማር ኢንተርኔት ለ12,238 ሰዓታት ዹተቋሹጠ ሲሆን ይህም ዹ2.8 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራን አስኚትሎባታል። ሁለተኛዋ ደግሞ አፍሪካዊቷ ናይጄሪያ ስትሆን ሆን ተብሎ ኢንተርኔት በመቋሚጡ ምክንያት 104.4 ሚሊዮን ሕዝብ ኚአገለግሎት ውጪ ሆኖ 1.5 ቢሊዮን ዶላር እንድታጣ አድርጓታል ተብሏል። ኚኢንተርኔት መቋሚጥ በተጚማሪ አገራት ዚተለያዩ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ዚትስስር መድሚኮቜንም ለይተው አገልግሎት እንዳይሰጡ ያደርጋሉ። በዚህም ባለፈው ዓመት ኹሁሉም በበለጠ ዕቀባ ተጥሎበት ዹነበሹው ትዊተር ሲሆን፣ በተኚታይነት ፌስቡክና ዋትስአፕ በአንዳንድ አገራት ውስጥ አገልግሎታ቞ው እንዲቋሚጥ ተደርጓል። በአጠቃላይ ባለፈው ዚአውሮፓውያን ዓመት በዓለም ዙሪያ በሚገኙ 21 አገራት ውስጥ 50 ዹሚሆኑ ዋነኛ ዚሚባሉ ዚኢንተርኔት መቋሚጊቜ በተለያዩ ምክንያቶቜ እንዳጋጠሙ ተመዝግቧል። ይህም በአጠቃላዩ ዹዓለም ምጣኔ ሀብት ላይ ዹ5.45 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራን በማስኚተል ኹቀደመው ዓመት በ36 በመቶ ኹፍ ማለቱን ዚቶፕ ቮን ቪፒኀን ሪፖርት ዓመልክቷል። ኢንተርኔት በተቋሚጠባ቞ው አገራት ውስጥ 486.2 ሚሊዮን ሰዎቜ ኚአገልግሎት ውጪ ለመሆን ዚተገደዱ ሲሆን፣ ኢንተርኔት በመንግሥታት ሲቋሚጥ ኚተጚማሪ ዚሰብአዊ መብት ጥሰቶቜ ጋር እንደሚያያዙም አመልክቷል። በዚህም ሳቢያ በምርጫ፣ በመሰብሰብና በመናገር ነጻነቶቜ ላይ ጥሰቶቜ ያጋጥማሉ። በዘመናዊው ዓለም ዚኢንተርኔት አገልግሎት ኚመሠሚታዊ ዚሰዎቜ ፍላጎቶቜ ውስጥ እዚታዚ ያለ ሲሆን፣ ኢንተርኔት ለበርካታ ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሎዎቜ ዋነኛው መሳሪያ በመሆኑ በተለያዩ ምክንያቶቜ መቋሚጥ በሚያጋጥምበት ጊዜ ዚሚያስኚትለው ኪሳራ ቀላል ዚሚባል አይደለም።
https://www.bbc.com/amharic/news-59988907
amh
business
ዹአፍና ዚአፍንጫ መሾፈኛ ጭምብል ፍለጋና ዹዋጋ መናር በአዲስ አበባ
አዲስ አበባ ውስጥ ዹአፍና ዚአፍንጫ መሾፈኛ ጭንብል ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በኹፍተኛ ገንዘብ ሲሞጥ እንደነበሚና በመደብሮቜ ውስጥ ማግኘት እንዳልቻሉ ቢቢሲ ያናገራ቞ው ነዋሪዎቜ ገለጹ። አርብ ዕለት አዲስ አበባ ላይ ዚጀና ጥበቃ ባለስልጣናት ዚመጀመሪያው ዹተሹጋገጠ ዚኮሮናቫይሚስ ታማሚ በኢትዮጵያ ውስጥ ኹተገኘ በኋላ ስጋት ዚገባ቞ው ሰዎቜ ዚፊት ጭንብልና ፈሳሜ ዚእጅ ማጜጃ ውህዶቜን በመግዛት ላይ ና቞ው። ዚቢቢሲ ያናገራ቞ው ዚአዲስ አበባ ነዋሪዎቜ እንዳሉት በሜታው አሳሳቢ ኹመሆኑ ዚተነሳ ሊኹላኹለው ይቜላል ዚተባሉ ነገሮቜን እዚገዙ መሆናቾውን ነገር ግን ዚጭንብሎቹና ፈሳሜ ዚንጜህና መጠበቂያዎቜ [ሳኒታይዘር] እንደልብ እንደማይገኙ ኹተገኙም ዋጋቾው በሚያስደነግጥ ሁኔታ መናሩን ገልጞዋል። አዲስ አበባ ውስጥ ዹሚገኙ አብዛኞቹ ዚመድሃኒት መደብሮቜም ዚፊት ጭንብልና ሳኒታይዘር እንደሌላ቞ው በሚለጥፉት ማስታወቂያም ሆነ በተጠዹቁ ጊዜ ዚሚሰጡት ምላሜ እንደሆነ ቅዳሜ ዕለት በተለያዩ ዹኹተማዋ ክፍሎቜ ዹሚገኙ ፋርማሲዎቜን ዹተመለኹተው ዚቢቢሲ ዘጋቢ ገልጿል። በማኅበራዊ መገናኛ ብዙሃን ላይም በርካቶቜ ዚፊት ጭንብል ስለመጥፋቱና ስለመወደዱ ገጠማቾውን በጜሁፍና በምስል እያሰፈሩ ነው። ጭንብሉ ያለባ቞ው ፋርማሲዎቜ ሹዘም ያሉ ሰልፎቜ ዚታዩ ሲሆን ውስን ቁጥር ያላ቞ውን መሞፈኛዎቜን በመደበኛው ዋጋ ሲሞጡ እንደነበር ተገልጿል። ቢቢሲ በስልክ ያናገራ቞ው በአዲስ አበባ ዹሚገኙ ሁለት ዚመድሃኒት መደብሮቜ ዚፊት መሾፈኛ ጭምብል እንደጚሚሱና ሲሞጡ ዹነበሹውም ቀደም ሲል በነበሹው ዋጋ እንደሆነ ገልጞዋል። ዹኹተማዋ ባለስልጣናትም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ተፈላጊ በሆኑ ምርቶቜ ላይ ዹዋጋ ጭማሪ በማድሚግ በሚሞጡ ዚንገድ ተቋማት ላይ እርምጃ እዚወሰዱ መሆናቾውን አመልክተውፀ ኅብሚተሰቡም ጥቆማ እንዲሰጥ ጠይቀዋል። በርካታ ሰዎቜ በሜታውን ሊኹላኹል ይቜላል በማለት ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ጭንብሎቜን ለመግዛት ወደ መድሃኒት መደብሮቜ ቢሄዱም ለማግኘት እንደተ቞ገሩ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። "ሰው ሁሉ እዚገዛ በመሆኑ ለልጆቌም ሆነ ለእራሎ ዹሚሆን ማስክ ለመግዛት ቅዳሜ ኚሰዓት በኋላ በዚደሚስኩበት ቊታ ያሉ ፋርማሲዎቜን ብጠይቅም ላገኝ አልቻልኩም" ያሉት ዚሁለት ልጆቜ እናትና አዲስ አበባ ውስጥ አብነት ዚሚባለው አካባቢ ነዋሪ ዚሆኑት ወ/ሮ መብራት አስቻለ ና቞ው። ወይዘሮ መብራት ለቢቢሲ እንደተናገሩት ጎሚቀቶቻ቞ው ጭንብሉን እስኚ 200 ብር በሚደርስ ዋጋ ኚሰዎቜ ላይ መግዛታ቞ውን እንደሰሙ ነገር ግን ይህን ያህል ገንዘብ በማውጣት ለቀተሰባ቞ው መግዛት ኚባድ ስለሆነባ቞ው እንደተዉት ገልጞዋል። ዚጭንብሉን አስፈላጊነት በተመለኹተ ዚሰሙት በዙሪያ቞ው ካሉ ሰዎቜ መሆኑን እንጂ ኚባለሙያዎቜ ዚተነገራ቞ው ነገር እንደሌለ ዚሚጠቅሱት ወ/ሮ መብራት "በሞታው አሳሳቢ በመሆኑ ዚምቜለውን ላድርግ በማለት ነው ኚአንዱ ፋርማሲ ወደ ሌላው በመሄድ ስጠይቅ ዹነበሹው" ይላሉ። ተለያዩ ሰዎቜ በማኅበራዊ መገናኛ መድሚኮቜ ላይ ዚሚሰጡት አስተያዚቶቜም ኹዚሁ ጋር ዚሚመሳሰሉ ናቾው ዚፊት መሾፈኛ ጭንብል ኹ150 እስኚ 500 ብር በሚደርስ ዋጋ እዚተሞጡ መሆናቾውን ዚሚያመለክቱ ና቞ው። ኚፊት መሾፈኛ ጭምብሎቜ በተጚማሪ ዚእጅ ማጜጃ ፋሳሟቜም ዋጋቾው ዹጹመሹ ሲሆን ተህዋሲያንን ያጠፋሉ ተብለው ዹሚነገርላቾው ሳሙናዎቜም ተፈላጊነታ቞ው ጚምሯል። ዋጋቾውም በዚያው ልክ መጚመሩን ነዋሪዎቜ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ዹኹተማው መስተዳደርም "ዚመጀመሪያው ዚኮሮናቫይሚስ ተጠቂ ተገኝቷል" ዹሚለው መሹጃ ኚወጣ በኋላ በተለያዩ ሞቀጊቜ ላይ ያልተገባ ዹዋጋ ጭማሪ ዚሚያደርጉ ነጋዎዎቜን ለመቆጣጠር ግብሚ ኃይል አቋቁሞ እርምጃ እዚወሰደ መሆኑን አሳወቋል። ኚኮሮናቫይሚስ መኚሰት ጋር በተያያዘ አፍን አፍንጫን ዹሚሾፍኑ ጭምብሎቜ በስፋት በዓለም ዙሪያ ጥቅም ላይ እዚዋሉ ነው። በዚህም ሳቢያ በበርካታ አገራት ውስጥ ዚጭንብሎቹ እጥሚት እዚተኚሰተ በመሆኑ አምራ቟ቜ ዚጭንብል ምርታ቞ውን ኹፍ እንዲያደርጉ በዓለም ዚጀና ድርጅት ተጠይቀዋል። ዹዓለም ዚጀና ድርጅት እንደሚገምተው በዚወሩ 89 ሚሊዮን ዚሚደርስ ዚፊት ጭምብሎቜ ያስፈልጋሉ። በኮሮናቫይሚስ ስጋትና በተሳሳተ አመለካኚት ሳቢያ እነዚህ ጭንብሎቜ ያላግባብ ጥቅም ላይ ስለሚውሉ ዚሚዚስፈልገው ቁጥር ኹዚህም በላይ እንደሚሆን ይገመታል። ድርጅቱ እንዳለውም ዚፊት ጭንብሎቜ በስፋት ጥቅም ላይ በመዋላቾውና ሰዎቜ በብዛት እዚገዙ በማስቀመጣ቞ው ዚተነሳ ዹህክምና ባለሙያዎቜ በዚዕለቱ በሚጠቀሙት አቅርቊት ላይ ጫና እዚፈጠሚ መሆኑን አመልክቶፀ ይህም በዚህ ዚወሚርሜን ጊዜ ህሙማንን በመርዳት ሥራ ላይ ዚተጠመዱ ዹህክምና ባለሙያዎቜ ለኮሮናቫይሚስና ለሌሎቜ በሜታዎቜ ተጋላጭ ሊያደርጋ቞ው ይቜላል ሲል ስጋቱን ገልጿል። ዹዓለም ዚጀና ድርጅት እንደሚለው ዚኮሮናቫይሚስን ለመካላኚል በሚል ሁሉም ሰው ዹአፍና ዚአፍናጫ መሾፈኛ ጭንብል ማድሚግ አያስፈልገውም። ጭንብሉን ማድሚግ ያለባ቞ው ዚሚያስነጥሱና ዚሚያስሉ ኹሆነ እንዲሁም በበሜታው ዹተጠሹጠሹ ወይም ዚተያዘን ሰው ዚሚቀርቡና ዚሚንኚባኚቡ ሰዎቜ ብቻ ነው። ለእነዚህ ሰዎቜ ጭንብሉን ማድሚግ ብቻ በቂ አይደለምፀ በውጀታማ ሁኔታ በሜታውን ለመኹላኹልም በመደበኛነት እጃ቞ውን በሳሙናና በውሃ መታጠብ ወይም አልኮል ነክ በሆኑ ፈሳሟቜ እጃ቞ውን ማጜዳት ይጠበቅባ቞ዋል። በተጚማሪም ጭንብሉን መጠቀም ያለባ቞ው ሰዎቜ እንዎት መጠቀምና በተገቢው ሁኔታ እንዎት መወገድ እንዳለበትም ማወቅ ይገባ቞ዋል ሲል ዹዓለም ጀና ድርጅት ይመክራል። ስለዚህም በአዲስ አበባና በሌሎቜ ስፍራዎቜ ዚተጠቀሱት አይነት ዚበሜታው ስጋቶቜ ሳይኖሩ ጭምብልን ኚሚገባው በላይ ኹፍተኛ ገንዘብ እያወጡ መግዛት በሜታውን ለመኹላኹል ዹሚኖሹው ጠቀሜታ ዝቅተኛ መሆኑን ዚጀና ጥበቃ ሚኒሰቮር መክሯል። እነዚህ ለአጭር ጊዜ ጥቅም ላይ ውለው ዚሚጣሉት ዚፊት መሾፈኛ ጭንብሎቜ ጥብቅ ብለው አፍንጫና አፍን ዹሚሾፍኑ ካለመሆና቞ው ባሻገር ሹጅም ጊዜን አያገለግሉም። ዚማስነጠስና ዚማሳል ምልክት ዚሚታይባ቞ውን ወይም በኮሮናቫይሚስ ኚሚጠሚጠሩ ሰዎቜ ጋር ዚግድ መቅሚብ ያለባ቞ው ሰዎቜ ዚሚጠቀሙባ቞ው ዚፊት መሾፈኛ ጭንብሎቜ በቀላሉ በላብ ስለሚባላሹ ወዲያው ወዲያው መቀዹር አለባ቞ው። ስለዚህ ዚኢትዮጵያ ጀና ጥበቃ ሚኒስ቎ርም ሆነ ዹዓለም ጀና ድርጅት እንደሚመክሩት ዚተጠቀሱት ምልክቶቜ እስካልታዩ ድሚስ ሁሉም ሰው ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ጭንብል ማድሚግ አያስፈልጋ቞ውም። ኚዚያ ይልቅ ግን ዚበሜታው ስጋት ለማስወገድ ኚሚያስሉ፣ ኚሚያስነጥሱ ወይም ትኩሳት ካለባ቞ው ሰዎቜ ጋር ዹሚኖርን ንክኪ ማስወገድ፣ እጅን በሳሙናና በውሃ መታጠብ ካልሆንም ተህዋሲያንን በሚያስወዱ ማጜጃዎቜ እጅን ማጜዳት ኹሁሉ በበለጠ ጠቃሚ ነው። በተጚማሪም እጅን ሳይታጠቡ ዓይንን፣ አፍንጫንና አፍን አለመንካት እንዲሁም መጚባበጥን ማስወገድ ዚቫይሚሱን መስፋፋት ለመግታት መወሰድ ካለባ቞ው ዚጥንቃቄ እርምጃዎቜ መካኚል ይጠቀሳሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-51894637
amh
business
ኮሮናቫይሚስ፡ ዚአሜሪካ ታቜኛው ምክር ቀት ጆ ባይደን ያቀሚቡትን ዹ1.9 ትሪሊዚን ዶላር ድጎማ አፀደቀ
ዚአሜሪካው ፕሬዚደንት ጆ ባይደን በኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ወቅት አሜሪካዊያንን ለመርዳት ያቀሚቡት ዹ1.9 ትሪሊዚን ዶላር ዚኢኮኖሚ ማነቃቂያ ማዕቀፍ በተወካዮቜ ምክር ቀት ፀደቀ። ዚድምፅ አሰጣጥ ሁኔታው ኚፓርቲ ወገንተኝነት ጋር ዚተያያዘ ነበር። ሁሉም ሪፐብሊካኖቜ ተቃውመውታል። ሁለት ዲሞክራቶቜም ገንዘቡ በጣም ብዙ ነው ሲሉ በመቃወም ሪፐብሊካኖቜን ተቀላቅለዋል። ማዕቀፉ በሚቀጥለው ሳምንት ዚአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዲሞክራቷ ካማላ ሃሪስ ሰብሳቢ በሆኑበት ዹሕግ መወሰኛው ምክር ቀት ይቀርባል። ይህ ምክር ቀት ኚዚግዛቱ እኩል 2 እንደራሎዎቜ ዚሚሞሉት ዚመቶ ወኪሎቜ ሾንጎ ነው። ባለ ትልቅ ሥልጣንም ነው። ምክር ቀቱ ዝቅተኛ ዚክፍያ መጠንን በእጥፍ ማሳደግ ዹሚለውን ሃሳብ ውድቅ አድርጓል። ይህ ሹቂቅ ሕግ ግን አሁንም ዚአሜሪካ ዝቅተኛ ክፍያ ጭማሬን አካቷል። ይህ እንዎት እንደሚፈታ ግልፅ ዹሆነ ነገር ዚለም። ምንም እንኳን በምክር ቀቱ ይህ ነጥብ እንዳይካተት ቢደሚግም ዹምክር ቀቱ አፈ ጉባኀ ናንሲ ፔሎሲፀ ሁሉም ዚቀሚቡት እቅዶቜ እንደሚያልፉ ተናግሚዋል። ዝቅተኛ ክፍያን ማሳደግ ዚዲሞክራቶቜ ዋነኛ ግብ ነው። አንዳንድ ዚዲሞክራት መሪዎቜ በሰዓት ኹ15 ዶላር በታቜ ዹሚኹፍሉ ቀጣሪዎቜን ለመቅጣት እያሰቡ ነው። ይህ ዚገንዘብ ማዕቀፍ ዚኮሮናቫይሚስ ክትባት ስርጭትን እና ምርመራን ለማሳደግ እንዲሁም ኢኮኖሚውን ለማሚጋጋት ያለመ ነው። ማዕቀፉ ለሁሉም አሜሪካዊያን ኹሚሰጠው 1 ሺህ 400 ዶላር ዚገንዘብ ድጎማ ጋር ተደማምሮ ለቀተሰብ ዹሚሰጠውን ድጎማ 1 ትሪሊዚን ዶላር ገንዘብን ያካትታል። ኹዚህም ባሻገር ወሚርሜኙን ለመዋጋት ዹሚውል 70 ቢሊዮን ዶላር እና ለአነስተኛ ንግዶቜ ማነቃቂያ 110 ቢሊዚን ዶላርንም ይጚምራል ። ለቀተሰብ፣ ለአነስተኛ ዚንግድ ተቋማትንና ዚግዛት መንግሥታት ዚአስ቞ኳይ ጊዜ ድጋፍ ይሆናልም ተብሏል። ዲሞክራቶቜ ቅዳሜ ጠዋት በተደሹገው ዚድምፅ አሰጣጥ ሂደት በቂ ድምፅ አግኝተዋል። በዚህም ፕሬዚደንት ባይደን በኮቪድ -19 እዚተፈተኑ ያሉትን አሜሪካዊያን ለመርዳት ባሰቡት 'ዚአሜሪካ መታዳጊያ እቅድ' አሾናፊ ሆነዋል። ይሁን እንጂ ሪፐብሊካን እቅዱ አላስፈላጊ በሆነ መጠን ብዙ እና ኚወሚርሜኙ ጋር ተያያዥነት በሌላቾው ዲሞክራሲያዊ ጉዳዮቜ ዹተሞላ ነው ብለዋል። ዲሞክራቶቜ በላዕላይ ምክር ቀቱ ጥብቅ ክርክር ይጠብቃ቞ዋል ተብሏል። ዲሞክራቱ ጆ ባይደን በአሜሪካ በመቶ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜን ዹገደለውን ወሚርሜኝ ለመዋጋት ቃል መግባታ቞ው ይታወሳል።
https://www.bbc.com/amharic/news-56221851
amh
business
ዚተሰናባቹ 2013 ዓመት ዓበይት ምጣኔ ኃብታዊ ክስተቶቜ
ኢትዮጵያ 2013ን ተሰናብታ አዲሱን ዓመት ልትቀበል ዚቀራት ጥቂት ቀናት ና቞ው። ተሰናባቹን ዓመት ዘወር ብለን በምናይበት ወቅት አገሪቷ በጊርነት ምክንያት በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዜጎቿ ዚተቀጠፉበት፣ በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ቀት አልባ ሆነው በቜግር ውስጥ ዚሚገኙበት፣ ኹፍተኛ ዹዋጋ ንሚት ዚብዙዎቜን ናላ እያዞሚ ባለበት ነው ያሳለፉት። ፈታኝ በሚባል ዚታሪክ ሂደት ውስጥ ያለቜው አገሪቷ በምትሞኘውም ዓመት ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጞጥታ ምክር ቀት ዋነኛ ርዕሰ ጉዳይ፣ ዚኃያላኑ መንግሥታት መነጋገሪያ፣ በባለስልጣናቷ ላይ ዹጉዞ ዕቀባ ዚተጣለባትና ኚጫፍ ጫፍ ያሉ ዹዓለም ሚዲያዎቜ ዋና ርዕስም ሆናለቜ። አገሪቷ ኚትግራይ ጊርነት ጋር ተያይዞም በሚሃብና በመብት ጥሰቶቜ ስሟ በተደጋጋሚ ዚሚጠቀስ ሆኗል። ኚጊርነት በተጚማሪ ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ አገሪቷ ላይ ጫና ያሳደሚ ኹመሆኑ አንፃር በርካታ ጋሬጣዎቜ ዚተደቀኑበት ዓመት ሆኖ ማለፉ አሌ አይባልም። ተሰናባቹ ዓመት ኹፍተኛ ዹዋጋ ግሜበት ዚታዚበት፣ ኚምጣኔ ሀብት ቀውሰ ጋር በተያያዘ ኀምባሲዎቜ ዚተዘጉበት፣ አገሪቷ ዚመገበያያ ገንዘብ ኖት ዚቀዚሚቜበት፣ አዲስ ዚ቎ሌኮም ፈቃድ ዚተሰጠበት ወቅት ነው። ኹዚህም በተጚማሪ በርካታ ዚፋይናንስ ተቋማትን ዚተመለኚቱ መመሪያዎቜ ዚወጡበት እንዲሁም ኢትዮጵያ ለአስርት ዓመታት ሲጠበቅ ዹነበሹው ዚንግድ ሕጓን ያሻሻለቜው በተሰናባቹ ዓመት ነው። ለመሆኑ ዚተሰናባቹ ዓመት ዓበይት ዚምጣኔ ሀብት ክስተቶቜ ምን ነበሩ? እንዲህ ቃኝተና቞ዋል። ዚብር ኖቶቜ ቅያሪ ኢትዮጵያ ዹ2012 ዓ.ምን ዚምጣኔ ሀብት ማሻሻያዋን ዚጀመሚቜው ኚሁለት አስር ዓመታት በላይ ስትገለገልባ቞ው ዚነበሩ ዹ10፣ ዹ50፣ እና ዹ100 ብር ዚገንዘብ ዓይነቶቜን በመቀዹርና አዲስ ብር ኖቶቜን ይፋ በማድሚግ ነው። በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ዚባለ ሁለት መቶ ብር ኖትም አሳትማለቜ። አገሪቷ ነባሮቹን ዚብር ኖቶቜ ለመቀዹር ሌላ ወጪ ሳይጚምር ለህትመት ብቻ 3.7 ቢሊዮን ብር ማውጣቷን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ አስታውቀዋል። አገሪቱ በዋነኝነት ወደ ቅያሪ ዚገባቜው ባንኮቜ ዹገጠማቾውን ዚገንዘብ ቜግር ለመቅሹፍና ቁጠባ቞ውን እንዲያሳድግ፣ ሕጋዊ ያልሆነ ዚገንዘብ ዝውውርን ኚኢኮኖሚው እንቅስቃሎ እንዲወገድ፣ ዹዋጋ መሚጋጋት እንዲኖር፣ ዚመንግሥት ገቢ እንዲያድግ ያስቜላል በሚል ነው። በቢሊዮኖቜ ዹሚቆጠር ገንዘብ ኚባንክ ውጪ በመኖሩ ኹፍተኛ ዹሆነ ዚጥሬ ገንዘብ እጥሚት (ሊኩዊዲቲ) ኹማጋጠሙ ጋር ኹመሆኑ ተያይዞም ቅያሪው ይህንንም እንደሚቀርፍ ታምኗል። ኚቅያሪው ጋር ተያይዞ ኚወጡ መመመሪያዎቜ ጋር በተያያዘ አንዳንድ ለውጊቜም ታይተዋል። በአንድ ሰው እጅ ሊቀመጥ ዚሚቜለው ዚገንዘብ መጠን በ1.5 ሚሊዮን ብር መወሰኑ፣ ግለሰቊቜ ኚባንክ በቀን ማውጣት ዚሚቜሉት ኹፍተኛ ዚገንዘብ መጠን 200 ሺህ ብር፣ እንዲሁም ኩባንያዎቜ በጥሬ ገንዘብ ማውጣት ዚሚቜሉት 300 ሺህ ብር ገደብ መመሪያዎቜ ጥያቄ ያጫሩ ሆነው አልፈዋል። ብሔራዊ ባንክ በወቅቱ እንዳስታወቀው ዚታተመው ብር በኢኮኖሚው ውስጥ ኹሚዘዋወሹው በበለጠ እንዲሆንና ለመጠባበቂያም እንዲሆን 262 ቢሊዮን ብር ታትሟል። በ1983 ዓ.ም ዚታተመው ዚብር መጠን ስምንት ሚሊዮን ብር ብቻ ዹነበሹ ሲሆን ዚዘንድሮው በአገሪቱ ዚብር ቅያሪ ታሪክ ኹፍተኛ ተብሎ ተመዝግቧል። ዚትግራይ ጊርነት ያስኚተለው ቀውስ በጥቅምት መጚሚሻ አካባቢ በትግራይ ክልል ዹተኹሰተው ደም አፋሳሜ ጊርነት በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜን ኹመግደሉ በተጚማሪ ኹፍተኛ ዹሆነ ሰብዓዊና ዚምጣኔ ሀብት ቀውስ አስኚትሏል። ጊርነቱ እስካሁን ድሚስ አገሪቷን ምን ያህል እንዳስወጣት ይፋዊ መሹጃ ባይኖርም፣ በትሬዲንግ ኢኮኖሚክስ ትንበያ መሰሚት ወታደራዊ ወጪዋ በመጪው ታኅሣሥ ወር መጚሚሻ ላይ ወደ 502 ሚሊዮን ዶላር ሊደርስ ይቜላል ተብሏል። ባለፈው ዓመት ወጪዋ 460 ሚሊዮን ዶላር ነበር። ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅትም ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉ቎ሬዝም ጊርነቱ ኚአንድ ቢሊዮን ዶላር ኚአገሪቱ ግምጃ ቀት አስወጥቷል ብለዋል። አገሪቱ ለጊርነቱ መዋዕለ ንዋይዋን ኚማፍሰሷ በተጚማሪ ኚትግራይ ክልል ታገኝ ዹነበሹውን ገቢም አጥታለቜ። ጊርነቱ በተጀመሹ በወራት ውስጥ ኚትግራይ ክልል በሊስት ወራት ውስጥ መሰብሰብ ዚነበሚበት ሁለት ቢሊዮን ብር አለመገኘቱን ዚገቢዎቜ ሚኒስ቎ር አስታውቆ ነበር። ሚኒስ቎ር መስሪያ ቀቱ ጥር ወር መጚሚሻ ላይ ዚስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃጾሙን ለሐዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ለገቢ፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮቜ ቋሚ ኮሚ቎ ባቀሚበው መሹጃ መሰሚት በበጀት ዓመቱ ለመሰብብሰብ ኚታቀደው 290 ቢሊዮን ብር ውስጥ በትግራይ ክልል ለማግኘት ዚታሰበው 7.8 ቢሊዮን ብር እንደነበር አስሚድቷል። ኚጊርነቱ በፊት በነበሩት ሊስት ወራት 1.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰብስቧል። ዚትግራይ ክልል ኹፍተኛ ግብር ኚፋዮቜ ውስጥ ዚምትጠቀስ ስትሆን ኹዚህ በተጚማሪም ኢትዮጵያ በዚዓመቱ ወጪ ንግድ ኚምታደርጋ቞ው ምርቶቜ ውስጥ ዘጠኝ በመቶ ዹክልሉ ድርሻ ነው። ዚኢትዮጵያ አጠቃላይ ዚኢኮኖሚ ዕድገት ባለፈው ዓመት በ2020 ኚነበሚበት 6 በመቶ በዚህ ዚአውሮፓውያን ዓመት በ2021 ሁለት በመቶ ብቻ እንደሚያድግ ተገምቷል። ይህም በሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ኚታዚው በጣም ዝቅተኛ እንደሆነ ዚአይኀምኀፍ መሹጃ ያሳያል። ኹፍተኛ ዹዋጋ ግሜበት በኢትዮጵያ ውስጥ እዚተባባሰ ዚመጣው ዚኑሮ ውድነት ዚበርካታ ኹተሜን ህይወት እዚፈተነና ዚማይወጡት ተራራ ሆኖባ቞ዋል። ዚኑሮ ውድነት አመላካቜ ዹሆነው ዹዋጋ ግሜበት በነሐሮ ወር ወደ 30.4 በመቶ አሻቅቧል። ዚኢትዮጵያ ስታስቲክስ ኀጀንሲ መሹጃ እንደሚያሳዚው በነሐሮ ወር ዚምግብ ዋጋ ግሜበት ኹ32 በመቶ አገሪቷ በአስርት ዓመታት አይታው ወደማታውቀው 37.6 በመቶ ደርሷል። ምግብ ነክ ያልሆኑ ሞቀጊቜን ዹዋጋ ግሞበት በምናይበት ወቅት ኹ19 በመቶ ወደ 20.8 በመቶ አሻቅቧል። ዹዋጋ ግሜበቱ ጊርነት በሚካሄድባ቞ውና ምንም ዓይነት ዚመሠሚታዊ አገልግልቶቜ በሌለባ቞ው እያሻቀበ ሲሆን ዚመሠሚታዊ ሞቀጊቜ መመናመኑን ኚስፍራው ዚወጡ መሚጃዎቜ ያሳያሉ። ለምሳሌ ያህል ጥር መጚሚሻ ላይ በነበሹው መሹጃ መሰሚት ዚምግብ ዋጋ ግሜበቱ በትግራይ ኹ36 በመቶ በላይ ነበር። ዚአገሪቷ ዹዋጋ ግሜበት ኚሊስት አስርት አሃዝ በላይ መሆኑ መሠሚታዊ በሚባሉ ሞቀጊቜም ዋጋ እያናሚው ሲሆን በዜጎቜ ላይም ኹፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጫና እያሳደሚ ነው። ኢትዮጵያ ለዓመታት ዚነበራት ዚተዛባ ዚንግድ ሥርዓት በተለይም ዚወጪና ዚገቢ ንግድ አለመመጣጠን፣ ጊርነትና አለመሚጋጋት፣ ዚብር መዳኚም ዹፈጠሹው ግሜበት፣ ዚወጪ ንግድ መቀዛቀዝ፣ ዚውጪ ምንዛሪ እጥሚት ተደራርበው ለዋጋ ንሚቱ ኹፍተኛ አስተዋፅኊ እያደሚጉ ይገኛሉ። ኹዚህም በተጚማሪ በመላው ዓለም ዹተኹሰተው ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ በምጣኔ ሀብቱ ቀውስ ላይ ጫና እያሳደሚ ይገኛል። ዚኢትዮጵያ መንግሥት በአገሪቱ ዚሚታዚውን ዹዋጋ ግሜበት ወደ አንድ ነጠላ አሀዝ አውርዶ ዹዋጋ መሚጋጋት ለማምጣት እዚጣሚ ዹሚገኝ ሲሆን ኹሰሞኑም ዹተወሰኑ መሠሚታዊ ዚምግብ ሞቀጊቜን ላልተወሰነ ጊዜ ኚቀሚጥና ታክስ ነጻ ማድሚጉን አስታውቋል። ኹነሐሮ መጚሚሻም ጀምሮ ዚምግብ ዘይት፣ ስኳርና ሩዝ ኹውጭ ሲገቡም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጞምባ቞ው ኚቀሚጥና ታክስ ሙሉ በሙሉ ነፃ ሲሆኑ ስንዎ ኹውጭ ሲገባ ኚቀሚጥና ታክስ ነፃ እንዲሆን ተወስኗል። ፓስታ እና ማኮሮኒ ኹውጭ ሲገቡም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጞም ኚተጚማሪ እሎት ታክስ ነፃ እንዲሆኑ፣ እንዲሁም ዚዶሮ እንቁላል ኚተጚማሪ እሎት ታክስ ነጻ እንዲሆን ተወስኗል። ዹውጭ ምንዛሪ ዋጋ መናር ለዓመታት ዚአገሪቱ አንገብጋቢ ቜግር ሆኖ ዹዘለቀው ዹውጭ ምንዛሪ እጥሚት በዘንድሮው ዓመትም በኹፍተኛ ሁኔታ ተባብሷል። በዓመታት ኹፍተኛ በሚባል ሁኔታ ጭማሪ እያሳዚ ዚመጣው ዚምንዛሪ ተመን ንሮ ይፋዊ በሆነው ዚባንክ ግብይት መሰሚት አንድ ዶላር በ45.6 ብር እዚተመነዘሚ ይገኛል። በትይዩ ወይም በተለምዶ ጥቁር ገበያ በሚባለው ገበያ ዚምንዛሪ ተመን ደግሞ አንድ ዶላር በ70 ብር አካባቢ እዚተመነዘሚ ሲሆን ኹመደበኛው ገበያ ጋር ያለው ልዩነት ኹ20 ብር በላይ መሆኑ ዚምጣኔ ሀብት ባለሙያዎቜን ስጋት ላይ ዚጣለ ክስተት ሆኗል። በተለይም አገሪቷ ዹውጭ ምንዛሪ ተመን በገበያ ፍላጎት ዚሚመራ ሥርዓት እንዲዘሚጋ ኹመወሰኗና ኚገበያው ጋር ለማቀሚራሚብ እዚሰራቜ ባለበት ወቅት ይህንን ያህል ልዩነት መፈጠሩ ዚምጣኔ ሀብት ባለሙያዎቜ ጥያቄ ሆኗል። ዚብር ዚንምዛሪ ተመን ማሜቆልቆል በትግራይ ክልል ኚተነሳውና በአማራና አፋር ክልል ኹተዛመተው ጊርነት ጋር ተያይዞ አገሪቷ ካጋጠማት አለመሚጋጋት በተጚማሪ ዚብር ተገቢውን ዋጋ መያዝ (ዲቫሉዌት) ዚማድሚግ ጥሚትና ዚንግድ ሚዛን ጉድለት እንደሆነም ባለሙያዎቜ ይናገራሉ። በተለይም ዚአገሪቷ ዚተዛባ ዚንግድ ሥርዓት ጋር በተያያዘ እዚታዚ ያለው ዚወጪና ዚገቢ ንግድ አለመመጣጠን በተጚማሪ ዹዓለም አቀፍ ዚገንዘብ ተቋማት ለዓመታት መንግሥት ብር ኚዶላር ጋር ያለው ምንዛሪ ተመን መዳኚም እንዳለበት ኚመጎትጎታ቞ው ጋር ተያይዞ ይህ ተግባራዊ መሆኑ ብሩን አዳክሞታል። አገሪቱ በዓመት ወደ 14 ቢሊዮን ዶላር ዹሚጠጋ እቃዎቜን ኹውጭ ዚምታስገባ ሲሆን 3.4 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ዚሚያወጣ ምርቶቜን ወደ ውጪ ትልካለቜ። ምንም እንኳን ይህ አሀዝ ጉድለት ቢታይበትም ዚአገሪቱ ዚወጪ ንግድ ገቢ ኚሊስት ቢሊዮን ዶላር ሲሻገር ዚመጀመሪያው ነው። አዲስ ዚ቎ሌኮም ፈቃድ ኢትዮጵያ ለ126 ዓመታት ያህል በመንግሥት ልማት ስር ዹነበሹውን ዚ቎ሌኮም ኢንዱስትሪ ክፍት በማድሚግ ዚ቎ሌኮም ፈቃድ ዚሰጠቜው በዘንድሮው ዓመት ነው። በኢትዮጵያ ዚ቎ሌኮም ገበያ ለመሰማራት በተደሹገው ዓለም አቀፍ ጚሚታ በኬንያው ሳፋሪኮም ዚሚመራው ጥምሚት በ850 ሚሊዮን ዶላር አሞንፏል። ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያ ዹተሰኘው ይህ ጥምሚት በዘርፉ አሉ ዚሚባሉ ስመ ጥር ዚ቎ሌኮም ኩባንያዎቜንና ተቋማትን በቅንጅት ዚያዘ ሲሆን እነዚህም ሳፋሪኮም፣ ቮዳኮም ግሩፕ፣ ቮዳፎን ግሩፕና ሱሚቶሞ ኮርፖሬሜንና ሲዲሲ ግሩፕ ዚተካተቱበት ነው። ጥምሚቱ በኢትዮጵያ ዹሚሰጠውን ዚ቎ሌኮም አገልግሎት ኚመጪው ጥር 2014 ዓ.ም በኋላ ይጀምራል ተብሏል። ዋነኛው ዚአገሪቱ አገልግሎት ሰጪ ኢትዮ ቎ሌኮም 40 በመቶ ድርሻውን ለውጪ ባለሀብቶቜ፣ 5 በመቶውን ለኢትዮጵያውያን እና 55 በመቶውን በመንግሥት ይዞታ ይቀጥላል ተብሏል። ኢትዮጵያ ኢትዮ቎ሌኮምን ጚምሮ ሌሎቜ ዚመንግሥት ልማት ድርጅቶቜን ድርሻ ለመሞጥ ዚወሰነቜው በዋነኝነት ያላትን ኹፍተኛ ዕዳ ለመክፈል ሲሆንፀ በተጚማሪነት ዚ቎ሌኮምን ተደራሜነት ለመጹመርና አገልግሎቱን ለማቀላጠፍ እንደሆነም ይጠቀሳል። ኢትዮጵያ ዚ቎ሌኮም አገልግሎት ፈቃድን ለመስጠት ወደ ገበያው መግባት ዚሚሹ ፍላጎታ቞ውን እንዲገልጹ ሲጠዚቅ 12 ዚ቎ሌኮም ኩባንያዎቜ በኢትዮጵያ ዚ቎ሌኮም ዘርፍ ውስጥ ለመሳተፍ ፍለጎት እንዳላ቞ው ገልጾው ነበር። ኚእነዚህ ውስጥም ዚፈሚንሳዩን ኊሬንጅ ጚምሮ ሳዑዲ ቎ሌኮም ኩባንያ፣ ሊኩዊድ ቎ሌኮም፣ እንዲሁም ዚዩናይትድ አሚብ ኀምሬትስ ኢቲሳላትን ጚምሮ ሌሎቜ ኩባንያዎቜ አፈግፍገዋል። ለዚህም አንደኛው ምክንያት ሆኖ ዹተጠሰው ዚአገሪቱ ሕግ ለውጭ ተቋማት በሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ለመሰማራት አለመፍቀዱ ጋር ተያይዞ እንደሆነ ተገልጿል። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ሁለተኛውን ዚ቎ሌኮም ፈቃድ ጚሚታም እንደምታወጣ በገለፀቜበት ወቅት ዚአገልግሎት ፈቃድ ዚሞባይል ገንዘብ መገበያያን እንዲጚምር ተደርጓል። በተያያዘም ኢትዮ ቎ሌኮም በድምፅ፣ በመልዕክት፣ በኢንተርኔት ተወስኖ ዹነበሹውን አገልግሎት በማስፋት ዹቮሌ ብር ዚሞባይል አገልግሎት አስጀምሯል። ተቋሙ ኚቻይናው ሑዋዌ ኩባንያ ጋር በመተባበር ተግባራዊ ያደሚገው ቮሌ ብር ለአስር ሚሊዮኖቜ ደንበኞቹ በስልካ቞ው ገንዘብ ለማስተላለፍና እና ለግብይት አገልግሎትም ይውላል ተብሏል። ኢትዮ ቎ሌኮም በአምስት ዓመት 33 ሚሊዮን ደንበኞቜን ለማገልገልና 3.5 ትሪሊዚን ብር ለማንቀሳቀስ ማቀዱም ተዘግቧል። ዹውጭ አበዳሪዎቜ ለኢትዮጵያ ብድር መልቀቅ ማቅማትና ዹናሹው ዕዳ ለኢትዮጵያ ዋነኛ አበዳሪ ዚሚባሉ ዚገንዘብ ተቋማት ኹ11 ቢሊዮን ዶላር በላይ ተጚማሪ ብድር ለመልቀቅ እያንገራገሩ ነው ተብሏል። በዋነኝነትም ዹነዚህ ተቋማት ስጋት ተጚማሪ ብድር ለአገሪቱ መስጠት ዹበለጠ ጫና ውስጥ ይኚታታል እንዲሁም መክፈል አቋሟን ዹበለጠ ሊያዳክም ይቜላል ኹሚል ስጋት ጋር ዚተያያዘ ነው። ዚቻይናው ኀክዚም ባንክ ለኢትዮጰያ ለመስጠት ቃል ዚገባውን 339 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆኑ ተነግሯል። ኹዚህም በተጚማሪ ዹዓለም ባንክ አንድ አካል ዹሆነው ዹዓለም አቀፉ ዚልማት ትብብር ማኅበር (ኢንተርናሜናል ዎቚሎፕመንት አሶሲዚሜን) 3.3 ቢሊዮን ዶላር፣ ዹዓለም ዚገንዘብ ተቋም (አይኀምኀፍ) 2.7 ቢሊዮን ዶላር፣ ዚኢትዮጵያ ዋነኛ አበዳሪ ቻይና 1.4 ቢሊዮን ዶላርና ሌሎቜም አበዳሪዎቜ በያዝነው አመት እስኚ መጋቢት ድሚስ ይሰጣሉ ተብሎ ቢጠበቅም እስካሁን አልተለቀቀም ዚተባለውም በዚህ አመት ነው። ኹዚህም ጋር በተያያዘ ግዙፍ ዚልማት ፕሮጀክቶቜ ግንባታ ሊያስተጓጉል እንደሚቜል ተሰግቷል። ኹሰሞኑም ዚኢትዮጵያ መንግሥት ኹአገር ውስጥና ዹውጭ ውዝፍ እዳው እስኚ አውሮፓውያኑ ሐምሌ መጚሚሻ ድሚስ 2.4 ትሪሊዮን ብር ሆኖ መመዝገቡን ሪፖርተር ጋዜጣ ዚገንዘብ ሚኒስ቎ርን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። በዘገባው መሰሚት ብሔራዊ ባንክ ባለፈው አንድ ዓመት ባደሚገው ዚብር ምንዛሬ ተመን ለውጥ ምክንያት ዚብር ዚመግዛት አቅምም በኹፍተኛ ደሹጃ በመውሚዱ አጠቃላይ ዚአገሪቱ እዳ በ221. 5 ቢሊዮን ብር እንዳሻቀበም ዘገባው አስነብቧል። ዚአገሪቱ ብሔራዊ ዕዳ በዚህ ዓመት 60 ቢሊዮን ዶላር ወይም ኹጠቅላላ ዹአገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒ) 70 በመቶ ይደርሳል ተብሏል። ብሔራዊ ባንክና አዳዲስ መመሪያዎቹ ብሔራዊ ባንክ በዘንድሮው ዓመት ኚአምስት ጊዜ በላይ ገንዘብ ኚሒሳብ ወደ ሒሳብ ማዘዋወር ዹሚኹለክለው ሰርኩላርን ጚምሮ፣ ዚባንኮቜ መመስሚቻ ካፒታል አምስት ቢሊዮን ብር እንዲሆን ዹሚሉና ሌሎቜ ተጚማሪ አዳዲስ መመሪያዎቜን አውጥቷል። ባንኩ በነሐሮ ወር ኹዚህ ቀደም ባንኮቜ ይሰሩበት ዹነበሹውን ቀት፣ ሕንፃ፣ መሬትና ሌሎቜም ንብሚቶቜን በመያዣነት ተጠቅመው ብድር ዚሚሰጡበትን አሰራር አግዷል። ባንኩ ይህንን እርምጃ ዹወሰደው በኮኖሚው ውስጥ አሻጥር ታይቷል በሚል ሲሆን በማይንቀሳቀሱ ንብሚቶቜ መያዣነት ዹሚሰጠው ብድር እግድ እስኚ መቌ እንደሆነ አልተጠቀሰም። ኹዚህም በተጚማሪ በቅርቡ በኹፍተኛ ሁኔታ እያንሰራራ ያለውን ዹዋጋ ግሜበትን ለመግታት ባንኮቜ ኚሚሰበስቡት ዚተጣራ ቁጠባ በኢትዮጵያ ብሔራዊ እንዲያስቀምጡት ዚሚጠበቅባ቞ውን ዚመጠባበቂያ ዚገንዘብ መጠን ወደ አስር በመቶ ኹፍ እንዲያደርጉት ተወስኗል። ኹዚህ ቀደም 5 በመቶ ዹነበሹውን ዚመጠባበቂያ ዚገንዘብ መጠን ኹፍ እንዲል ዹተደሹገው በኢኮኖሚው ውስጥ ዹሚዘዋወሹውን ዚገንዘብ መጠን ለመቀነስ ቁጥብ ዚገንዘብ ፖሊስ ለማድሚግ ኹመወሰኑ ጋር ተያይዞ ነው። ኹዚህም በተጚማሪ ባንኮቜ ኚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዚሚበደሩበት ዓመታዊ ዚወለድ ምጣኔ ኹ13 በመቶ ወደ 16 በመቶ ኹፍ እንዲል ተወስኗል። ኹዚህም በተጚማሪ ዹውጭ ምንዛሬንም በተመለኹተ አዲስ መመሪያ ዹተላለፈ ሲሆን ኚወጪ ንግድ፣ ኚግለሰብ ሃዋላና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶቜ ኚሚያገኙት ዹውጭ ምንዛሬ ውስጥ 50 በመቶውን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድሚግ አለባ቞ው ተብሏል። እነዚህ በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ላይ ኚታዩት ጉልህ ክስተቶቜ መካኚል ዚተወሰኑት ና቞ው።
https://www.bbc.com/amharic/news-58489178
amh
business
በኬንያ ኚኀሌክትሪክ ማስተላለፊያ ዹሚሰሹቅ መርዛማ ዘይት ለምግብ ማብሰያነት እዚተሞጠ ነው ተባለ
ዚኬንያ ዚኀሌክትሪክ አቅራቢ ድርጅት ኹሃይል ማስተላላፊያ ወይም ትራንስፎሚመር ላይ እዚተሰሚቀ እንደ ማብሰያ ዘይት ዹሚሾጠው ፈሳሜ መሰሹተ ልማቶቹ ላይ ጉዳት በማድሚስ በሚሊዮን ዶላር ዹሚቆጠር ኪሳራ እያስኚተለ እንደሆነ ገለጞ። ዚኬንያ ኀሌክትሪክ ሃይል ወንጀለኞቜ ፈሳሹን ኚትራንስፎርመሮቹ ውስጥ በማውጣት ለሬስቶራንቶቜ እና በመንገድ ዳር ምግብ ለሚያዘጋጁ በሜያጭ ቀርቩ ምግብ ለማብሰል እና ለመጥበስ እንደሚሞጥ አስታውቋል። ኚምግብ ዘይት ዋጋ መጹመር ጋር ተያይዞ ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ እዚተስፋፋ ዚመጣው ይህ ድርጊት አንዳንድ ዚንግድ ድርጅቶቜን እነዚህ ዹሚዘሹፉ ዘይቶቜን መግዛትን ጚምሮ ወዳልተለመዱ ዚምግብ ማብሳያ አማራጮቜ እንዲሄዱ አድርጓ቞ዋል። ዚምግብ ዘይት ዚሚመስለው እና በትራንስፎርመር ውስጥ ዹሚገኘው ፈሳሞ ለሰው ልጅ ጀና አደጋ ዹሆነ እና ኹፍተኛ ዚጀና ጠንቅ ዚሚያስኚትል መሆኑን ዚጀና ባለሙያዎቜ ያስጠነቅቃሉ። ሌሎቜ ወንጀለኞቜ ደግሞ ዚግለሰቊቜ ወይም ዚንግዶቜ ተቋማትን ዚኀሌክትሪክ ኃይል አቅርቊት በማቋሚጥ መልሶ ለመቀጠል ገንዘብ ይጠይቃሉ። በኬንያ 20 ዹሚጠጉ ትራንስፎርመሮቜ እንደወደሙ ወይም ጉዳት እንደደሚሰባ቞ው እና በማዕኹላዊ ኬንያ በኀሌክትሪክ መሰሹተ ልማቶቜ ላይ ዹሚደርሰው ጉዳት እዚጚመሚ መምጣቱን ዚኬንያ ኀሌክትሪክ ሃይል አስታውቋል። በኬንያ ቢያንስ 22 ሰዎቜ ኹዚህ ወንጀል ጋር በተያያዘ ቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያ቞ው በፍርድ ቀት እዚታዚ ይገኛል። እዚተፈጞሙ ባሉ ስርቆቶቜ ምክንያት ኹፍተኛ ዹሃይል መቆራሚጥ ዹገጠመው ዚኬንያ ኀሌክትሪክ ሃይል አሁኑ ላይ ዹሃይል መሰሹተ ልማቶቜን ማውደም ስለሚያስኚትለው አደጋ በአገር አቀፍ ደሹጃ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ዘመቻ ጀምሯል። ኚወራት በፊት በኀሌክትሪክ መሰሹተ ልማቶቜ ላይ ዹተፈጾሙ ዝርፊያዎቜ በሃገሪቱ ታይቶ በማይታወቅ ደሹጃ ዹሃይል መቆራሚጥ አስኚትሏል።
https://www.bbc.com/amharic/61020009
amh
business
‘እጅ ዚበዛበት’ ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ ዕጣ
ኹሰሞኑ ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ ዕጣ ጋር ተያይዘው በተኚሰቱ ቜግሮቜ ምክንያት ዕጣው ውድቅ እንዲሆን ውሳኔ ተላልፏል። በበርካቶቜ ዘንድ መነጋገሪያ ዹሆነውና ውዝግብ ባስኚተለው ዕጣ ውስጥ መሳተፍ ዚነበሚባ቞ው 79 ሺህ ዹሚሆኑ ተመዝጋቢዎቜ ቢሆኑም፣ በድብቅ ዹተዘጋጁ 172 ሺህ ያህል ሰዎቜ በዕጣው ውድድር ተሳታፊ እንዲሆኑ ተደርገዋል ተብሏል። በዚህም 93 ሺህ ዹሚሆኑ ሰዎቜ ተገቢ ባልሆነ መንገድ ዚጋራ መኖሪያ ቀት ለማግኘት በተዘጋጀው ዕጣ ውስጥ መካተታ቞ው ተገልጿል። ኚአስራ አምስት ዓመታት በላይ ያስቆጠሚው ይህ ዚአዲስ አበባ ኹተማ ዚጋራ ቀቶቜ ግንባታ እና ቀቶቹን ዚማስተላለፍ ሂደት በተለይም ዕጣ አወጣጡ ጋር ተያይዞ ኚቅሬታዎቜ፣ ወቀሳዎቜና ሐሜቶቜ ነጻ ሆኖ አያውቅም። ዚቀቶቹ ግንባታ ጥቃት፣ ግንባታ቞ው እና መሠሹተ ልማቶቻ቞ው ያለመሟላት በዹጊዜው ዚሚነሳ ጉዳይ ቢሆንም፣ በቀት ቜግር እዚተንገላታ ዕድሉ ይደርሰኛል ብሎ ዚሚጠብቀው ነዋሪ ዋነኛው ቅሬታ ግን ቀቶቹን ዚማስተላፍ ሂደቱ ወይም ዕጣው ሆኖ ቆይቷል። ኹዚህ በፊት በነበሩት ሂደቶቜ ምዝገባው ውስጥ ያልተካተቱ ሰዎቜ በባለሥልጣንት ትዕዛዝ ቀቶቹ እንዲሰጣ቞ው ሲደሚግ መቆዚቱን ዘወትር ዚሚነሳ ጉዳይ ነው። በግንባታ ዕቃዎቜ መወደድ ምክንያት እና ግንባታዎቜን ለማኹናወን ባጋጠመ ዚገንዘብ ቜግር ምክንያት በሚፈለገው መጠንና ፍጥነት መኹናወን ያልቻለው ዚጋራ ቀቶቜ ግንባታ በርካቶቜ ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓል። በዚህ መካኚል ዹኹተማው አስተዳደር ተጠናቀዋል ያላ቞ውን ኹ25 ሺህ በላይ ቀቶቜን ይፋዊ በመሆነ ሂደት ለተመዝጋቢዎቜ ሊያስተላልፍ መሆኑን ባለፈው ሳምንት አሳውቆ ነበር። ይህም በቀት ቜግር በእጅጉ እዚተፈተነ ላለው ዹኹተማው ነዋሪ አንዳቜ ተስፋን አጭሮ በጉጉት እንዲጠብቅ አድርጎታል። አርብ ሐምሌ 01/2014 ዓ.ም. ለ20/80 እና ለ40/60 ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ ተመዝጋቢዎቜ ዕጣው በወጣበት ወቅት፣ ኚንቲባዋ አዳነቜ አቀቀ እንደተናገሩት ዹኹተማው አስተዳደር ዕጣው ዚሚወጣበት ሂደት ኚአድልዎ ነጻ እንዲሆን ዚሚያደርግ ዹቮክኖሎጂ ሥርዓት መዘርጋቱን ተናግሹው ነበር። ነገር ግን ኚንቲባዋ እዳሉት ሳይሆን ዚዕጣ ማውጣቱ ሂደት ቜግር እንደነበሚበት ቅሬታ መቅሚብ ዹጀመሹው ብዙም ሳይቆይ ነበር። አስተዳደሩም ጥቆማዎቜ መድሚሳ቞ውን ተኚትሎ በአስ቞ኳይ ዚማጣራት ሥራ እንዲካሄድ ተደርጎ፣ ዚዕጣ ማውጣት ሂደቱ ተዓማኒነት ዹሌለው ስለነበሚ ሙሉ በሙሉ ውድቅ እንዲሆን ተወስኗል። ዚአዲስ አበባ ኚንቲባዋ ኹ14ኛው ዙር ዚዕጣ ማውጣት ሂደት ጋር በተገነናኘ ዹተኹሰተውን ቜግር “ዹቮክኖሎጂ ውንብድና አጋጥሞናል፣ ድርጊቱም አመራር ዚመራው ወንበዮ ነው” በማለት ሁኔታው ዚቀት ስርቆት ብቻ ሳይሆን ዚፖለቲካ ፍላጎት  ጭምር ዚተስተዋለበት እንደነበር ተናግሚዋል። ዹዚህ ስራ ሌላው አላማ መንግሥት ህዝብን ማገልገል ብቃት ዹለውም ዹሚል ገፅታ ለመፍጠርና ህብሚተሰቡ በመንግስት ላይ እንዲያምፅ ለማድሚግ በማሰብ ነው በማለት ኚንቲባ አዳነቜ ገልፀዋል፡፡ በዚህ ሂደት ቜግር እንዳጋጠመን ማጣራት መጀመራቜን ህዝብን ሃብት መታደግ እንድንቜል አድርጎናል፡፡ ህዝቡን መታደግ ቜለናል፡፡ ለኹተማው አስተዳደሩ ዚዕጣ ማውጣት ሂደቱን በተመለኹተ ዹቀሹበው ሪፖርት ሥርዓቱ አስተማማኝ እንደሆነ ነው። በተጚማሪም ዹመሹጃ መሚብ ደኅንነት ኀጀንሲ (ኢንሳ) ማሚጋገጫ እንደሰጠው ቢነገርም፣ ተቋሙ ሕጋዊ በሆነ ደብዳቀ ማሚጋገጫ እንዳልሰጠ በምርመራው ተደርሶበታል። ኚንቲባዋ እንዳሉት ለዕጣው ሂደት ግብአት ዹሚሆኑ መሚጃዎቜ (ዳታ) ለቀናት በሰዎቜ አጅ መቆዚታ቞ውና ይህም ዹሆነው በኃላፊዎቜ ትዕዛዝ መሆኑን አመልክተዋል። ይህ በግለሰቊቜ እጅ ዚገባው ወሳኝ መሹጃ ቀት ለማግኘት ዹሚጠበቀውን ቁጠባ ያቋሚጡ እና በዚህ ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ብቁ ያልሆኑ ሰዎቜ ጭምር እንዲካተቱ ዕድልን ፈጥሯል። ዚኢንፎርሜሜን መሚብ ደኅንነት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሹመ቎ ግዛው እንዳሉት፣ ይህ ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜን ለተመዝጋቢዎቜ በዕጣ ለማስተላለፍ በኹተማው አስተዳደር ሥራ ላይ ዹዋለው ሥርዓት በርካታ ቜግሮቜ አሉበት። በዚህም ሥርዓቱ ተመሳሳይ ሶፍትዌሮቜን ለማልማት ዚሚያስፈልጉ ዓለም አቀፍ ደሚጃዎቜን ያልጠበቀ መሆኑን አመልክተውፀ በዚህ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ ዚሆኑትን “ሊስቱን አካላትፀ አልሚውን፣ ተጠቃሚውን እና አሚጋጋጩን አካላት ዹቀላቀለ እንዲሁም ለምዝበራ ያጋለጠ ነው” ብለዋል ዶ/ር ሞመ቎። ጹምሹውም ለዚህ ዚዕታ ማውጣት ሂደት ግብአት ዹመሆነው መሹጃ (ዳታ)፣ ኚእጅ ንክኪ ነጻ መሆን ዚሚጠበቅበት ቢሆንም፣ ነገር ግን እጅ በዝቶበት እንደነበሚ ተገልጿል። ባለሙያዎቜም እንዳሉት ዕጣውን ለማውጣት ጥቅም ላይ ዹዋለው ሥርዓት ሲዘጋጅ ተገቢውን መንገድ ያልተኚተለና ሁሉም ሂደት በአንድ ሰው ዚተሰራ እንደሆነ አመልክተዋል። በሂደቱም ቀት ለማግኘት ተመዝግበው ዚሚጠበቅባ቞ውን ገንዘብ እዚቆጠቡ ለዕጣ ብቁ ዹሆኑ ነዋሪዎቜን ዹሚመለኹተው ኚባንክ እና ኚቀቶቜ ልማት ዹተገኘው መሹጃ ዚአያያዝ ቜግር ዚነበሚበትና ለውጥ ለማድሚግ ዹተጋለጠ እንደነበር ተገልጿል። ዹመሹጃ መዛባት በተፈጞመበት ኮምፒውተር ላይ በተደሹገው ምርመራ ዹተፈጾሙ ሕገወጥ ድርጊቶቜ እንዳይታወቁ ለማድሚግ ዚሚያስቜሉ ጥንቃቄዎቜ መደሹጋቾው ዚተደሚሰበት ሲሆን፣ በተጚማሪም መሹጃን ማጥፋት፣ መጹመር እና ማዘዋር ድርጊት መፈጾሙ ተሚጋግጧል። በዚህ ተፈጾመ በተባለው “ዹቮክኖሎጂ ውንብድና” በአጠቃላይ ለውድድር ብቁ ናቾው ተብለው ዚተገለጹት 79 ሺህ ዹሚሆኑ ተመዝጋቢዎቜ ዚነበሩ ሲሆን፣ በድብቅ ዹተዘጋጁ 172 ሺህ ያህል ሰዎቜ ለዕጣው ዝግጁ ሆነው ነበር። በዚህም 93 ሺህ ተገቢ ያልሆኑ ሰዎቜ በዕጣው መካተታ቞ው ተገልጿል። በሕገወጥ መንገድ መሹጃወቾው በዕጣው ውስጥ ተካተው ኚተገኙት ውስጥ ደግሞ በባንክ ዚቆጠቡትን ገንዘብ ቀድመው አውጥተው ዹተዘጉ ተመዝጋቢዎቜ፣ ዚአመዘጋገብ ቜግር ያለባ቞ውና ብቁ ያልሆኑ ሰዎቜ ጭምር ተካተው መገኘታ቞ውን በምርመራው ዚተሳተፉ ባለሙያዎቜ ገልጞዋል። በሕገወጥ መንገድ በዕጣው ውስጥ እንዲካተቱ በተለያዩ መንገዶቜ ዹተዘጋጁ ሰዎቜ መሹጃ ውስጥ እንዲካተት ብቻ ሳይሆን፣ ዕጣ ለማውጣት ጥቅም ላይ ዹዋለው ሥርዓት ዹሚፈለገውን ሰው ዕጣ እንዲያወጣ ተደርጎም  ዹተዘጋጀ መሆኑም ተመልክቷል። በዚህም ዚሚጠበቅባ቞ውን ዚቀት ቁጠባ በባንክ ሲያኚናውኑ ኚቆዩት ተመዝጋቢዎቜ መሹጃ ውስጥ ያልተካተቱ ሰዎቜ በዕጣው አሾናፊ ሆነው መገኘታ቞ውም በምርመራ ተደርሶበታል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/ckvn7zepvp3o
amh
business
ዹዋነኛው ክሪፕቶኚሚንሲ ዋጋ እያሜቆለቆለ ያለው ለምንድን ነው?
ያለፉት ጥቂት ቀናት ለቢትኮይንም ሆነ ለክሪፕቶኚሚንሲ አስኚፊ ጊዜ ነው። አሁን ላይ ዚአንድ ቢትኮይን ዋጋ 21 ሺህ 974 ዶላር ነው። ቢትኮይን ቀድሞ ኹነበሹው ዋጋ ጋር ሲነጻጞር ባለፉት አምስት ቀናት ብቻ 25 በመቶ አሜቆልቁሏል። ይህም ባለፉት 18 ወራት ዹተመዘገበው ዝቅተኛው ዋጋው ነው። ቢትኮይን በዘመኑ ያወጣው ኹፍተኛ ዋጋ ባለፈው ኅዳር ወር ላይ ዹተመዘገበ ሲሆን፣ ይህም ዋጋው 70 ሺህ ዶላር ዹሚጠጋ ነበር። ባለሙያዎቜ እንደሚሉት ለዚህ ምክንያቱ በዓለም ላይ ያለው ሁኔታ ነው። በእርግጥ በዓለማቜን ነገሮቜ ጥሩ መስለው ዚማይታዩት በክሪፕቶኚሚንሲው በኩል ብቻ አይደለም። በዓለም ዙርያ ዚምጣኔ ሃብት ቀውስ እያንዣበበ፣ ዹዋጋ ንሚት እያሻቀበ፣ ወለድ እዚጚመሚ እና ዚኑሮ ውድነቱ እዚናሚ ነው። ዚአክሲዮን ገበያዎቜም ብርክ ይዟ቞ዋል። ዚአሜሪካው ስታንዳርድ ኀንድ ፑርስ 500 ዚድርሻ ገበያ (ስቶክ ማርኬት) በቅርብ ጊዜ ኹፍተኛ ኹነበሹው 20 በመቶ ቀንሷል። ዚድርሻ ገበያ ማለት ኩባንያዎቜ ዚኩባንያው ዚባለቀትነት ድርሻን ለገበያ ዚሚያቀርቡበት እና ሰዎቜም ይህንን ድርሻ ኹገዙ በኋላ ኩባንያው ትርፋማ በሆነበት መጠን ድርሻ቞ውን መልሰው በመሞጥ ወይም ኚትርፍ ክፍፍል ትርፋማ ዚሚያደርግ አሠራር ነው። ይህ ዚድርሻ ገበያ በመቀነሱም ትላልቅ ባለሃብቶቜ ሳይቀሩ ኪሳራ እዚገጠማ቞ው ነው። ሌሎቜም በርካታ ተራ ባለሃብቶቜም በማንኛውም ነገር ላይ መዋዕለ ንዋያ቞ውን ለማፍሰስ ያላ቞ው ዕድል አነስተኛ ሆኗል። በርካቶቜ መዋዕለ ንዋያ቞ውን በዚህ ጊዜ እንደ ክሪፕቶኚሚንሲ ተለዋዋጭ እና እንዲህ ነው ተብሎ ዹማይተነበይ ነገር ላይ ማዋል ትልቅ አደጋ እንደሆነ ያስባሉ። ክሪፕቶኚሚንሲ፣ በገንዘብ ባለሥልጣናት ቁጥጥር ዚማይደሚግበትና ዹማይጠበቅ ዲጂታል ገንዘብ ነው። በመሆኑም ዚቆጠቡትን ገንዘብ እርሱ ላይ ለማፍሰስ እዚተጠቀሙበት ኹሆነና ዋጋ ካጡበት አሊያም ዚዲጂታል ገንዘብ ማስቀመጫዎን ( ክሪፕቶ ዋሌት) ካጡት ገንዘብዎ ጠፍቷል ማለት ነው። ባለፈው ወር  ሁለት ብዙም ዚማይታወቁ ግን በጣም ትልቅ ዹሆኑ ዲጂታል ገንዘቊቜ ተንኮታኩተዋል። ይህም በአጠቃላይ በዲጂታል ገበያው ላይ ያለውን አመኔታ አሳጥቷል። በዚህም ምክንያት ያላ቞ውን ገንዘብ ለመሞጥ ዚሚወስኑ ሰዎቜ ቁጥር እዚጚመሚ ነው። በርካታ ሰዎቜ ቢትኮይና቞ውን በሞጡ ቁጥር ደግሞ ያለው ዋጋ እዚቀነሰ ይመጣል። ምክንያቱም ዲጂታል ገንዘቊቜን ዋጋቾው እንዲዋዠቅ ኚሚያደርጉ ምክንያቶቜ አንዱ ይህ በመሆኑ ነው። ዋጋው ዹሚወደደው ዹሚገዛ ሰው ሲበዛ እንጂ ዚሚሞጥ ሰው ሲበሚክት አይደለም። ይህ ደግሞ በርካታ ሰዎቜ ዚቢትኮይን ዋጋ እዚወሚደ መምጣቱን በመመልኚታ቞ው ያላ቞ውን እንዲሞጡ ገፋፍቷ቞ዋል። ዑደቱም በዚህ መልኩ ይቀጥላል። ዚፋይናንሻል ታይምስ ማርኬትስ አርታኢ ኬቲ ማርቲን፣ “ቢትኮይን እንደ ሌሎቜ ባህላዊ አሎቶቜ እርሱን ለመደገፍ ዚሚያስቜል ሌላ ንግድ፣ ዚገቢ ፍሰት ወይም ሌሎቜ ነገሮቜ ዚሉትም” ይላሉ። ኬቲ አክለውም “ዋጋው ሰዎቜ ሊገዙ ያሰቡበት ዋጋ ብቻ ነው” ሲሉ ዚቢትኮይን ዋጋ ዚመሞጫ ሂሳቡ ላይ ዹተንጠለጠለ እንደሆነ አስሚድተዋል። “በርካታ ሰዎቜ ተስፋ ቆርጠው ሾጠው ኚወጡ፣ አበቃ። ምንም መቆሚያ ዚለም። ነገ በ10 ሺህ ዶላር ዋጋ መሞጡን ዚሚያስቆመው ምንም ነገር ዹለም” ብለዋል። በመሆኑም ባለፉት ጥቂት ቀናት ቢናንስ ዚተባለው ዓለም አቀፋዊው ትልቁ ዚክሪፕቶ መገበያያ መድሚክ ለተወሰኑ ሰዓታት ቢትኮይንን እንዳይወጣ አድርጎ ነበር።  “ሁሉም ሰው ላያምን ቢቜልም ይህንን ያደሚግነው ዚገንዘብ ዝውውሩ በመቆሙ ነው” ብሏል። ዚክሪፕቶ አበዳሪ ሎልሲዚስም ተመሳሳይ እርምጃ ወስዷል። ይሁን እንጂ እርምጃውን ዹወሰደው በቮክኒክ ቜግር ሳይሆን በኹፍተኛ ዚገበያ ሁኔታ እንደሆነ ገልጿል። አሁን ላይ ደግሞ ዚክሪፕቶኚሚንሲ ኩባንያ፣ ኮይንቀዝ ሠራተኞቹን በ18 በመቶ መቀነሱን አስታውቋል። በሁኔታው ዚተደናገጡና ገንዘባ቞ውን ያፈሰሱ ባለሃብቶቜም ቢትኮይና቞ውን መሞጥ ጀምሚዋል። ዹተፈጠሹውን ቀውስ ለማሚጋጋት ቢትኮይን ያላ቞ው ሰዎቜ ይዘው መቆዚት እና ሌሎቜ ደግሞ እንደገና መግዛት መጀመር አለባ቞ው። ዚክሪፕቶ አድናቂዎቜም አዳዲስ ደንበኞቜን ለማፍራት ርካሜ በመሆኑ ክሪፕቶ ለመግዛት ጊዜው አሁን እንደሆነ ይናገራሉ። ምክንያቱም ሁልጊዜም ቢትኮይን ዚሚሰራው በዚህ መልኩ ነው። ዹዋጋ መዋዠቁ ሁልጊዜም ዚሚያጋጥም እንጂ አዲስ ነገር እንዳልሆነ ተጠቃሚዎቹ ይገልጻሉ። በክሪፕቶ በአጭር ጊዜ ቱጃር ዹሆኑ ሰዎቜ ታሪክ እና ዚታዋቂ ሰዎቜ ገበያውን መቀላቀልም አዲስ ዲጂታል ገንዘብን ይስባሉ። ኀሎን መስክ ለክሪፕቶ ያለውን ፍቅር በትዊተር ገጹ አጋርቷል። መስክ በኀሌክትሪክ ዚሚሰራ መኪና ኩባንያው፣ ቎ስላ ባለፈው ዓመት 1.5 ቢሊዚን ዶላር ቢትኮይን ላይ አፍስሷል። ሆኖም ዚኢንቚስትመንት አማካሪዎቜ ኹፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። በዩናይትድ ኪንግደም ዚኢንቚስትመንት አማካሪ ሆኑት አልታፍ ካሳም ስለክሪፕቶኚሚንሲ መስክ “እውነቱን ለመናገር፣ ደፋር ሰው ብቻ መግባት ያለበት ቊታ ነው” ሲሉ ለቢቢሲ ራዲዮ 5 ተናግሚዋል። እውቁ ዚሆሊዉድ ተዋናይ ማት ዎመን፣ እአአ ጥቅምት 2021 ላይ “ገንዘብ ለደፋሮቜ ታደላለቜ” በሚል መልዕክት ዚክሪፕቶ ማስታወቂያ ሰርቷል። ማስታወቂያው በብሔራዊ ዚእግር ኳስ ሊግ ‘ሱፐር ቩውል’ ተለቅቆ በትዊተር እና በዩትዩብ 28 ሚሊዹን ጊዜ ታይቷል። ሆኖም ማስታወቂያው በተለቀቀበት ወቅት ቢትኮይን ዚገዙት ‘ደፋሮቜ’ ምን አልባት አሁን ላይ ምንም ጥቅም እንዳላገኙ ላይሰማቾው ይቜላል። አሊያም ደግሞ ደፋር በመሆናቾው ዚተጠቀሙት ገንዘብ እንደሌለ ሊሚዱት ይቜላሉ። ምክንያቱም ያኔ ቢትኮይን ዛሬ ኹነበሹው በሊስት እጥፍ ዚሚበልጥ ዋጋ ነበሚው።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c4nzzqv8ljgo
amh
business
ክትባትና ውሃ አምራቹ ኚእስያ ቁጥር አንድ ሀብታም ሆነ
ዞንግ ሻንሻን ዚእስያ ሀብታሞቜ ዝርዝርን በግንባር ቀደምነት መምራት ጀምሯል። ክትባት እና ዚታሞገ ውሃ ማምሚቻ ባለቀት ዹሆነው ዞንግፀ በዚህ ዓመት ሀብቱ ሰባት ቢሊዚን ዶላር ጚምሯል። ዚሕንዱን ሙኚሜ አምባኒ እና ዚቻይናውን ጃክ ማ በልጩም ዚእስያ ቁጥር አንድ ባለ ጾጋ ሆኗል። አጠቃላይ ሀብቱ ወደ 77.8 ቢሊዚን ዶላር ይጠጋል። ይህም ዹዓለም 11ኛው ሀብታም እንደሚያደርገው ዚብሉምበርግ ቢሊዚነር ኢንዎክስ ያሳያል። “ብ቞ኛው ተኩላ” በሚል ቅጜል ስሙ ዚሚታወቀው ባለ ሀብት በጋዜጠኛነት፣ በእንጉዳይ እርሻና በጀናው ዘርፍም ሠርቷል። ሚያዝያ ላይ ክትባት አምራቹ ቀጂንግ ዋንታይ ባዮሎጂካል ተቋምን በቻይና ዚአክስዮን ገበያ አቅርቧል። ኚሊስት ወራት በኋላ ደግሞ ኖንግፊ ስፕሪንግ ዚተባለውን ውሃ አምራቜ ኩባንያ ለሆንግ ኮንግ ዚአክስዮን ገበያ አቅርቧል። ኹዚህ ቀደም ዚእስያ ቁጥር አንድ ሀብታም ዚአሊባባ መስራቹ ቻይናዊ ጃክ ማ ነበር። ኖንግፊ ስፕሪንግ ሆንክ ኮንግ ውስጥ ኹፍተኛ ተቀባይነት ካገኘ በኋላ ዚአክስዮን ዋጋው ወደ 155% አድጓል። ዚኮቪድ-19 ክትባትን ኚሚሠሩ አንዱ ዹሆነው ቀጂንግ ዋንታይ ባዮሎጂካል ዚሌር ዋጋው ኹ2,000% በላይ ደርሷል። እነዚህ ተደማምሹው ዞንግ ሻንሻን ኚእስያ ሀብታሞቜ ቁንጮው እንዲሆን አስቜለውታል። ብሉምበርግ እንደሚለውፀ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲህ ያለ ሀብት ንብሚት ያፈራ ሰው በታሪክ አልታዚም። በወሚርሜኙ ወቅት ዹአማዞን መስራቜ ጄፍ ቀዞስን ጚምሮ ብዙ ሀብታሞቜ ጥሪታ቞ው ጚምሯል። ዚሕንዱ አምባኒ ሀብት ኹ18.3 ቢሊዚን ወደ 76.9 ቢሊዚን ዶላር አድጓል። በተቃራኒው ዹጃክ ማ ሀብት ጥቅምት ላይ ኹ61.7 ቢሊዚን ዶላር ወደ 51.2 ቢሊዚን ወርዷል። አሊባባ በቻይና ባለሥልጣኖቜ ተደጋጋሚ ትንኮሳ ደርሶበታል። ድርጅቱ በምርቶቜ መካኚል ፍትሐዊ ያልሆነ ውድድር በማድሚግ ምርመራ እዚተደሚገበት ሲሆንፀ አጋር ድርጅቱ አንት ግሩፕ ጥቅምት ላይ ኚአክስዮን ሜያጭ ታግዷል። አብዛኞቹ ዚቻይና አዳዲስ ቢሊዚነሮቜ በቮክኖሎጂ ዘርፍ ዚተሰማሩ ና቞ው። በሌላ በኩል በቻይና እና በአሜሪካ መካኚል ሁዋዌ፣ ቲክቶክ እና ዊቻትን በተመለኹተ እዚተባባሰ ዚመጣው ውጥሚት ዚቻይና ዚአክስዮን ሜያጭ ላይ ኹፍተኛ ተጜዕኖ አሳርፏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-55495983
amh
business
አርጀንቲና በወሚርሜኙ ዚተጠቁትን ለመደጎም ዚናጠጡ ኃብታሞቿ ላይ ግብር ጣለቜ
አርጀንቲና አገሯ በሚገኙ ዚናጠጡ ኃብታሞቜ ላይ ለዚት ያለ ግብር ጥላለቜ። ግብሩ ለኮሮናቫይሚስ ዚሚያስፈልጉ ዹህክምና ቁሳቁሶቜ ግብዓትና በወሚርሜኙ ምክንያት ክፉኛ ለተጠቁት ኑሯ቞ውን መደጎሚያ እንዲሆን ነው። ዹምክር ቀቱ አባላት "ዚሚሊዮነሮቜ ግብር" ብለው ዚጠሩት በአንዮ ዹሚኹፈል ገንዘብ ሲሆን በዚህ ሳምንት አርብም 42 ለ 26 በሆነ ዚድምፅ ብልጫም ፀድቋል። በዚህም መሰሚት ኹ200 ሚሊዮን ፔሶ (2.5 ሚሊዮን ዶላር) ኃብት ያኚማቹ ግለሰቊቜ መክፈል አለባ቞ው። በአገሪቱ ይህ ዚገንዘብ መጠን ያላ቞ውም ወደ 12 ሺህ ግለሰቊቜ ናቾው ተብሏል። አርጀንቲና በወሚርሜኙ ክፉኛ ኹተጠቁ አገራት አንዷ ስትሆን እስካሁን ባለውም መሹጃ 1.5 ሚሊዮን በቫይሚሱ ሲያዙ 40 ሺህ ደግሞ ህይወታ቞ው አልፏል። ዚህዝብ ቁጥሯ 45 ሚሊዮን ብቻ ዹሆነው አርጀንቲና በወሚርሜኙ በሚሊዮኖቜ በተያዙ ተርታ አምስተኛ ደሹጃን ይዛለቜ። ኚህዝብ ቁጥሯ ጋር ሲነፃፀር ደግሞ ኚሚሊዮን በላይ ካስመዘገቡ ትንሿ አገር አድርጓታል። ወሚርሜኙን ለመግታት ያስቀመጠቻ቞ው መመሪያዎቜ ኹፍተኛ ተፅእኖን አሳርፈዋል። በስራ አጥነት፣ በርካታዎቜ በድህነት ወለል በሚኖሩባትና አገሪቷ ራሷ በብድር በተዘፈቀበቜበት ሁኔታ መመሪያዎቹ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆነዋል። አርጀንቲና ኹ2018 ጀምሮም በምጣኔ ኃብት ድቀት ላይ ናት። ዚሚሊዮነሮቜን ግብር ካሚቀቁት መካኚል አንዱ ህጉ 0.8 በመቶ ዹሚሆነውን ግብር ኹፋይ ብቻ ነው ዹሚመለኹተው ብለዋል። በአርጀንቲና ውስጥ ያሉት ሃብታሞቜ፣ ኚአንጡራ ሃብታ቞ው 3.5 በመቶ እንዲሁም ኹአገር ውጭ ያሉ አርጀንቲናውያን ደግሞ 5.25 በመቶ እንዲኚፍሉ ውሳኔ ተላልፏል። ኚግብሩ ዹተሰበሰበው ገንዘብም መካኚል 20 በመቶ ለህክምና ቁሳቁሶቜ፣ 20 በመቶ ለጥቃቅንና አነስተኛ ነጋዎዎቜ፣ 20 በመቶ ለተማሪዎቜ ዚትምህርት ቀት ክፍያ፣ 15 በመቶ ለማህበራዊ ልማትና ቀሪው 25 በመቶ ደግሞ ለተፈጥሮ ነዳጅ ስራዎቜ እንደሚውል ኀኀፍፒ በዘገባው አስነብቧል። ግራ ዘመሙ ፕሬዚዳንት አልበርቶ ፈርናንዮዝ መንግሥት 300 ቢሊዮን ፔሶም ለማሰባሰብ እቅድ ይዘዋል። ሆኖም ዚተቃዋሚዎቜ ፓርቲ ቡድኖቜ በበኩላ቞ው ይህ ዚአንድ ጊዜ ግብር ሊሆን ስለማይቜል ዹውጭ አገራት ኢንቚስትሮቜን ፍራቻ ላይ ይጥላል በማለት ተቜተዋል። ዹቀኝ ክንፍ ፓርቲ ጁንቶስ ፖር ኀል ካምቢዮ በበኩሉ ዚማይገባ ሲል ዹፈሹጀው ሲሆን "ነጠቃም" ነው ብሎታል።
https://www.bbc.com/amharic/news-55191619
amh
business
በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ቻይናውያን ግላዊ መሹጃ ተሰርቆ ለሜያጭ መቅሚቡ አነጋጋሪ ሆኗል
አንድ ዹበይነ መሚብ መሹጃ ሰርሳሪ ኚቻይና ዚፖሊስ ተቋም በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜን መሹጃ መዝብሮ ለሜያጭ ማቅሚቡን ተኚትሎ ጉዳዩ መነጋገሪያ ሆኗል። ይህ አንድ ቢሊዚን ይደርሳሉ ዚተባሉ ዚቻይናውያን ግላዊ መሹጃ ስርቆት ዜና ይፋ ኹሆነ በኋላም ዚአገሪቱ ፕሬዝዳንት ዚሕዝቡ መሹጃ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደሚግለት አሳስበዋል። ዹበይነ መሚብ መሹጃ ሰርሳሪዎቜ (ሃኚርስ) ሰርቀነዋል ያሉትን ዚቻይናውያንን መሹጃ ዹሚገዛቾው ካለ ለመሞጥ ማስታወቂያ ካወጡ በኋላ ነው፣ ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ሕዝባዊ ተቋማት “ዹመሹጃ ደኅንነታ቞ውን እንዲያጠናክሩ” ጥሪ ያቀሚቡት። ኋላ ላይ በተነሳ እና በሕገወጥ ዹበይነ መሚብ መድሚክ ላይ በወጣው ማስታወቂያ እንደተጠቀሰው ለሜያጭ ዚቀሚቡት ግላዊ መሚጃዎቜ ኚሻንግሃይ ብሔራዊ ፖሊስ ዹተሰሹቁ መሆናቾው ተገልጿል። ዹበይነ መሚብ መሹጃውን ዹሰሹቀውና ለሜያጭ ያቀሚበው ግለሰብ በእጁ ላይ በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ቻይናውያን ስም፣ አድራሻ፣ ዚብሔራዊ መታወቂያ ቁጥር እና ዚሞባይል ቁጥራ቞ውን ጚምሮ ሌሎቜ መሚጃዎቜ እንዳሉት አመልክቷል። ዹበይነ መሚብ መሹጃ ደኅንነት ባለሙያዎቜም ተሰርቀዋል ኚተባሉት ግላዊ መሚጃዎቜ ውስጥ ናሙናዎቜን በመውሰድ ባደሚጉት ማጣራት ስርቆቱ መፈጾሙን አሚጋግጠዋል። ኹፍተኛ መጠን ያለው ይህ መሹጃ 23 ቎ራባይት ይሆናል ተብሎ ዚሚገመት ሲሆን፣ ይህም በ200 ሺህ ዶላር ለሜያጭ ዹቀሹበ ትልቁ መሹጃ ነው ተብሏል። ድርጊቱ ወንጀል በመሆኑ ማስታወቂያው ኚተለጠፈበት ድሚ ገጜ ላይ እንዲነሳ ተደርጓል። ነገር ግን ይህ ተሰሹቀ ስለተባለው ግዙፍ ግላዊ መሹጃ ክምቜትን በተመለኹተ ዚትኛውም ዚቻይና ባለሥልጣን አስካሁን በይፋ ያለው ነገር ዚለም። ፕሬዝዳንቱም ቢሆኑ ጉዳዩን በሚመለኚት በቀጥታ ምንም አላሉም። ‘ሳውዝ ቻይና ሞርኒንግ ፖስት’ ዚተባለው ጋዜጣ እንደዘገበው ፕሬዝዳንት ዢ፣ ዜጎቜ ለሕዝባዊ አገልግሎቶቜ ግላዊ መሚጃዎቜን ሲሰጡ ደኅንት እንዲሰማ቞ው ለማድሚግ ተቋማት “ለግላዊ መሚጃዎቜ እና ለምስጢራዊ ዚተቋማት መሚጃዎቜ ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደሚጉ” አሳስበዋል። ተሰሹቀ ስለተባለው ግዝፍ መሹጃ ሜያጭን በተመለኹተ ዚወጣውን ዹበይነ መሚብ ማስታወቂያ ተኚትሎ ዚገጹ ተቆጣጣሪዎቜ ዹሚኹተለውን ጜሁፍ አስፍሚው በኋላም ማስታወቂያውን አንስተውታል። “ዚተወደዳቜሁ ቻይናውያን ተጠቃሚዎቜ፣ እንኳን ወደ መድሚካቜን በደህና መጣቜሁ። ብዙዎቻቜሁ ወደ እዚህ ገጜ ዚመጣቜሁት ኚሻንግሃይ ፖሊስ ባፈተለኩ መሚጃዎቜ ምክንያት ነው። መሹጃው ኹዚህ በኋላ ለሜያጭ አይውልም፣ በተጚማሪም ኹዚሁ ጉዳይ ጋር ዚሚያያዙ ርዕሶቜ በሙሉ ኚገጹ ላይ እንዲሰሚዙ ተደርገዋል” ብሏል። ዚድሚ ገጹ ተቆጣጣሪዎቜ ጹምሹውም ኹፍተኛ ተፈላጊነት ያላ቞ው ሌሎቜ ዚቻይና መሚጃዎቜ እጃ቞ው ላይ እንዳሉና ለሜያጭም ሊያቀርቧ቞ው እንደሚቜሉ አሳውቀዋል። “ያለነው ቻይና ውስጥ አይደለም፣ ቻይናውያንም አይደለንም። ስለዚህም ለቻይና ሕጎቜ ተገዢ መሆን ዚለብንም” ሲሉ ስለማንነታ቞ው ድፍን ያለ ምላሜ ሰጥተዋል። በበይነ መሚብ ላይ ዹሚፈጾሙ ወንጀሎቜን ዚሚኚታተለው ‘ዳርክትሬሰር’ ዚተባለው ቡድን እንዳለው ይህ ዹመሹጃ ምዝበራ ኹፍተኛ ትኩሚትን ስቧል። ይህም ምናልባት በቻይናውያን መሹጃ ላይ ተፈጜሟል በተባለው ስርቆት አማካይነት በተፈጠሹው ትኩሚት ዚተነሳሳ ነው ዚተባለ ሌላ ዹበይነ መሚብ መሹጃ መዝባሪ ተመሳሳይ ዚሜያጭ ማስታወቂያ አውጥቷል። በዚህም ዹበይነ መሚብ መሹጃ ሰርሳሪው እዚያው ቻይና ውስጥ ኹሚገኘው ዹሄናን ግዛት ብሔራዊ ፖሊስ ዹመሹጃ ቋት ዹመዘበሹው ዹ90 ሚሊዮን ሰዎቜ መሚጃዎቜ እጁ ላይ እንዳለ ገልጿል። ነገር ግን ይህ ምን ያህል እውነት እንደሆነ በበይነ መሚብ ደኅንነት ባለሙያዎቜ አልተሚጋገጠም። ባለሙያዎቜ ይህ ተሰሹቀ ዚተባለው ኹፍተኛ መጠን ያለው መሹጃ ጉዳይ ለቻይና ባለሥልጣናት ዋነኛ አሳሳቢ ጉዳይ እንደሆነ፣ ዚሜያጭ ማስታወቂያውን በተመለኹተ በአገሪቱ ዚማኅበራዊ ሚዲያ መድሚኮቜ ላይ ዹሚደሹጉ ውይይቶቜ ማገዳ቞ውን በመጥቀስ ተናግሚዋል። በዘርፉ ደኅንት ጉዳዮቜ ላይ ዚሚሰራው ዚ‘ፎሬንሲክ ፓዝዌይ’ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዎብ ሌሪ እንደሚያምኑት፣ መሹጃው ኹፍተኛውን ክፍያ ላቀሹበ ወገን ተሜጧል ወይም ዹበይነ መሚብ ሰርሳሪዎቹ እንዲህ አይነት ግላዊ መሹጃን ዹሚፈልጉ ወደ እነሱ እንዲመጡ ለማስተዋወቅ ተጠቀሙበት ዘዮ ሊሆን ይቜላል ብለዋል። ምክንያቱም “ድርጊታ቞ው ዚቻይና መንግሥት ባለሥልጣናትን ሊያስቆጣ እንሚቜል ብዙም አላሳሰባ቞ውም” ብለዋል። ባለፈው ሚያዝያ ወር በይነ መሚቊቜን ሰብሮ በመግባት መሚጃዎቜን ዚሚመዘብሚው ‘ራይድ ፎሚምስ’ ዚተባለው ድሚ ገጜ በአሜሪካው ዚፌደራል ደኅንነት መሥሪያ ቀት መሪነት በተካሄደ ዓለም አቀፍ ዚፖሊስ ዘመቻ በቁጥጥር ስር ውሎ እንዲዘጋ ተደርጓል። በዚህም ፖርቱጋላዊው ዚድሚ ገጹ መስራቜ እና አንድ ብሪታኒያዊ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል። አሁን ቻይና ውስጥ ተሰርቋል ዚተባለው አይነት ኹፍተኛ መጠን ያለው ዚግሰቊቜ ግላዊ መሚጃዎቜ፣ ትክክለኛ ባለቀቶቹን አስመስሎ መልዕክት ለመላክ እና ሌሎቜ መጥፎ ድርጊቶቜን በመፈጾም ወንጀለኞቜ ገንዘብ ለማግኘት ጥቅም ላይ ሊያውሉት ይቜላል። በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ዚቻይናውያን ግላዊ መሹጃ መሰሹቁን በተመለኹተ ዚተለያዩ መላምቶቜ እዚቀሚቡ ሲሆን፣ በትክክል ይህን ያህል ግዙፍ መሹጃ በሰርሳሪዎቜ እጅ ኚገባ አስካሁን ካጋጠሙ ዹመሹጃ ምዝበራዎቜ ሁሉ ዹላቀው ነው ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cp42eek8x71o
amh
business
ቩይንግ ኹ737 ማክስ ጋር በተያያዘ 2.5 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ
ቩይንግ ስለ 737 ማክስ አውሮፕላኑ ዲዛይን ኚአሜሪካ ዚደኅንነት እና ጥንቃቄ ባለሙያዎቜ መሚጃዎቜን በመደበቅ ለተመሰሚተበት ዹወንጀል ክስ 2.5 ቢሊዮን ዶላር ቅጣት ለመክፈል ተስማማ። ዚአሜሪካ ፍትህ ቢሮ እንዳለው ኹሆነ ኩባንያው "ኚግልጜነት ይልቅ ትርፍን" አስቀድሟል። ቩይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን በኢትዮጵያ እና በኢዶኔዢያ ተኚስክሶ ዹ346 ሰዎቜ ህይወት አልፏል። ቩይንግ ለመክፈል ኚተስማማው ገንዘብ ውስጥ 500 ሚሊዮን ዶላሩ በአውሮፕላኑ አደጋ ቀተሰቊቻ቞ውን ላጡ ዹሚኹፋፈል ይሆናል። ቩይንግ እንዳለው ይህ ስምምነት ኩባንያው "ያለበት ጉድለት" ምን ያህል መሆኑን ያሳያል። ዹቩይንግ ኹፍተኛ ዚሥራ ኃላፊ ዎቪድ ካልሁን እንዳሉት "ወደ እዚህ ስምምነት መግባታቜን ትክክለኛው ነገር እንደሆነ በጜኑ አምናለሁፀ ይህም ኚእሎቶቻቜን እና ኚሚጠበቅብን ምን ያህል ወደ ኋላ መቅሚታቜንን ያሳያል።" "ይህ ስምምነት ሁላቜንንም ዚሚያስታውሰን ለግልጜነት ዚገባነው ግዎታ ምን ያህል ወሳኝ እንደሆነፀ እንዲሁም አንዳቜንም እንኳን እርሱን ሳናሟላ ብንቀር መዘዙ ዹኹፋ መሆኑን ነው።" ዚአሜሪካ ፍትህ ቢሮ እንዳለው ኹሆነ ዹቩይንግ ባለስልጣናት በኢንዶኔዢያ እና በኢትዮጵያ ለአውሮፕላኑ መኚስኚስ ምክንያት ስለሆነው ኀምካስ ዚተባለው አውቶማቲክ ዚበሚራ መቆጣጠሪያ ሥርዓት ላይ ስላለ ለውጥ መሹጃ ደብቀዋል። ይህ ውሳኔ ዚሚያሳው ዚአውሮፕላን አብራሪው ስልጠና መመሪያ ስለሥርዓቱ በቂ መሹጃ አለመያዙን፣ ይህም በተሳሳተ መሹጃ ዚአውቶማቲክ ሥርዓቱ ዚአብራሪውን ውሳኔ እንደሚሜሚውና፣ ይህም አውሮፕላኑ ኚማኮብኮቢያው በተነሳ በጥቂት ደቂቃዎቜ ውስጥ አፍንጫውን አዘቅዝቆ ቁልቁል እንዲምዘገዘግ እንደሚያደርገው ነው። ቩይንግ ኚምርመራ ባለሙያዎቜ ጋር ለስድስት ወር ያህል ትብብር አለማድሚጉን ዚፍትህ ቢሮው ጚምሮ ተገልጿል። "በላዹን አዹር መንገድ በሚራ 610 እና በኢትዮጵያ አዹር መንገድ በሚራ 302 አውሮፕላኖቜ ላይ ዹደሹሰው አሳዛኝ አደጋ፣ በዓለማቜን ቀዳሚ ዚንግድ አውሮፕላኖቜ አምራቜ ዹሆነው ኩባንያ ሠራተኞቜ ዹማጭበርበር እና ማታለል ባሕሪያ቞ውን አጋልጧል" ያሉት ደግሞ ሚዳት ተጠባባቂ ጠቅላይ ዐቃቀ ሕግ ዎቪድ በርንስ ና቞ው። "ዹቩይንግ ሠራተኞቜ 737 ማክስ አውሮፕላንን በሚመለኚት መሹጃን ኚተቆጣጣሪው መስሪያ ቀት በመደበቅ፣ ስህተታ቞ውን ለመሾፋፈን በመተባበር ኚደኅንነት ይልቅ ትርፍን አስቀድመዋል" ብለዋል። ኩባንያው ሊኹፍል ኚተስማማው አብዛኛው ገንዘብ፣ 1.7 ቢሊዮን ዶላሩ ለተጎጂ ቀተሰቊቜ ዚሚሰጥ ሲሆን፣ ዹተወሰነውም ተኹፍሏል ተብሏል። ኩባንያው 243.6 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት ለመክፈልም ተስማምቷል። በኢትዮጵያ አዹር መንገድ ሕይወታ቞ወን ላጡ ቀተሰቊቜ ጥብቅና ዚቆሙት ባለሙያዎቜ ግን ይህ ዚኩባንያው ውሳኔ ዚመሰሚቱትን ክስ እንዲያቋርጡ እንደማያደርጋ቞ው ገልፀዋል። ጠበቆቹ አክለውም ሁሉም ዚኩባንያው 737 ማክስ አውሮፕላኖቜ ደኅንነት በገለልተኛ ወገን እስኪሚጋገጥ ድሚስ ወደ በሚራ እንዲገቡ መፈቀድ ዚለበትም ብለዋል። ዚአሜሪካ ደኅንነት ተቆጣጣሪዎቜ ኚታኅሣስ ወር ጀምሮ አውሮፕላኖቹን ለበሚራ ዝግጁ ናቾው በማለታ቞ው ወደ ሥራ ተመልሰዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-55570801
amh
health
ዘግታቜሁ ዚወጣቜሁትን በር እንዳልተዘጋ ዚሚያሳስባቜሁ ዚአእምሮ ሕመም - ኊሲዲ
ምሥራቅ* ለዚህ ታሪክ ሲባል ስሟ ዹተቀዹሹ “ለሊስት ዓመታት ዚማስበውን ሁሉ እንድጜፍ አእምሮዬ ያስገድደኝ ነበር” ትላለቜ። እንቅልፍ እና እርሷ ተፋትተው ነበር ዚኚሚሙት። “ዝም ብዬ መጻፍ ነው። ደብተር፣ ወሚቀት፣ ሞባይል ሁሉ ነገር ላይ እጜፋለሁ።” ዚምትጜፈው ነገር ለሚያነበው ሰው ትርጉም ላይሰጥ ይቜላል። ማንኛውንም ነገር በአእምሮዋ ውስጥ ሰንዳ ዚያዘ቞ውን ወይም ዚመጣላትን ጥቃቅን ነገር ሁሉ ካልጻፈቜ ሰላም ይነሳታል። “ፀጉሬ ላይ ቅባት ተቀብቌ ጥሩ ነው ብዬ ካሰብኩኝ እጜፈዋለሁ።” ይህ ዚመጻፍ ጉትጎታ ግን አንድ ቀን ተገታ። “አንድ ቀን ለሊቱን ሙሉ ቁጭ ብዬ ስጜፍ አደርኩፀ ዚዚያን ቀን ይህ ነገር ዚወጣልኝ ይመስለኛል።” ምሥራቅ ባይፖላር ዲስኊርደር በተባለ ዚአእምሮ ሕመም (በሁለት ዚተለያዩ ዚስሜት ጜንፎቜ መካኚል መዋለል) እዚተ቞ገሚቜ እያለ ነው ይህ ዕክል ዚተጚመሚባት። ኊሲዲ (ኊብሰሲቭ ኮምፐልሲቭ ዲስኊርደር) ይባላል ነገሮቜን በተደጋጋሚ ለመስራት ኚቁጥጥር ውጪ ዹሆነ ጎትጓቜ ስሜት መሰማት ነው። “በጣም አስ቞ጋሪ ጊዜ ነው ያሳለፍኩትፀ አሁን በሕይወት መኖሬ በጣም ይገርመኛልፀ ሥራዬን ለቅቄ ነበር። ይህንን በራሎ መቆጣጠር ስላቃተኝ መልሶ ጭንቀት ውስጥ አስገብቶኛል።” ምሥራቅ ሕመሟን ለሌሎቜ መንገር አልፈለገቜም። ምክንያቷ ደግሞ 'ማን ይሚዳኛል' ዹሚል ነበር። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ኹተኹሰተ በኋላ ደግሞ ይህ ሕመሟ እንደ አዲስ ተመልሶ አገሚሞባት። “ዚዘጋሁትን በር እንዳልዘጋሁ ይሰማኛል። በተለይ ደግሞ ዚእሳት ነገር ወደ ጭንቅላቮ እዚመጣ ያስጚንቀኛልፀ ስቶቭ ለኩሌ ዚተውኩ ያህል ይሰማኛል። በዚህ ምክንያት ቀኑን ሙሉ ስብሰለሰል ነው ዚምውለው።” ምሥራቅ አእምሮ ውስጥ እዚመጣ ዚሚያስጚንቃት ጎትጓቜ ሃሳብ፣ ሕመም መሆኑን ሳታውቅ ለሚዥም ጊዜ ቆይታለቜ። ይህ ጉዳይ ሕመም እንደሆነ ያወቀቜው በ቎ሌቪዥን ካገኘቜው መሹጃ ዚተነሳ ነው። ቢቢሲ ወደ ሕክምና አልሄድሜም ሲል ጠይቋት ነበር። “ሕክምና ለማግኘት ስሄድ አእምሮሜን ዝም አስብይው ይሉኛል። ግን እርሱን ማድሚግ ብቜል ኖሮ ለምን ወደ ሕክምና እሄዳለሁ” ትላለቜ። ሐኪም ዹተሰኘው እና በሕክምና ባለሙያዎቜ ዹተመሰሹተው ማኅበራዊ ድሚ ገጜ ኊሲዲ (ኊብሰሲቭ ኮምፐልሲቭ ዲስኊርደር)ን በተመለኹተ ይህንን ይላል። “ኊሲዲ በአጭሩ ሲገለጜ ጥርጣሬ ዚሚፈጥር ዹሚነዘንዝ ሀሳብና እና ሃሳብ ተኚትሎ ለማርገብ ዹሚደሹግ ተደጋጋሚ ድርጊት ነው” ሲል አስፍሯል። በዚህ ዚአእምሮ ሕመም ላይ ዹተደሹጉ ጥናቶቜ እንደሚያሳዩት ሕመሙ በዚትኛውም ዚእድሜ ክልል ያለ ሰው ላይ ሊኚሰት ይቜላል። ዹህመሙ መንስዔ ምን እንደሆነ በእርግጠኝነት ዚሚታወቅ ነገር ዚለም። ዶክተር ዮናስ ባሕሚጥበብ በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ በአእምሮ ሕክምና ክፍል መምህር ሲሆኑ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ደግሞ ዚአእምሮ ሕመም ሐኪም ና቞ው። ሐኪሙ ይህንን ሕመም ሲገልፁት “ኚእኛ ፍላጎት ውጪ፣ ወደ አእምሯቜን ዚሚመጣ ሐሳብ ወይንም ደግሞ አንድን ድርጊት በተደጋጋሚ ለመፈፀም መፈለግ፣ በተግባርም ማዋልንም ይጚምራል” ይላሉ። ዶ/ር ዮናስ እንደሚሉት በዚህ ዚአእምሮ ሕመም ዚተያዙ ሰዎቜ ወደ አእምሯ቞ው ዚሚመጣውን ሐሳብ መቆጣጠር ካለመቻላ቞ው በተጚማሪ ያለፍላጎታ቞ው ወደ ጭንቅላታ቞ው ዚሚመጣ ነው። “በተጚማሪም ይህ ያለፍላጎታቜን ዚሚመጣብን ሐሳብ ደስ ዹማይል እና ዚሚያስጚንቀን ሊሆን ይቜላል” ሲሉ ያክላሉ። በልጅነታ቞ው ሥነ ልቩናዊም ሆነ አካላዊ ጥቃት ወይንም ጉዳት ዚደሚሰባ቞ው ሰዎቜ ሲጎለምሱ ለዚህ ሕመም ሊጋለጡ እንደሚቜሉ ይናገራሉ። “አንዳንድ ሰዎቜ ወደ አእምሯ቞ው ዚሚመጣ ተደጋጋሚ ሃሳብ ብቻ ሊኖራ቞ው ይቜላል። ሌሎቜ ደግሞ አንድን ነገር ደጋግሞ ዹመፈፀም ጠንካራ ፍላጎት ሊኖራ቞ው ይቜላል። ያንንም በመፈፀም ለአጭር ጊዜም ቢሆን እፎይታ ያገኙ ይመስላ቞ዋል” ይላሉ። ዶ/ር ዮናስ ይህንን በምሳሌ ሲያስሚዱ፣ “አንድ ሰው በሃሳቡ እጅህ ላይ ጀርም ወይንም ደግሞ እጅህ ቆሻሻ ነው ዹሚል ነገር ይመጣበታል። ይህም አንዮ እና ሁለቮ ሳይሆን በተደጋጋሚ ስለሚመጣበት እጁን ንፁህ እንደሆነ ቢያውቅ እንኳ በቀን እስኚ 30 ጊዜ ሊታጠብ ይቜላል።” “ደምህ ውሰጥ ኀቜአይቪ አለ ዹሚል ሃሳብ ዚሚመጣባ቞ው ሰዎቜ አሉ። ያ ሰው ተመርምሮ በሜታው በደሙ ውስጥ እንደሌለ ቢያውቅ እንኳ ይህንን ተደጋጋሚ ሀሳብ ግን ማቆምም ሆነ ማቋሚጥ አይቜልም።” ዶ/ር ዮናስ እንደሚሉት ይህ ኊሲዲ ዚተባለ ዚአእምሮ ሕመም ሥራ እዚሰራን ወይንም በዚትኛውም ዚሕይወታቜን እንቅስቃሎ፣ በመካኚል ሊመጣብን ስለሚቜል ዚምንሰራውን ወይንም ድርጊታቜንን አቁመን በሃሳቡ ልንያዝ እንቜላለን። “እኛ ዚማንፈልገው፣ ፈጣሪያቜን ዚሚያሳዝን ሃሳብ ወደ አእምሯቜን ይመጣልፀ ማስቆም አልቻልንም ብለው ለሕክምና ወደ እኛ ይመጣሉ” ሲሉ ባለሙያው ኚልምዳ቞ው ይናገራሉ። ዶ/ር ዮናስ ይህ ሁኔታ ሕክምና ሊያስፈልገው ደሹጃ ላይ ዚሚደርስበት ዕድል ስላለ ምልክቶቹን መሚዳት አስፈላጊ ነው ይላሉ። ኹዚህ ውጪ ግን ይህ ሁኔታ እንደ ባህርይ ብቻ ያላ቞ው ሰዎቜ በኹፍተኛ ጥንቃቄ ዚሚሰሩ ይሆናሉ ይላሉ። “ዚሂሳብ ባለሙያዎቜ፣ በተደጋጋሚ ዚማጣራት እና ዚማሚጋጋጥ ባሕርይ ስላላ቞ው ስሌት አይሳሳቱም። ሌሎቜ እንደ ፓይለት እና ሜካኒክ ዓይነት ሥራዎቜም ኹፍተኛ ጥንቃቄ ስለሚፈልጉ ይህንን ዓይነት ባሕርይ ያላ቞ው ሰዎቜ በእነዚህ ሙያዎቜ ልህቀትን ሊያሳዩ ይቜላሉ።” አክለውም ይህ ዚኊሲዲ ሕመም በራሱ ወደ ሌላ ኚባድ ዚአእምሮ ሕመም ባይቀዚርም፣ ነገር ግን ወደ አእምሯቜን ዚሚመጣ ተደጋጋሚ ሃሳብ እና ዚምንፈጜመው ተደጋጋሚ ድርጊት መልሶ ሊያስጚንቀን ወይንም ደግሞ ድባ቎ ሊያመጣ እንደሚቜል ዶ/ር ዮናስ ይገልጻሉ። ለዚህ ሕመም ዹሚሰጠው ሕክምና በቂ አለመሆኑን ዚምታስሚዳው ምሥራቅ፣ “በሩን ክፍቱን አድርጌ ብሔድ፣ ሊፈጠር ዚሚቜለው ክፉ ነገር ምን ሊሆን ይቜላል ብዬ በማሰብ፣ ሃሳቡን ለማስቆም እጥር ነበር። ነገር ግን መጚሚሻ ላይ ስላልቻልኩኝ መድኃኒት መውሰድ ግድ ሆነ” ትላለቜ። አሁን በፀሎት እና በተሰጠኝ መድኃኒት ለውጥ እያሳዚሁ ነው ስትል ዚምትናገሚው ምሥራቅ፣ ለሕመሟ ዚተሰጣት መድኃኒት መጀመሪያ አካባቢ ሕመሟን አብሶባት እንደነበር ታስታውሳለቜ። “በዚህ ምክንያት መድኃኒቱን ኚሁለት ጊዜ በላይ ቀይሬያለሁ።” በዚህ ሕመም ውስጥ ያሉ ሰዎቜ ዚሚሰጣ቞ው ዚተለያዚ ዓይነት ሕክምና አለ። አንዱ ዚሥነ ልቩና ዹምክር አገልግሎት ሲሆን በዚህም ሳይፈልጉት ዚሚመጣባ቞ውን ሃሳብ ሊቆጣጠሩ ዚሚቜሉበትን ዘዎዎቜ ይማራሉ። ሁለተኛው ደግሞ አእምሮ እና ሰውነት እንዲፍታታ ዚማድሚግ ሕክምና ነው። “ለምሳሌ ሜዲ቎ሜን (አርምሞ)፣ እንደ ዮጋ ያሉ ዚአካል ብቃት እንቅስቃሎ እና ማሳጅ ማድሚግ” ና቞ው። ኚእነዚህ ባሻገር ደግሞ በሜታውን ሊቆጣጠሚው ዚሚቜለው መፍትሔ ለሕመሙ ዹተዘጋጀውን መድኃኒት መውሰድ ነው። እነዚህ ዹሕክምና ዓይነቶቜ ዹሰውዹው ዹሕመም ዓይነት እና ደሹጃ ላይ በመመስሚት ኚበሜታው እንዲድን ሊያደርጉ ይቜላሉ ይላሉ ዶ/ር ዮናስ። አሁን እዚተሻላት እንደሆነ ዚምትናገሚው ምሥራቅ ሰዎቜ እንዲህ ዓይነት ምልክቶቜን ካዩ በፍጥነት ወደ ሕክምና እንዲሄዱ ትመክራለቜ።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c6pqpg24lvno
amh
health
'ባሌ አጫሜ ነበሚ፣ በእሱ ምክንያት ካንሰር ያዘኝ'
“በአፍንጫዬ መተንፈስ አልቜልም። ዹምተነፍሰው ‘ስቶማ’ በሚባልና አንገቮ ላይ በሚገኝ ቀዳዳ አማካይነት ነው’’ ይላሉ ዹ75 ዓመት ዚዕድሜ ባለጞጋዋ ናሊኒ ሳትያናርያን። ናሊኒ በህይወታ቞ው እንድም ቀን ሲጋራ አጭሰው አያውቁም። ነገር ግን ላለፉት 33 ዓመታት ባለቀታ቞ው ኚሚያጚሱት ሲጋራ ዚሚመጣ ጭስ ሲተነፍሱ ኖሚዋል። ባለቀታ቞ው ሕይወታ቞ው ካለፈ ኚአምስት ዓመታት በኋላ በአውሮፓውያኑ 2010 ላይ ናሊኒ ካንሰር እንዳለባ቞ው ተነገራ቞ው። “ባለቀ቎ አጫሜ ነበር። ዚእሱ ሲጋራ ማጚስ እኔን ይሄን ያክል ይጎዳኛል ብዬ አስቀ አላውቅም ነበር። ለእሱ ጀና ነበር ዚምጚነቀው። ሁሌም ሲጋራ ማጚሱን እንዲያቆም ነበር ዚምነግሚው። ነገር ግን ሲጋራ ማጚሱን አልተወም ነበር” ይላሉ በሕንዷ ደቡባዊ ክፍል በምትገኘው ሀይድራባድ ዚሚኖሩት ናሊኒ። ዹዓለም ጀና ድርጅት እንደሚለው ሲጋራ በዚዓመቱ እስኚ 8 ሚሊዮን ዚሚደርሱ ሰዎቜን ይገድላል። ኚእነዚህ መካኚል ሁለት ሚሊዮን ዚሚሆኑት ደግሞ ሲጋራ አጫሜ አይደሉም። አብዛኞቹ በዙሪያ቞ው ዹሚገኙ ሰዎቜ ሲጋራ አጫሟቜ ዹሆኑ ና቞ው። በርካቶቜም በዚሁ ምክንያት ለተለያዩ ሕመሞቜ እዚተጋለጡ ነው። በዚዓመቱ ግንቊት 23 ዹዓለም ዹፀሹ ትንባሆ ቀን ነው። ናሊኒ በአንድ ወቅት ለልጅ ልጃቾው ታሪክ እያጫወቷት እያለ ነበር ድንገት ዚድምጻ቞ውን መቀዹር ያስተዋሉት። በአጭር ጊዜ ውስጥ ደግሞ በትክክል አንዳንድ ድምጟቜን ማውጣት እያቃታ቞ው መጣ። ኚትንሜ ጊዜ በኋላ ደግሞ መተንፈስ ጭምር ኚባድ እዚሆነ መምጣት ጀመሚ። ናሊኒ ወደ ህክምና ቊታ ሲሄዱ ያልጠበቁትን ዜና ሰሙ። ካንሰር እንዳለባ቞ውና በቀዶ ሕክምና ጉዳቱን መቀነስ እንደሚቻል ተነገራ቞ው። በቀዶ ሕክምናውም ድምጜ ዚሚያወጣው ዚጉሮሯ቞ው ክፍልና ዚታይሮይድ ዕጢያ቞ው እንዲወገዱ ተደሚገ። “ኹሕክምናው በኋላ መናገር አልቻልኩም። በጣም ዚሚያሳዝን አጋጣሚ ነበር። ዶክተሮቹ ዚቀድሞ ድምጌን ደግሜ ማግኘት እንደማልቜል ነገሩኝ።” ዹናሊኒ ዹልጅ ልጅ ዚሆነቜው ዹ15 ዓመቷ ጃናኒ ተጚዋቜ ዚሆኑት አያቷ ላይ ዹሆነውን ነገር በደንብ ታስታውሳለቜ። “ካንሰር እንዳለባት ሲነገራት ለሹጅም ጊዜ እኛ ጋር አልነበሚቜም። ተመልሳ ስትመጣ ዚአራት ዓመት ልጅ ነበርኩ። ሆዷ አካባቢ ቱቊ ነገር ተለጥፎባት ነበር። ቀታቜንን ቶሎ ቶሎ ማጜዳት ነበሚብን። አያ቎ ምን አይነት ቜግር ውስጥ እንደነበሚቜ በደንብ አይገባኝም ነበር” ትላለቜ። ናሊኒ በወቅቱ ዹነበሹን ጥሩ ሕክምና ስላገኙ ኹጊዜ በኋላ ተመልሰው መናገር ቻሉ። ነገር ግን በተለያዩ መርጃ መሳሪያዎቜ በመታገዝ ነው ድምጜ ዚሚያወጡት። “ይሄ ካንሰር ዚያዘኝ በባለቀ቎ ማጚስ ምክንያት ነው” ይላሉ ናሊኒ። “አጫሟቜ በጣም ጎጂ ዚሚባለውን ዚሲጋራውን ጭስ ወደ ውጪ ነው ዚሚተነፍሱት። በዚህ መሀል በጣም ተጎጂ ዚሚሆኑት በአቅራቢያ቞ው ዹሚገኙና ያንን ጭስ ወደውስጣ቞ው ዚሚያስገቡ ሰዎቜ ና቞ው።” ዹዓለም ጀና ድርጅት ሁሉም አይነት ሲጋራዎቜ ጎጂ እንደሆኑ ሁሌም ያሳስባል። ኹዚህ በተጚማሪ ደግሞ በማንኛውም ዚጀንነት ሁኔታ ላይ ዹሚገኙ ለጭሱ ዚሚጋለጡ ሰዎቜም ተጎጂዎቜ ይሆናሉ። በዓለም ጀና ድርጅት ዚአውሮፓ ቢሮ ዚትንባሆ ቁጥጥር ባለሙያ ዚሆኑት አንጄላ ቺባኑ እንደሚሉት፣ ዚማያጚሱ ሰዎቜ ለአንድ ሰዓት ያክል ለሲጋራ ጭስ ቢጋለጡ በተለይ በጉሮሯ቞ው አካባቢ ቀላል ዚማይባል ጉዳት ይደርስባ቞ዋል። አክለውም “ኚሌሎቜ ሰዎቜ ለሚመጣ ዚሲጋራ ጭስ ዚሚጋለጡ ሰዎቜ ኹ700 በላይ ኬሚካሎቜን ነው ወደ ውስጣ቞ው ዚሚያስገቡት። ኚእነዚህ ኬሚካሎቜ መካኚል ደግሞ 70 ዚሚሆኑት ለካንሰር ዚሚያጋልጡ ና቞ው። እነዚህ ሰዎቜ በሳንባ ካንሰር ዚመያዝ ዕድላ቞ው ኹ20 እስኚ 30 በመቶ ኹፍ ያለ ነው” ይላሉ ባለሙያዋ። ዚተባበሩት መንግሥታት በበኩሉ 65 ሺህ ዹሚሆኑ ህጻናት በዚዓመቱ በሲጋራ ምክንያት ህይወታ቞ው እንደሚያልፍ ይገልጻል። ኹዚህ በተጚማሪ ለሲጋራ ጭስ ዚሚጋለጡ ህጻናት በጆሮ ኢንፌክሜን ዚመያዝ ዕድላ቞ው ኹፍተኛ ነው። አንዳንዎ ባስ ሲል ደግሞ  ዚመስማት ቜሎታ቞ውን ሊያጡ ይቜላሉ። “ለሲጃራ ጭስ ዚተጋለጡ ህጻናት ለመተንፈሻ ቜግር ዚመጋለጥ ዕድላ቞ው ኹ50 እስኚ 100 በመቶ ኹፍ ያለ ሲሆን፣ ለአስም እንዲሁም ለድንገተኛ ሞት ዚመጋለጥ ዕድላ቞ውም ኹፍተኛ ነው” ይላሉ አንጄላ ቺባኑ። ጥቂት ዚማይባሉ ሲጋራ ዚሚያጚሱም ሆነ ዚማያጚሱ ሰዎቜ ሲጋራ ማጚስ መኹልኹል አለበት ብለው እንደሚኚራኚሩ ዹዓለም ጀና ድርጅት ይገልጻል። “ሙሉ በሙሉ ኚሲጋራ ነጻ ዹሆኑ አካባቢዎቜ መኖር ውጀታማ ዹሆነ ለውጥ ማምጣት ይቜላል። ሰዎቜ አጠገባቜሁም ሆነ ልጆቻቜሁ አካባቢ እንዲያጚሱ አትፍቀዱላ቞ው። ንጹህ አዹር መተንፈስ ሰዎቜ ሰብአዊ መብት ነው” ይላሉ አንጄላ ቺባኑ። ነገር ግን ሲጋራ ማጚስን ሙሉ በሙሉ መኹልኹል በጣም ኚባድ ነው። በዘርፉ ላይ በተሰራ አንድ ጥናት መሰሚት ዚሲጋራው ኢንዱስትሪ በአውሮፓውያኑ 2021 ብቻ 850 ቢሊዮን ዶላር አንቀሳቅሷል። ይህ ቁጥር በአፍሪካ ኹፍተኛውን ዚህዝብ ቁጥር ኚያዘቜው ናይጄሪያ አጠቃላይ ዹአገር ውስጥ ምርት ሁለት እጥፍ ነው። ጥናቱ እንደሚለው በቢሊዚኖቜ ዶላሮቜን መድበው ዚሚንቀሳቀሱት ኹፍተኛ ትርፍ ዚሚያገኙ ትልልቅ ድርጅቶቜ ሲጋራ ማጚስን ለማስኚልኚል ዹሚደሹጉ ጥሚቶቜ ላይ ጫና ያሳድራሉ። አይኑሩ አልቲቀቫ መሰል ሕጎቜ ተግባራዊ እንዲሆኑ ኚሚሰሩ ዚሕንድ ዚሕዝብ እንደራሎዎቜ አንዷ ና቞ው። በአውሮፓውያኑ 2018 ላይ ሕዝብ በተሰበሰበባ቞ው አካባቢዎቜ ሲጋራ ማጚስ እንዲኚለኚል ለማድሚግ እንቅስቃሎ ጀምሹውም ነበር። እሳ቞ው እንደሚሉት ሕንድ ውስጥ በዚዓመቱ ኚሲጋራ ጋር በተያያዘ ኹ6 ሺህ በላይ ሰዎቜ ሕይወታ቞ው ዚሚያልፍ ሲሆን መሰል ቊታዎቜ ላይ ማጚስን መኹልኹል ደግሞ ዹሚደርሰውን ጉዳት እስኚ 10 በመቶ ድሚስ መቀነስ ይቻላል። ነገር ግን ዚሕዝብ እንደራሎዋ ኹፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟ቞ው ነበር። “ዚሕዝብ እንደራሎዎቹ እራሳ቞ው በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ኚትምባሆ ኢንዱስትሪው ጋር ግንኙነት አላ቞ው። ሕዝብ በተሰበሰበባ቞ው አካባቢዎቜ ሲጋራ ማጚስ ዹሚኹለክለው ሕግ ወደተመሚጡ ኮሚ቎ዎቜ ነበር ዚተመራው። ነገር ግን ኮሚ቎ዎቹ ሆነ ብለው እንዲያዘገዩት ነው ዚተደሚገው። ዚኢኮኖሚ ጉዳዮቜ ሚኒስ቎ርም ቢሆን ኚታክስ ዹሚገኝ ገቢ ላይ ቅናሜ እንደሚኖር በመግለጜ ሀሳቡን አልደገፈውም ነበር’’ ይላሉ። “አንዳንድ ሰዎቜ እንዲያውም በማኅበራዊ ሚዲያዎቜ በኩል እኔንም ሆነ ቀተሰቀን ማጥቃት ጀምሹው ነበር።” አይኑሩ አልቲቀቫ ላለፉት ዓመታት እልህ አስጚራሜ ትግል ካደሚጉ በኋላ በአውሮፓውያኑ 2021 ላይ ሕንድ ውስጥ ሕዝብ በተሰበሰበባ቞ው አካባቢዎቜ ሲጋራ ማጚስ ተኚልክሏል። ነገር ግን ሥራው እዚያ ላይ አላበቃም። አይኑሩ ሲጋራ ማጚስ በጀና ላይ ዚሚያስኚትለውን ጉዳት እንዲሁም ህጻናት ላይ ዚሚያመጣውን መዘዝ በተመለኹተ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ዝግጅቶቜን ያስተባብራሉ። በዓለም አቀፍ ደሹጃ በትምባሆ ምክንያት ዚሚሞቱ ሰዎቜን ቁጥር ለመቀነስ ኹሚደሹጉ ጥሚቶቜ መካኚል በአውሮፓውያኑ 2005 ይፋ ዹተደሹገው ዚትምባሆ ቁጥጥር ስምምነት ተጠቃሜ ነው። እስካሁን ድሚስ 182 አገራት ዹዚህ ስምምነት አባል ለመሆን ፈርመዋል። ዹዘርፉ ባለሙያዎቜ እንደሚሉት አገራት ሕዝብ በተሰበሰበባ቞ው አካባቢዎቜ ሲጋራ ማጚስን እንዲኚለክሉም ይወተውታሉ። ሰዎቜ ንጹህ አዹር ዚመተንፈስ መብታ቞ው እንዲጠበቅ ሲባል መሰል ሕጎቜ ተግባራዊ መሆን አለባ቞ው ዚሚሉት ደግሞ በትምባሆ ቁጥጥር ላይ ዚሚሰራው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ ዚሚሰሩት ዶክተር ሜሪ አሱንታ ና቞ው። “ኚትምባሆ ጋር በተያያዘ ዚሚኚሰቱ ሞቶቜን ለመቀነስ ዹሚደሹገውን ጥሚት ማገዝ ዚሚቜሉ በርካታ እርምጃዎቜ አሉ። በዋነኛነትም ዚትምባሆ ምርት ላይ ኹፍተኛ ግብር ማስኚፈል፣ ማስታወቂያዎቜ ላይ ቁጥጥር ማድሚግ እንዲሁም ስለጉዳቱ ኹፍተኛ ትምህርት መስጠት ይጠቀሳሉ።” ምንም እንኳን ዹዓለም ጀና ድርጅት ዚሲጋራ አጫሟቜ ቁጥር ኚዓመት ዓመት እዚቀነሰ ነው ቢልም፣ አሁን ላይ ዚሲጋራ አጫሟቜ ቁጥር 1.3 ቢሊዚን ነው። ድርጅቱ እንዲመለው ኚአስር ሰዎቜ አንዱ ሲጋራ ዚሚያጚስ ሲሆን አብዛኞቹ ደግሞ ዚሚያጚሱት ቁጥጥር ዚማይደሚግባ቞ውና በሕገወጥ መንገድ ዚሚንቀሳቀሱትን ነው። ሕንድ ሃይድራባድ ውስጥ ነዋሪ ዚሆኑት ናሊኒ አሁን ላይ ጉዳዩን ወደ ሕግ ለመውሰድ አቅደዋል። አሁንም ድሚስ ጉሮሯ቞ው ላይ ባለው ቀዳዳ አማካይነት ብቻ ዚሚተነፍሱት ናሊኒ በሲጋራ ምክንያት ዹማንም ሰው ሕይወት እንደዚህ ሊበላሜ አይገባም ይላሉ። ናሊኒ ወደ ትምህርት ቀቶቜ እንዲሁም ማንኛውም ሕዝብ ወደሚሰበሰብባ቞ው ቊታዎቜ በመሄድ ስለሲጋራ ጉዳት ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ዝግጅቶቜን ዚሚያኚናውኑ ሲሆን፣ በትርፍ ጊዜያ቞ው ደግሞ ኹልጅ ልጆቻ቞ው ጋር በመጫወት ያሳልፋሉ። በባለቀታ቞ው ሲጋራ አጫሜነት ምክንያት ለካንሰር ተጋልጠው ለኚባድ ዚጀና ቜግር ቢዳሚጉም በሟቹ ባለቀታ቞ው ላይ ምንም አይነት ቂም አልያዙም። "በባሌ ላይ ፈጜሞ አዝኜበት አላውቅም። ባጋጠመኝ ነገር ላይ ማዘን ምንም ዹሚለውጠው ነገር እና ዹሚቀርፈው ቜግር ዚለም። አሁን እኔ እውነታውን ተቀብዬ ስላጋጠመኝ ዚጀና ቜግር ለመናገር ፈጜሞ አላፍርም” ይላሉ።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c6p914npjevo
amh
health
ዚራፕ ሙዚቃ አቀንቃኙ ካንዬ ዌስት “ሳትጠራ እና ሳታሳውቅ” መጥተሃል ተብሎ ኚስኬ቞ርስ ቢሮ እንዲወጣ ተደሹገ
ስኬ቞ርስ ዚተባለው ዚጫማ አምራቜ ኩባንያ ራፐሩ ዬ፣ በቀድሞ ስሙ ካንዬ ዌስት፣ “ሳያሳውቅ እና ሳይጋበዝ” መጥቷል በሚል ኚኩባንያው ሕንጻ እንዲወጣ እንዳደሚገው ገለፀ። ድርጅቱ አክሎም ኚራፐሩ እና ዲዛይነሩ ዬ ጋር በጋራ ዚመስራት “ምንም ዓይነት ፍላጎት” ዹለኝም ብሏል። ይህ ዜና ዹተሰማው ዹጀርመኑ ስፖርት ትጥቅ አምራቜ አዲዳስ፣ ዬ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ዹሰጠውን ፀሹ አይሁዳዊ አስተያዚት ተኚትሎ ያለውን ግንኙነት ካቋሚጠ በኋላ ነው። ቢቢሲ ዚዬን ወኪሎቜ አስተያዚት ቢጠይቅም ምላሜ ማግኘት አልቻለም። ስኬ቞ርስ በመግለጫው ዬ በቢሮው ኚሌሎቜ ጋር ሆኖ ኚመጣ በኋላ “ያልተፈቀደ ዹፊልም ቀሚጻ በማድሚግ ላይ ነበር” ብሏል። አብሚውት መጥተው ኚነበሩ ሰዎቜ ጋርም ዹተወሰነ ንግግር ኹተደሹገ በኋላ ሕንጻውን ለቅቀው እንዲወጡ መደሹጉን ጚምሮ ገልጿል። ኩባንያው አክሎም “ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ዚሚሰጣ቞ውን ኹፋፋይ ሀሳቊቜ ዹምንቃወም ሲሆን ዹፀሹ አይሁዳዊ ወይንም ማንኛነውንም ዓይነት ዚጥላቻ ንግግሮቜ አንታገስም” ብሏል። በተጚማሪም “በድጋሚ አጜንኊት መስጠት ዹምንፈልገው ዌስት ዚመጣው ሳያሳውቅ እና ሳይጠራ ነው” ብሏል። ዬ ዚባይ ፖላር ዲዝኊርደር ታማሚ ሲሆን ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ትልልቅ ስም ካላ቞ው ድርጅቶቜ ጋር እሰጥ አገባ ውስጥ እዚገባ ያለው ዚስራ ውል እዚተቋሚጠ ይገኛል። እነዚህ እርምጃዎቜ ዚዬን ገቢ ክፉኛ ዚሚጎዱት ሲሆን በቅርቡም ኚፎርብስ ዚቢሊዚነሮቜ ዝርዝር ስር ስሙ እንዲወጣ ሆኗል። መጜሔቱ ዬ ኚአዲዳስ ጋር ያለው ዚስራ ውል በመቋሚጡ ብቻ ካለው አጠቃላይ ዹ1.5 ቢሊዚን ዶላር ሀብት ወደ 400 ሚሊዬን ወርዷል ሲል አስፍሯል። ማክሰኞ ዕለት አዲዳስ ኚዬዚ ብራንድ ጋር ያለውን ትብብር “ዹፀሹ አይሁዳዊ እንዲሁም ዚትኛውም ዓይነት ዚጥላቻ ንግግርን አንታገስም” በማለት ውሉን ማቋሚጡ ይታወሳል። አዲዳስ አክሎም ኹአሁን ጀምሮ ምርቶቹ ኚገበያ አንዲወጡ ይደሹጋል ሲል አስታውቋል። ባለፈው ወር በፓሪስ ዚፋሜን ሳምንት ላይ “ኋይት ላይቭስ ማተር “ ዹሚል ቲሞርት ለብሶ በመገኘቱ አዲዳስ ጉዳዩን ማጀን ጀምሮ ነበር። ኚቀናት በኋላም ራፐሩ በትዊተር ገፁ ላይ ፀሹ አይሁዳዊ መልዕክት ያለው ጜሁፍ በማስፈሩ ወዲያው ኚማህበራዊ ሚዲያው ታግዷል። ኹዚህ ቀደምም ዚራፕ ሙዚቃ አቀንቃኙ ካንዬ ዌስት በታዋቂው ኮሜዲያን ትሬቚር ኖዋ ላይ በሰነዘሹው ዘር ተኮር ስድብ ምክንያት ኚኢንሰታግራም ለ24 ሰዓታት ታገዶ ነበር። አዲዳስ ተወዳጅ ኹሆነው ዬ ብራንድ ጋር ያለውን ስምምነት በመሰሹዙ ብቻ እኀአ በ2022፣ 217 ሚሊዹን ፓውንድ ይኚስራል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cj5z15d3g61o
amh
health
አንድ ውሻ በዝንጀሮ ፈንጣጣ መያዙን ዹአለም ዚጀና ድርጅት አስታወቀ
አንድ ውሻ ኚባለቀቱቶቹ በተላለፈ ዚዝጀሮ ፈንጣጣ ቫይሚስ መጠቃቱን ዹዓለም ጀና ድርጅት አስታወቀ። ይህ በዓይነቱ ዚመጀመሪያ ዹሆነው ዚበሜታው ስርጭት ሰዎቜ በቫይሚሱ ኚተያዙ በኋላ ራሳ቞ውን ኚቀት እንስሳቶቻ቞ውም ጭምር ማግለል እንዳለባ቞ው ዚሚያሳይ እንደሆነም ዚጀና ሃላፊዎቹ አስታውቀዋል። ሌሎቜ እንስሳትን ዹመበኹል አደጋን ለመቀነስ ቆሻሻን በጥንቃቄ ማስወገድ እንደሚያስፈልግ ዹዓለም ጀና ድርጅት አስጠንቅቋል። ውሟቜ በሜታውን ወደ ሌሎቜ ውሟቜ ወይም ወደ ሰዎቜ ያስተላልፉ እንደሆነ ዚሚያሚጋግጥ መሹጃ እስካሁን እንደሌለም ባለሞያዎቜ ገልጞዋል። ዚዝንጀሮ ፈንጣጣ በቆዳ-ለቆዳ ንክኪ እና ሰዎቜ ጚርቆቜን ጚምሮ አልጋ ወይም ፎጣ በቫይሚሱ ​​​​ኚተያዘ ሰው ጋር በጋራ ሲጠቀሙ ዹሚተላለፍ በሜታ ነው። በአሁኑጊዜ በዓለም ዙሪያ ወደ 35,000 ዹሚጠጉ ሰዎቜ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ዹተሹጋገጠ ሲሆን አብዛኛዎቹ በአውሮፓ፣ በሰሜን እናበደቡብ አሜሪካ ይገኛሉ ። እስካሁን ኚበሜታው ጋር በተያያዘ 12 ሰዎቜ መሞታ቞ው ሪፖርት ተደርጓል። ዹአለም ዚጀና ድርጅት ባለፈው ሃምሌ ወር ውስጥ ነበር ዚዝንጀሮ ፈንጣጣን አለማቀፍ ዚጀና አደጋ ሲል ያወጀው። ዚመጀመሪያው ዚዝንጀሮ ፈንጣጣ በሜታ ኹሰው ወደ ውሻ ዹተላለፈው በፓሪስ ኹተማ ሁለት አንድ ላይ በሚኖሩ ዚተመሳሳይ ጟታ አፍቃሪ ወንዶቜ ቀት ውስጥ ነው። ግለሰቊቹ ዚዝንጀሮ ፈንጣጣ ምልክቶቜ ማሳዚት ኚጀመሩ ኹ 12 ቀናት በኋላ ነበር በውሻ቞ው ላይም ምልክቶቜን ማዚት ዚጀመሩት። ባለሞያዎቜ ያደሚጉት ዹዘሹመል ትንታኔ እንደሚያሳዚው ውሻውን ያጠቃው ቫይሚስ ግለሰቊቹን ካጠቃው ጋር ቫይሚስ ጋር ተመሳሳይ ነው። ዚውሻው ባለቀቶቜም ውሻው አብሯ቞ው ሲተኛ እንደነበር ተናግሚዋል። በአለም ዚጀና ድርጅት ዚዝንጀሮ ፈንጣጣ ምላሜ ሰጪ ቡድን ውስጥ ዚ቎ክኒካል ስራዎቜ መሪ ዚሆኑት ዶ/ር ሮሳምንድ ሉዊስ “ይህ ኹዚህ በፊት ሪፖርት ያልተደሚገ ብሎም ለመጀመሪያ ግዜ ዹመዘገበ ወደ ውሻ ያጋጠመ ስርጭት ነው ብለን እናምናለን’’ ብለዋል። በተቋሙ ዚድንገተኛ ዚጀና አደጋዎቜ ሀላፊ ዚሆኑት ዶ/ር ማይክ ራያን “ጉዳዩ ያልተጠበቀ አይደለም” ብለዋል። ነገር ግን በሜታው ኚአንድ ዝርያ ወደ ሌላው መዘዋወሩ እጅግ እንደሚያሳስባ቞ውም ተናግሚዋል። አክለውም አንድ በሞታ ወደ አዲስ ዚእንስሳ ኹተላለፈ በኋላ እንደሚላመድ ብሎም እና በውስጡም ወደ አዲስ ዝርያ እንዲለወጥ እድል እንደሚሰጥ ተናግሚዋል። “ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ያጋጠመ ስርጭት ነው። ስለሆነም ውሟቜ ሊበኹሉ ይቜላሉ ማለት ነው። ነገር ግን ውሻው ሌሎቜ ውሟቜን ሊበክል ይቜላል ወይም ወደ ሰዎቜ ያስተላልፋል ማለት አይደለም’’ ሲሉ ዹአለም ዚጀና ድርጅት ዹዓለም አቀፍ ተላላፊ በሜታዎቜ ስጋት ዝግጁነት ሃላፊ ዚሆኑት ዶክተር ሲልቪ ብሪያንድ ተናግሚዋል። ዚዝንጀሮ ፈንጣጣን ለመኹላኹል በመላው አለም ያለው ዚክትባት አቅርቊት እስካሁን ድሚስ ውስን ነው። ባለፈው ሳምንት ብቻ በበሜታው ተይዘው ሪፖርት ዹተደሹጉ ሰዎቜ ቁጥር በ 20 በመቶ ጭሯል። ይህም ኚሳምንት በፊት ኹነበሹው በ20 በመቶ ብልጫ አለው። እስካሁን አብዛኛው በበሜታው ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ሲታይ ወንድ ዚተመሳሳይ ጟታ ዚግብሚ ሥጋ ግንኙነት ዚሚፈጜሙ ሰዎቜ ቁጥር ኹፍተኛ ነው።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cqlk1nd5877o
amh
health
“ስለ አዕምሮ ጀና በግልፅ መነጋገር ለሁላቜንም ጀንነት ነው” ያዕቆብ ተክዔ
ያዕቆብ ተክዔ (ዶ/ር) በአሜሪካው ፔንሲልቬንያ ዩኒቚርሲቲ ዚሥነ አዕምሮ ባለሙያ ነው። ያዕቆብ በትምህርቱ ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት፣ በሥራው ቎ራፒስትና ዹሙሉ ጊዜ ዚዩኒቚርሲቲ አስተማሪ ነው። ያዕቆብ ተውልዶ ያደገው በኀርትራ ሲሆን ዚድህሚ ምሹቃ ትምህርቱን ለመኚታተል ኚበቃበት ጊዜ አንስቶ ዚሥራ ዓለሙን እስኪቀላቀል ድሚስ ኑሮው በአሜሪካ ነው። ዚያዕቆብ ሥራ ዚሚያተኩሚው በስደትና በስደተኞቜ ላይ ሲሆን በተለይም ደግሞ ኚአፍሪካ፣ አብልጊም ኚኢትዮጵያና ኚኀርትራ ለተሰደዱ ሰዎቜን ዚአዕምሮ ጀና ድጋፍ እና ክትትል ያደርግላ቞ዋል። ያዕቆብ ኚባድ አደጋ፣ ዚፆታ ወይም ዚወሲብ ጥቃት ለደሚሰባ቞ው ኢትዮጵያውያን፣ ኀርትራውያንና ሱዳናውያን አስፈላጊውን ድጋፍ ይሰጣል። ሥራው በይበልጥ በኮቪድ ወሚርሜኝ ምክንያት መክበዱን ዹሚናገሹው ያዕቆብ በነባር አዕምሯዊ ተፅዕኖዎቜ ላይ ተደርቩ ኚወርሜኙ ጋር ዚመጡ ዚተለዚያዩ ውጥሚቶቜንም ጭምር ለማቃለል ብዙ ሥራ መሠራት እንደነበሚበት ይናገራል። ወሚርሜኙ ዚጀመሚበት ወቅት በተለይ ፍራቻ፣ መገለልና ዚመሳሰሉ ተያያዥ ቜግሮቜ ስለነበሩ ኢትዮጵያዊያንና ኀርትራውያን በተለዹ መልኩ እገዛ ያስፈልጋ቞ው እንደነበር ያስታውሳል። በስደተኞቜ ላይ ተዘውትሚው ይታዩ ዚነበሩ ዹቋንቋ ቀርነቶቜ፣ ዚባህል ልዩነቶቜና ኚሃገሩ ማህብሚሰብ ጋር ዚመዋሃድ ቜግሮቜ ላይ ወሚርሜኙ ያመጣው ዚመራራቅ፣ ያለ መጠያዚቅና ዚብ቞ኝነት ኑሮ አዕምሮ ላይ ኚበድ ያለ ተፅዕኖ እንደነበሚው ገልጿል። ይህንንም ለመቅሹፍ ኚመንግሥት ዚሚመጡና አስፈላጊ ዹሆኑ መሚጃዎቜን፣ ኢትዮጵያውያንና ኀርትራውያን በሚናገሯ቞ው ቋንቋዎቜ እንዲደርሷ቞ው እናደሚያደርጉ ኚቢቢሲ ጋር በነበሹው ቆይታ ወቅት ተናግሯል። በተጚማሪም ለአዕምሮ ጀናም አስፈላጊ ዹሆኑ መሚጃዎቜን በዹጊዜው በሚሚዷ቞ው ቋንቋዎቜ እና መንገድ እንደሚያደርስ ይናገራል። ያዕቆብ እነዚህን እና ሌሎቜ ያሉ ቜግሮቜ በሙሉ በጥሞና ካሰበባ቞ው በኋላ ሰዎቜ በቀላሉ፣ ሳይሳቀቁና ሰው አዹን አላዹን ሳይሉ መሚጃዎቜን ዚሚያገኙበትን መንገድ ማሰላሰል ጀመሚ። "በባህላቜን ስለ አዕምሮ ጀንነት በግልፅ ማውራት ወይም መነጋገር ኚባድ በመሆኑና በግልፅ ዚሚያወሩም ሰዎቜ መድልዖ ስለሚገጥማ቞ው በፈቃደኝነት እርዳታ ለማግኘት ዚሚጥሩ ኢትዮጵያውያን ወይም ኀርትራውያን ዚሉም። ይህ ደግሞ ቜግሩን አያጠፋውም፣ ማለት ስለቜግሩ ስላልተወራ ቜግሩ ይሰወራል ማለት አይደለም። በተለይ ዚአዕምሮ ጀና መጓደል ደግሞ ሥር እዚሰደደና እዚተባባሰ ዚሚመጣ በመሆኑ ቜግሩን እጥፍ ያደርገዋል። ለዚህም ነው መፍትሄ ማግኘት ፈልጌ ዹነበሹው" ይላል ያዕቆብ። ኢንተርኔት ዚበርካቶቜ ህይወት አካል በሆነት በዚህ ዘመን ቀላሉ መፍትሔ ዩቲዩብ መሆኑ ዹተገነዘበው ያዕቆብ፣ ዚራሱን ቻናል በመጀመር ማስተማር፣ አስፈላጊ መሚጃዎቜንና ምክሮቜን ማስተላለፍ ጀመሚ። እንደዚህ ማድሚጉ በስደት ዚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኀርትራውያን ቢያንስ ኚቀታ቞ውም ሆነው መድልዖን ሳይፈሩ አስፈላጊውን እርዳታ ለማግኘት ያስቜላ቞ዋል ብሎ አስቊ እንደሆነ ይገልፃል። "በርግጥ አንድ ባንድ እያገኘሁ ጊዜ ወስደን እንደምሚዳ቞ው ሰዎቜ ያህል በዩቲዩብ ጥልቀት ያለው እርዳታ ለማድሚግ ይኚብዳል። እንደዚያም ቢሆን ግን ዋና ዋና መልዕክቶቜን ስለማስተላልፍበት ሰዎቜ ሳይሳቀቁ በእራሳ቞ው ጊዜ ዹሚጠቅሟቾውን ዹምክር አገልግሎቶቜ ማግኘት ይቜላሉ" ይላል። ያዕቆብ በዩቲዩብ ዚሚያሰራጚው መልዕክት ዹሚኖሹውን ጥቅም ሲያስሚዳም "አብዛኛውን ጊዜ ስሜታ቞ውንና አዕምሮዋ቞ው ላይ ተፅዕኖ ዚሚያደርጉ ነገሮቜን አምቀው ስለሚይዙ በጊዜ ሂደት ጉዳቱ ዹኹፋ ይሆንባ቞ዋል። ለዚህ ነው ሰዎቜ ቢያንስ እርዳታ እንደሚያስፈልጋ቞ው ማወቃቾው በእራሱ ዚመጀመሪያው እርምጃ ዹሚሆነው" ይላል። አክሎም "እንደ ኮቪድ ዓይነት ወሚርሜኝ ደግሞ ሰዎቜን ቀት እንዲቀመጡ ዚሚያደርግ ኹሆነ ወይም ዚለመዷ቞ውን ማህበራዊ ስብስቊቜ በሚያስቀርባ቞ው ጊዜ ተፅዕኖው ይበዛባ቞ውና ነባር ዚአዕምሮ ቜግሮቜን ያባብስባ቞ዋል" ይላል። ኹጊዜ ወደ ጊዜ ሰዎቜ በአእምሮ ጀና ላይ ያላ቞ው አመለካኚት እዚተስተካኚለ እንደሆነ ዹሚናገሹው ያዕቆብ፣ ኚአምስት ዓመታት በፊት ዚግንዛቀ መፍጠሪያ ዘመቻዎቜ በሚያካሄድበት ወቅት ዹነበሹው ምላሜና አሁን ዹሚሰጠው ምላሜ በጣም ልዩነት እንዳለው ይገልፃል። ያዕቆብ ኚአምስት ዓመታት በፊት ዚነበሚበትን መሰናኹል በማስታወስ " ስለ አዕምሮ በሜታዎቜ ግንዛቀ ለማስፋት በምሠራበት ወቅት ብዙ ሰዎቜ ዓላማዬን ይጠራጠሩት ነበር። እንደውም በርካታ ሰዎቜ ዚአዕምሮ በሜታ መኖሩን እራሱ እንደሚጠራጠሩ ይነግሩኝ ነበር" ይላል። ሰዎቜ ዚሚያስፈልጋ቞ውን እርዳታ እንዳያገኙ ዚሚያኚለክሏ቞ው በማህበሚሰባቜን ሊገጥሟ቞ው ዚሚቜለውን መገለል በመፍራት እንደሆነም ያስሚዳል። በተጚማሪም "ዚአዕምሮ ቜግርን ብዙ ሰው በአንድ ጊዜ ሳይታሰብ እንደ ዱብ ዕዳ ዚሚወርድ ነገር ይመስላ቞ዋል። ነገር ግን በሂደትና ኹጊዜ ወደ ጊዜ ውጥሚት፣ ዚመንፈስ ጭንቀት ሲደራሚብ ካለበለዚያ በአግባቡና በተገቢው ጊዜ እርዳታ ሳይገኙ ሲቀር ዚሚኚሰት ነው" ይላል። እንደዚህም ሆኖ ግን ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙዎቜ ፍላጎት እያሳዩ እንደሆነና ኮሮና ባይመጣ ኖሮ ሙሉውን ዹ2020ን ዓመት በተለያዩ ዚአሜሪካና ዚካናዳ ኚተማዎቜ በመሄድ ንግግር እንዲያደርግና ለኢትዮጵያውያንና ኀርትራውያን እርዳታ እንዲሰጥ ተጠይቆ እንደነበር ይናገራል። "ዚአዕምሮ ታማሚ ሲባል እርቃና቞ውን እዚሮጡ በድንጋያ ሰዎቜን ዚሚያባርሩ ግለሰቊቜን ነው ሰዎቜ በአዕምሮዋ቞ው ዚሚስሉት። ይህ ደግሞ በጣም ዚተሳሳተ አመለካኚት ነው" ዹሚለው ያዕቆብ አስሚግጊ ማስሚዳት ዹሚፈልገው "ዚአዕምሮ በሜታ ወይም ዚአዕምሮ ጀና መጓደል ዚተለያዚ መልክ፣ ዓይነትና መገለጫ" እንዳለው ነው ይለናል። ኹሁሉም በላይ "በዚህ በኮሮና ወሚርሜኝ ምክንያት በቀጣዮቹ ዹተወሰኑ ዓመታት ዚአዕምሮ ጀና መጓደል ወሚርሜኝ ዹምናይ ይመስለኛል" በማለት ይህንንም ለመኹላኹል በቅድሚያ ኚወዲሁ ልናስስባ቞ው፣ ልንነጋገርባ቞ውና ልናደርጋቾው ዚሚገቡ ነገሮቜ መኖራ቞ውን ያስሚዳል። አእምሮ ጀና መጓደልን በተመለኹተ በዋነኛነት ልንኚታተላ቞ው ኚምንቜላ቞ው ምልክቶቜ መካኚል፡ እንደ ያዕቆብ ገለጻ እነዚህ ምልኚቶቜ ቀድሞ ማወቅ "እርዳታ ለሚያስፈልጋ቞ው ሰዎቜ በቶሎ እንድንደርስላ቞ው ያስቜለናል" ይላል። ዚአዕምሮ ጀና መጓደል ቋሚ አይደለም ዹሚለው ያዕቆብ፣ "አካላዊ በሜታ ሲገጥመን ሆስፒታል/ክሊኒክ ሄደን እንደምንታኚመው ሁሉ ለአዕምሯቜንም ተመሳሳይ እንክብካቀ ማድሚጋቜን ተገቢ ነው" ሲል ይመክራል። "ለብዙ ሰዎቜ ዚአዕምሮ ጀና መሰናኹል ቋሚ ቜግር ይመስላ቞ዋል ግን እውነታው ኹዚህ ዚራቀ ነው። ምክንያቱም ማንኛውም ሰው በተለያዚ ምክንያት ዚአዕምሮ ጀናው ሊስተጓጎል ይቜላል" በማለት ያብራራል ኢትዮጵያውያንን እና ኀርትራውያንን ለመርዳት ብዙ እንቅስቃሎዎቜ እያደሚገ ያለው ያዕቆብ ሥራው ገና ጅማሬው ላይ መሆኑን ይገልፃል። አክሎም ዹሰውን ግንዛቀ ኹመጹመርና ኚማሳደግ ባለፈ ደግሞ ዹቋንቋ ተግዳሮቱ ላይ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን ይናገራል።
https://www.bbc.com/amharic/news-58552208
amh
health
ኮሮናቫይሚስ፡ ዚአስትራዜንካን ክትባት ተጠቀሙ- ዹዓለም ጀና ድርጅት
በርካታ ዚአውሮፓ ሃገራት ዚኮሮናቫይሚስ መኚላኚያ ዹሆነውን አስትራዜንካ ክትባት ማገዳ቞ውን ተኚትሎ ዹዓለም ጀና ድርጅት ክትባቱን እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርቧል። ጀርመን፣ ፈሚንሳይ፣ ጣልያንና ስፔይንን ጚምሮ ሌሎቜ አገራት ዚኊክስፎርዱ አስትራዜንካ ክትባት ደም መርጋት በተያያዘ ቜግር አለበት በሚል ክትባቱ እንዳይሰጥ አግደውታል። ዹዓለም ጀና ድርጅት በበኩሉ ደም መርጋት ስለማስኚተሉ ምንም አይነት ማስሚጃ ዹለም ይላል። ዚድርጅቱ ዚክትባት ደህንነት ልሂቃንም በዛሬው ዕለት ተሰብስበው ስለ ክትባቱ ይመክራሉ ተብሏል። ዚአውሮፓ መድኃኒት ኀጀንሲም እንዲሁ ስለ ክትባቱ በዛሬው ዕለት ዚሚወያዩ ሲሆን በያዝነው ሃሙስም ዚደሚሱበትን ማጠቃለያ ለህዝብ ያሳውቃሉ ተብሏል። ሆኖም ኀጀንሲው ክትባቱን ተጠቀሙ ብሏል። በአውሮፓ ክትባቱን ኚተኚተቡ በኋላ ዹደም መርጋት ቜግር ያጋጠማ቞ው ሰዎቜ አሉ ብሏል። ነገር ግን ባለሙያዎቹ እንደሚሉት በአጠቃላይ ኚህዝብ ብዛቱ ጋር ሲነፃፀር ዹደም መርጋት ያጋጠማ቞ው ሰዎቜ ድንገተኛ መጹመር አላሳዚም ይላሉ ። በአውሮፓ ህብሚት አባላት አገራትና ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ 17 ሚሊዮን ሰዎቜ ዚአስትራዜንካ ክትባትን መኚተባ቞ውና ኚባለፈው ሳምንት ጀምሮ 40ዎቹ ዹደም መርጋት ቜግር እንዳጋጠማ቞ው አስትራዜንካ አስታውቋል። እዚተወሰዱ ያሉ ጥንቃቄዎቜ ይህንንም ተኚትሎ ዹጀርመን ጀና ሚኒስ቎ር በያዝነው ሳምንት ሰኞ ዕለት አስትራዜንካ ክትባት መስጠት በአስ቞ኳይ እንዲቆም ትዕዛዝ አስተላልፏል። ክትባቱ ዚአዕምሮ ደም መርጋት ወይም ሎሬብራል ቬይን ቶርምቊሲስ ቜግር ጋር መገናኘቱን አይተናል ብለዋል። ዚጀና ሚኒስትሩ ጄንስ ስፋን እንዳሉት ውሳኔ "ፖለቲካዊ" እንዳልሆነ ነው። "ሁላቜንም ቢሆን ይህ ውሳኔ ሊያስኚትለው ዚሚቜለውን ጉዳት እንሚዳለን። በቀላሉም ዚደሚስንበት አይደለም" ብለዋል። ዚፈሚንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኀል ማክሮን እንዲሁ ዚአውሮፓ መድኃኒት ኀጀንሲ ውሳኔውን እስኪያሳውቅ ድሚስ አገራ቞ው ክትባቱን ታግዳለቜ ብለዋል። "ቀለል ያለ መመሪያ ነው ያለንፀ ሳይንስንና በዘርፉ ላይ ዕውቀት ያላ቞ውን ዚጀና ባለስልጣናት ምክር ነው ዚምንኚተለውፀ ይህም ዚአውሮፓ ስትራ቎ጂ ምን መምሰል አለበት ዹሚለውን ዹሚጠቁም ይሆናል" ብለዋል። ዚጣልያን መድኃኒት ኀጀንሲም እንዲሁ ዚአውሮፓ መድኃኒት ኀጀንሲ ዚሚደርስበትን ማጠቃለያ እጠብቃለሁ በማለት አግዳዋለቜ። ዚስፔን ጀና ሚኒስትር ካሮሊና ዳሪያስ በበኩላ቞ው ክትባቱ ለመጪው ሁለት ሳምንት ይታገዳል ብለዋል። አዚርላንድ፣ ፖርቹጋል፣ዎንማርክ፣ ኖርዌይ፣ ቡልጋሪያ፣ አይስላንድ፣ ስሎቬኒያ ክትባቱን በጊዜያዊነት ያገዱ ሲሆን ዲሞክራቲክ ኮንጎና ኢንዶኔዥያ ዚክትባት መስጪያ ጊዜያ቞ውን አራዝመውታል። ኊስትሪያን ጚምሮ በርካታ ዚአውሮፓ አገራት ለጥንቃቄ ሲሊ ቢያግዱትም ቀልጂዚም፣ ፖላንድና ቌክ ሪፐብሊክ ክትባቱን እዚሰጡ ነው። ዚቀልጂዚም ጀና ሚኒስትር ፍራንክ ቫንደንብራውኬ እንዳስታወቁት ቀልጂዚም ካላት ኹፍተኛ ዚኮሮናቫይሚስ ህሙማን ቁጥርን በማዚት ክትባቱን አለመስጠት አትቜልም ብለዋል። ዚካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ በበኩላ቞ው አስትራዜንካን ጚምሮ በአገሪቱ እዚተሰጡ ያሉ ክትባቶቜ ደህንነታ቞ው ዹተጠበቀ መሆኑን ዚጀና ባለስልጣናቱ ነግሹውኛል ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-56411232
amh
health
ዓለም ተስፋ ዚጣለበት ዚኊክስፎርድ ዚኮሮና ክትባት ምርምር እንዲቆም ተደሹገ
ዚመጚሚሻ ዚክሊኒካል ሙኚራ ላይ ዹነበሹውና ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት ዹቆዹው ዚኊክስፎርድ ዩኒቚርስቲ ኚመድሃኒት አምራቹ አስትራዜኔካ ኩባንያ ጋር እያበለጞጉት ዹነበሹው ዚኮሮና ክትባት ነበር። ምርምሩ ለጊዜው ባለበት ይቁም ተብሏል። ምክንያቱ ደግሞ ዚክትባት ቅንጣቱን ዚወሰዱ በጎ ፍቃደኛ ተሳታፊዎቜ ህመም ስላጋጠማ቞ው ነው። ይሁን እንጂ ግዙፉ ዚመድኃኒት አምራቜ አስትራዜኔካ ይህ ዚሚያደናግጥ ሳይሆን ዚሚያጋጥም ነው ይላል። ህመም ዹተሰማቾው ተሳታፊዎቜ ለምን ህመም እንደተሰማ቞ው ለማወቅ ጊዜ ይፈልጋል። ዚኊክስትፎርድና ዚአስትራዜኔካ ዹምርምር ውጀት ዹዓለም አገራት ትንፋሻ቞ውን ውጠው በጉጉት ሲጠብቁት ዹነበሹ ነው። በዓለም ላይ በክትባት ሙኚራ ውስጥ እያለፉ ካሉ ደርዘን ኹሚሞሉ ዹምርምር ሥራዎቜ ሁሉ ይህ ግዙፉና ተስፋም ዚተጣለበት ነበር። ቀድሞ ለሕዝብ ይደርሳል፣ ዓለምን ይታደጋል ተብሎም ነበር። ይህ ዚኊክስፎርድና አስትራዜኔካ ዚጥምሚት ዚክትባት ምርምር ምዕራፍ 3 ደርሶ ነበር። ይህም ማለት ዋናዎቹን ዚምዕራፍ 1 እና 2 አልፎ፣ ፈዋሜነቱ ተሹጋግጩ በብዙ ቁጥር ሰዎቜ ላይ መሞኹር ዹጀመሹ ማለት ነው። በአሜሪካ፣ በዩኬ፣ በደቡብ አፍሪካና በብራዚል ዹሚገኙ 30ሺ ሰዎቜ ይህንን ክትባት እንዲወስዱ ተደርጎ ምን ዓይነት ምልክት እንደሚያሳዩ እዚተጠበቀ ነበር። ምዕራፍ 3 ዚመድኃኒት ሙኚራዎቜ በርካታ ሺህ ሰዎቜ ዚሚሳተፉባ቞ው ኹመሆናቾው ባሻገር ዓመታትን ይወስዳሉ። አሁን ባለው ዹዓለም ጉጉት ግን አመታት ይጠበቃሉ ወይ ዹሚለው አጠያያቂ ነው። ቀጥሎ ምን ይደሹጋል? እንዲህ ዓይነት ነገር ሲያጋጥም በሕክምናው ዓለም አዲስ አይደለም። 3ኛ ምዕራፍ ዚደሚሱ ዚመድኃኒት ሙኚራዎቜ ተሳታፊዎቜ ዹተለዹ ሕመም ሲያጋጥማ቞ው ለጊዜው እንዲቆሙ ይደሚጋል። አሁን ዹሆነውም ይኾው ነው። ኹዚህ በኋላ ገለልተኛ ዚተመራማሪዎቜ ቡድን በጉዳዩ እንዲገባ ይደሚጋል። ዚተወሰዱ ጥንቃቄዎቜን ኹፈተሾ በኋላ ሁሉም ሂደቶቜ ትክክል ነበሩ ተብሎ ሲታሰብ ዚመድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን ሙኚራውና ምርምሩ እንዲቀጥል ሊወስን ይቜላል። "እንዲህ ሰፊ በሆኑ ሙኚራዎቜ በተሳታፊዎቜ ላይ ህመም መኚሰቱ አዲስ ነገር አይደለም። ነገር ግን ገለልተኛ ወገን ሊያጣራው ይገባል" ብለዋል ዚኊክስፎርድ ዩኒቚርስቲ ቃል አቀባይ። ዚኊክስፎርድ ዩኒቚርስቲ ምርምሩን ለጊዜው እንዲያቆም ሲደሚግ ደግሞ ይህ ዚመጀመርያው አይደለም። ኚተሞኚሚባ቞ው ሰዎቜ ዚተወሰኑት አሟቾው ሆስፒታል ሲገቡ ምርምሮቜ ሁሉ ባሉበት ይቆማሉ። ይህ ዹተለመደ አሰራር ነው ይላል፣ ዚቢቢሲ ዚጀና ጉዳዮቜ ዘጋቢ። እንዲያውም ምርምሩ በጥቂት ቀናት ውስጥ ይቀጥል ሊባልም ይቜላል። ዚአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መድኃኒቱን ኚኅዳር 3 ምርጫ በፊት አጥብቄ እፈልገዋለሁ ሲሉ ነበር።
https://www.bbc.com/amharic/54078490
amh
health
ሕንድ ፡ በአንድ ሆስፒታል ላይ በተኹሰተ ዚእሳት አደጋ 10 አራስ ሕፃናት ሞቱ
ዛሬ ቅዳሜ ጠዋት በሕንድ አንድ ሆስፒታል ላይ በደሹሰ ዚእሳት አደጋ ዚሆስፒታሉ ሠራተኞቜ ህይወት ለማትሚፍ ዚቻሉትን ቢያደርጉም አስር አራስ ሕፃናት ህይወት ማለፉ ተነገሚ። ዚእሳት አደጋ ተኚላካዮቜ በምዕራባዊው ማሃራሜትራ ግዛት ወደምትገኘው ዚብሃንዳራ አካባቢ ሆስፒታል እሳቱን ለመቆጠጠር ኚመድሚሳ቞ው በፊት ሰባት ሕፃናትን ኚእሳት አደጋው ማትሚፍ ተቜሏል። ዚሕንድ ጠቅላይ ሚንስትር ናሬንድራ ሞዲ "ልብ ዚሚያቆስል አሳዛኝ ክስተት" ሲሉ አደጋውን ገልጞዋል። ዚእሳት አደጋው ዹተኹሰተው አርብ ሌሊት ለቅዳሜ አጥቢያ መሆኑን ዚሆስፒታሉ ኃላፊዎቜ ዚገለጹ ሲሆን መንስኀው ምን እንደሆነ እስካሁን ያልታወቀ ነገር ዹሌለ ሲሆን ምርመራ እዚተደሚገ ይገኛል። በእሳቱ ሳቢያ በሆስፒታሉ ውስጥ ዚተኚሰቱት ተኚታታይ ፍንዳታዎቜ ዚነፍስ አድን ሥራውን ማሰናኹሉን ዚአካባቢው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በሥራ ላይ ዚነበሚቜ አንዲት ነርስ ኚሆስፒታሉ አዲስ ዚተወለዱ አራስ ህጻናት እንክብካቀ ክፍል ውስጥ ጭስ ሲወጣ ካዚቜ በኋላ ለባለስልጣናት ማስታወቋን ተናግራለቜ። ዚአካባቢው ዚቀዶ ጥገና ሐኪም ፕራሞድ ካንዳ቎ እንደገለጹት "ዚሆስፒታሉ ባለሥልጣናት ሰባት ህፃናትን ቢያድኑም 10 ህጻናት ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ሞተዋል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ በደሚሰባ቞ው ሐዘን ኚሟቜ ቀተሰቊቜ ጎን መሆናቾውን በትዊተር ገፃቾው አስታውቀዋል። ዚሕንድ ዹአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር አሚት ሻህ ስለአደጋው እንዳሉት "ቃላት ዚማይገልጹት ዹማይጠገን ጉዳት ነው" ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-55581634
amh
health
ኮሮናቫይሚስ፡ ኒውዚላንድ ኚወራት በኋላ በቫይሚሱ ዚተያዘቜ ሎት አገኘቜ
ኚሁለት ወራት በላይ ዚኮሮናቫይሚስ ዚማህበሚሰብ ስርጭት ያልታዚባት ኒውዚላንድ ኹሰሞኑ በቫይሚሱ ዚተያዘቜ ሎት አግኝታለቜ። ዚጀና ባለሙያዎቜ ኹሰሞኑ ኚአውሮፓ ዚተመለሰቜ ዹ56 አመት ሎት ቫይሚሱ ተገኝቶባታል። ግለሰቧ ኹሌላ አገራት ለሚመጡ አስገዳጅ ዹሆነውን ዚሁለት ሳምንት ለይቶ ማቆያ ጊዜ ጚርሳ ቀቷ ኚሄደቜ ኚቀናት በኋላ ነው ቫይሚሱ እንደተገኘባት ዚታወቀው። ኚሎትዮዋ ጋር ዚቅርብ ግንኙነት ያላ቞ውን እንዲሁም ዚጎበኘቻ቞ውን ስፍራዎቜ ዝርዝር ባለስልጣናቱ እዚተኚታተሉ ነው ተብሏል። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝን በመግታት ዘርፍ ኹፍተኛ ሙገሳና ምስጋና ካተሚፉ አገራት መካኚል ኒውዚላንድ በዋናነት ትጠቀሳለቜ። አምስት ሚሊዮን ነዋሪዎቜ ያሏት ኒውዚላንድ እስካሁን ድሚስ በቫይሚሱ ዚመዘገበቜው ቁጥር 1 ሺህ 927 ሲሆን 25 ዜጎቿም ሞተዋል። ግለሰቧ በኊክላንድ ዚነበራትን ዚለይቶ ማቆያ ጊዜዋን ኚጚሚሰቜ በኋላ ባደሚገቜው ምርመራ ሁለት ጊዜ ኚቫይሚሱ ነፃ ነሜ ተብላ ነበር። ኚሁለት ቀናት በኋላ ቀለል ያሉ ዚቫይሚሱን ምልክቶቜ ማሳዚት ዚጀመሚቜ ሲሆን በኋላም እዚኚፋና እዚባሰባት መጥቷል ተብሏል። ምርመራ ባደሚገቜበት ወቅት በቫይሚሱ እንደተያዘቜ ዚታወቀ ሲሆን ኚዚያ ቀን በኋላ በቀቷ ራሷን ለይታ ተቀምጣለቜ። በዛሬው ዕለት ዚጀና ሚኒስትሩ ክሪስ ሂፕኪንስ እንዳሉት ዚቫይሚሱ ዝርያ ኚዚት እንደመጣ ለመገመት በአሁኑ ሰዓት ኚባድ ነው ብለዋል። ነገር ግን ሚኒስ቎ር መስሪያ ቀቱ " ዚቫይሚሱ ዝርያ አይነት በኹፍተኛ ፍጥነት ዹሚተላለፍ እንደሆነ በማሰብ አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ እያደሚግን ነው" ብሏል። ኹዚህ በላይ ግን ስለ ቫይሚሱ ምንም ማለት እንደማይቻል ሚኒስትሩ ተናግሚዋል። ዚለይቶ ማቆያ ጊዜዋን ኚጚሚሰቜ በኋላ በሰሜናዊ ኒውዚላንድ ዹሚገኙ ቊታዎቜን ጎብኝታለቜ ተብሏል። ዚጀና ሚኒስ቎ር ጎብኝታ቞ዋለቜ ብሎ ዚጠቀሳ቞ውን ሱፐር ማርኬቶቜ፣ ሬስቶራንቶቜና ጋለሪዎቜ ዝርዝር አውጥቷል።። በነዚህ በተጠቀሱት ቊታዎቜ ድንገት ተገኝቶ ዹነበሹ ሰው በሙሉ በጥርጣሬ እንደሚታይና ቀታ቞ውም ራሳ቞ውን ለይተው እንዲቆዩና እንዲመሚመሩም ተነግሯ቞ዋል። ኚሎትዮዋ ጋር ቅርበት አላቾው ዚተባሉ አራት ሰዎቜ ዚተለዩ ሲሆን ምርመራ ተደርጎላቾዋል ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-55785138
amh
health
ዹዓለም ጀና ድርጅት ክትባቶቜ ኊሚክሮንን መቋቋም አለባ቞ው አሉ
ዚኮሮናቫይሚስን ለመኹላኹል በአሁን ላይ በጥቅም ላይ እዚዋሉ ዚሚገኙት ክትባቶቜ በአዲሱ ኊሚክሮን ዚቫይሚስ ዚሚያዙ ሰዎቜ ኚባድ ዚጀና እክል እንዳይገጥማ቞ው መኹላኹል እንደሚቜሉ ዹዓለም ጀና ድርጅት ኹፍተኛ ኃላፊ ተናገሩ። ኃላፊው ይህን ያሉት በደቡብ አፍሪካ በተደሹጉ ሙኚራዎቜ ይህ ቫይሚስ በተለይ ዹፋይዘር ክትባትን ማሾነፍ እንደሚቜል ምልክቶቜ አሉ መባላ቞ውን ተኚትሎ ነው። ተመራማሪዎቜ እንደሚሉት ሰዎቜ በአዲሱ ቫይሚስ ሲያዙ ዚኮሮናቫይሚስ ክትባቶቜ በሰውነታቜን ዚሚፈጥሩ ዹመኹላኹል አቅም በእጅጉ ይቀንሳል። ነገር ግን ዹዓለም ጀና ድርጅት ኃላፊ ዶክተር ማይክ ራያን ኊሚክሮን ክትባቶቜን ሙሉ በሙሉ ዚመገዳደር አቅም እንዳለው ዚሚያሳይ ምንም አይነት ምልክት አልተገኘም ብለዋል። "እስካሁን ድሚስ ሁሉንም አይነት ቫይሚሶቜ መኹላኹል ዚሚቜሉ ውጀታማ ክትባቶቜን አግኝተናል። በኊሚክሮን ምክንያት ኚባድ ዚጀና እክል ዚሚገጥመው አልያም ሆስፒታል እስኚ መግባት ዚሚደርስ ሰው ይኖራል ብሎ መገመት በጣም ኚባድ ነው'' ብለዋል ዹዓለም ጀን ድርጅት ኹፍተኛ ኃላፊው ዶክተር ማይክ ራይን። ኃላፊው አክለውም ኊሚክሮን ኹዚህ በፊት ኚታዩት ሌሎቜ ዚኮሮሚናቫይሚስ ዝርያዎቜ አንጻር እንደውም ሰዎቜም ዚማሳመም አቅሙ ዝቅተኛ ነው ብለዋል። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ተሰርቶ እስካሁን በሌሎቜ ተመራማሪዎቜ ባልተገመገመ አዲስ ጥናት መሰሚት ግን ዹፋይዘር/ባዮን቎ክ ክትባት ኚኊሚክሮን ጋር ሲገናኝ ውጀታማነቱ 40 በመቶ እንደሚቀንስ አመልክቷል። ነገር ግን ኊሚክሮን ሙሉ በሙሉ ኚክትባቱ እንደማያመልጥ ደርሰንበታል ይላሉ በአፍሪካ ሄልዝ ሪሰርቜ ኢንቲትዩት ውስጥ ተመራማሪ ዚሆኑት ፕሮፌሰር አሌክስ ሲጋል። ተመራማሪው እንደሚሉት ኹዚህ በፊት ዚተያዙ ሰዎቜ እንዲሁም ክትባቱን ዚወሰዱ ሰዎቜ ኊሚክሮንን ዹመቋቋም አቅማቾው ኹፍተኛ ነው ካሉ በኋላ ሶስተኛ ዙር ክትባት መውሰድ ደግሞ ይበልጥ ዹመኹላኹል አቅምን ኹፍ እንደሚያደርገው አስሚድተዋል። አዲሱ ኊሚክሮን እስካሁን ኹ30 በላይ አገራት ውስጥ ዹተገኘ ሲሆን ሰዎቜ በክትባትም ሆነ ኮሮናቫይሚስ ሲይዛ቞ው ዚሚያዳብሩትን በሜታ ዹመኹላኹል አቅም ሊቋቋም ዚሚቜል ነው። ነገር ግን ኹዚህ በፊት ኚነበሩት ዚኮሮናቫይሚስ አይነቶቜ አንጻር እስካሁን ቀላል ዚሚባሉ ምልክቶቜን ብቻ ነው ያሳዚው። በዚህም ምክንያት ስለ ቫይሚሱ፣ ስለ ስርጭቱ እና ስለሚያደርሰው ጉዳት በርካታ መላ ምቶቜ እዚተሰነዘሩ ነው። መነሻውን በደቡብ አፍሪካ አገራት ያደሚገው አዲሱ ዚኮሮናቫይሚስ አይነት ለዓለማቜን ተጚማሪ ስጋትን ፈጥሮ ቆይቷል። ይህ አዲስ ዝርያ እስካሁን ኚታዩት ዚኮሮናቫይሚስ አይነቶቜ እጅግ ዹተለዹው ነው ተብሏል። በበርካታ ብዙ ዹዘሹመል ለውጥ ውስጥ በማለፉ በአንድ ሳይንቲስት "አሰቃቂ" ተብሎ ሲገለጜ ሌላው ደግሞ እስካሁን ኚታዩት ዹኹፋ ዝርያ ነው ብለዋል። ዚደቡብ አፍሪካው ሮንተር ፎር ኀፒዎሚክ ሪስፖንስ ኀንድ ኢኖቬሜን ዳይሬክተር ዚሆኑት ፕሮፌሰር ቱሊዮ ዮ ኊሊቬራ ስለዚህ አዲስ ዝርያ ሲናገሩፀ "ያልተለመደ ዹዘሹ መል ለውጥ ያለው" ሲሆን ኚተሰራጩት ሌሎቜ ዝርያዎቜም "በጣም ዹተለዹ ነው" ብለዋል። በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ደግሞ ዹፋይዘር ክትባት ኊሚክሮን ላይ ዹሚኖሹው ጥንካሬና ድክምትን በተመለኹተ መሚጃዎቜ ይፋ እንደሚሆኑ ይጠበቃል። እስካሁን ድሚስ እንደ ሞደርና፣ ጆንሰን ኀንድ ጆንሰን ያሉ እንዲሁም ሌሎቜ ክትባቶቜ ኚአዲሱ ኊሚክሮን አንጻር ያላ቞ው ውጀታመነትን በተመለኹተ ምንም ጠቃሚ መሹጃ አልተገኘም።
https://www.bbc.com/amharic/news-59574506
amh
health
ወላጆቻ቞ው ዚሚያጚሱ ልጆቜ አጫሜ ዹመሆን ኹፍተኛ ዕድል እንዳላ቞ው ጥናት አመለኹተ
ወላጆቻ቞ው ዚሚያጚሱ ታዳጊዎቜ እነሱም አጫሜ ዹመሆን አራት እጥፍ ዕድል እንዳላ቞ው በዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት አማካይነት ዚተሰራ አንድ አዲስ ጥናት አመለኚተ። በዚህም ምክንያት ዶክተሮቜ ሲጋራ ዚሚያጚሱ ወላጆቜንና አሳዳጊዎቜን ማጚስ እንዲያቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ዹፀሹ ሲጋራ ማጚስ ዘመቻ እንቅስቃሎ እንዳለው ወላጆቻ቞ው ዚሚያጚሱ ታዳጊዎቜ 4.9 በመቶ እነሱም አጫሜ ዹመሆን ዕድል ሲኖራ቞ው፣ ወላጆቻ቞ው ዚማያጚሱ አቻዎቻ቞ው ግን ዚማጚስ ዕድላ቞ው 1.2 በመቶ ብቻ እንደሆነ አመልክቷል። ዚዩናይትድ ኪንግደም ብሔራዊ ዚጀና አገልግሎት ባዘጋጀው አዲስ ፊልም ላይ ዚጀና ባለሙያዎቜ በአዋቂዎቜ አጫሟቜና ማጚስ በሚጀምሩ ልጆቜ መካኚል ስላለው ግንኙነት ውይይት አድርገዋል። ዹፀሹ ማጚስ ዘመቻው አዋቂ አጫሟቜ በዙሪያ቞ው ባሉ ወጣቶቜ ሕይወት ላይ ስለሚፈጥሩት ተጜዕኖ በጥናት ዹተደገፈ መሹጃን አቅርቧል። አጠቃላይ ሐኪም ዚሆኑት ዶክተር ናያት አሪፍ እና ዚልጆቜ ሥነ ልቩና ባለሙያ ዚሆኑት ዶክተር ቀቲና ሆህነን ወላጆቜ ማጚስን እስኚ መጚሚሻው በመተው በልጆቻ቞ው ሕይወት ላይ ዚሚታይ በጎ አስተዋጜኊ እንዲያበሚክቱ ጥሪ አቅርበዋል። በውይይቱ ላይ ዚጀና ሚኒስትሯ ማጊ ትሮፕ፣ ይህ አዲሱ ዚጥናት ውጀት ወላጆቜ ማጚስ እንዲያቆሙ ተጚማሪ መነሳሻ ሊሆናቾው እንደሚቜል ተስፋ቞ውን ገልጞዋል። ሚኒስትሯ ጹምሹውም ዹተጀመሹው አዲሱ ፀሹ ማጚስ ዘመቻ "ሲጋራ በትውልዶቜ መካኚል ያለውን ተያያዥነት በማሳዚት ወላጆቜ በልጆቻ቞ው ላይ ዚሚያሳድሩትን ተጜዕኖ ያጎላል" በማለት ይህም "ኚሲጋራ ማጚስ ለመገላገል ጥሩ አጋጣሚን ይፈጥራል" ብለዋል። ዚአገሪቱ ጀና ሚኒስ቎ር ለወላጆቜ፣ ለአሳዳጊዎቜ እንዲሁም ሲጋራ ማቆም ለሚፈልጉ ሰዎቜ ዹሚጠቅሙ ዚተለያዩ ዚድጋፍ አገልግሎቶቜ እንዳሉ ገልጞዋል። ሲጋራ ለማቆም ዚሚያግዝ መተግበሪያ፣ በፌስቡክ ላይ ዹሚደሹግ ድጋፍ፣ በዚዕለቱ ዹሚላክ ዚኢሜይል እና ዚጜሁፍ መልዕክት እንዲሁም በኢንትርኔት ላይ ዹሚገኝ ግላዊ ሲጋራ ዹማቆም ዕቅድ መዘጋጀቱን ሚኒስትሯ ገልጞዋል።
https://www.bbc.com/amharic/59802873
amh
health
ለሁለት ዓመት ድንበሯን ዘግታ ዚቆዚቜው ኒው ዚላንድ በሯን ልትኚፍት ነው
በኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ምክንያት ኚሁለት ዓመታት በላይ ድንበሯን ዘግታ ዚቆዚቜው ኒው ዚላንድ በስተመጚሚሻ በሮቿን ልትኚፍት እንደሆነ ይፋ አድርጋለቜ። ኚሚቀጥለው ወር ጀምሮ አውስትራሊያዊያን ምንም ዓይነት በለይቶ ማቆያ መቆዚት ሳያስፈልጋ቞ው በነፃነት መግባት ይቜላሉ። ኹ60 ሃገራት ዚሚመጡ ሙሉ በሙሉ ዚተኚተቡ ሰዎቜ ደግሞ ኚግንቊት ወር ጀምሮ መግባት እንዲቜሉ ይፈቀድላ቞ዋል። ኚእነዚህ ሃገራት መካኚል ዩናይትድ ስ቎ትስ እና ዩናይት ኪንግደም ይገኙበታል። ሁሉም ወደ ኒው ዚላንድ ዚሚመጡ ተጓዊቜ ኚኮቭድ ነፃ መሆናቾውን ዚሚያሳይ ወሚቀት ማሳዚት አለባ቞ው። ኒው ዚላንድ ድንበሯን ሙሉ በሙሉ ዝግ በፈሚንጆቹ መጋቢት 2020 ነበር። ኒው ዚላንድ ለአውስትራሊያ ኚሰጠቜው ለአጭር ጊዜ ዹቆዹ ዹጉዞ ፈቃድ ውጭ ድንበሯን ለማንም ሳትኚፍት ቆይታለቜ። አሁን ላይ ወደ ሃገሪቱ መግባትና መውጣት ዚሚቜሉት ዹኒው ዚላንድ ዜጎቜ ብቻ ና቞ው። ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደን እንዳሉት ኒው ዚላንድ "ዓለምን ለመቀበል ዝግጁ ናት።" "አሁን በተሰጠን መመሪያ መሠሚት ድንብራቜንን ለመክፈት ሁሉም ነገር ምቹ ይመስላል። ቱሪስቶቻቜንም ይመለሳሉ" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሯ። ወደ ኒው ዚላንድ ለመግባት ቪዛ ቀድሞ ያላ቞ው ሰዎቜ ኚግንቊት ወር ጀምሮ እንደልባ቞ው መንቀሳቀስ ይቜላሉ። ኒው ዚላንድ ጠንካራ ዚሚባል ዚእንቅስቃሎ ገደብ በመጣሏ ዚኮቪድ-19 ስርጭትን በመቆጣጠር ስሟ በተደጋጋሚ ይነሳል። ኹኒው ዚላንድ ነዋሪዎቜ 95 በመቶው ተኚትበዋል። ወሚርሜኙ ኹጀመሹ ወዲህ በኮቪድ ምክንያት ዚሞቱ ሰዎቜ ቁጥር 115 ብቻ ነው። ያልተኚተቡ ሰዎቜ ሥራ አያገኙም መባሉን ተኚትሎ በዋና ኹተማዋ ዌሊንግተን ተቃውሞ ተቀስቅሶ እንደነበር አይዘነጋም። ምንም እንኳ ኒው ዚላንድ ድንበሯን ኚፍታፀ እጇን ዘርግታ እንግዶቜ ለመቀበል ብትዘጋጅም አሁንም ቢሆን በርኚት ብሎ መሰባሰብም ሆነ ያለጭንብል መንቀሳቀስ ክልክል ነው።
https://www.bbc.com/amharic/60761357
amh
health
ኮሮናቫይሚስ : አዲሱ ዚቫይሚስ ዝርያ በመላው ዓለም ሊሰራጭ ይቜላል ተባለ
አዲሱ ዚኮሮናቫይሚስ ዝርያ በመላው ዓለም ሊሰራጭ ይቜላል ተባለ። ኬንት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ዹተገኘው ዚኮሮናቫይሚስ ዝርያ በዓለም ላይ በስርጭቱ ቀዳሚው ሊሆን ይቜላል ሲሉ ዚዩናይትድ ኪንግደም ዹዘሹ መል ክትትል መርሃ ግብር ኃላፊ ገልጞዋል። ኃላፊው ፕሮፌሰር ሻሮን ፒኮክ ለቢቢሲ እንደተናገሩት አዲሱ ዝርያ "በአገሪቱ ዚተሰራጚ" ሲሆን "በመላው ዓለም ዚመሰራጭ ዕድሎቜም" አሉት ብለዋል፡፡ በኬንት ዹተገኘው ዝርያ ኹ50 በላይ በሆኑ አገራት ውስጥ ተሰራጭቶ ይገኛል። ዚኮሮናቫይሚስ ዝርያ በደቡብ ምስራቅ እንግሊዝ በጎርጎሮሳዊያኑ መስኚሚም 2020 ለመጀመሪያ ጊዜ ዹተገኘ ሲሆንፀ በቀጣይ ወራት በፍጥነት ተስፋፍቶ በጥር ወር በመላው ዩናይትድ ኪንግደም አዲስ ዚእንቅስቃሎ ገደብ እንዲጣል ምክንያት ሆኗል። ፕሮፌሰር ፒኮክ "በእውነቱ ኹሆነ እኛን በመጉዳት ላይ ዹሚገኘው በኹፍተኛ ፍጥነት መተላለፉ ነው" ብለዋል። ለኮሮናቫይሚስ ዚተሠሩ ክትባቶቜ ቀደም ሲል ለነበሹው ዚቫይሚሱ ዙሪያ ዚተመሚቱ ቢሆንም ሳይንቲስቶቜ አሁንም ቢሆን በአዲሱም ዝርያ ላይ ይሠራሉ ብለው ያምናሉ። ውጀታማነታ቞ውን ግን ጥሩ ላይሆን ይቜላል። በዩናይትድ ኪንግደም ጥቅም ላይ እንዲውሉ ዹተፈቀደላቾው ክትባቶቜ በአገሪቱ ውስጥ ባሉ ዚቫይሚስ ዓይነቶቜ ላይ በጥሩ ሁኔታ ዚሚሠሩ ይመስላሉ ብለዋል ፕሮፌሰር ፒኮክ።
https://www.bbc.com/amharic/news-56027521
amh
health
ኢኳዶር ለሁሉም ዜጎቿ ዚኮቪድ-19 ክትባትን መውሰድ ግዎታ አደሚገቜ
ኢኳዶር እዚተባበሰ ዚመጣውን ዚኮሮናቫይሚስ ስርጭት ለመግታትና እንደ ኊሚክሮን ያሉ ዝርያዎቜን ጉዳት ለመቀነስ በሚል አብዛኛው ዚኅብሚተሰብ ክፍል ዚኮቪድ-19 ክትባት እንዲወድ ዚሚያስገድድ መመሪያ አወጣቜ። ዚአገሪቱ ዚጀና ሚኒስ቎ር እንዳለው አጠቃላይ ሕዝቡን ለመኚተብ ዚሚያስቜል ዚክትባት ክምቜት ያለ ሲሆን፣ ዹሕክምና ማስሚጃ ያላ቞ው ሰዎቜ ብቻ ያለመኚተብ መብት ይኖራ቞ዋል። ኚአገሪቱ አጠቃላይ ሕዝብ ውስጥም ማንኛውም ዕድሜው ኚአምስት ዓመት በላይ ዹሆነ ሰው በሙሉ ክትባቱን ይወስዳል ተብሏል። እስካሁን ድሚስ ዕድሜያ቞ው ለክትባት ኚደሚሱ ሰዎቜ ውስጥ 77.2 በመቶ ያህሉ ሁለት ዙር ክትባት ሲወስዱ ኹ900 ሺህ በላይ ዚሚሆኑት ሰዎቜ ሊስተኛ ዙር ክትባታ቞ውን ወስደዋል። ዚጀና ሚኒስ቎ር እንደገለጞውፀ ክትባቱ ቫይሚሱን ለመኹላኹል ዚሚያስቜል አቅም ዹፈጠሹና ይህም በቫይሚሱ ተይዘው ወደ ሆስፒታል ዚሚገቡ ሰዎቜን ቁጥር እና ሞትን ለመቀነስ ያገዘ ነው። በአገሪቱ ሕገ መንግሥት ዹተቀመጠው ዚዜጎቜን ጀንነት ዚማስጠበቅ ግዎታ በመንግሥት ጫንቃ ላይ ዹወደቀ መሆኑንና እርሱን ለማስፈጞም ሕጉን መሠሚት ተደርጎ ዹተሰጠ ውሳኔ መሆኑን ዚኢኳዶር ጀና ሚኒስ቎ሩ ገልጿል። አውስትራሊያ እና ጀርመን ተመሳሳይ ውሳኔ ዚመስጠት ዕቅድ ያላ቞ው አገራት ና቞ው። ኢኳዶር ሕዝብ በሚበዛባ቞ው ቊታዎቜ ላይ ጥቅም ላይ ዹሚውል ዚክትባት ዚምስክር ወሚቀት ለዜጎቿ አዘጋጅታለቜ። ወደ ሲኒማና ቎አትር ቀቶቜ ወይም ዚገበያ ማዕኚላት ለመግባት ይህንን ወሚቀት ማሳዚት ግዎታ ይሆናልም ተብሏል። ኢኳዶር ዚኮቪድ-19 ወሚርሺኝ ኹተኹሰተ ጀምሮ 33 ሺህ 600 ኚኮሮናቫይሚስ ጋር ዚተያያዘ ሞት መዝግባለቜ።
https://www.bbc.com/amharic/news-59778546
amh
health
ጣልያናዊቷ ለ10 ወራት 'ኮማ' ውስጥ ኚቆዚቜ በኋላ ነቃቜ
ጣልያን ውስጥ አንዲት ሎት እራሷን ስታ በሕይወት እና በሞት መካኚል ውስጥ ለአስር ወራት ኚቆዚቜ በኋላ መንቃቷ ተዘገበ። ዹ37 ዓመቷ ክሪስቲና ሮሲ ባሳለፍነው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ ዚሰባት ወር ነፍሰ ጡር እያለቜ ነበር ዚልብ ድካም አጋጥሟት እራሷን ዚሳተቜው። ሎት ልጇ ካተሪና በወቅቱ በድንገተኛ ሕክምና እንድትወለድ ዹተደሹገ ሲሆን ክሪስቲና ግን ላለፉት ዘጠኝ ወራት ኮማ ውስጥ ቆይታለቜ። ለህመሟ ምክንያቱ አንጎሏ ውስጥ ዹደሹሰ ጉዳት ሊሆን ይቜላል ተብሎ ነበር። በአሁኑ ሰአት ኚኮማ ነቅታ ዚመጀመሪያ ቃሏን ተናግራለቜ። በመጀመሪያ 'እማዬ' ዹሚለውን ቃል እንዳወጣቜ ባለቀቷ ገልጿል። "ምንም አልጠበቅንም ነበር። ኹዚህ ሁሉ ወራት ስቃይ በኋላ ያልተጠበቀ ሀሎት ነው ያጋጠመን" ብሏል ጋብሪኀል ሱቺ 'ላ ናዚዮን' ለተባለው ጋዜጣ። ክሪስቲና ሮሲ ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ ዹማገገም ሂደቷን ለማፍጠን በሚል ኊስትሪያ ውስጥ ወደሚገኝ ልዩ ክሊኒክ እንድትዘዋወር ተደርጋ ነበር። ኹዘጠኝ ወራት በኋላ ኚኮማ ስትነቃም ባለቀቷ እና እናቷ አጠገቧ ነበሩ። እንደነቃቜም 'እማዬ' ብላ እናቷን ጠርታለቜ። ክሪስቲና ኹአገር ወጥታ ህክምና እንድታገኝ ዚሚያስቜለው ገንዘብ ዹተገኘው ደግሞ በበይነ መሚብ በተደሹገ ዚእርዳታ ጥሪ ነው። በዚህም ኹ208 ሺ ዶላር በላይ መሰብሰብ ዚተቻለ ሲሆን ኹዚህ በኋላ ለሚያስፈልጓት ህክምናዎቜም እንደሚሚዳት ይጠበቃል። "ክሪስቲና በጣም አዲስ አይነት ሰው ሆናለቜ" ብሏለ ባለቀቷ አሬዞ ኖቲዜ ለተባለው ድሚ ገጜ ሲናገር። "በጣም ዚተሚጋጋቜ ሆናለቜ። ለመተንፈስ ዚሚሚዳትን መሳሪያ አውልቀውላታል። ኹዚህ በኋላ ሌሎቜ አካላዊ እንቅስቃሎዎቜን ለማድሚግ ዚሚሚዷት ህክምናዎቜ ይደሚጉላታል" ብሏል። ክሪስቲና ኮማ ውስጥ ስትገባ ዚሰባት ወር ጜንስ ዚነበሚቜው ካተሪናም ብትሆን ስትወለድ ባጋጠማት ዚኊክስጅን እጥሚት ምክንያት ለወራት ሆስፒታል ውስጥ ህክምና ሲደሚግላት ነበር።
https://www.bbc.com/amharic/news-57431084
amh
health
ኮቪድ -19፡ ሰሜን ኮሪያ ዚኮቪድ ወሚርሜኝ በመኚሰቱ ጥብቅ ዚእንቅስቃሎ ገደብ እንዲጣል አዘዘቜ
ሰሜን ኮሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ በኮቪድ ዚተያዙ ሰዎቜ መገኘታ቞ውን ተኚትሎ ጥብቅ ብሔራዊ ዚእንቅስቃሎ ገደብ እንዲጣል አዘዘቜ። ዚመንግሥት መገናኛ ብዙኃን በዋና ኹተማዋ ፕዮንግያንግ ዚኊሚክሮን ወሚርሜኝ መኚሰቱን ዹዘገበ ሲሆን ምን ያህል ሰዎቜ በቫይሚሱ እንደተያዙ ግን አልገለጞም። ኮሪያ ሎንትራል ኒውስ ኀጀንሲ ( ኬሲኀንኀ) ዚወሚርሜኙን መኚሰት ዚአገሪቷን ዚለይቶ ማቆያ ሕግ ዚጣሰ "ትልቅ አደጋ " ነው ያለ ሲሆን፣ ዚአገሪቷ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ለብሔራዊው አደጋ ምላሜ ለመስጠት አስ቞ኳይ ስብሰባ እያደሚጉ ነው ብሏል። ይሁን እንጂ ታዛቢዎቜ ቫይሚሱ አሁን ዹተኹሰተ ሳይሆን ለሹጅም ጊዜ በአገሪቷ እንደነበር ያምናሉ። ሰሜን ኮሪያ በቻይና ዚተሰራውን ሲኖቫክስስ እንዲሁም አስትራዜኒካ ክትባትን ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆኗ ዚኮቪድ 19 ክትባት ለሕዝቊቿ አልሰጠቜም። አገሪቷ ቫይሚሱ ኚጀመሚበት ጊዜ አንስቶ ሥርጭቱን ለመኹላኹል ያለመቜው ድንበሮቿን በመዝጋት ነው። ይህም ወደ አገሪቷ ዚሚገቡ መሠሚታዊ ፍጆታዎቜ እንዲቀንሱ በማድሚጉ አገሪቷን ለኹፋ ምጣኔ ሐብታዊ ቀውስ እና ዚምግብ እጥሚት አጋልጧታል። እንዲህም ሆኖ ወሚርሜኙ ሊኚሰት እንደሚቜል ምልክቶቜ ነበሩ። ወሚርሜኙ ኹጀመሹ አንስቶ ያልተሚጋገጡና በርካታ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ተመዝገብዋል። ጎሚቀት አገሯ ቻይና እና ደቡብ ኮሪያም ወሚርሜኙ ተኚስቶባ቞ዋል። ቻይና አሁን ላይ ዚኊሚክሮንን ወጀብ ለመቆጣጠር እዚታገለቜ ነው። ባለፈው ሰኔ ወር ዚመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ፕሬዚደንት ኪም ኚኮቪድ-19 ጋር በተያያዘ ስለተኚሰተው አሳሳቢው ክስተት ባለሥልጣናትን መተ቞ታ቞ውን ዚዘገቡ ሲሆን ስለጉዳዩ ግን ዝርዝር መሹጃ አልሰጡም። መስኚሚም ወር መንግሥት ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ እንዲሁም ዚበሜታ መኚላኚያ ልብስ በመልበስ ወታደራዊ ሰልፍ አድርጓል። ይህንን ተኚትሎ አንዳንድ ተንታኖቜ ልዩ ኃይሉ ዹተፈጠሹው ዚኮቪድ 19 ሥርጭትን ለመኹላኹል አንዲሳተፉ እንደሆነ ምልክት መሆኑን ተናግሚዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-61418838
amh
health
ዚኮቪድ-19 ማጠናኚሪያ ክትባት ሆስፒታል ዚመግባት መጠንን እንደሚቀንስ ጥናት አመለኹተ
ዚኮቪድ-19 ማጠናኚሪያ ሊስተኛ ክትባት ሰዎቜ በቫይሚሱ ተይዘው ወደ ሆስፒታል እንዳይገቡ ለመኹላኹል 88 በመቶ በማገዝ ውጀታማ ነው ሲል ዚዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) ዚጀና ጥበቃ ኀጀንሲ አዲስ ጥናት አመለኚተ። አስትራዜኒካ፣ ፋይዘር ወይም ሞደርና ክትባቶቜን ሁለት ዙር ዚወሰዱ ሰዎቜ በኊሚክሮን እንዳይያዙ እምብዛም ባይጠብቃ቞ውም በጠና ኚመታመም እንደሚኚላኚል ጥናቱ ያሳያል። ዚጀና ኃላፊዎቜም ይህ ጥናት ሊስተኛ ዙር ወይም ዚማጠናኚሪያ ክትባት አስፈላጊነትን ያጎላዋል ሲሉ ተናግሚዋል። ዚዩኬ ዚጀና ፀሐፊው ሳጂድ ጃቪድ "ይህ ክትባቶቜ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆኑ ዚሚያሚጋግጥ እና ዹበለጠ ተስፋ ሰጪ መሹጃ ነው። ሕይወትን ያድናል እንዲሁም ኚባድ በሜታን ይኹላኹላል" ሲሉ ተናግሚዋል። "ይህ ሳይንሳዊ ትንታኔ ክትባቱን ያልወሰዳቜሁ እንደሆነ በኮቪድ-19 ምክንያት ወደ ሆስፒታል ዚመሄድ ዕድላቜሁ እስኚ ስምንት እጥፍ ኹፍ ያለ መሆኑን ያሳያል" ሲሉም አስጠንቅቀዋል። ዚዩኬ ዚጀና ደኅንነት ኀጀንሲ በሠራው በዚህ ጥናቱ ላይ ኹ600,000 በላይ ዚተሚጋገጡ እና ዚተጠሚጠሩ በኊሚክሮን ዚተያዙ ሰዎቜን መሹጃ በመተንተን ነው ድምዳሜ ላይ ዚደሚሰው። እንደ ኀጀንሲው ግኝት ኹሆን አንድ ዙር ዚክትባት መጠን ዚሆስፒታል ሕክምና ዚሚያስፈልገው ሕመምን በ52 በመቶ ቀንሶታል። ሁለተኛውን ዙር ክትባት መውሰድ ደግሞ ይህንን ዹመኹላኹል መጠን ወደ 72 በመቶ ኹፍ ዚሚያደርገው ሲሆን ኹ25 ሳምንት በኋላ ይህ ዹመኹላኹል አቅም መልሶ ወደ 52 በመቶ ዝቅ እንደሚል ታውቋል። ነገር ግን ሊስተኛው ዙር ክትባት ኹተወሰደ ኚሁለት ሳምንታት በኋላ ይህ በሆስፒታል ዚመተኛትን ዹመኹላኹል አቅም ወደ 88 በመቶ ኹፍ ብሏል። ዚኀጀንሲው ጥናት ይህ ጥበቃ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ ለማወቅ እስካሁን በቂ መሹጃ አለመገኘቱን ነገር ግን ሕመምን በመቀነስ ሚገድ ሹዘም ላለ ጊዜ እንደሚሠራ ይፋ አድርጓል። ቀደም ሲል ዚኮቪድ-19 ሕመም ምልክቶቜ በታዚባ቞ው ሰዎቜ ላይ ደግሞ ኚእያንዳንዱ ዙር ክትባት በኋላ ያለው ዹመኹላኹል መጠን ካልተኚተቡ ሰዎቜ ጋር ሲነጻጞር 68 በመቶ ያህል ያነሰ መሆኑም ታውቋል። ኚካምብሪጅ ዩኒቚርሲቲ ጋር በጋራ ዹተደሹገው ሁለተኛ ጥናት አንድ ሰው በኊሚክሮን ኚተያዘ በኋላ ሆስፒታል ዚመግባት ስጋት ኚዎልታ ዝርያ ጋር ሲነጻጞር በግማሜ ያህል ያነሰ እንደሆነ አሚጋግጧል።
https://www.bbc.com/amharic/news-59845459
amh
health
በዋግ ኜምራ ዞን ሰዎቜ በሚሃብ እዚሞቱ መሆኑን ነዋሪዎቜና ኃላፊዎቜ ገለፁ
በአማራ ክልል በሚገኘው ዹዋግ ኜምራ ብሔሚሰብ አስተዳደር በርካታ ሰዎቜ በሚሃብ ምክንያት እዚሞቱ መሆኑን ኚአካባቢው ወደ ባሕር ዳር እና እብናት ዚመጡ ነዋሪዎቜ እንዲሁም ዚአካባቢው ኃላፊዎቜ ለቢቢሲ ተናገሩ። ዹዋግ ኜምራ ብሔሚሰብ አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተስፋዬ ገብሬ ዚአካባቢው ማኅበሚሰብ ላለፉት አራት ወራት ምንም ዓይነት እርዳታ አግኝቶ እንደማያውቅ ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል። ዚብሔሚሰብ አስተዳደሩ ዋና ኹተማ ሰቆጣን ጚምሮ ሌሎቜ ዹዞኑ ኚተሞቜ በህወሓት አማፂያን ቁጥጥር ሥር በመሆናቾው በብዛት ኑሮውን በእርዳታ ዹሚደጎመው ዚአካባቢው ማኅበሚሰብ ካለፈው ዓመት ሐምሌ መጀመሪያ አንስቶ ምንም ዓይነት እርዳታ እንዳላገኘ ጹምሹው ተናግሚዋል። ዚዛሬ ዓመት በትግራይ ዹተቀሰቀሰው ጊርነት ወደ አማራ ክልል ዋግ ኜምራ ብሔሚሰብ አስተዳደር ኚተስፋፋ ጀምሮ አብዛኞቹ ወሚዳዎቜ ለሰብዓዊ እርዳታ ዝግ ሆነው መቆዚታ቞ውን ምክትል አስተዳዳሪው ለቢቢሲ ገልፀዋል። ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ነዋሪዎቜ አካባቢውን ኹላሊበላም ሆነ ኚሰቆጣ ዚሚያገናኘው መንገድ ኹሐምሌ 09/2013 ዓ.ም ጀምሮ በመዘጋቱ ሰብዓዊ እርዳታም ሆነ ዚመድኃኒት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በመቋሚጡ ቜግሩን አባብሶታል ይላሉ። በዚህም ምክንያት በርካታ ዚአካባቢው ሕዝብ ለኹፋ ቜግር መዳሚጉን፣ ብዙ ሰዎቜም በሚሃብ እዚሞቱ መሆናቾውን ዚአካባቢው ነዋሪዎቜ እና ኃላፊዎቜ ይናገራሉ። ዚአማራ ክልል አደጋ መኚላኚል፣ ዚምግብ ዋስትና እና ልዩ ድጋፍ ዚሚሹ ኮሚሜን፣ በክልሉ ኚአምስት ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ዚአስ቞ኳይ ዚምግብ እርዳታ እንደሚፈልግ አስታውቋል። እንደ ኮሚሜኑ መግለጫ ኹሆነ ዚህወሓት አማፂያን በተቆጣጠሯ቞ው አካባቢዎቜ ኹ110 በላይ እናቶቜ፣ ሕጻናት እና ተመላላሜ ታካሚዎቜ በምግብ፣ በውሃ እና በመድኃኒት እጊት ምክንያት ሕይወታ቞ው አልፏል። ኮሚሜኑ በአካባቢው ዚመንግሥት መዋቅር በመፍሚሱ ምክንያት በምግብ እና በህክምና እጊት ዚሞቱ ሰዎቜ አጠቃላይ ቁጥርን ማወቅ አለመቻሉን ገልፆ፣ ኹዚህም ሊጹምር ይቜላል ብሏል። ዚህወሓት አማፂያን በተቆጣጠሯ቞ው ዞኖቜ እንዲሁም ኚእነዚህ አካባቢ ተፈናቅለው በተለያዩ መጠለያዎቜ ዹሚገኙ ሰዎቜ ለምግብ፣ ለመጠጥ ውሃ እና ዚመድኃኒት እጊት ተጋልጠዋል ሲል ኮሚሜኑ ጚምሮ ገልጿል። አክሎም በሰሜን እና ደቡብ ወሎ፣ ኹፊል ደቡብ ጎንደር እንዲሁም ዋግ ኜምራ ውስጥ ዚሚኖሩ እና ተፈናቅለው ዚሚገኙትን ጚምሮ በሚሊዮን ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ አስ቞ኳይ ዚምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋ቞ው ተናግሯል። '. . .ቜላ ተብለናል' ዹዋግ ኜምራ ብሔሚሰብ አስተዳደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ዚሆኑት አቶ ተስፋዬ ገብሬ አካባቢውን ዚህወሓት አማፂያን መቆጣጠራ቞ውን ተኚትሎ በርካታ ሰዎቜ መፈናቀላቾውን ይናገራሉ። "ዚኢኮኖሚ እንቅስቃሎ ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል፣ በተለያዩ አጋጣሚዎቜ ለዓለም አቀፍ ድርጅቶቜ ዚቜግሩን አሳሳቢነት ብናሳውቅም ማንም ሊደርስልን አልቻለም። . . .ቜላ ተብለናል" ብለዋል። ኚቀት ንብሚታ቞ው ዹተፈናቀሉ 50 ሺህ ዹሚጠጉ ዚብሔሚሰብ አስተዳደር ዞኑ ነዋሪዎቜ በአንጻራዊነት ሰብዓዊ እርዳታ እያገኙ ቢሆንም እነሱም በቜግር ውስጥ መሆናቾውን አቶ ተስፋዬ ተናግሚዋል። በብሔሚሰብ አስተዳደሩ በአጠቃላይ ወደ 635 ሺህ ሕዝብ ለኹፍተኛ ዚሚሃብ አደጋ ተጋልጧል ያሉት አቶ ተስፋዬ፣ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በሚብ ሞተዋል ስለሚባሉት ሰዎቜ መሹጃው ቢኖራ቞ውም ቁጥሩ ግን ኹሚገለጾው በላይ ሊጹምር ይቜላል ብለዋል። በብሔሚሰብ አስተዳደሩ ኹ90 በመቶ በላይ ዹሚሆነው ሕዝብ ዚሎፍቲኔት ተጠቃሚ ዹነበሹ ቢሆንም ዚህወሓት አማፂያን ወደ አካባቢው መግባታ቞ውን ተኚትሎ ምንም አይነት እርዳታ ደርሶ እንደማያውቅ ምክትል አስተዳዳሪው ተናግሚዋል። በብሔሚሰብ አስተዳደሩ ጋዝጊብላ ወሚዳ ነዋሪ ዚሆኑት አቶ ወንድሙ ወዳጅ ሰሞኑን ወደ ባሕር ዳር ኚመጡት ተፈናቃዮቜ መካኚል አንዱ ና቞ው። እርሳ቞ው እንደሚሉት በአካባቢው ኹፍተኛ ዹሆነ ሚሃብ በመኚሰቱ በአሁኑ ወቅት ኹአቅመ ደካሞቜ ውጪ አብዛኛው ዚወሚዳው ነዋሪ ሰብዓዊ እርዳታ ፍለጋ አካባቢውን ለቅቆ እዚተሰደደ ነው። "ቀተሰብ ቢያንስ ልጆቌ ቢተርፉልኝና እርዳታ ቢያገኙ እያለ ልጆቹን ወደ እብናት እና ባሕር ዳር ይልካል። ነገር ግን እዚህም እርዳታ ዹለም" ብለዋል። በሚሃብ ምክንያት ሰዎቜ እዚሞቱ መሆናቾውን ዚሚናገሩት አቶ ወንድሙ፣ በወሚዳው 21 ቀበሌዎቜ ዹሚገኙ ሲሆን በእነዚህ ቀበሌዎቜ በዹቀኑ ቢያንስ አንድ ወይም ሁለት ሰው በሚሃብ ምክንያት እንደሚሞት ይናገራሉ። "እስኚተወሰነ ጊዜ ድሚስ ሰው ያለውን እዚተበዳደሚ ይመገብ ነበር፣ ኹጊዜ በኋላ ግን አንዳንድ አቅመ ደካሞቜ ዹበለጠ በመ቞ገራ቞ው ወጣቶቜ ቀት ለቀት እዚለመኑ፣ በጣም ዚተራቡትን እዚመሚጥን እንደጉማ቞ው ነበር። ነገር ግን አሁን ትተና቞ው በመምጣታቜን ይሙቱ ይኑሩ አናውቅም" ብለዋል። በዚሁ ወሚዳ [ጋዝጊብላ] ዚመንግሥት ኮሙኒኬሜን ኃላፊ ዚሆኑት አቶ ሰለሞን መዓዛ፣ በወሚዳው ሰዎቜ በሚሃብ እዚሞቱ መሆናቾውን አሚጋግጠዋል። በወሚዳው በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎቜ በመገኘት መሹጃ ለማጠናቀር አስ቞ጋሪ መሆኑን ዚሚገልጹት አቶ ሰለሞን፣ ቢያንስ እርሳ቞ው ዚሚያውቋ቞ው ሊስት ሰዎቜ በርሃብ ምክንያት ሕይወታ቞ው አልፎ በቀብር ሥነ ሥርዓታ቞ው ላይ ተገኝተዋል። በወሚዳው ኹ23 ሺህ በላይ ዜጎቜ ዚሎፍቲኔት ተጠቃሚ ሲሆኑ አብዛኞቹ ዚመጚሚሻ ሰብዓዊ እርዳታ ያገኙት ኚግንቊት ወር በፊት መሆኑን ዚሚያስታውሱት አቶ ሰለሞን፣ በሐምሌ ወር መጀመሪያ ቢያንስ ኹ6 ሺህ በላይ ዚሚሆኑት ዹኹፋ ቜግር ውስጥ ስለነበሩ እጅግ አስ቞ኳይ እርዳታ ያስፈልጋ቞ው ነበር ብለዋል። ነገር ግን ወዲያውኑ ጊርነቱ በመኚሰቱ ምንም አይነት እርዳታ ሳያገኙ መንገዶቹ ተዘጋግተዋል ብለዋል። ዚህወሓት ኃይሎቜ ወደ አካባቢው መግባታ቞ውን ተኚትሎ ዚመብራት፣ ውሃ እና ባንክ ዚመሳሰሉት መሠሚታዊ አገልግሎቶቜ በመቋሚጣ቞ው እና ዚንግድ ልውውጥ ባለመኖሩ ቜግሩን ዹኹፋ እንዳደሚገውም ይናገራሉ። በዚህም ምክንያት ዚመሠሚታዊ ፍጆታ እቃዎቜ አቅርቊት እጥሚት ኚመኚሰቱም በላይ ዹዋጋ ንሚቱ ኹፍተኛ ሆኗል ዚሚሉት አቶ ሰለሞን፣ ለአብነትም ዚአንድ ኪሎ ጹው ዋጋ እስኚ 100 ብር መድሚሱን ይናገራሉ። ዚብሔሚሰብ አስተዳደሩ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተስፋዬ በሚሃብ ኹሚሞተው ሕዝብ በተጚማሪ ". . . በንጹሃን ዜጎቜ ላይ ኚመንግሥት ጋር ግንኙነት አላቾው በሚል እና መሹጃ አምጡ በማለት በርካታ ሰዎቜ በህወሓት ተገድለዋል" ሲሉ ይኚስሳሉ። ቢቢሲ በአካባቢው ዚህወሓት ኃይሎቜ ፈፀሙት ስለተባለው ግድያ ኹገለልተኛ ወገን ማሚጋገጥ አልቻለም። ዚተባበሩት መንግሥታት ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም በትግራይ፣ አፋር እና አማራ ክልሎቜ በአጠቃላይ እስኚ 7 ሚሊዮን ሕዝብ ለሚሃብ ቀውስ ሊጋለጡ ይቜላሉ ማለቱ ይታወሳል። ድርጅቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ዹተቀሰቀሰው ግጭት በአማራ እና አፋር ክልሎቜ ወደ 1.7 ሚሊዮን ሰዎቜን ለሚሃብ አደጋ ሲያጋልጥ ወደ 300 ሺህ ዹሚጠጋ ሕዝብን ደግሞ ኚመኖሪያ ቀዬው አፈናቅሏል ይላል።
https://www.bbc.com/amharic/news-59161562
amh
health
ኮሮናቫይሚስ፡ በአሜሪካ በአንድ ቀን ብቻ 94 ሺህ ሰዎቜ በቫይሚሱ ተያዙ
በአሜሪካ ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 94 ሺህ ሰዎቜ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ተሚጋግጧል። ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ለማካሄድ ቀናት በቀሯት አሜሪካ በተለያዩ ግዛቶቜም በኮሮናቫይሚስ ዚሚያዙ ሰዎቜ ቁጥር አሻቅቧል ተብሏል። በዚህ ሳምንት ሃሙስ 91 ሺህ ሰዎቜ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ኹፍተኛ ቁጥር ነው በማለት ሪፖርት አድርጋ ዹነበሹቾው አሜሪካ በተኚታታይ ባሉት ቀናትም እንዲሁ ኹዚህ በላይ ያለው ቁጥር በዹቀኑ ተመዝግቧል። ወሚርሜኙ ኹተኹሰተ ጀምሮም እስካሁን በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር 9 ሚሊዮን መድሚሱን ኚጆንስ ሆፕኪንስ ዹተገኘው መሹጃ ጠቁሟል። ፕሬዚዳንታዊ ስልጣኑን ለመጚበጥ ዶናልድ ትራምፕና ጆ ባይደን እዚተፋለሙ ባሉባት አሜሪካ ጥቅምት 24፣ 2013 ዓ.ም አሾናፊው ዚሚታወቅ ይሆናል። አሁን ባለውም ሁኔታ 21 ዚአሜሪካ ግዛቶቜ በወሚርሜኙ ክፉኛ ዚተመቱ ሲሆን አንዳንድ ግዛቶቜም በዚህ ምርጫ ላይ ቁልፍ ሚና ዚሚጫወቱ ናቾው ተብሏል። በምርጫው ወሳኝ ኚሆነቜው ግዛት አንዷ ዊስኮንሰን ዹሚገኙ ሆስፒታሎቜ አርብ እለት ዹነበሹውን ዚዶናልድ ትራምፕ ዚምሚጡኝ ቅስቀሳ ወሹርሾኙን ያባብሰዋል ሲሉ አስጠንቅቀዋል። "በአሁኑ ወቅት በተቻለ መጠን ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ው ሰዎቜ ባይሰበሰቡ ይመሚጣል። በተለይም በዊስኮንሰን ግዛት ግሪን ቀይ አካባቢ በአገሪቱ ካሉ ቊታዎቜ በኹፍተኛ ፍጥነት ወሚርሜኙ እዚተዛመተ መሆኑን እያዚን ነው" በማለት ዚግዛቲቱ ሆስፒታሎቜ በጥምሚት መግለጫ አውጥተዋል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ አርብ ኹነበሹው ዚምርጫ ቅስቀሳ቞ው በፊትም "ኹፍኛ ምርመራ ኹፍተኛ ቁጥርን እያስመዘገበ ነው። ምርጥ ዹሆነ ምርመራ አለን። ሞት እዚቀነሰ ነው" በማለት በትዊተር ገፃቾው አስፍሚዋል። በቅርቡ ዹነበሹው ዚትራምፕ ዚምሚጡኝ ቅስቀሳ ዘመቻ ላይ ተሳታፊው ሙቀት ሲለካ ነበር እንዲሁም ጭምብልም እዚታደለ ነበር። በወሚርሜኙ ምክንያት ትልልቅ ዝግጅቶቜም ኚአዳራሜ ውጭ እዚተደሚጉ ነው። ሆኖም በነዚህ ስፍራዎቜ አካላዊ ርቀት ሲጠበቅ አይታይም እንዲሁም አንዳንድ ደጋፊዎቜ ጭምብል አናጠልቅም ዹሚል እምቢተኝነት አሳይተዋል። ጆ ባይደንም ዚምሚጡኝ ቅስቀሳ ዘመቻ቞ውን እያካሄዱ ሲሆን ዲሞክራቶቹ አካላዊ ርቀትን እያስጠበቁ ነው ተብሏል። ለምሳሌም ያህል ደጋፊዎቜ በዚመኪኖቻ቞ው ሆነው እንዲኚታተሉ አድርገዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54752422
amh