Datasets:
mteb
/

Modalities:
Text
Formats:
parquet
ArXiv:
Libraries:
Datasets
Dask
License:
Dataset Viewer
Auto-converted to Parquet
category
large_stringclasses
7 values
headline
large_stringlengths
10
171
text
large_stringlengths
1
26.4k
url
large_stringlengths
13
180
lang
large_stringclasses
16 values
business
የናይጄሪያ ፖሊስ በሩዝ ፋብሪካ ተቆልፎባቸው እንዲሰሩ የተገደዱ 300 ሰራተኞችን ነፃ ማውጣቱን ገለፀ
የናይጄሪያ ፖሊስ በሩዝ ፋብሪካ ውስጥ ተቆልፎባቸው የነበሩ 300 ሰራተኞችን ነፃ ማውጣቱን ገልጿል። ሰራተኞቹ ከመጋቢት አጋማሽ ጀምሮ ከፋብሪካው እንዳይወጡ እግድ ተጥሎባቸውና ተቆልፎባቸው ይሰሩ ነበር ተብሏል። በሰሜናዊ ናይጄሪያ ግዛት በምትገኘው ካኖ በሚገኝ ፋብሪካ ውስጥ የሚሰሩት ሰራተኞች የኮሮናቫይረስ አስገዳጅ የቤት መቀመጥ አዋጅን ተከትሎ ወደቤታቸው እንዳይሄዱና በየወሩም ከሚያገኙት 2 ሺህ 600 ብር ደመወዝ በተጨማሪ 500 ብር እንደሚጨመርላቸው የፋብሪካው አስተዳዳሪዎች ቃል ገብተውላቸው ነበር። ወደቤታችን እንሄዳለን የሚሉት ደግሞ ከስራ እንደሚባረሩ ማስፈራራሪያም ደርሷቸዋል። በፋብሪካው ለመስራት የተስማሙ ሰራተኞች ከፋብሪካው ወጥተው መሄድ እንደማይችሉም ተነግራቸዋል። ይህንንም ተከትሎ አምስት አስተዳደር ላይ ያሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል። የህንዶች የሆነው ፖፑላር ፋርምስ የተሰኘው ፋብሪካ ከቢቢሲ በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጥ ቢጠየቅም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል። የፖሊስ ቃለ አቀባይ አብዱላሂ ሃሩና ለቢቢሲ እንደተናገሩት ፋብሪካው እንደተዘጋና ባለቤቶቹም ሰራተኞቹን ያለፍቃዳቸው በመቆለፋቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል። አንዳንድ ሰራተኞች ለቢቢሲ እንደተናገሩት የነበሩበት ሁኔታ ከእስር ያልተናነሰ እንደሆነና ትንሽ ምግብም ብቻ ይሰጣቸው እንደነበር ገልፀዋል። "በጣም ለአጭር ጊዜ ብቻ እንድናርፍ ነበር የሚፈቀደልን። ፀሎት ማድረግ እንዲሁም ቤተሰብ እንዲጠይቀን አይፈቀድልንም ነበር" በማለት የ28 አመቱ ሃምዛ ኢብራሂም ለቢቢሲ ተናግሯል። ፖሊስ ጉዳዩን የተረዳው አንደኛው ሰራተኛ ለሰብዓዊ መብት ድርጅት እንዲያድኗቸው በመማፀን ከላከው ደብዳቤ ነበር። "ያየሁት ሁኔታ በጣም ልብ የሚሰብር ነው። ሰራተኞቹ ለእንስሳ እንኳን በማይመጥን ሁኔታ ነው እንዲቆዩ የተደረጉት" በማለት የግሎባል ሂውማን ራይትስ ኔትወርክ ሰራተኛ ካሪቡ ያሃያ ካባራ ለቢቢሲ ገልፀዋል። አክለውም "የሚሰጣቸው ምግብ በጣም አነስተኛ ነበር። ታመው ለነበሩትም ሕክምና ተከልክለዋል፤ የመድኃኒት አቅርቦት አልነበራቸውም" ያሉት ካሪቡ ለሰራተኞቹ ፍትህንም እንደሚሹ ጠይቀዋል። የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት እንዲቻል ናይጄሪያ ሁሉም ፋብሪካዎችም ሆነ የንግድ ቦታዎች እንዲዘጉ ያዘዘችው መጋቢት አጋማሽ ላይ ነበር። በናይጄሪያ እስካሁን 20 ሺህ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን መዲናዋ ሌጎስም የስርጭቱ ማዕከል ሆናለች። ከሌጎስ በመቀጠልም የናይጄሪያ ሁለተኛ ትልቋ ከተማ ካኖም በቫይረሱ በተያዙ ሰዎች ቁጥር ትከተላለች። ወረርሽኙን ለመግታት የተላለፉ መመሪያዎች በሌሎች ቦታዎች ቢላሉም በካኖ ግን የቤት መቀመጥ አዋጁ እንዳለ ነው። ዜጎች ሰኞ፣ ረቡዕና አርብ መንግሥት በወሰነው ሰዓት ብቻ ምግብና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለመሸመት ይወጣሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-53127360
amh
business
ኢትዮጵያ፡ በደረሰው የጎርፍ አደጋ 130 ሺህ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል
በኢትዮጵያ እስከ ነሐሴ ወር አጋማሽ ድረስ የጣለው ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የተነሳ 170 ሺህ ያህል ነዋሪዎች ጉዳት ሲደርስባቸው 130 ሺህ ሰዎች ደግሞ ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክትል ኮሚሽነር ለቢቢሲ ገለፁ። ኮሚሽነሩ አቶ ዳመነ ዳሮታ ከዚህ በፊት የነበረውን ልምድ ከግንዛቤ በማስገባት በዚህ ዓመት ክረምት ወቅት በጎርፍ ምክንያት ወደ 2 ሚሊየን ያህል ሰዎች ሊጎዱ እንዲሁም 434 ሺህ ያህሉ ደግሞ ሊፈናቀሉ ይችላሉ ተብሎ ግምት መያዙን ተናግረዋል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ ከሆነ እስካሁን ድረስ በአዋሽ ወንዝ ሙላት የተነሳ በአፋር ክልል የተጎዱ ሰዎች ቁጥር ወደ 67 ሺህ 885 አካባቢ ሲሆን፣ 40 ሺህ 130 አካባቢ ደግሞ መፈናቀላቸውን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ኮሚሽነር ዳመነ አክለውም ደቡብ ኦሞ ዳሰነች አካባቢ በኦሞ ወንዝ ሙላትና የግቤ 3 የኃይል ማመንጫ ግድብ ውሃ በተወሰነ መልኩ መልቀቁን ተከትሎ በደረሰ የጎርፍ አደጋ በኦሞ በሚገኙ ከ15 ሺህ በላይ ሰዎች እንዳይጎዱ ከሚኖሩበት አካባቢ የማውጣት ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል። እነዚህ ሰዎች በጊዜያዊ መጠለያ እንዲቆዩ መደረጉን ገለፀው ከ10ሺህ በላይ ለሚሆኑት የተለያዩ ድጋፎች ደርሷል ብለዋል። ለቀሪዎቹ 5ሺ ሰዎች ደግሞ ድጋፍ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን አክለዋል። ዘንድሮ በጎርፍ የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር መጨመሩን ለቢቢሲ የገለፁት ኮሚሽነሩ፣ ነገር ግን ኮሚሽኑም ሆነ መንግሥት ከሌሎች ጊዜያት በተሻለ ሁኔታ ዝግጅት ያደረጉበት ዓመት እንደነበር ለቢቢሲ አብራርተዋል። በዚህ ዓመት በልግ ወቅት በደረሰው የጎርፍ አደጋ ምክንያት 470 ሺህ ያህል ነዋሪዎች ጉዳት ሲደርስባቸው ከ300 ሺህ በላይ ደግሞ መፈናቀላቸውን ኮሚሽነሩ ጨምረው አስረድተዋል። ኮሚሽኑ ይህን የበልግ ወቅት አደጋን በመቋቋም ላይ ባለበት ወቅት የክረምቱ ዝናብ ከበልጉ ዝናብ ጋር ተያይዞ በመምጣቱ ወንዞችና ግድቦች በመሙላታቸው በርካቶች ለአደጋ መጋለጣቸውን ተናግረዋል። ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም ከነበረው ልምድ በተለየ ሶስት ጊዜ የጎርፍ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ማውጣቱን ገልፀው ሁለቱ ማስጠንቀቂያዎች የወጡት በዚህ ክረምት ወቅት መሆኑን አብራርተዋል። እስከ መስከረም መጨረሻ ተከታታይ ዝናብ ስለሚኖር ጎርፍና የመሬት መንሸራተት ሊከሰት እንደሚችል የገለፁት ኮሚሽነሩ ነሐሴ መጨረሻዎቹ ላይ የተንዳሆ ግድብ ሊሞላ ስለሚችል ቀጣይም ጥንቃቄ እንደሚያስፈልግ፣ እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስም የከሰምና፣ የቆቃ ግድቦች እየሞሉ እንደሚሄዱ በመግለጽ ሁሉም አካላት አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል። በመከላከኛውና፣ የታችኛው አዋሽ ላይ ከፍተኛ የመከላከል ስራ እየተሰራ መሆኑን ጨምረው በመግለፅ በዚህም የተነሳ በአዋሽ ወንዝ ሙላት የተነሳ በዚህ የክረምት ወቅት የደረሰው ጉዳት መቀነሱን ተናግረዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-53852369
amh
business
አየር መንገዶች ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን እንዳያበሩ ዳግም ታገዱ
ከሁለት የመከስከስ አደጋ በኋላ ዳግም እንዲበር ፍቃድ አግኝቶ የነበረው የቦይንድ 737 ማክስ አውሮፕላን ዳግም አጣብቂኝ ውስጥ ገባ። የኢትዮጵያ እና የኢንዶኔዢያው ላየን አየር መንገድ ንብረት የሆኑት የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች የመከስከስ አደጋ ካጋጠማቸው በኋላ በመላው ዓለም አውሮፕላኑ እንዳይበር እግድ ተጥሎበት እንደነበረ ይታወሳል። ከስድስት ወራት በፊት ግን የአሜሪካ የበረራ ደህንነት ተቋማት አውሮፕላኑ ዳግም እንዲበር ፈቃድ ሰጥተው ነበር። ይሁን እንጂ አውሮፕላኑ ሌላ የኤሌክትሪክ ችግር እንዳለበት በመታወቁ ዳግም ሌላ አጣበቂኝ ውስጥ መግባቱ ተነግሯል። አውሮፕላኑ ዳግም ለማብረር የወሰኑ በመላው ዓለም የሚገኙ 24 አየር መንገዶች አውሮፕላኑን እንዳያበሩ ተነግሯቸዋል። ይህም ብቻ ሳይሆን ቦይንግ ያመረታቸውን አውሮፕላኖች ከማከፋፈል ተቆጥቧል። ቦይንግ እና የአሜሪካ የፌደራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍኤኤ) ለችግሩ መፍትሄ ለመስጠት እየሰራን ነው ብለዋል። በአውሮፕላኑ ላይ የኤሌክትሪክ ችግር መገኘቱ ቀድሞውኑ አውሮፕላኑ ጥብቅ የደህንነት ፍተሻ ሳይካሄድበት ለበረራ ብቁ ነው መባሉ ሲተቹ ለነበሩ ሌላ የመከራከሪያ ነጥብ ሆኖላቸዋል። ቦይንግን አጥቦቆ በመተቸት የሚታወቁት የቀድሞ የቦይንግ አስተዳዳሪ ኤድ ፒርሰን፤ በቦይንግ ፋብሪካ ያለው ደካማ የምርት ጥራት የኤሌክትሪክ ችግር እንደምክንያት በማንሳት የበርካቶችን ህይወት ለቀጠፉት አደጋዎች ምክንያቱ ይህ ሊሆን ይችላል ይላሉ። ቦይንግ እና ኤፍኤኤ አውሮፕላኑ ላይ የተገኘው ችግር የኤሌክትሪክ ኃይል በሚያመነጨው ስርዓት ላይ ነው ብለዋል። ለዚህ መንስዔው የኤሌክትሪ ግነኙነቶች ሥራ ጥራት ደካማ መሆኑ ነው ይላሉ። ኤፍኤኤ እንደሚለው የአሌክትሪክ ችግር፤ “መሠረታዊ የሆኑ የአውሮፕላኑ ስርዓት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ይኖረዋል።” ኤፍኤኤ ይህ የአውሮፕላኑ የኤሌክትሪክ ችግር ሳይቀረፍ አውሮፕላኑ አገልግሎት መስጠት የለበትም በማለት ከሁለት ሳምንት በፊት "አውሮፕላኑ ለመበረር የደህንነት ስጋት አለበት" የሚል መመሪያ አውጥቶ እንደነበረም ተጠቅሷል። ቦይንግን 737 ማክስ አውሮፕላን የበረራ ቁጥር ኢቲ302 ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም ተሳፋሪዎች መሞታቸው ይታወሳል። ተመሳሳይ የኢንዶኔዥያ ላየን ኤር ንብረት የሆነ አውሮፕላን ከኢንዶኔዢያ ተነስቶ ባህር ውስጥ መከስከሱ ይታወሳል። በሁለቱ አደጋዎች በአጠቃላይ 346 ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-57075420
amh
business
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ500 ቢሊዮን ብር በላይ ዓመታዊ በጀት አዘጋጀች
የኢትዮጵያ ዓመታዊ በጀትን ለመጀመሪያ ጊዜ ከ500 ቢሊዮን ብር በላይ የሚያደርግ ረቂቅ በጀት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸደቀ። የመጪው ዓመት የኢትዮጵያ መንግሥት በጀት ከዘንድሮው በ85 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያዘጋጀው ረቂቅ በጀት አመልክቷል። ምክር ቤቱ የቀጣዩ ዓመት የፌደራል መንግሥቱ በጀት 561 ቢሊዮን ብር በላይ በላይ እንዲሆን የወሰነ ሲሆን በ2013 ካለው የ476 ቢሊዮን ብር በጀት በ18 በመቶ ከፍ ብሏል። ይህም የየ85 ቢሊዮን ብር ጭማሪ ታይቶበታል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2014 ዓ.ምን በጀት ከማጽደቁ በፊት በቀዳሚነት ለዚህ ዓመት ባስፈለገው ተጨማሪ በጀትና የመንግሥት ወጪን ለመሸፈን ያስፈለገው ማስተካከያ ተግባራዊ እንዲሆን በቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ላይ መክሯል። በዚህም መሠረት ለ2013 ዓ.ም ተጨማሪ በጀት ያስፈለገው በሰሜን የአገሪቱ ክፍል ከተከሰተው ጦርነት ጋር ተያይዞ ላጋጠሙ ወጪዎች፣ በድርቅ ለተጎዱ፣ ለተፈናቀሉ እና ለተመላሾች የእለት እርዳታ አቅርቦት፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል፣ ለማዳበሪያ አቅርቦት ድጎማ፣ ለጎርፍ መከላከል እንደሆነ ተገልጿል። በተጨማሪም ለማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የአቅም ግንባታ ፕሮጀክትና "የመጠባባቂያ በጀት በማለቁ በቀጣይ ወራቶች ለሚያስፈልጉ የተለያዩ ወጪዎች የመጠባበቂያ በጀት መመደብ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው" ሲል የሚኒስትሮች ምክር ቤት መግለጫ አመልክቷል። የተጠየቀው 26.4 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ከተለያዩ ምንጮች የሚገኝ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ምክር ቤቱም ይህንኑ ተቀብሎ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቶታል። ከዓመት ዓመት ጭማሪ እያሳየ የመጣው የፌደራል መንግሥቱ ዓመታዊ በጀት በቀጣዩ 2014 ዓ.ም 561.67 ቢሊዮን ብር እንዲሆን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወስኗል። ይህም አስካሁን አገሪቱ ከያዘችው ዓመታዊ በጀት ሁሉ የላቀው ነው። ለቀጣይ ዓመት የተያዘው በጀት ለመደበኛ ወጪዎች 162 ቢሊዮን ብር፣ ለካፒታል ወጪዎች 183.5 ቢሊዮን ብር፣ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ 203.95 ቢሊዮን ብር፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ 12 ቢሊዮን ብር መያዙ ተገልጿል። ቅዳሜ ዕለት ግንቦት 28/2013 ዓ.ም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ ላይ የተወሰነው ተጨማሪ በጀትና ረቂቅ በጀት ለተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ መጽደቅ ይኖርበታል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የነበራትን ዓመታዊ በጀት ስንመለከት በ2012፣ 386 ቢሊዮን 954 ሚሊዮን 965 ሺህ 289 የነበረ ሲሆን በ2011 ደግሞ 346 ቢሊዮን 915 ሚሊዮን 451 ሺ 948 ተመድቦ ነበር። በ2010 የነበረው በጀት 320.8 ቢሊዮን ብር ሲሆን፤ ከ60 በመቶ የሚበልጠው ለትምህርት፣ ለግብርናና ለመሰረተ ልማትና ለጤና ማስፋፊያ እንዲሆን ተብሎ የተበጀተ ገንዘብ ነበር። ከ300 ቢሊዮን ብር በታች የነበረው የኢትዮጵያ ዓመታዊ በጀት በ2009 ዓ.ም ላይ 274.3 ቢሊዮን በጀት መሆኑ የሚታወስ ነው።
https://www.bbc.com/amharic/news-57372163
amh
business
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ስዊፍት ምንድን ነው?
ስዊፍት የአገራት ድንበሮች ሳይገድቡት በተመቸ እና በፈጣን ሁኔታ የገንዘብ ዝውውር የሚደረግበት ዓለም አቀፍ የገንዘብ ማስተላላፊያ ሥርዓት ነው። ስዊፍት [Swift] ሶሳይቲ ፎር ኢነትረባንክ ፋይናንሻል ቴሌኮምዩኒኬሽን [Society for Worldwide Interbank Financial Telecommunication] የሚለው ስያሜ አህጽሮተ ቃል ነው። በሥርዓቱ የተካተቱ በዓለም ዙሪያ ያሉ ባንኮች ያለምንም ተጨማሪ ውጣ ውረድ ገንዘብ ይላላኩበታል። ስዊፍት እንደ አውሮፓውያኑ በ1973 የተጀመረ ሲሆን መሰረቱ ቤልጂየም ነው። የስዊፍት ሥርዓት ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ200 በላይ አገራት ውስጥ የሚገኙ 11 ሺህ ባንኮችን እና የፋይናንስ ተቋማትን አስተሳስሯል። ስዊፍት ከመደበኛው የባንክ ሥርዓት ጋር የሚመሳሰል አይደለም። ይህ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ዝውውር ክፍያዎች ሲደርሱና ሲፈጸሙ ለተጠቃሚዎች የሚያሳውቅ አጭር የጽሁፍ መልዕክት ሥርዓት ነው። በስዊፍት ትሪሊየን ዶላሮች በኩባንያዎች እና በመንግሥታት ስለሚዘዋወር በቀን ከ40 ሚሊዮን በላይ መልዕክቶችን ይልካል። ከእነዚህ መልዕክቶች ውስጥ ሩሲያ ከአንድ በመቶ በላይ ክፍያዎችን ታስተናግዳለች ተብሎ ይታሰባል። ይህ ግን በገንዘብ ሲሰላ ቀላል የሚባል አይደለም። ሩሲያ ከስዊፍት እንድትታገድ ጥሪ የሚቀርበው ለምንድን ነው? በሺዎች የሚቆጠሩ ባንኮች ከሚጠቀሙበት ከዚህ የገንዘብ ማዘዋወሪያ ሥርዓት ሩሲያን ማገድ የአገሪቱን የባንክ ኔትዎርክ እና የገንዘብ አቅርቦትን ይጎዳል። ነገር ግን ተጎጂዋ ሩሲያ ብቻ አይደለችም። ይህ ማዕቀብ የራሳቸውን ኢኮኖሚ እና ኩባንያ መልሶ እንዳይጎዳ በርካታ መንግሥታት ይሰጋሉ። ለአብነት ከሩሲያ ነዳጅ የሚቀርብላቸው አገራት በዕገዳው ምክንያት ነዳጅ ሊስተጓጎልባቸው ይችላል። ዩናይትድ ኪንግደም ሩሲያ ከስዊፍት እንድትታገድ በአገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር ቤን ዋላስ በኩል ጥሪ ብታቀርብም ብቻዋን ልታሳካው እንደማትችል ገልጻለች። "እንዳለመታደል ሆኖ የስዊፍት ሥርዓት በእኛ ቁጥጥር ውስጥ አይደለም። በአንድ ወገን ውሳኔ የሚሳካ አይደለም" ብለዋል። ጀርመን ሩሲያ ከስዊፍት እንዳትታገድ የማትፈልግ አገር እንደሆነች ይታማናል። በተመሳሳይ የፈረንሳይ የገንዘብ ሚኒስትር ብሩኖ ለሜሬ እና የኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩት ውሳኔው የመጨረሻ አማራጭ ብቻ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባው ጠቁመዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ሩሲያን አሁን ላይ ከስዊፍ ማገድ አማራጭ ሆኖ እንዳልቀረበ ገልጸዋል። ምንም እንኳን "የተቀረው የአውሮፓ ክፍል አሁን ለመውሰድ የሚፈልገው እርምጃ ይህ ባይሆንም" አማራጭ ሆኖ እንደሚቆይ ግን ተናግረዋል። የስዊፍትን ባለቤትና ተቆጣጣሪ ማነው? ስዊፍት የተጀመረው አንድ ተቋም ሥርዓቱን ዘርግቶ የባንኮች የገንዘብ ዝውውር ሥርዓትን በብቸኝነት ጠቅልሎ እንዳይዝ ባቀዱ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ባንኮች አማካይነት ነው። ሥርዓቱን ከ2,000 የሚልቁ ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በጋራ ባለቤትነት ይዘውታል። ይህ የስዊፍት ዓለም አቀፍ የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት በቤልጂየም ብሔራዊ ባንክ ቁጥጥር የሚደረግበት ሲሆን የአሜሪካ ፌዴራል ግምጃ ቤትን እና የእንግሊዝ ባንክን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ያሉ ዋና ዋና ማዕከላዊ ባንኮችም በቁጥጥሩ ይሳተፋሉ። ስዊፍት በአባል አገራት መካከል ደኅንነቱ የተጠበቀ ዓለም አቀፍ ንግድ እንዲኖር የሚረዳ ሲሆን ግጭቶች ሲኖሩ ለማንም እንዳይወግን ይጠበቃል። ሆኖም ከዚህ መርኅ በተቃራኒ ኢራን በኒውክሌር መርሃ ግብሯ ላይ በተጣለባት ማዕቀብ ምክንያት እንደ አውሮፓውያኑ በ2012 ከስዊፍት ታገደች። በዚህም ምክንያት ወደ ውጭ ከምትልከው የነዳጅ ሽያጭ ገቢዋ ግማሹን ያጣች ሲሆን 30 በመቶ የውጭ ንግዷንም አጥታለች። ስዊፍት ግን ማዕቀቡ እንዲጣል ምንም አይነት ተጽእኖ እንዳላደረገ እና ውሳኔው በመንግሥታቱ ላይ የተመሰረተ ነው ብሏል። ሩሲያን ከስዊፍት ማገድ ምን ተጽዕኖ ይኖረዋል? ሩሲያ ከስዊፍት ሥስርዓት ከታገደች የአገሪቱ ኩባንያዎች በስዊፍት በኩል የሚያገኙት መደበኛ፣ የተመቸ እና ፈጣን የገንዘብ ልውውጥን ያጣሉ። በተጨማሪም ለኃይል አቅርቦት እና ለእርሻ ምርቶች ክፍያዎች የሚፈጸምበት መንገድ ክፉኛ ይስተጓጎላል። እንደ አውሮፓውያኑ በ2014 ሩሲያ ክሪሚያን መውረሯን ተከትሎ ከስዊፍት ልትታገድ እንደምትችል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷት ነበር። ሩሲያ እርምጃውን ጦርነት ከማወጅ አሳንሳ እንደማትመለከተው አሳውቃ ነበር። በወቅቱም ምዕራባውያኑ በውሳኔው ባይገፉበትም ሩሲያ ግን የራሷን ተመሳሳት ሥርዓት እንድትፈጥር አጋጣሚ የፈጠረላት ነበር። እንዲህ ያለውን ማዕቀብ ለመቋቋም የሩሲያ መንግሥት ለካርድ ክፍያዎች የሚሆን 'ሚር' የተሰኘ ብሔራዊ የክፍያ ካርድ ሥርዓት ዘርግቷል። ነገር ግን ጥቅም ላይ የዋለው በጥቂት አገራት ውስጥ ብቻ ነው። ምዕራቡ በስዊፍት ላይ ለምን ተከፋፈለ? ሩሲያን በስዊፍት እንዳትጠቀም ማገድ ከአገሪቱ ጋር የንግድ ልውውጥ ያላቸውን ወይም ምርት የሚያቀርቡ እና የሚገዙ ኩባንያዎችን ይጎዳል። በተለይም ጀርመን የመጀመሪያዋ ተጎጂ ትሆናለች። ሩሲያ የአውሮፓ ሕብረት የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ዋነኛ አቅራቢ ስትሆን፣ ለሕበረቱ አማራጭ አቅርቦቶችን ማግኘት ቀላል አይሆንም። የነዳጅ ዋጋ እየጨመረ የመጣ ሲሆን በዚህ ሳቢያ መሰል ችግር እንዲፈጠር መንግሥታቱ አይፈልጉም። እንዲሁም በሩሲያ ዕዳ ያለባቸው ኩባንያዎች ክፍያ የሚያገኙበት አማራጭ መንገዶችን መፈለግ ግድ ይላቸዋል። የሩሲያ ከስዊፍት መውጣት የዓለም አቀፍ የባንክ ሥርዓት ላይ የሚፈጥረው ቀውስ ቀላል እንዳሆነ ይታመናል። የሩሲያ የቀድሞ የፋይናንስ ሚኒስትር አሌክሲ ኩድሪን የአገሪቱ ስዊፍት መታገድ ምጣኔ ሀብቷን በ5 በመቶ እንዲያሽቆለቁል ሊያደርገው ይችላል ብለዋል። ይሁን እንጂ ውሳኔው በሩሲያ ኢኮኖሚ ላይ ዘላቂ ተጽእኖ ስለማምጣቱ አጠራጣሪ ነው። ምክንያቱም የሩሲያ ባንኮች የራሷ የክፍያ ሥርዓት ያላት ቻይናን ጨምሮ በሌሎች ማዕቀብ ባልጣሉ አገሮች በኩል የመጠቀም እድል ስላላቸው ነው። ሩሲያ ስዊፍት እንድትታገድ የአሜሪካ የሕግ አውጪዎች ግፊት እያደረጉ ነው። ሆኖም ፕሬዝዳንት ባይደን ምርጫቸው ይህ ሳይሆን ሌሎች ማዕቀቦች ናቸው። ምክንያቱም ውሳኔው ሌሎች አገራትን እና ምጣኔ ሀብታቸውን ስለሚጎዳ ነው። እናም ሩሲያ ከዚህ ሥርዓት እንድትታገድ የአውሮፓ አገራትን ድጋፋ ይፈልጋል። አገራቱ ደግሞ ውሳኔው ራሳቸውን መልሶ የሚጎዳ በመሆኑ ብዙም ሊደፍሩት የሚፈልጉ አይመስሉም።
https://www.bbc.com/amharic/news-60630455
amh
business
የሳምሰንግ ትርፍ ከ50 በመቶ በላይ አሽቆለቆለ
የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች አምራቹ ሳምሰንግ በሁለተኛው ሩብ ዓመት የምርቱ ትርፋማነት እንዳሽቆለቆለበትና ይህም ወደፊት ተግዳሮቶች ሊያጋጥሙት እንደሚችል ማስጠንቀቂያ እንደሆነ አስታወቀ። • የአዲሱ ሳምሰንግ ጋላክሲ S9 በካሜራ ብቃት ላይ አተኩሯል •ሳምሰንግ እንደ መጽሐፍ የሚገለጥ ስልክ አመረተ የዓለማችን ትልቁ ዘመናዊ ስልኮችንና የኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን አምራቹ ኩባንያ- ሳምሰንግ እንዳለው ትርፋማነቱ ከዚህ ዓመት ቀድሞ ባለው የበጀት ዓመት በ56 በመቶ ቀንሷል። ለዚህም በአሜሪካና በቻይና መካከል እየተካሄደ ያለው የንግድ ጦርነት ምክንያት ነው ተብሏል። ይህም ብቻ ሳይሆን አምራች ድርጅቱ በሶልና ቶክዮ ባለው የንግድ ወረፋ ምክንያት ችግር እያጋጠመው እንደሆነ ገልጿል። በደቡብ ኮሪያ የሚገኘው ድርጅቱ እስከ ሰኔ ወር ባሉት ሦስት ወራት የሥራ ማስኬጃን በመቀነስ ከሚገኝ ትርፍ 6.6 የኮሪያ ዋን (5.6 ቢሊየን ዶላር)፤ ባለፈው ዓመት ከነበረው ተመሳሳይ ወቅት ትርፉ 14.87 የኮሪያ ዋን (12.6 ቢሊየን ዶላር) ጋር ሲነፃፀር፤ 56 በመቶ መቀነሱን አስታውቋል። ሳምሰንግ ባወጣው መግለጫ እንዳለው በፍላጎት ደረጃ ትንሽ መሻሻሎች ቢታይም በምርቶቹ ላይ የገበያ ማጣትና የዋጋ ቅናሽ ግን ታይቷል። "ኩባንያው እያጋጠመው ያለው ተግዳሮት በንግዱ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ የማክሮ ኢኮኖሚክ ሁኔታ መለዋወጥም ተፈታትኖታል" ብሏል በመግለጫው። ጃፓን በቅርቡ ወደ ውጭ የሚላኩ የኢንዱስትሪ ቁሳቁሶች፤ 'ሴሚ ኮንዳክተርስ' እና 'ስክሪኖች' ለመስራት የሚውሉ ምርቶች ላይ ቁጥጥር ማድረግ ጀምራለች። ይህ እንቅስቃሴም ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጅ እቃዎች አቅርቦት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ያሳድራል በሚል አሳሳቢ ጉዳይ ሆኗል። በመሆኑም የሳምሰንግን የወደፊት የምርት አቅርቦት ሊፈታተነው እንደሚችል ተጠቁሟል። ኩባንያው በቅርቡ እንዳስተዋወቀው ተጣጣፊ ስልኩ፤ አዳዲስ ምርቶች ማስተዋወቅ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ እና በሦስተኛው ሩብ ዓመት ላይ ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። • ታጣፊው የሳምሰንግ ስልክ የ'ስክሪን' መሰበር ወቀሳ ቀረበበት ሳምሰንግ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ አዲሱን ተጣጣፊ ስልኩ የስክሪን መሰበር ወቀሳ ካጋጠመው በኋላ ለገበያ ለማቅረብ እንደዘገየም አስታውሰዋል። በአዲሱ ስልኩ ላይ ያጋጠመው ችግር በድርጅቱ ላይ አመኔታን ያሳጣ ሲሆን ይህም የዘመናዊ ስልኮች ሽያጭ ለመቀነሱና ከቻይናው ሁዋዌ ጋር ካለው የንግድ ውድድር ላይ መጥፎ አሻራ እንዳሳረፈ ተገልጿል። ሳምሰንግ ተጣጣፊው ጋላክሲ ስልኩ ተሻሽሎ በመጭው መስከረም ወር ለገበያ እንደሚቀርብ ያስታወቀው ባለፈው ሳምንት ነበር።
https://www.bbc.com/amharic/news-49174785
amh
business
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስካሁን አንድ ቢሊየን ዶላር ያህል ገቢ አጥቷል
ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ በኮሮናቫይረስ ምክንያት በአየር ትራንስፖርት ዘርፉ ላይ በተፈጠረው መስተጓጎል ሳቢያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንዳጣ ተገለጸ። የኮሮናቫይረስ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ በአየር መንገዶች ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ቀውስ ማምጣቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም ይናገራሉ። ከ90 በመቶ በላይ የመንገደኛ በረራዎች መቆማቸውን ለቢቢሲ የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፣ ያንን ተከትሎ ደግሞ ከየካቲት እስከ ሰኔ መጨረሻ ድርጅቱ መንገደኛ በማጓጓዝ ሊያገኘው ይገባ የነበረው ወደ አንድ ቢሊየን ዶላር ገቢ ሳያገኝ መቅረቱን ገልፀዋል። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከተከሰተ በኋላ የዓለም አንድ ሦስተኛ የሚሆነው ሕዝብ ከቤቱ እንዳይወጣ ከተደረገ ወራት አልፈዋል። ይህ ማለት በአየር የሚደረግ ጉዞ ሙሉ በሙሉ ቆሟል። ይህም በአየር መንገዶች ዓይን በሚታይበት ወቅት በአሁን ሰዓት ብዙ አየር መንገዶች አውሮፕላኖቻቸውን አቁመዋል ይላሉ ይላሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚው። "የመንገደኛ በረራ ቆሟል። በኢትዮጵያ አየር መንገድም ከ90 በመቶ በላይ የመንገደኞች አውሮፕላኖቻችን ቆመዋል።" "ይኼ ለአንድ አየር መንገድ እጅግ በጣም ትልቅ የፋይናንስ ቀውስ ነው የሚያመጣው። ይህም ምንም የሚካድ አይደለም እጅግ ተጎድተናል" በማለትም የዚያን ያህል ደግሞ አየር መንገዱ ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ የሚያኮራ ሥራ ሰርቷል ሲሉ ድርጅቱ የሰራቸውን ሥራዎች ዘርዝረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢበርም ባይበርም በወር አምስት ቢሊየን ብር ያወጣል ያሉት አቶ ተወልደ ከመጋቢት ወር ጀምሮ የመንገደኞች ጉዞ በሚቆምበት ጊዜ የድርጅቱን ቋሚ ወጪዎች ለመሸፈን፣ አውሮፕላን ለመግዛት የተበደርውን ብድር ከነወለዱ መመለስ ይተበቅበታል። በተጨማሪም አውሮፕላኖችን የተከራየንበት ወርሃዊ የኪራይ ወጪ ለመክፈል፣ እንዲሁም የሠራተኛ ደሞዝ፣ ጥቅማጥቅም፣ አበል፣ ለመሸፈን የሚያስችለውን "በየወሩ አምስት ቢሊየን ብር በየወሩ እንዴት ነው የምናገኘው? ይህ ወረርሽኝ ከቀጠለስ ምን እናደርጋለን?" በማለት መወያየታቸውን ይጠቅሳሉ። በዚህ ወቅት "መጀመሪያ እድገት የነበረውን ስትራጂያችንን ወደ ሕልውና ማረጋገጥ ለወጥን" በማለትም ከመንገደኛ ማጓጓዝ ባሻገር ያለውን እድል በመፈተሽ የጭነት አገልግሎት መስጠትን በወቅቱ ያገኙት ጥሩ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅሰዋል። አየር መንገዱ በዚህ ረገድ አስር 777 በጭነት ትራንስፖርት ምርጥ የሚባሉ አውሮፕላኖች፣ በተጨማሪም ሁለት 737 አውሮፕላኖች ስላሉት፤ እንዲሁም አንድ ሚሊዮን ቶን ማስተናገድ የሚችልና ከነሲንጋፖር ከነሆንክ ኮንግ ከነአምስተርዳም ጋር ሊወዳደር የሚችል በጣም ዘመናዊ የካርጎ ተርሚናል ስላለው ይህንን እንደ ዕድል መጠቀማቸውን ለቢቢሲ ገልፀዋል። በዚያ ወቅት የኮቪድ-19 መከላከያ ቁሳቁሶች በጣም የሚፈለጉበት ጊዜ ነበር ያሉት አቶ ተወልደ ያለውን የገበያ ፍላጎት በመመልከት ወደ አውሮፓ፣ አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አፍሪካ በርካታ ጭነቶችን ማጓጓዛቸውን ያስረዳሉ። የድርጅቱ ገበያ እየጨመረ ሲመጣም ቁሳቁሶቹን በጭነት አውሮፕላኖች ብቻ ማንሳት ስላልተቻለ በፍጥነት የ25 የመንገደኞች አውሮፕላኖችን ወንበራቸውን በማውጣት ወደ ወደ ካርጎ ማዞራቸውን ይጠቅሳሉ። ይህንን በማድረጋቸው የተገኙ ጥቅሞችን ሲገልጹም ሠራተኛ ከሥራ አለማሰናበታቸውን፣ የሠራተኛ ደሞዝ አለመቀነሱን እና ነጥቅማጥቅሙ መከፈሉን፣ ሶስተኛ ምንም አይነት የገንዘብ ድጋፍ ከማንም አለመጠየቃቸውን ያነሳሉ። አክለውም ለጊዜው ሥራ ማስኬጃ የሚሆን ብድር አልወሰድንም፤ ብድራችንም እንዲራዘምልን አልጠየቅንም በማለት በኮቪድ-19 ወቅት በወሰዷቸው እርምጃዎች ያገኟቸውን ስኬቶች ይዘረዝራሉ። አየር መንገዱ ይህንን ሲያደርግ በዚህ በወረርሽኝ ጊዜ ህይወት የማትረፍ ሥራ መስራቱን ያነሳሉ። "የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኢትዮጵያ ተነስቶ ስፔንን ረድቷል። የኮቪድ-19 መከላከያ እቃዎችን በማቅረብ። ያ ማለት ሕይወት አትርፈናል ማለት ነው።" ፖርቹጋል፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ፣ ብራዚል እና አፍሪካ ሊደርስ ይችል የነበረውን ቀውስ መከላከል የሚያስችሉ የመከላከያ እቃዎችን ሕክምና መሳሪያዎችን በወቅቱ በማድረሳቸው ምክንያት አገሮችና ሕዝቦች ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትልቅ ክብርና ውለታ እንዳላቸውም ጠቅሰዋል። "የጃክማ ፋውንዴሽን እርዳታን ከቻይና አምጥተን በስድስት ቀን ውስጥ አፍሪካ ውስጥ አከፋፍለናል" ያሉት አቶ ተወልደ "ፍጥነታችን በጣም ተደንቋል።" ሲሉ የአፍሪካ አገሮችም የአሊባባ ፋውንዴሽንም በሥራው መደነቃቸውን ይጠቅሳሉ። ይህንን ተከትሎም የዓለም የምግብ ድርጅት አዲስ አበባን የተባበሩት መንግሥታት በሙሉ የሰብዓዊ እርዳታ ማከፋፈያ አድርጓታል ሲሉ ለቢቢሲ ገልፀዋል። ራሳችንን ጠቅመን፣ አየር መንገዱን አድነን፣ ሠራተኞቻችንን ሳንበትን፣ የሠራተኞቻችንን ደሞዝ ሳንቀንስ እና ሕይወት ማትረፍ በመቻላችን እንደ አንድ ዜጋ ትልቅ ኩራት እንደሚሰማቸው ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች በሥራ ባህሪያቸው ምክንያት ለቫይረሱ ተጋላጭ መሆናቸውን ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አስፈላጊውን የግንዛቤ መስጫ ትምህርቶችን በማድረግና ጥንቃቁዎችን በመውሰድ ወደ 17 ሺህ የሚጠጉ የድርጅቱ ሠራተኞች በጤና እንደሚገኙ ገልፀዋል። ድርጅቱ ከዚህ ቀደም አምስት ሠራተኞቹ ቫይረሱ እንደተገኘባቸው በማስታወስ ሁሉም ማገገማቸውንና አሁን ደግሞ ባለፈው ሳምንት ሁለት ሠራተኞች ኮቪድ-19 ተገኝቶባቸው በድርጅቱ ለይቶ ማቆያና ማከሚያ ውስጥ እንደሚገኙ አብራርተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሮናቫይረስን ስርጭት ለመከላከል የሚረዱ ሥራዎችን በአግባቡ ተግባራዊ እንደሚያደርግ የገለፁት አቶ ተወልደ "በረራ ባለማቋረጣችን ለዚህ ልምድ አግኝተናል" ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/53075791
amh
business
ዚምባብዌ የዋጋ ንረትን ለመግታት የወርቅ ሳንቲሞችን አስተዋወቀች
የዚምባብዌ ማዕከላዊ ባንክ ከአገሪቱ ኢኮኖሚ ማሽቆልቆል ጋር ተደምሮ እየናረ የመጣውን የዋጋ ንረት ለመግታት የወርቅ ሳንቲሞችን በመገበያያነት ለመጠቀም ይፋ አድርጓል። የአገሪቱ ዓመታዊው የዋጋ ግሽበት ከ190 በመቶ በላይ ማደጉን ተከትሎ የማዕከላዊ ባንቡ በያዝነው ወር የወለድ ተመኑን ከእጥፍ በላይ በማሳደግ 200 በመቶ አድርሷል። እያንዳንዱ ሳንቲም በዓለም አቀፍ ገበያ አንድ አውንስ ወርቅ የሚኖረውን ዋጋ ብሎም 5 በመቶ ሳንቲሙን ለማምረት የወጣውን ተጨምሮ ያወጣል። ባሳለፍነው አርብ አንድ አውንስ ወርቅ 1,724 ዶላር ያወጣ ነበር። የዚምባብዌ ሪዘርቭ ባንክ ገዥ ጆን ማንጉዲያ እንዳሉት ሳንቲሞቹ የሚጠበቀውን ለውጥ ካመጡ በቀጣይ በሱቆች ውስጥ መጠቀም ሊጀመር ይችላል። ሳንቲሙ "ሞሲ-ኦአ-ቱኒያ" የሚል ጽሑፍ ያረፈበት ሲሆን ትርጉሙም "የነጎድጓድ ጭስ" ማለት ነው። ይህም በዚምባብዌ እና ዛምቢያ ድንበር ላይ የምትገኘውን ቪክቶሪያ ፏፏቴ የሚያመነጨውን ጭስ ያመለክታል። ለዓመታት ሲያሽቆለቁል የቆየው የዚምባብዌ ዶላር በዚህ ዓመት ከዋና ዋና ምንዛሬዎች አንጻር ዋጋው የበለጠ ወድቋል። አገሪቱ ለአራት አሥርት ዓመታት ያህል በሥልጣን ላይ በነበሩት ሟቹ ሮበርት ሙጋቤ የሥልጣን ዘመን መፈጠር የጀመረውን የኢኮኖሚ ቀውስ አሁንም ድረስ እያስተናገደች ትገኛለች። በዚሁ የዋጋ ግሽበት ምክንያት እአአ በ2009 የዚምባብዌ ዶላርን ለመገበያያነት ላለመጠቀም ተገዳለች። በምትኩ የውጭ ምንዛሬዎችን በተለይም የአሜሪካን ዶላር በሰፊው ጥቅም ላይ ይውላል። የአገር ውስጥ ምንዛሪ ከአሥር ዓመታት በኋላ እንደገና ወደ ሥራ ገብቷል። ነገር ግን በፍጥነት ዋጋውን እንደገና አጥቷል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cx0qqnwwevxo
amh
business
ቢትኮይንን ለሁሉም አገልግሎትና ግብይት የምትጠቀመው አገር
የቢትኮይን ዋጋ ከሌላው ጊዜ በተለየ በእዚህ ሳምንት በጣም ቀንሷል። የኤል ሳቫዶር መንግሥት ግን ቢትኮይንን ሕጋዊ መገበያያ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ቀጥሏል። ይህንን ለማበረታታትም በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው። ይህ ውሳኔ ከተወሰነ ከ9 ወር ወዲህ መንግሥት 200 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለቢትኮይን ፈሰስ አድርጓል። አሁን ደግሞ የውሻ ባለቤቶች በቢትኮይን የሚከፍሉ ከሆነ በጣም በርካሽ እንዲታከሙ አንድ ሆስፒታል አመቻችቷል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cgr9yx339elo
amh
business
የአርሶ አደሮችን ሕይወት ለማቅለል ዘመናዊ ጎተራ የሠራችው ወጣት
ደራርቱ ደረጀ በጅማ ዩኒቨርስቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ውስጥ የባዮ ሜዲካል ትምህርት ክፍል መምህርት ናት። እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪዋን ባዮ ሜዲካል ኢሜጂንግ በሚባል የትምህርት ዘርፍ እየተማረች ሲሆን፣ ከትምህርቷ ጎን ለጎን ፈጠራዎች ላይ ተሰማርታለች። ከሥራዎቿ መካከል አንዱ የሆነው ደግሞ አርሶ አደሮችን መሠረት በማድረግ የሠራችው ዘመናዊ ጎተራ ነው። "ገበሬዎቻችን የሚጠቀሙበት ጎተራ ከጭቃ አልያም ከአፈር ስለሚሠራ የታፈነ ነው። በዚህም ምክንያት እህሉ በነቀዝ እንዲበላ ይሆናል" ትላለች ደራርቱ። ደራርቱ አርሶ አደሮች የሚጠቀሙበት ባሕላዊው ጎተራ ምርታቸውን እንዲባክን ያደርጋል በማለት፣ ይህ ችግርም የከፋ እና ገበሬዎቹን ለምግብ ዋስትና እጥረት የሚያጋልጥ ነው ትላለች። የዓለም የምግብ ድርጅት፣ እያደጉ ባሉ አገራት ውስጥ የሚገኙ አርሶ አደሮች ከየሚያመርቱት ምርት፣ 40 እጅ ያህሉ ከማጠራቀሚያ ቦታ እጥረት የተነሳ እንደሚባክን ይገልጻል። አስተማማኝ የእህል ማጠራቀሚያ አለመኖር ደግሞ አርሶ አደሮች ጉልበት እና ጊዜያቸውን የፈጁበት ምርት በተባይ እንዲበላ እና በእርጥበት ምክንያት ለብልሽት እንዲጋለጥ ያደርጋል። ይህ የእህል ብክነትም በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቤተሰቦችን ለምግብ ዋስትና ችግር እንዲጋለጡ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል ቀዳሚው ነው። ብዙ አርሶ አደሮች የሚጠቀሙበት ጎተራ ከእንጨት እና ከጭቃ የተሰራ መሆኑን የምትናገረው ደራርቱ "ብዙ አርሶ አደሮች ይቸገራሉ። እህላቸውን ነቀዝ ይበላዋል" ትላለች ደራርቱ። የምርት ማከማቻው አሰራር ነፍሳት ወደ ጎተራው በቀላሉ በመግባት እህል ውስጥ እንዲራቡ እንደሚያደርገቸውም ታስረዳለች። በተጨማሪም ይህ በባህላዊ መንገድ የሚሠራ ጎተራ፣ እንደ ልብ አየር ስለማይዘዋወርበት በውስጡ ያለው ሙቀት እንደ ነቀዝ ላሉ ነፍሳት መራቢያነት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። "የኢትዮጵያ ገበሬዎች አሁን እየተጠቀሙበት ያለው ጎተራ፣ ነፍሳት ውስጥ ገብተው በቀላሉ እህሉን እንዲያበላሹት ያስችላቸዋል። ስለዚህም ገበሬዎቹ ከሚያመርቱት 44.7 በመቶ ያህሉ በዚህ ሁኔታ ይባክናል" ስትል ታስረዳለች። ዘመናዊው ጎተራ ደራርቱ ይህንን የአርሶ አደሮች ችግር መሠረት በማድረግ አልሙኒየም በመጠቀም ዘመናዊ ጎተራ መስራቷን ትናገራለች። ይህ ከአልሙኒየም የተሰራው ጎተራ ነፍሳት ወደ ጎተራው በቀላሉ እንዳይገቡ የሚከላከል መሆኑንም ታስረዳለች። ይህ ጎተራ "አየር እንዲያስገባ ሆኖ ነው የተሰራው። ይህም ጎተራ ውስጥ ሙቀት እነዳይፈጠር ይረዳል። ነፍሳት ወደ ጎተራው ቢገቡ እንኳ ቶሎ እንዲሞቱ ያደርጋቸዋል" በማለት ታስረዳለች። አየር ወደ ጎተራው እንዲገባ የሚያደርገው መላ የባትሪ ኃይልን በመጠቀም የተሰራ ነው። "ለወደፊቱ ግን የፀሐይ ብርሃንን በመጠቀም እንዲሰራ ለማድረግ እያሰብን ነው" ስትል ለቢቢሲ ተናግራለች። ደራርቱ የሠራችው ይህ ዘመናዊ ጎተራ አነስተኛ የሚባለው እስከ 50 ኪሎ መያዝ የሚችል ሲሆን፣ በሰዎች ፍላጎት ላይ በመመስረት ትልልቅ ጎተራዎችን መስራት ይቻላል። ደራርቱ ይህንን ጎተራ ለመስራት ወጪውን ራሷ መሸፈኗን ገልጻ፣ በሥራው ላይ ግን የሚያማክራት ሰው እንዳለ ትናገራለች። በሌላ በኩል ይህ ፕሮጀክት በተፈለገበት መልኩ ሥራ ላይ እንዳይውል እንቅፋት የሆነባት የገንዘብ ችግር መሆኑን በማንሳትም፣ ይህንን ለመቅረፍ የተለያዩ ውድድሮች ላይ እየተሳተፈች ነው። በዚህም መሠረት በአሁኑ ወቅት 'ቶታል ኢነርጂስ ስታርት አፐር' የሚባል ውድድር ላይ የመጀመሪያውን ዙር ማለፏን ትገልጻለች። "አሁን ማነቆ የሆነብን የገንዘብ እጥረት ነው። ይህንን ውድድር ካለፍን በቀላሉ ገበሬዎቻችን ጋር መድረስ እንችላለን" ብላለች ደራርቱ።
https://www.bbc.com/amharic/news-60906496
amh
business
ቤይሩት ውስጥ በመሳሪያ አስገድዶ ገንዘቡን ከባንክ የወሰደው ጀግና ተባለ
መሳሪያ ታጥቆ ከቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው የሊባኖስ ዜጋ በሕዝቡ ጀግና ተብሎ ተወደሰ። ሊባኖስ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ተከትሎ ባንኮች ደንበኞቻቸው ወጪ በሚያደርጉት ገንዘብ ላይ ገደብ ጥላለች። ይህ ግለሰብ ግን መሳሪያ ታጥቆና ባንክ ውስጥ ነዳጅ አርከፍክፎ ለሆስፒታል ክፍያ ለመፈጸም የሚያስፈልገው ገንዘቡ እንዲሰጠው በኃይል መጠየቁን ኤኤፍፒ ዘግቧል። በግለሰቡ እና በባንኩ መካከል ለስድስት ሰዓታት ከቆየ ፍጥጫ በኋላ ግለሰቡ የጠየቀውን ገንዘብ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስ ማግኘት ችሏል። ይህ በስም ያልተጠቀው ግለሰብ ተግባርም በሕዝቡ ዘንድ አድናቆትን አስገኝቶለታል። ከባንኩ ውጪ ተሰብስበው የነበሩ ሰዎች “ጀግና ነህ” እያሉ ጠርተውታል። የግለሰቡ ወንድም ለጋዜጠኞች ሲናገር፤ “ወንድሜ በባንክ ሂሳቡ 210ሺህ ዶላር አለው። የሆስፒታል ወጪውን ለመሸፈን 5ሺህ 500 ዶላር ፈልጎ ነበር” ብሏል። ከባንኩ ውጪ የነበሩት የግለሰቡ ወንድም እና ባለቤት፤ “ሁሉም ሰው ሊያደርገው የሚገባው ይሄን ነው። የራሳቸው የሆነውን ማግኘት አለባቸው" ብለዋል። ኤልቢሲ የተሰኘ የቴሌቪዥን ጣቢያ የግለሰቡ ቤተሰብ አባላት በሆስፒታል እንደሚገኙ እና ገንዘብ እጅጉን ያስፈልጋቸው እንደነበር ዘግቧል። የቴሌቪዥን ጣቢያው ጨምሮ እንደዘገበው ወደ ባንኩ በኃይል ከገባው ግለሰብ ጋር ድርድር ከተደረገ በኋላ ከቁጠባ ሂሳቡ 35ሺህ ዶላር ተሰጥቶታል። ፖሊስ ግለሰቡን እና በእገታ ስር የቆዩ የባንክ ሠራተኞችን ከአካባቢው ይዞ የወጣ ሲሆን በግለሰቡ ላይ ክስ ይመሰረት እንደሆነ እስካሁን የተባለ ነገር የለም። እአአ 2019 ላይ ሊባኖስ የገጠማትን ምጣኔ ሃብታዊ ቀውስ ለመቋቋም ያስችለኛል ብላ ተግባራዊ ካደረገቻቸው ውሳኔዎች መካከል ሰዎች ከቁጠባ ሂሳባቸው ወጪ በሚያደርጉት የገንዘብ መጠን ላይ ገደብ መጣል ነው። ከዚህ በተጨማሪም ከአገር ውጪ በሚላክ የገንዘብ መጠን ላይም ገደብ ተጥሏል። ይሁን እንጂ እነዚህ ክልከላዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። በሊባኖስ የተከሰተው ምጣሄ ሃብታዊ ቀውስ የአገሪቱ ገንዘብ ዋጋውን ከ90 በመቶ በላይ እንዲያጣ አድርጎታል። የዋጋ ግሽበት ጣሪያ ነክቷል፤ እንደ መድሃኒት እና ስንዴ ባሉ ምርቶች ላይ እጥረት አጋጥሟል። የተባበሩት መንግሥታት ከአምስት ሊባኖሳዊያን አራቱ በድኅነት ውስጥ ይኖራሉ ይላል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c4n30811d2no
amh
business
ኬንያ ገንዘብ ከመቀየሯ ጋር ተያይዞ ከሰባት ቢሊዮን ሺልንግ በላይ ጥቅም አልባ ሆነ
የኬንያ ማዕከላዊ ባንክ እንዳሳወቀው ኬንያ የመገበያያ ገንዘብ ከመቀየሯ ጋር ተያይዞ ከ95% በላይ የሚሆነው የአንድ ሺ ሺልንግ ተመልሶ በአዲሱ ተተክቷል። በዚህ መካከል ግን መሃል ላይ ተንሳፎ የቀረ ገንዘብ እንዳለም ተገልጿል። "ይህ ማለት 7.3 ቢሊዮን ሺልንግ ጥቅም አልባ ሆኗል፤ እንደ ወረቀት ነው የሚቆጠረው" በማለት የባንኩ አስተዳዳሪ ፓትሪክ እንጆሮጌ ለጋዜጠኞች አስረድተዋል። •የኢትዮጵያ ሙዚቃ- ከመስከረም እስከ መስከረም •ከአንደኛ ክፍል ዲግሪ እስኪጭኑ ከልጃቸው ጋር የተማሩት አባት ባንኩ እንዳሳወቀው አዲስ የመገበያያ ገንዘብ የታወጀው ሰኔ አንድ ቀን ሲሆን ከዚያ ዕለትም ጀምሮ ሲዘዋወር የነበረ 217 ሚሊዮን ሽልንግም ተገኝቷል። ከመስከረም ሃያ ጀምሮ አሮጌው የመገበያያ ገንዘብ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። በዚህ ወቅትም ከሶስት ሺ የሚበልጡ አጠራጣሪ ልውውጦች ሪፖርት የተደረጉ ሲሆን በሚመለከተው የመንግሥት አካልም ምርምራ እንደሚደረግም ኢንጆሮጌ አክለው ገልፀዋል። የገንዘብ ቅየራው በሃገሪቷ ውስጥ የተንሰራፋውን ሙስና ለማስቀረትና ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርንም ለመቆጣጠር እንዲያስችል ነው። •ኬንያ ሳንቲሞቿ ላይ የነበሩ መሪዎችን በእንስሳት ቀየረች አፍሪካ ታክስ ጀስቲስ ኔትወርክ የተባለ ድርጅት እንዳሳወቀው በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ምክንያት ኬንያ በየአመቱ 400 ሚሊዮን ዶላር እንደምታጣ አስታውቋል። ባንኩ እንዳስታወቀውም የገንዘብ ቅይይሩ መሳካቱንና ከዚህ በኋላ ስርአት ባለው መንገድ የገንዘብ ዝውውር እንደሚከናወን ነው።
https://www.bbc.com/amharic/49916629
amh
business
"ለ15 ዓመታት ኮንዶሚኒየም እየጠበቅኩ ሁለት ልጆች ወልጃለሁ" የአዲስ አበባ ነዋሪ
"ለ15 ዓመታት ኮንዶሚኒየም እየጠበቅኩ ሁለት ልጆች ወልጃለሁ" ይህ የተሰማው ስሜ አይጠቀስ ካሉ አንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ ነው። ቤት የመኖር ተስፋቸውን ሰንቀው የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ይደርሰኛል ብለው የተመዘገቡት በ1997 ዓ.ም ነበር። የጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲሰጣቸው በማህበር ተደራጅተው ከተመዘገቡት የመጀመሪያው ዙር ተመዝጋቢም መካከል ናቸው። ለአስራ አምስት ዓመታትም ያህል ቤት ይደርሰኛል ብለው ጠብቀዋል። በእርሳቸው ማህበር ውስጥ ከሚገኙት ከሃያ አባላቱ በላይ በሙሉ የቤት ባለቤት ቢሆኑም እርሳቸው ግን አልደረሳቸውም። ከእርሳቸው የሚጠበቅባቸውን በየወሩ ምንም ሳያዛንፉ ከመቆጠባቸውም አንፃር ለምን አልደረሰኝም ብለው ሲያስቡም የሚሰጡት ምክንያት "ዕጣው ፍትሃዊ ስላልሆነ ነው" የሚል ነው። "በመተዋወቅና በመጠቃቀም ቢሆን ነው እንጂ ይህንን ያህል ዓመት ጠብቄ የማይደርሰኝ ምክንያት የለውም" ይላሉ። ከዚያም በተጨማሪ ያልተመዘገቡ ሰዎች ቤት እየተሰጣቸው እንደሆነም ሲሰሙ ይህንኑ ጥርጣሬያቸውን አረጋገጠላቸው። ሆኖም ለዓመታትም ቤት ይኖረኛል በሚል ተስፋም የቆጠቡትን ብር ሊነኩም አልፈለጉም "ለሌላ ነገር እንዳላደርገው ሁሉ ይዞኛል" ይላሉ። ሲመዘገቡ ገና ወንደላጤ ነበሩ አሁን ሁሉ ተቀይሮ ትዳር ይዘዋል። የሁለት ልጆች አባት ሆነዋል፤ ሆኖም የተመዘገቡት ኮንዶሚኒየም የውሃ ሽታ በመሆኑ "ላም አለኝ በሰማይ..." ሆኖባቸዋል። ለአመታትም የኮንዶሚኒየም ዕጣ ሲወጣ በጉጉት ይጠብቃሉ። ይከታተላሉ ግን አልሆነም። የሚያውቋቸው ሰዎች ቤት አግኝተው ሳይኖሩበት ወይ ሲሸጡት ሲያዩ እርሳቸው በኪራይ ቤት መንከራተት ያሳዝናቸዋል። በተከታታይም ቤቶች ልማት ሄደው ሲጠይቁም የተመዝጋቢዎች ዝርዝር ውስጥ እንዳሉ ይነግሯቸዋል። "ሌሎች ሰዎች እየደረሳቸው ነው እንዴት ነው ነገሩ ብለን ስንጠይቅም 'ያው ስምህ አለ'" ከማለት ውጭ ሌላ ምላሽ ለዓመታት አልተሰጣቸውም። "ጠብቅ" የሚለውም ምላሽ ተስፋ እያስቆረጣቸው እንደመጣ የሚናገሩት እኚህ ግለሰብ፤ ከሰሞኑ ደግሞ ከህገወጥ መሬት ወረራና ኢ-ፍትሃዊ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እደላ ጋር ተያይዞ በሚሰሙ መረጃዎች የነበረቻቸውም ትንሽ ተስፋ ተሟጠጠች። "በጣም ያሳዝናል፤ ያሳፍራል፤ ከዚህ በኋላ ተስፋ አላደርግም" ይላሉ። ቤት (መጠለያ) መሰረታዊ ጥያቄና መብት ቢሆንም በኢትዮጵያ ባሉ ትልልቅ ከተሞች በተለይም በአዲስ አበባ ሰዎች የግል ቤት መኖር ማለት እንደ ቅንጦት የሚታይበት ነው። በርካቶች በማይቀመስ ኪራይ ብራቸውን እየገፈገፉ ለመኖርም ተገደዋል። ገዝቶ የቤት ባለቤት መሆን የሚታሰብ ባይሆንም የጋራ መኖሪያ ቤቶች የጥራትና ሌሎች ጉድለቶች ቢኖርባቸውም፤ ለብዙዎች የቤት ባለቤት የመሆን ተስፋቸው ሆኖ ቆይተዋል። ሆኖም ለዓመታት ጠብቀው ቤት ሳያገኙ የቀሩ እንዲሁም ቤቱ ደርሷቸው ያልተቀበሉ በርካቶች አሉ። ሌላኛው የአዲስ አበባ ነዋሪ በ40/60 የቁጠባ ፕሮጀክት ተመዝግበው በሁለተኛው ዙር የቤት እጣ እድለኛ እንደሆኑ ተነገሯቸው። ከስድስት ዓመታት በፊት ተመዝግበው ዕጣው ወጥቶ ቤቱ ከደረሳቸው በኋላ፤ በድልድሉ መሰረት ውል ቢዋዋሉም ቤቱን ሳይረከቡ አንድ ዓመት አለፋቸው። ሙሉውን መክፈል የሚችሉ መቶ በመቶ እንዲከፍሉ ካለበለዚያ ደግሞ በወጣው እቅድ መሰረት አርባ በመቶ ከፍለው ቀሪውን ደግሞ ከባንክ ጋር ውል ተፈፅሞ ቤታቸውን እንዲረከቡ ነበር። የዛሬ ዓመትም የሚጠበቅባቸውን አርባ በመቶ ክፍያ ከፈፀሙ በኋላ ቁልፍ ለመረከብና ከቤቶች ልማትም ቤታቸውን ሊረከቡ የደረሳቸው ነገርም የለም። በቅርቡ እንዲሁ እጣ የደረሳቸው ሰዎች በማህበር ሲደራጁ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ሲነገሩም ቤቱ አልቋልና ተረከቡ ተብለው ወደደረሳቸው አካባቢ ሄዱ። በሁለተኛው ዙር 18 ሺህ ያህል እድለኞች መኖራቸውን የሚናገሩት እኚሁ ግለሰብ "ልንረከብ ሄደን ቤቱ አላለቀም፤ ቁልፍ ልንረከብ ሄደን ጭራሽ ቤቱ በር የለውም፤ ይሄ እንዴት ይሆናል? የማይሆን ሥራ ነው እየሰሩብን ያሉት" ብለዋል። የአያት አካባቢ ነዋሪ የሆኑት እኚሁ ግለሰብ በሚኖሩበት አካባቢ የሚገኙ መሬቶች በአስደናቂ ፍጥነት መታጠራቸው ጥያቄያቸውን አጭሮታል። በሳምንቱ መጀመሪያ፣ ሰኞ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በአዲስ አበባ ከተማ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች እየተባባሰ የመጣ፣ የመንግሥታዊ መዋቅሮች ድጋፍ ያለው ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ እንዳለ ባካሄድኩት ጥናት ደርሼበታለሁ ሲል ማስታወቁ ይታወሳል። የጋራ ቤቶችን በተመለከተም የከተማው አስተዳደር ባወጣው ደንብ መሰረት "በምንም መስፈርት የቤት ተጠቃሚ ሊሆኑ የማይገባቸው ግለሰቦችና ቡድኖች ቤትና የነዋሪነት መታወቂያ ተሰጥቷቸዋል" ሲል በጋራ የመኖሪያ ቤቶች በኩል አሉ ያላቸውን የአሰራር ችግሮች ጠቅሷል። ጥናቱ እንዳለው በከተማዋ የተለያየ አይነት ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራ ተግባራት እንደተከናወኑ አመልክቶ፤ እነዚህም በጅምር ቤት ስም ከባለ ይዞታዎች ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ በመግዛት ግንባታ የማካሔድ፣ ባዶ መሬቶችን በቡድንና በግለሰብ ደረጃ በማጠር የመያዝ እንዲሁም ለሌላ ወገን የማስተላለፍ በተጨማሪም "በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በተዘረጋው ሰንሰለት በጥቅም ተጋሪነትና በዝምድና" ሠፋፊና ቁልፍ ቦታዎችን መያዝ በከተማዋ ውስጥ መታየቱን ገልጿል። የቀድሞው የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ እና የአሁኑ የማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) በበኩላቸው፤ በቀጥታ የኢዜማን ጥናት ባይጠቅሱም ማክሰኞ ዕለት በፌስቡክ ገጻቸው ላይ በሰጡት ምላሽ የቀረበውን ሪፖርት " ሐሰተኛ" ብለውታል። አቶ ታከለ እንዳሰፈሩት "የመሬት ወረራን በተመለከተ ከመጀመሪያዋ ቀን ጀምሮ እስከ መጨረሻዋ እለት ድረስ ጠንካራ የሆነ እርምጃ ስንወስድበት የቆየንበት ጉዳይ ነው" ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/53996764
amh
business
ፈረንሳዊው ቢሊየነር በፓሪስ ተደብድበው ተዘረፉ
የፈረንሳዩ ቢሊየነር በርናንድ ታፒ በፓሪስ ኩምላቪል መኖርያ ቤታቸው ውስጥ ሳሉ ነው ዘራፊዎች ገብተው የደበደቧቸው፡፡ ባለቤታቸውም ክፉኛ ተጎድተዋል፡፡ ቢሊየነሩ በርናንድ ታፒ የዝነኛው የአዲዳስ የስፖርት ትጥቅ አምራች የቀድሞ ባለቤት ናቸው፡፡ የቢሊየነሩን ቤት የደፈሩት ዘራፊዎች ቁጥርና ማንነት እስከአሁን አልታወቀም፡፡ ዘራፊዎቹ ቢሊየነሩን በርናንድ ታፒ እና ባለቤታቸው ሌሊት ላይ ከእንቅልፋቸው ቀስቅሰው በኤሌክትሪክ ገመድ ካሰሯቸው በኋላ ነበር ጠቀም ያለ ገንዘብ ለመዝረፍ የሞከሩት፡፡ ሆኖም በቢሊየነሩ ቤት እምብዛምም የፈለጉትን አላገኙም፡፡ የታፒንና ባለቤታቸውን የወርቅ ጌጣጌጦች ግን ሰብስበው ወስደዋል፡፡ የ78 ዓመቱ በርናንድ ታፒ በፈረንሳይ አወዛጋቢ ባለሀብትና ፖለቲከኛ ናቸው፡፡ ሽቅርቅርና ሁሌም የሚዲያ መነጋገርያ መሆን የሚወዱት ታፒ ከዚህ ቀደም ሚኒስትር ነበሩ፡፡ በተለይ ዝነኛውን የአዲዳስ ኩባንያን ከመሸጣቸው ጋር ተያይዞ ስማቸው በሙስና ተደጋግሞ ይነሳል፡፡ የ70 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ባለቤታቸው ወ/ሮ ዶሚኒክ እና ቢሊየነሩ በርናንድ ታፒ ሌሊት 6 ሰዓት ተኩል ግድም በተኙበት ነው ቢያንስ ከ4 በላይ የሆኑ ዘራፊዎች የቤታቸውን አጥርና የጥበቃ ሰንሰለቱን አልፈው በመግባት በቁጥጥር ያዋሏቸው፡፡ ይህ የሆነው ደግሞ ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ሌሊት ነው፡፡ ዘራፊዎቹ ቢሊየነሩን በርናንድን ጸጉራቸውን ይዘው መሬት ለመሬት እየጎተቱ ከወሰዷቸው በኋላ ውድ ጌጣጌጦችንና የሚያስቀምጡበትን ቦታ እንዲጠቁሟቸው ሞክረዋል፡፡ ሆኖም ቤት ያስቀመጡት እዚህ ግባ የሚባል ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጣ ንብረት ባለመኖሩ ዘራፊዎቹ ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ እንደከተታቸው ተነግሯል፡፡ በዚህ ብስጭትም ቢሊየነሩን በዱላ ነርተዋቸዋል፡፡ በዚህ መሀል የ70 ዓመት ባለቤታቸው ወ/ሮ ዶሞኒክ ዘራፊዎቹን አምልጠው ለጎረቤት ቤታቸው እየተዘረፈ መሆኑን በማሳወቃቸው ፖሊስ ደርሶ አድኗቸዋል፡፡ ባለቤታቸው በዘራፊዎቹ ክፉኛ በመደብደባቸው አሁን ሆስፒታል ነው የሚገኙት፡፡ ሌቦቹ እስከ አሁን ወሰዱ የተባለው 2 ውድ ሮሌክስ የእጅ ሰዓቶችን፣ የጆሮ ጌጦችን፣ የእጅ አምባሮችን እና ቀለበቶችን ብቻ ነው፡፡ ቢሊየነሩ በርናንድ ታፒ ከ1992 እስከ 93 የፈረንሳይ የከተማ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ነበሩ፡፡ የታዋቂው የስፖርት ቁሳቁስ አምራች አዲዳስ ከፍተኛ የአክስዮን ባለቤት ነበሩ፡፡ በኋላ ደግሞ የዝነኛው የኦሎምፒክ ዴ ማርሴይ የእግር ኳስ ቡድን ባለቤት ሆነዋል፡፡ ላ ፕሮቬንሴና ሌሎች በርካታ ሚዲያዎችንን በባለቤትነት አስተዳድረዋል፡፡ እሳቸውም ቢሆን በመተወን፣ በመዝፈን እና የራዲዮና የቴሌቪዥን ትዕይነት በማሰናዳት ዝነኛ ነበሩ፡፡ በ1990ዎቹ ኩባንያቸው ኪሳራ በማወጁ ከሒሳብ ማጭበርበር፣ ከግብር ስወራና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ተከሰው 5 ወራት እስር አሳልፈዋል፡፡ በርናንድ ላለፉት 20 ዓመታት በፍርድ ቤት ከአዲዳስ ኩባንያ ሽያጭ ጋር በተያያዘ እየተካሰሱ ይገኛሉ፡፡ ኩባንያውን በወቅቱ የሸጡት በግማሽ ቢሊዮን ዶላር ነበር፡፡
https://www.bbc.com/amharic/news-56636712
amh
business
የሲዳማ ቡና በኪሎ ለምን እስከ አርባ ሁለት ሺህ ብር ተሸጠ?
ያለፉት ሦስት ዓመታት ለሲዳማ ቡና ‘ቡናማ’ ዓመታት ናቸው። ወርቃማ እንዳይባሉ ቡና ከወርቅም በላይ ነኝ ያለባቸው ዓመታት ናቸው። ከዚህ ጀርባ ደግሞ ሦስት ስሞች ቀድመው ወደ አዕምሮ ይመጣሉ። ንጉሤ ገመዳ፣ ታምሩ ታደሠ እና ለገሠ በጦሳ ናቸው። ሦስቱም የሲዳማ ቡናን ይዘው ለውድድር ቀርበው አላፈሩም። ይህ የቡና ውድድር ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ ይባላል። ውድድሩ ቡናን በጥራት ይለያል። ቀጥሎ በዓለም አቀፍ ጨረታ ለገበያ ያቀርባል። ንጉሴ አንድ ኪሎ ቡናውን በ407 ዶላር ሸጠዋል። የታምሩ ቡና ደግሞ 330 ዶላር ይገባዋል ተብሎ ዋጋ ተቆርጦለታል። የለገሠ ቡና ግን ከሁለቱም የላቀ ነው። አንዱ ኪሎ ቡና 884.10 ዶላር ተሽጧል። በዚህ ዋጋ የተሸጠ የኢትዮጵያ ቡና የለም። አንድ ኪሎ ቡና 47 ሺህ 236 ብር ተሽጧል። ስኬቱን ምስጋና “በቡና፣ ሻይ እና ቅመማ ቅመም ዙሪያ ለተሠራው ሪፎርም” የሚሉት አቶ ምንዳዬ ምትኩ የሲዳማ ክልል ቡና ፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማትና ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ናቸው። ለአቶ ምንዳዬ ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ ከውድድርም በላይ ነው። ‘አርሶ አደሮችንም ክልሉንም እየጠቀመ ያለ ውድድር ነው።’ መነቃቃት እና የሥራ ዕድልም ፈጥሯል። “አርሶ አደሮቹና አቅራቢዎች በቀጥታ ተጠቃሚ የሚሆኑበት አሠራር ተዘርግቷል። በዚህም የሲዳማ ክልል በጣም ተጠቃሚ ነው። ከሦስት ዓመት ወዲህ በቡና ላይ ለውጡ ትልቅ ነው” ይላሉ። እውነትም ለውጥማ አለ። በመጀመሪያው ዓመት ያሸነፈው አርሶ አደር አሁን ሌላ ህይወት እየመራ ነው። አርሶ አደር ከሚባለው ማዕረግ በተጨማሪ ላኪነትንም ደርቧል። “ቀደም ሲል አነስተኛ ካፒታል ነበረው። (ከውድድሩ) በኋላ ግን የላኪነት ፈቃድ አውጥቶ ወደ ላኪነት አድጎ ሸላሚም ሆኗል።” ይህ የአንድ ግለሰብ ብቻ ታሪክ ነው። ተመሳሳይ ታሪክ ያላቸው ሰዎች ቁጥራቸው እየጨመረ ነው። “ይህ የክልሉ ሃብት ነው። ክልሉ ከእነዚህ ትልቅ ጥቅም ያገኛል፤ ገቢው ያድጋል። አርሶ አደሮቹ ህይወት ሲለወጥ ገበያውም ይነቃቃል። የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያለውን ትልቅ ችግር ይፈታል” የአቶ ምንዳዬ ሃሳብ ነው። ይህንን የሰሙ ‘እኛስ?’ ያሉበት ነው። በዚህ ዓመት ውድድርም በርካቶች ተሳትፈዋል። በዚህ ዓመት ደግሞ አርሶ አደሮች ብቻ እንዲያቀርቡ ተደርጓል። ባላቸው መሬት እና የመሬት ይዞታ አቅርበው እንዲወዳደሩ ነው የተደረገው። በዘንድሮው ውድድር አንደኛ እና ሁለተኛ የወጡት የሲዳማ ቡናዎች ናቸው። “አንደኛ የወጣው ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ያገኘበት እጅግ በጣም አነስተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የነበረ ሰው ነው።” ጥራታቸውም ቢሆን ምርጥ ነበር። የአቶ ምንዳዬ “ዘንድሮ ከፍተኛ ጥራት ያለው ቡና ነው ያቀረብነው። አርሶ አደሩም የጥራቱን ሁኔታ ያሻሻለበት እና ፊቱን ወደ ቡና ልማት ያዞረበት ነው” ብለዋል። ዘንድሮ ለፍጻሜ የደረሱ 40 ተወዳዳሪዎች ነበሩ። 14ቱ ደግሞ ከሲዳማ ክልል ናቸው። የሲዳማን ቡና ምን እንዲህ ተፈላጊ፣ ተመራጭ እና ውድ አደረገው? ትልቁ ነገር አየሩ ነው። “በጣም ውጤታማ እየሆኑ ያሉት ደጋማ አካባቢ ያሉ ቡናዎች ናቸው” ይላሉ አቶ ምንዳዬ። ሌላው ደግሞ ‘ኦርጋኒክ’ (ተፈጥሯዊ) ቡና መሆኑ ነው። ምንም ዓይነት ኬሚካል አይዞርበትም። “የጥላ ዛፍም አላቸው። የቡና ፓኬጅ መጠቀማቸውም ሌላው [ምክንያት] ነው። የአየሩ ሁኔታም የረዳን ይመስላኛል” ይላሉ አቶ ምንዳዬ ምክንያቱ ብዙ መሆኑን በመጥቀስ። በተለይ የደጋ አካባቢ ቡናዎች ተመራጭ ሆነዋል። አሁን ቡና ወደ ደጋማው ሲዳማ አካባቢ እየሰፋ ነው። እነ አርቤጎና፣ ቡራ፣ ደንሳ፣ አሮሬሳ አካባቢዎች ቡና ማለትስ የእናንተ ተብለዋል። “በሌሎችም አካባቢ ይስፋፋል የሚል እምነት አለን። እነ ቦና አካባቢም ይጠቀማሉ ብለን እናስባለን” ይላሉ አቶ ምንዳዬ። አስገራሚው ነገር እነዚህ ቦታዎች ከቡና ጋር አይተዋወቁም ነበር። ለምሳሌ የዘንድሮው አሸናፊ ለገሠ በጦሳ ነዋሪነቱ አርቤጎና ወረዳ ቡርሳ ቀበሌ ነው። አርቤጎና አካባቢ በጣም ደጋማ አካባቢ ነው። አልቲቲዩዱም በጣም ከፍተኛ ነው። “አሁን ግን [በእነዚህ ቦታዎች] ከፍተኛ መነቃቃት ነው ያለው።” ቀደም ሲል እንሰት፣ ስንዴ እና ገብስ ያመርቱ ነበር። ጊዜ ሲቀየር እነሱም ተቀየሩ። ጊዜው ሲቀየር የሚያመርቱትም ተቀይሯል። “የኤክስቴንሽን ድጋፍ ይደረጋል። የቡና ፓኬጅ እንዲጠቀሙ ይደረጋል። ያረጁ ቡናዎች የመተከታት ሥራ ይከናወናል። ለባለሙያዎችም የስልጠና ድጋፍ እንሰጣለን። በተራው ባለሙያው እስከ ታች ወርዶ ይደግፋል። የተሻሻሉ ቡናዎች እንዲያመርቱ የበሽታ መከላከል ስራዎችን በተመለከተ ስልጠና፣ ክትትል እና ድጋፍ ይደረጋል” የአቶ ምንዳዬ ሃሳብ ነው። ቢቢሲ፡ እርስዎ ቡና ይጠጣሉ? አቶ ምንዳዬ፡ እኔ በጣም ቡና የምወድ ሰው ነኝ ቢቢሲ፡ ሌላ ቦታም ሄደው ቡና ይጠጣሉ? አቶ ምንዳዬ፡ [ሳቅ] ሌላ ቦታም ቡና እጠጣለሁ ቢቢሲ፡ እና የሲዳማ ቡና ከሌሎች በምን ይለያል? አቶ ምንዳዬ፡ ስለለመድኩት መሰለኝ የሲዳማ ቡና ይለያል። የቅመም ጣዕም አለው። በዚህ በኩል የራሱ ባህሪ አለው። የሲዳማ ቡና መጠጣት ከለመድክ ከፍተኛ ሱስ ነው የሚያሲዝህ። በቀን ቢያንስ 3 ስኒ ቡና ሳልጠጣ አልውልም። ሌላም ቦታ ስሄድ እጠጣለሁ። ብዙ ምርጥ ምርጥ ቡናዎች አሉን። የይረጋጨፌ ቡናም በጣም እወዳለሁ። በአጠቃላይ ቡና እጠጣለሁ። የሲዳማ ቡና ጥሩ ስሙ የገነነ ነው። ዕውቅናው እንዲጎለበት ከክልል እስከ ፌደራል ድረስ እየተሠራ መሆኑ ተነግሮናል። በአንድ ወቅት የቡና ዋጋ ወረደ። አርሶ አደሮች ቁጭ ብለው እንዲያስቡ ያደረገ የዋጋ መውረድ ነበር። በምን ልተካው ሲሉ ወደ አዕምሯቸው ሽው ያለላቸው ጫት ነበር። ጫት ቡናን እግር በእግር ተካ። ግን አልዘለቀበትም። አሁን ደግሞ ቀኝ ኋላ ነው ጉዞው። ቡና ግዛቴን አላስደፍርም አለ። “ጫት እና ባህር ዛፍ እየነቀሉ ወደ ቡና እየቀየሩ ያሉ በርካታ አርሶ አደሮች አሉ” ይላሉ አቶ ምንዳዬ። ከአንድ ኪሎ ቡና በአርባ ሺህዎች ከታፈሰ ጫት ለምኔ ነው ነገሩ። “ከዋጋውጋር ተያይዞ የመጣ [ለውጥ] ነው።” “ቀደም ሲል የልፋታቸውን አያገኙም ነበር። ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ሰንሰለቱ ብዙ እና አስቸጋሪ ዘርፍ ነበር። [አርሶ አደሩ] ካመረተው የጉልበቱን ዋጋ እያገኘ ባለመሆኑ ወደ ሌሎች ሰብሎች እየገባ ነበር። አሁን ከተሻሻለ በኋላ ነው ወደ ቡና የገባው።“ “[አሁንም] ዓለም ላይ ካለው ዋጋ አንጻርም ቢሆን ሙሉ ለሙሉ ተጠቃሚ ነው ማለት አይቻልም” የአቶ ምንዳ ሃሳብ ነው። እንደካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ ያሉት ለገበያው መሻሻል ትልቅ ጥቅም እየሰጡ ነው። ለዚህ ለውጥ ደግሞ ከቡናና ሻይ ባለስልጣን ጀምሮ የተዘረጋውን አሠራር በምክንያትነት ያቀርባሉ። ሁለት እና ከዚያ በላይ ሄክታር ያላቸው አርሶ አደሮች ቡናቸውን በተገቢው አዘጋጅተው ወደ ውጭ መላክ ይችላሉ። “የምርት እና ምርታማነት ማሻሻል ላይ ይሠራል። ከግብይት ስርዓቱ ህገወጦችን የመከላከል ስራዎችም ይሠራል። ይህን የሚከላከል ግብረ ሃይልም አለ። ሌላው ደግሞ የግብዓት አቅርቦት ነው። በዚህ በኩልም ማሻሻል አለ።” “የሲዳማ ቡና አልን እንጂ የኢትዮጵያ ቡና ማለት ነው። ቀደም ሲል መዳረሻ ያልነበሩ አካባቢዎችም የኢትዮጵያን ቡና ይፈልጋሉ። እንደ ክልል ስንጠቀም እንደሃገርም እንጠቀማለን። በክልል ደረጃም ቢሆን ከፕሬዝዳንቱ ጀምሮ እስከ ታች ድረስ በዚህ ልክ ይሠራል።“ ቡና ተተክሎ ምርት ለመስጠት ሦስት ዓመት ይጠይቃል። ቡና እየሰጠ 15 እስከ 18 ዓመት ይቆያል። ከዓመታት በኋላል እርጅና ሲጫነው መታደስ ይፈልጋል። ካልሆነ ምርት ይቀንሳል። ቡና ይህን ሁሉ አልፎ ነው ለገበያ የሚቀርበው። የካፕ ኦፍ ኤክሰለን ‘አውራ ፓርቲ’ ሆነናል የሚሉት አቶ ምንዳዬ ሦስቱንም ዓመት “የፕሬዚዳንሺያል ሽልማት” ማግኘታቸውን አንስተው በቀጣይም ማንም አይነቀንቀንም ይላሉ። “ከዚህ በኋላ ወደ ኋላ መመልከት የለም። የክልሉም ፕሬዝዳንተ የሚመሩት ስለሆነ ከላይ እስከታች በትኩረት ስለሚሰራ ከዚህ በላይ መስራት እችላለን” ነው መልሳቸው እንዴት ተብለው ሲጠየቁ።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c28wxj81xveo
amh
business
"በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ፈርተው ዛሬ መደብር አልከፈቱም"
የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት የጃኮብ ዙማን እስር ተከትሎ በአገሪቱ ሰላማዊ ሰልፎችና ነውጥ መቀስቀሱን ተከትሎ በጆሀንስበርግ የሚሠሩ ኢትዮጵያውያን ዛሬ መደብራቸውን ዘግተው እንደዋሉ በከተማዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊን ለቢቢሲ ተናገሩ። በንግድ ሥራ የተሰማራው ዳዊት ተወልደመድኅን፤ በጆሀንስበርግ በተለይም ጂፒ ጎዳና እና ብሪ ጎዳና በሚባሉት አካባቢዎች በርካታ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ጥቃት እንዳይደርስባቸው ፈርተው ዛሬ ሐምሌ 5/2013 ዓ.ም. መደብራቸውን ዘግተው ለመዋል መገደዳቸውን ተናግሯል። ትላንት ሐምሌ 4/2013 ዓ.ም. በዚያው አካባቢ በተነሳው ነውጥ የኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሌሎች አገራት ስደተኞች መደብሮች ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ፖሊስ እንደተከላከለ ዳዊት ይናገራል። በደቡብ አፍሪካ የተባበሩት ኢትዮጵያ ማኅበሰረብ ማኅበር ዋና አስተባባሪ ኮሚቴ አባል የሆነው ንጉሥ ተመስገን እንደሚናገረው ኢትዮጵያውያን፣ ኤርትራውያን፣ ፓኪስታናውያን እንዲሁም ሌሎችም የሚነግዱበት አካባቢ ዛሬ ተዘግቶ ውሏል። "ኒውካስል አካባቢ ሁለት ኢትዮጵያውያን ጥቃት ደርሶባቸዋል። ከባድ ግን አይደለም። ዛሬ ሶዌቶ አካባቢ አመጽ ስላለ በንግድ የተሰማራው የሀበሻው ማኅበረሰብ ሱቁን ዘግቷል። ደርባን ትላንት ሌሊት ሲዘረፍ፣ መኪና ሲቀጠል ነበር" ይላል። ከኢትዮጵያውን ማኅበረሰብ እና ከፖሊስ በተገኘው መረጃ መሠረት ከባድ የሚባል ጉዳት እስካሁን እንዳልደረሰ ያክላል። "ትላንት የስደተኞች መደብሮች ላይ ጥቃት እየተሰነዘረ እንደሆነ ኢትዮጵያውን ሲሰሙ ተሰብስበው ወደ ጂፒ ስትሪት ሄደው ሱቆቻቸውን ተከላከሉ። ፖሊሶችም ሀበሾችን ሲረዱ ነበር። ኢትዮጵያውያኑ ተሰብስበው ባይሄዱ ኖሮ የከፋ ነገር ይፈጠር ነበር" ይላል ነጋዴው ዳዊት። በተለይም ጆሀንስበርግ ውስጥ ረብሻ ሲነሳ ጥቃት የሚሰነዘረው ስደተኞች እንዲሁም የንግድ ተቋሞቻቸው ላይ እንደሆነ በተደጋጋሚ ታይቷል። የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝደንት ጃኮብ ዙማ በሥልጣን ዘመናቸው ተፈጽመዋል የተባሉ የሙስና ጉዳዮች እየተመለከተ በሚገኘው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተጠይቀው ሳይገኙ በመቅረታቸው ፍርድ ቤትን በመድፈር ጥፋተኛ ተብለው የ15 ወራት እስር ተፈርዶባቸዋል። የጃኮብ ዙማን እስር ተከትሎ የእሳቸው ደጋፊ የሆኑ ደቡብ አፍሪካውያን የተቃውሞ ድምጻቸውን ለማሰማት አደባባይ መውጣት የጀመሩት ጃኮብ ዙማ እጃቸውን ለፖሊስ ከሰጡ በኋላ ነው። ከዚህ ተቃውሞ ጋር ተያይዞ በተነሳው ነውጥ ሕንጻዎች እና ተሽከርካሪዎች ወድመዋል። መደብሮችም ተቃጥለዋል። ግርግር፣ ዝርፊያና ንብረት ማቃጠል ጆሃንስበርግ ውስጥ በንግድ ሥራ የሚተዳደሩት ወ/ሮ መዓዛ ተስፋዬ እንደተናገሩት ረብሻው መቀስቀሱን ተከትሎ በጣም አሳሳቢ እና አስፈሪ ሁኔታ ተከስቷል። ግርግር፣ ዝርፊያና ንብረት የማቃጠል ድርጊት በየቦታው እንደነበርና መንገዶችም በተቃዋሚዎቹ በሚቃጠሉ ጎማዎች ተዘግተው እንደነበር ገልጸዋል። ተቃውሞው በጃኮብ ዙማ መታሰር የተቀሰቀሰ ይሁን እንጂ ቢቢሲ ያናጋራቸው ኢትዮጵያውያን እንደሚሉት፤ ከተቃውሞው ባሻገር በተለያዩ ስፍራዎች ዝርፊያዎችና የንብረት ውድመት ተፈጽሟል። በተለይ የንግድ ሱቆች የተቃዋሚዎቹ የጥቃት ኢላማ በመሆናቸው በንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት ሱቆቻቸውን ዘግተው ቤታቸው ተቀምጠዋል። ረብሻው እሳቸው በሚኖሩበት ጆሃንስበርግና ደርባን ከተሞች ውስጥ የበረታ መሆኑን የሚናገሩት ወ/ሮ መዓዛ፤ ፖሊስ አመጸኞቹን ለመቆጣጠርና የንብረት ውድመት ለማስቆም እየጣረ ነው ብለዋል። ለሁለት ቀናት ከዘለቀ ተቃውሞና የንብርት ውድመት በኋላ ከትናንት ዕሁድ በተሻለ ሰኞ ዕለት መረጋጋት በጆሃንስበርግ መመለሱን የተናገሩት ወ/ሮ መዓዛ "ከተማው ጸጥ ብሏል" ብለዋል። የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን በረብሻው የወደሙ ንብረቶችናና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ ተከታታይ ዘገባዎችን እያቀረቡ ሲሆን ወ/ሮ መዓዛና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ለሁለት ቀናት ከሥራ ውጪ ሆነው መቆየታቸውን ገልጸዋል። ሌሎች ኢትዮጵያውያንና የመገኛኛ ብዙኃን እንደሚሉት ረብሻው ከተከሰተ በኋላ ከጆሃንስበርግ ይልቅ በደርባን ከባድ ጉዳት መድረሱን እንደተረዱ ጠቅሰዋል። "ረብሻ ሲነሳ ጥቃት የሚደርሰው ስደተኞች ላይ ነው" ንጉሥ እንደሚለው፤ ማንኛውም አይነት ነውጥ ሲነሳ ያንን ሰበብ በማድረግ የንግዱ ማኅበረሰብ ላይ ጥቃት ይሰነዘራል። አሁን የተነሳው አይነት አለመረጋጋት ሊቀሰቀስ እንደሚችል ባለፉት ጥቂት ቀናት ሲነገር እንደነበር እና ሸቀጣቸውን ከመደብር ያወጡ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች እንዳሉ ገልጿል። "ዛሬ ጥቃት እንደሚደርስ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ስለተነገረ መላው ኢትዮጵያዊ ማኅበረሰብ ከቤቱ አልወጣም" ብሏል። ኮሮናቫይረስን ለመከላከል የወጣው የእንቅስቃሴ ገደብ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ላይ ያሳደረው ጫና ላይ አሁን የተነሳው ነውጥ ሲጨመር ማኅበረሰቡ ላይ ከፍተኛ የምጣኔ ሀብት ቀውስ እንደሚያስከትልም ንጉሥ ይናገራል። ዳዊት እንደሚለው፤ ከዚህ ቀደምም እንደታየው አንዳች ነውጥ ሲነሳ ስደተኞች ላይ ጥቃት ይሰነዘራል። ይህንን የሚያውቁት ኢትዮጵያውያን ስጋት ስለገባቸው ዛሬ መደብራቸውን አልከፈቱም። "ትላንት ኢትዮጵያውኑ ተሰብስበው ሳይሄዱ በፊት ጉዳት የደረሰባቸው ሱቆች ነበሩ። ዛሬም ምን ሊፈጠር እንደሚችል ስለማይታወቅ ኢትዮጵያውያን ሱቃቸውን ዘግተው ውለዋል" ይላል። ትላንት የናይጄርያውያን መኪና መሸጫ፣ የሸቀጣ ሸቀጥ መደብርና ሌሎችም የንግድ ተቋማት ላይ ጉዳት እንደደረሰ ይናገራል። "ትላንት ሀበሾች በቁጣ ሱቃቸውን ለመጠበቅ ወጡ። ፖሊስም አገዛቸው። ከዚህ በፊት ፖሊሶችም ጭምር ችግር ይፈጥሩብን ነበር" ይላል። ኢትዮጵያውያኑ ስጋት ውስጥ እንደሆኑና የጃኮብ ዙማ የፍርድ ቤት ጉዳይ እልባት እስኪያገኝ ወይም እስኪረግብ ድረስ ወደ ሥራ መመለስ እንደሚያስቸግር ዳዊት ለቢቢሲ ገልጿል። ሁሌም ረብሻ ሲነሳ ስደተኞች ጥቃት እንደሚደርስባቸው የሚጠቅሰው ነጋዴው፤ "ድንገት መጥተው ሊዘርፉን ወይም ሊያጠቁን ስለሚችሉ ዘግቶ መጠበቅ ይሻላል" ሲል ያስረዳል። ጆሃንስበርግ ውስጥ የሚነግዱ ኢትዮጵያውያን በማንኛውም ጊዜ ነውጥ ሊነሳ እንደሚችል እንደሚሰጉ ገልጾ "የለመድነው ችግር ስለሆነ ሁሌም በተጠንቀቅ ነው የምንጠብቀው። ረብሻ ሲነሳ ጥቃት የሚደርሰው ስደተኞች ላይ ነው" ብሎም አክሏል። ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያውያን እና ሌሎችም ስደተኞች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች ብዙ ጊዜ ተፈጽመዋል። ዳዊት "ስደተኞች ሲጠቁ ዓለም የደቡብ አፍሪካ መንግሥትን ስለሚጠይቅ ስደተኞችን ለማጥቃት ምክንያት ይፈለጋል" ሲል ሁኔታውን ያስረዳል። በደቡብ አፍሪካ መከላከያ ሠራዊቱ ስለመሰማራቱ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት፤ በጃኮብ ዙማ የትውልድ ቦታ ክዋዙሉ-ናታለ ተቀስቅሶ በመላው አገሪቱ እየተንሰራፋ የመጣውን አለመረጋገት ለማርገብ የአገሪቱን መከላከያ ሠራዊት እንዳሰማራ ተገልጿል። ዘረፋ ተፈጽሞባቸዋል በተባሉ ስፍራዎች ፖሊስ ምላሽ እየሰጠ ሲሆን እስካሁን ድረስ 60 ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉንም ይፋ አድርጓል። ትናንት በርካታ ቁጥር ያላቸው ተቃዋሚዎች ዱላ እና ፍልጥ ይዘው በጆሃንስበርግ ከተማ መሃል ታይተዋል። ቅዳሜ ዕለት ደግሞ ወደ 300 የሚጠጉ ሰዎች የጆሃንስበርግን ዋና ጎዳናን ዘግተው ነበር። ከትናንት በስቲያ በነበረው ተቃውሞ ሕንጻዎች እና መኪኖች በእሳት ወድመዋል። አሌክሳንድራ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ወደ 800 የሚጠጉ ሰዎች ተሳትፈውበታል በተባለው አመጽ አንድ የፖሊስ አባል በጥይት መመታቱ ተዘግቧል። ፕሬዝደንት ሲርል ራማፎሳ ትናንት ምሽት ግጭት እያስከተሉ ያሉ ተቃውሞዎች እንዲቆሙ የጠየቁ ሲሆን፤ "ለዚህ አመጽ እና የንብረት ውድመት ምንም ዓይነት ምክንያት ሊቀርብ አይችልም" ብለዋል። ፍርድ ቤትን በመድፈር ጥፋተኛ ተብለው የ15 ወራት እስር የተፈረደባቸው ጃኮብ ዙማ በሥልጣን ዘመናቸው ምንም ዓይነት ሙስና አለመፈጸማቸውን ይከራከራሉ። የጃኮብ ዙማ ጠበቆች ዛሬ ለአገሪቱ ፍርድ ቤት ይግባኝ በማለት የፍርድ ጊዜውን ለማሳጠር ይሞክራሉ ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-57808849
amh
business
ኮሮናቫይረስ፡ አፍሪካ በወረርሽኙ ሳቢያ ከተጎዳው ምጣኔ ሐብት ለማገገም 1.2 ትሪሊየን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ
አፍሪካ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ካጋጣት የኢኮኖሚ ውድቀት ለማገገም እንዲሁም የጤና ወጪ 1.2 ትሪሊየን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ዓለም አቀፉ ገንዘብ ተቋም [አይኤምኤፍ] አስታወቀ። ገንዘቡ ያስፈልጋታል የተባለው ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት መሆኑ ተገልጿል። የተቋሙ ዳሬክተር ክርስታሊና ጆርጂቫ እንዳሉት ዓለም አፍሪካ ከገባችበት ቀውስ እንድታገግም ለመደገፍ ዓለም ብዙ መስራት አለበት ብለዋል። በአፍሪካ በኮሮናቫይረስ የተያዙ እንዲሁም የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከሌሎች አህጉራት ያነሰ ነው፤ ነገር ግን የዓለም ባንክ በወረርሽኙ ሳቢያ ተጨማሪ 43 ሚሊዮን የሚሆኑ አፍሪካዊያን ለከፋ ድህነት የመጋለጥ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ብሏል። በወረርሽኙ ሳቢያ የሥራ እድሎች በመታጠፋቸው እና የቤተሰብ ገቢ በ12 በመቶ በመቀነሱ የደረሰው የኢኮኖሚ ተፅእኖ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአፍሪካ እየታየ የነበረውን ጠንካራ እድገት እየቀለበሰው መሆኑን የገንዘብ ተቋሙ ዳሬክተር በበይነ መረብ በነበራቸው የተቋሙ ስብሰባ ላይ ተናግረዋል። ችግሩንም ለማቃለል በርካታ አፍሪካ አገራት መንግሥታት ከልማት እቅዳቸው 2.5 በመቶ ያስወጣቸውን ፖሊሲዎች አስተዋውቀዋል። አይኤም ኤፍ የአፍሪካ አገራት ከደረሰባቸው ተፅዕኖ እንዲያገግሙ 26 ቢሊዮን ዶላር የለገሰ ቢሆንም፤ የግል አበዳሪዎች እና በሌሎች አገራት ድጋፍ ቢኖርም፤ አሁንም ግን ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ እጥረት አለ ብለዋል። "አንዳንድ አገራት ከብድር አግልግሎትና ተጨማሪ የማህበራዊና ጤና ወጪዎች መካከል እንዲመርጡ የሚያስገድዳቸውን የዕዳ ጫናዎች እየተጋፈጡ ነው" ብለዋል ኃላፊዋ። ይህንን ችግር ለመፍታትም ተበዳሪዎች ብድራቸውን የሚከፍሉበት ጊዜ እንዲራዘም ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፤ ለብድር የሚሆን ተጨማሪ ገንዘብ ማቅረብ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። በአፍሪካ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን፤ ወደ 37 ሺህ የሚጠጉት ሕይወታቸውን አልፏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54498317
amh
business
የወቅቱ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ተግዳሮቶች
የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የአገር ውስጥ ምርት እድገት (ጂዲፒ) ባለፉት 10 ዓመታት በየዓመቱ በአማካኝ 9.4 በመቶ እያደገ መሆኑን ይናገራል። ኢትዮጵያ ከጥቅምት 24/2013 ጀምሮ በትግራይ ክልል የቀሰቀሰው ጦርነት፣ በቅርቡ የተከሰተው ከፍተኛ ሆነ የምንዛሬ እጥረት እንዲሁም ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ንረት ኢኮኖሚውን እየተፈታተነው ይገኛል። ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ አንድ ዶላር በጥቁር ገበያው ከ64 እስከ 68 ብር ድረስ በመመንዘር ላይ እንደሚገኝ እና በተለያዩ ሁኔታዎች ይህ ዋጋ እስከ 72 ብር ድረስ ከፍ እንደሚል ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ግለሰብ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር። በመደበኛው የምንዛሬ ገበያ አንድ ዶላር በ45 ብር እየተመነዘረ ይገኛል። የአገሪቱ የዋጋ ግሽበትም ቢሆን ከእለት ወደ እለት እየጨመረ እንደሚሄድ ያሳያል። ዓለም አቀፍ ተቋማት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በኮቪድ-19 ምክንያት ተጽዕኖ እንደደረሰበት እና 2 በመቶ ገደማ ዕድገት እንደሚያስመዘገብ ጠቅሰው ነበር። ወርቅነሽ ሲማ የአዲስ አበባ ነዋሪ ናት። ከምታገኘው ገቢ በላይ ወጪዋ ሰማይ መንካቱን በመግለጽ የኑሮ ውድነት እንዳማረራት ትናገራለች። "የቤት ኪራይ፣ በርበሬ፣ ዘይት እና ጤፍ ዋጋቸው ሰማይ የነካ ነው" የምትለው ወርቅነሽ በአሁኑ ጊዜ ገቢያችን እና ወጪያችን የተመጣጠነ አይደለም ስትል ለቢቢሲ አስረድታለች። ወርቅነሽ መንግሥት ለኑሮ ውድነቱ መፍትሄ ያበጅለታል ብላ ተስፋ ብትጥልም "ለእኛ ግን በጣም ፈታኝ ነው" ስትል ኑሮ እንደከበዳት ትገልጻለች። በንግድ ሥራ ላይ የተሰማራው ለማ አበበ ደግሞ በአሁኑ ሰዓት ስላለው የአገሪቱ ምጣኔ ሀብት ሲናገር "እያደገ ነው" በማለት ነው። አክሎም "የዋጋ ግሽበት እና የኑሮ ውድነቱም በዚያው መጠን እያደገ ነው። ይህ ደግሞ ገበሬውን ሳይሆን ኑሮውን በየወሩ በሚያገኘው ደሞዝ ላይ ያደረገውን መካከለኛ ገቢ የሚያገኝ ነዋሪ እየጎዳው ነው። ገበሬው ግን ያመረተውን በገበያው ዋጋ ስለሚሸጥ አትራፊ ነው" ሲል ያስረዳል። አቶ ለማ የሚታየውን የኑሮ ውድነት ለመቆጣጠር የአገር ውስጥ ምርትን መጠቀምን ማበረታታ እና ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን መቀነስ መፍትሄ ይሆናል ብሎ ያምናል። የተለያዩ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ባለፉት አሥር ዓመታት መንግሥት በከፍተኛ መጠን ከተፈተነባቸው ችግሮች መካከል አንዱ የዋጋ ንረት ነው። መንግሥት የዋጋ ንረትን መቆጣጠር አቅቶታል ብለው የሚተቹ ወገኖች በርካታ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግሥታቸው የዋጋ ንረት ለመከላከል እንደ ሸገር ዳቦ ፋብሪካ ያሉ ተቋማትን እያቋቋመ መሆኑን ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ወደ ስልጣን መምጣት ተከትሎ ኢኮኖሚውን ነፃ ለማድረግ በሚል በመንግሥት ይዞታ ስር የሆኑትን ቴሌኮምዩኒኬሽንን፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድን በከፊል ወደግል ለማዘዋወር ተወስኖ ነበር። ከእነዚህ ድርጅቶች በተጨማሪም የኢንደስትሪ መንደሮችን፣ የስኳር ፋብሪካዎችን፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች አምራች ድርጅቶችን ወደ ግል ለማዞር ተወስኗል። ይህ ውሳኔ የተወሰነው የአገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠል፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረቱንና የዋጋ ግሽበቱን ለመቋቋም፣ የገቢ ማመንጨት አቅምን ለማጠናከርና የወጪ ንግዱን ለማቀላጠፍ በሚል ነው። ለዚህ ውሳኔ ሌላኛው ምክንያት የሆነው የኢትዮጵያ የብድር መጠን ከፍ ማለቱ እንደሆነም ይነገራል። ኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ተቋማት ክፍት እንደምታደርግ ያስታወቀችው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ይፋ በተደረጉ የለውጥ እርምጃዎች ነው። በቅርቡም ኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፍ እንዲሳተፍ ግሎባል ፓርትነርሽፕ ፎር ኢትዮጵያ ለተሰኘው ጥምረት ፍቃድ መስጠቷ ይታወሳል። በዚህም የተነሳ ከፍተኛ መጠን ያለው መዋዕለ ነዋይ ወደ አገሪቱ እንዲገባ እና በርካታ የሥራ ዕድሎችን እንደሚፈጥር ተነግሯል። እንደ ማዕከላዊ ስታትስቲክ ባለስልጣን መረጃ ከሆነ በኢትዮጵያ ያለው የኑሮ ውድነት በሰኔ ወር ብቻ 24.5 በመቶ ደርሷል። ኢትዮጵያ ከተለያዩ የውጭ አገራት የተበደረችው 42.8 ቢሊዮን ዶላር መሆኑ ይነገራል። ኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብቷን ለማሳደግ ከወሰደቻቸው እርምጃዎች መካከል አንዱ የተለያዩ ኢንደስትሪ ፓርኮችን ለውጭ ገበያ የሚሆኑ ምርቶችን እንዲያመርቱና እንዲልኩ ማበረታታት ነው። ማርታ ገላነው በአገሪቱ ካሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች መካከል በአንዱ ተቀጥራ ትሰራለች። የአውቶሜሽን ኢንጂነር ባለሙያ የሆነችው ማርታ በአገሪቱ እየተስፋፉ ያሉ የኢንደስትሪ መንደሮች የወደፊት ተስፋዋን ብሩህ ማድረጋቸውን ትናገራለች። በአሁኑ ጊዜ ገና በመቋቋም ባለ ፋብሪካ ውስጥ እየሰራች ቢሆንም ለወደፊት ግን "እንደ አውቶሜሽን ኢንጂነርነቴ በየትኛውም ትልልቅ ፋብሪካዎች ውስጥ ያሉ ማሽኖችን ማንቀሳቀስ እችላለሁ" ስትል ታስረዳለች። በደብረብርሃን የኢንደስትሪ ፓርክ የእንስሳት መኖ ለማምረት በማሰብ ግንባታ እያካሄዱ መሆኑን የሚናገሩት የባጃኢ ኢትዮ ኢንደስትሪያል ሶሉሽን ባለቤት ባጃኢ ናይከር ናቸው። በደብረብርሃን ኢንደስትሪያል ፓርክ ውስጥ እያስገነቡት ባለው የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ድብልቅ የእንስሳት መኖ ለኢትዮጵያውያን እንስሳት አርቢዎች ለማምረት እየሰሩ ነው። ፋብሪካው ከዚህ ቀደም ከውጭ እየመጣ የነበረውን የእንስሳት ቫይታሚንና ሚነራሎችን ለማስቀረት የሚያስችል እቅድ አለው። ፋብሪካው የአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለውጭ ገበያም የማቅረብ ሃሳብ እንዳለው ባለቤቱ ለቢቢሲ ተናግረዋል። እንደ ሚስተር ባጃኢ ከሆነ መንግሥት በዚህ የኢንደስትሪ መንደር ፋብሪካቸውን እንዲገነቡ የተለያዩ ማበረታቻዎችን አድርጎላቸዋል። በኢንደስትሪ ፓርክ ውስጥ ሲሰሩ ለተወሰነ ዓመታት ከታክስ ነጻ እንደሚሆኑ፣ ከውጭ የተወሰኑ እቃዎችን ከቀረጥ ነጻ የማስገባት እድል እንደተመቻቸላቸው፣ መሬት በርካሽ ማግኘታቸውን እንዲሁም በዚህ ኢንደስትሪ መንደር ለእንስሳት አምራቾች የተለየ ትኩረት መሰጠቱ እርሳቸውን ከሳቧቸው ጉዳዮች መካከል ናቸው። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በመላ አገሪቱ 15 የኢንደስትሪ ፓርኮች እንዳሉና ተጨማሪ 20 ደግሞ የመገንባት እቅድ እንዳለው ያስረዳል። የትግራይ ጦርነት እና የአገሪቱ ምጣኔ ሀብት የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት እድገት እያሳየ ቢሆንም በትግራይ፣ በአፋር እና በአማራ የተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ ያለው ጦርነት ግን የአገሪቱን ምጣኔ ሀብት ፈተና ላይ ጥሎታል። የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት እና የፌርፋክስ አፍሪካ ፈንድ የበላይ ኃላፊ አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ባለሀብቶች የረዥም ዓመት እቅድ ይዘው መሆኑን ይናገራሉ። በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ያለው ግጭት የአጭር ጊዜ መሆኑን እና አገሪቱም እንደምትወጣው ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል። ለኢትዮጵያውን ዋነኛ የምጣኔ ሀብት ስጋት የዋጋ ግሽበት መሆኑን የሚያብራሩት አቶ ዘመዴነህ፣ ባለፉት 10 ዓመታት የግሽበት መጠኑ በእጥፍ መጨመሩን በመግለጽ ይህም መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ኢትዮጵያውያን ተግዳሮት ሆኖ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ለዋጋ ግሽበቱ መናር ምክንያት ነው ብለው ከጠቀሷቸው መካከል ከፍተኛ የሆነ የፍላጎት መጨመር ሲኖር የአቅርቦት መጠን በዚያው ልክ ማደግ አለመቻሉን ነው። በአቅርቦትና በፍላጎት መካከል ያለ ከፍተኛ አለመመጣጠን በተለይ ደግሞ የአገር ውስጥ ምርቶች ከፍላጎት ጋር በተመጣጠነ መልኩ አለማደጋቸውን ያነሳሉ። ሌላው የጅምላ፣ የችርቻሮ እና የማከፋፈል ስርዓት በአገሪቱ ውስጥ አሁንም ኋላ ቀርነት እንዳለው አንስተዋል። ለዚህም መዋቅራዊ ለውጥ መካሄድ አስፈላጊ መሆኑን ይመክራሉ። ኢትዮጵያ ከ126 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የቴሌኮምዩኒኬሽኑን ዘርፍ ለግል ባለሀብቶች መስጠቷን የሳፋሪኮም ስምምነትን በመጥቀስ የገለፁት አቶ ዘመዴነህ፤ "ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያ ለተለያዩ ቢዝነሶች በሯን መክፈቷን ያሳያል" ሲሉ ተናግረዋል። በቴሌኮም ዘርፉ የውጭ ባለሀብቶች መምጣታቸው የአገልግሎት ጥራት፣ የዋጋ ውድድር በመፍጠር ለቴሌኮሙም ሆነ ለፋይናንስ ዘርፉ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ያብራራሉ። አቶ ዘመዴነህ ኢትዮጵያ በግብርና፣ በአምራች እንዲሁም በቱሪዝምና ሌሎች ዘርፎች በቀጣዩቹ ሦስትና አምስት ዓመታት እድገት እንደምታሳይ ያላቸውን ተስፋም ገልፀዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-58185460
amh
business
እሷ ማናት? #4፡ ከሒሳብ ጋር በአጋጣሚ ነው የተዋደድነው
በሒሳብ ትምህርት የዶክትሬት ዲግሪዋን (ፒኤች ዲ) ለማግኘት እየሰራች ነው። ሰዎች እምብዛም ገፍተው በማይሄዱበት የትምህርት ዓይነት እንዴት ውጤታማ ልትሆን እንደቻለች አጫውታናለች። ስሜ ኤቢሴ አዱኛ ይባላል። ተወልጄ ያደኩት በነቀምት ከተማ ነው። የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርቴን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪ ደግሞ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተምርያለሁ። በአሁን ሰዓት ደግሞ የሦስትኛ ዲግሪ ትምህርቴን በዴንማርክና በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች እየተከታተልኩ ነው። • የኮምፒዩተር ትምህርት ለኬኒያ ሴት እስረኞች ሁለተኛ እድል ይሰጣቸው ይሆን? • አንድም ሴት የፓርላማ አባል የሌላት ሃገር ሒሳብ መረጠሽ ወይንስ መረጥሽው ? የሙያ ሕይወቴ ከሒሳብ ጋር የተቆራኘ ይሆናል ብዬ አልገመትኩም ነበር። ለመጀመሪያ ዲግሪ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተመደብኩበት ወቅት የሒሳብ ትምህርት ሳልመርጥ በአጋጣሚ ደረሰኝ። ከዚያ በኋላ ግን እኔና ሒሳብ በጣም ተዋደድን። እኔ ልምረጠው ሒሳብ ይምረጠኝ የሚታወቅ ነገር የለም። የሒሳብ ትምህርትን ከድሮም ፈርቼው አላውቅም። ዩኒቨርሲቲ ገብቼ ትምህርቱ ሲደረሰኝ ጥሩ ነጥብ ማስመስገብ ጀመርኩኝ፤ እየወደድኩትም መጣሁ። በዚያ ላይ ይህ ትምህርት ለሴት ይከብዳል ለወንድ ደግሞ ይመቻል የሚል አመለካከት የለኝም። ማንም ሰው ፍላጎት ካለው፣ ከጣረና በሥራ ካስደገፈው ይሳካል ብዬ ስለማስብ የሒሳብ ትምህርትን አጥብቄ ይዤ ቀጠልኩበት፤ እዚህም ደረስኩኝ። አሁንም ቢሆን ከምወዳቸው ትምህርቶች መካከል ትልቁን ቦታ የያዘው ሒሳብ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ እያለሁ 'ጊዜ ቤት' ላይ ሌሎች ልጆች ሸምድደው በፍጥነት እንደሚሉት አልነበርኩም፤ ነገር ግን በልጅነቴ በተወሰነ ደረጃ ይህንን 'የጊዜ ቤት' እሠራ ነበር። በዚያ ወቅት ተማሪ እያለሁ አባቴ የሒሳብ መምህር ስለነበረ በሒሳብ ጥሩ መረዳት እንዲኖረኝ አድርጓል። በጭንቅላቴ ሸምድጄ ከመያዝ ይልቅ ተረድቼ ማስላት ይቀለኝ ነበር። የሒሳብ ጥቅም የተለያየ ነው። ለምሳሌ ሒሳብ በሁለት ይከፈላል፤ 'ፕዩር ማቴማቲክስና አፕላይድ ማቴማቲክስ' ተብለው ይለያሉ። • ሴት ተመራቂዎች ለምን ሥራ አያገኙም? • ሚሼል ኦባማ በአሜሪካ እጅግ ተወዳጇ ሴት ተባሉ እኔ የምማረው 'አፕላይድ ማቴማቲክስ' በተጨባጭ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የሚጠቅም ነው። ለምሳሌ የምመረምራቸው ስሌቶች ኤች ሲቪ ለተባለው የጉበት ቫይረስ መፍትሔ ለማግኘት የሚረዳ ነው። ስለዚህ ሒሳብ በሕይወታችን ያሉን ተጨባጭ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት የሚረዳ የትምህርት ዓይነት ነው። ነገ የሚሆንን ነገር ለመተንበይ ሒሳብ ችግሮቻችንን በቁጥር አስልተን ለማስቀመጥ ይረዳናል። የሒሳብ ምሁሮች ከስሌቱ በኋላ ቀመሩን ከነመፍትሔው ያስቀምጡልናል። የምህድስና ሙያ ያላቸው ሰዎች ደግሞ እንዲህ ዓይነት ቀመሮችን በሥራ ላይ ያውላሉ። ስለዚህ ከሒሳብ ሙያተኞች ይልቅ በምህንድስና ውስጥ የተሰማሩ ሰዎች በይበልጥ ማስረዳት ይችላሉ። ውጣ ውረዶችን ለማለፍ በሥራም ሆነ በኑሮ እንደማንኛውም ሰው የተለያየ መሰናክል ይገጥመኛል። ነገር ግን የችግሩን ያህል ሳይሆን ነገሮችን ከአቅሜ አንፃር ነው የምገመግማቸው። ችግር እንደሚያበረታኝና እንደሚያጠነክረኝ ስለማውቅ ሁሌም መውጫ ቀዳዳ ነው የምፈልገው። አንዳንዴ ሰዎች ፊቴንና ዕድሜዬን አይተው ይገምቱኛል። አንዳንዴ ጊዜ እንዲያውም በሴትነቴ ጭምር ለመመዘን ይሞክራሉ። እንደዚህ ዓይነት ሁኔታዎች ሲገጥሙኝ ደግሞ እራሴን በደንብ አስተዋውቃለሁ። ምን ማድረግ እንደምችል፣ ማን እንደሆንኩ እና ፍላጎቴ ምን እንደሆነ አስፈላጊ በሆነበት ቦታ ሁሉ እናገራለሁ። ይህ ደግሞ በሕይወቴ የምፈልገውን ነገር በሙሉ እንዳገኝ አድርጎኛል በዚያ ላይ ተግባቢ ሰው ነኝ። ሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪ መማር ጊዜን ስለሚፈልግ የጊዜ እጥረት ያጋጥማል። የፒኤች ዲ ትምህርት ምግብ የምበላበት ጊዜ እንኳን አይሰጥም፣ ያስጨንቃል ደግሞም ድብርት ያስከትላል። ቢሆንም ግን ያለኝን ጊዜ አብቃቅቼ ከጓደኞቼም ሆነ ከቤተሰቦቼ ጋር ጊዜ አሳልፋለሁ። ከዚህ ሁሉ ግን ያለንን ጊዜ በደንብ ከተጠቀምንበት የምንፈልገውን ማሳካት ይቻላል ብዬ አስባለሁ። • ሴት አስገድዳ ከወንድ ጋር ወሲብ ብትፈጽም፤ አስገድዶ መድፈር ይባላል? • ከመጀመሪያው 'የብላክ ሆል' ምስል ጀርባ ያለችው ሴት እንደሚታወቀው በአገራችን ሴት ልጅ ስትበልጥ ወንዶች ብዙ ደስተኛ አይደሉም፤ ሁሉም እንዲዚህ ናቸው ማለቴም አይደልም ነገር ግን እንዲህ ዓይነት አስተሳብ አለ። በሁሉም መንገድ ወንድ የበላይ ሆኖ አንዲታይ የሚፈልጉ አሉ። እንደእኔ አመለካለከት የትምህርት ደረጃ እና ፍቅር የተለያዩ ናቸው። ስኬቴ ችግር የሚሆንበት ካለ ለማስተናገድ አልችልም። የቤተሰቤ አባላት በማደርገው ጥረት ላይ በጣም የደግፉኛል። ጓደኛና የምወደው ሰው የምለውም ሰው ልክ እነደዚህ የሚደግፈኝ መሆን አለበት። ለምን ትበልጠኛለች ካለ ግን ይህ ፍቅር ነው ወይንስ ቅናት? ብዙ ሴቶች ያለንን አቅም የተረዳነው አይመስለኝም። እንችላለን ብለን ካመንን ማድረግ አያቅተንም። ይህን ከተረዳን ደግሞ በውበት፣ በጋብቻ እና በገንዘብ መወሰን የለብንም። እራሳችን ያለምነው ትልቅ ቦታ ላይ መድረስ እንደምንችል ማሰብና መጣር ነው ያለብን። ስለዚህም የሚያጋጥሙንን መሰናክሎች በእራሳችን ማለፍ መቻል አለብን። እንደዚህ ወደፊት ከተራመድን አገራችንን ወደፊት ለመምራት አያቅተንም። ያለንን አቅማችንንና መላ የማበጀት ጥበባችንን እንጠቀምበት ብዬ ለሴቶች ምክሬን እሰጣለሁ።
https://www.bbc.com/amharic/news-50218736
amh
business
ሲም ካርድ ያለው ሁሉ ገንዘብ መበደር የሚችልበትን ዕድል የፈጠረው ቴሌብር
ከአስራ አራት ወራት በፊት ወደ አገልግሎት የገባው ቴሌብር የተሰኘው የኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለፈው ሳምንት አርብ ከቁጠባ እና ብድር ጋር የተያያዙ አዳዲስ አገልግሎቶችን መስጠት ጀምሯል። ከቢቢሲ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ አዳዲሶቹ አገልግሎቶች በፋይናንስ ሥርዓት ያልተሸፈነውን 60 በመቶ የሚሆን የኅብተረሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል። የነዳጅ ድጎማ እና የግብር ክፍያን ጨምሮ ባለፉት 14 ወራት ገንዘብ ለመላላክ፣ የግብይትና የአገልግሎት ክፍያን ለመፈጸም እንዲሁም ከውጭ አገራት ገንዘብ ለመቀበል ሲውል የነበረው ቴሌብር አሁን ደግሞ  ‘መላ’፣ ‘እንደኪሴ’ እና ‘ሰንዱቅ’ የተሰኙ አገልግሎቶችን ይፋ አድርጓል። ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌብር ደንበኞች ገንዘብ እንዲቆጥቡ፣ ሲያስፈልጋቸው እንዲበደሩ የሚረዱት አዳዲሶቹን አገልግሎቶች ለማስጀመር አስራ አራት ወራት በላይ ዘግይቷል። ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ ቴሌኮም እነዚህን አገልግሎቶች ለማስጀመር ከአንድ ዓመት በላይ የዘገየበትን ምክንያት ሲያስረዱ “የተሰጠን ፍቃድ እሱን አልፈቀደልንም ነበር። ስለዚህ በቴሌ ብር ሌሎቹን አገልግሎቶች እየሰጠን ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ለማግኘት ሥራዎችን ስንሰራ ቆይተናል” ብለዋል። ለመሆኑ አገልግሎቶቹ ምንድን ናቸው? በቴሌብር አማካኝነት በቅርቡ የተጀመሩት ሦስት አገልግሎቶች ተጠቃሚዎች ያለዋስትና/ማስያዣ እንዲበደሩ ወይም እንዲቆጥቡ የሚያስችሉ መሆናቸውን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ለቢቢሲ ገልጸዋል። ይህ የቴሌብር አገልግሎት ደንበኞች ገንዘብ የሚቆጥቡበት ሲሆን፣ ለተቀማጭ ገንዘብ ወለድ የሚከፈልበትን እና ከወለድ ነጻ የሆነ አመራጮችን አካቷል። እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ገለጻ፣ ወለድ የሚከፈልበት ቁጠባ በየቀኑ የሚሰላ እና ደንበኞች በቀን ያገኙትን መጠን የሚያመላክት ነው። የቴሌብር ደንበኞች ግብይት እየፈጸሙ ገንዘብ በሚያንሳቸው ጊዜ ቀሪውን ገንዘብ የሚያገኙት ሥርዓት ደግሞ እንደኪሴ ይሰኛል። እንደኪሴ ደንበኞች ለግብይት ከሚያጥራቸው ገንዘብ በተጨማሪ እንደ የኤሌክትሪክ እና ውሃ ያሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመፈጸምም ያስችላል። ይህ አሰራር ደንበኞች ለክፍያ የጎደላቸውን እስከ 2 ሺህ ብር የሚሸፍንም ነው። ቴሌብር መላ፣ ደንበኞች የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት መንገድ ሲሆን ግለሰቦችን እና የንግድ ተቋማትን የሚያካትት ነው። በቴሌብር መላ ግለሰቦች በወር እስከ 10 ሺህ ብር፣ የንግድ ተቋማት ደግሞ እስከ 100 ሺህ መበደር እንደሚችሉ የሚያስረዱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ ግለሰቦች የተበደሩትን በቀን፣ በሳምንት እና በወር መመለስ የሚችሉበትን አሰራር ማቀፉን ጠቅሰዋል። ለንግድ ተቋማት ደግሞ ለግለሰቦች ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ በተጨማሪ የ3፣ የ6 እና የ9 ወር የሚመልሱበትን አሰራር አካትቷል። ቴሌብር መላ “ለሥራ ማስኬጃ እንዲሁም አዳዲስ ሃሳብ ኖሯቸው ወደ ንግድ መግባት ለሚፈልጉ ሰዎችን ታሳቢ አድርጎ የቀረበ ነው። ለዚያ ነው በፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽ ያልሆነውን ማኅበረሰብ፣ ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ አቅም ይሆናል ብለን ያሰብነው” ሲሉም አክለዋል። መላ፣ እንደ ኪሴ እና ሰንዱቅ በተሰኙት የቴሌብር አገልግሎቶች በመጀመሪያ ዓመት ውስጥ በየወሩ በአማካኝ ከ3 እስከ 4 ሚሊዮን ደንበኞችን ለማገልገል እና ከ19.5 እስከ 20 ቢሊዮን ብር ለማንቀሳቀስ ማቀዱን ኃላፊዋ ጠቅሰዋል። ከዚህም ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚወስደው የብድር አገልግሎቱ ወይም ቴሌብር መላ ሲሆን 9.8 ቢሊዮን ብር ይሸፍናል። 6.4 ቢሊዮን ብር ክፍያን ለማጠናቀቅ ወይም እንደ ኪሴ ለተባለው አገልግሎት እንዲሁም 3.3 ቢሊዮን ብር ደግሞ በቁጠባ ወይም ሳንዱቅ በተሰኘው አገልግሎት የሚጠቃለል ነው። ደጋግመው ብድር የሚወስዱ ደንበኞችን ጨምሮ በዓመት 108 ሚሊዮን ደንበኞችን ለማገልገል ማታቀዱንም አስረድተዋል። አገልግሎቶቹ በተጀመሩ በቀናት ውስጥ የዕለት ብድር ወስደው የሚመልሱ እንዲሁም የሚቆጥቡ ደንበኞች መኖራቸውን ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ተስፋ ሰጪ እና “አስገራሚ” ሁኔታዎች መኖራቸው ገልጸዋል። በቴሌብር መላ የሚሰጠው ብድር በሙሉ ዋስትና ወይም ማስያዣ እንደማይጠየቅበትም ጨምረው አስረድተዋል። የፋይናንስ ተቋማት ለሚያበድሩት ገንዘብ ዋስትና ወይም ማስያዣን መጠየቅ የተለመደ አሰራራቸው ነው። ከዚህ አሰራር በተቃራኒ በቴሌብር የሚቀርቡ ብድሮች ዋስትና አይጠየቅባቸውም። ሆኖም ሥርዓቱን በሚንቀሳቀስበት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የደንበኞችን የወጪ ገቢ ዝውውር በመመልከት የብድሩን መጠን ይፈቀዳል። ሥርዓቱ ደንበኛውን በገንዘብ ዝውውሩ በመመልከት በተለያዩ ደረጃዎች የሚገለጽ ነጥብ የሚሰጥ ሲሆን፣ ብድር ለሚመልሱ ደንበኞች ደግሞ የተሻለ ቡድር ማግኘት የሚቻልበትን ነጥብ ይሰጣል። አገልግሎቱ በቴሌብር ሞባይል መተግብሪያ  ወይም #127# አጭር ቁጥር አማካኝነት የሚቀርብ ሲሆን፣ የኢትዮ ቴሌኮም ሲምካርድ ላላቸው ደንበኞች በሙሉ በቴሌብር ያላቸውን የገንዘብ ዝውውር መሰረት አድርጎ ብድርን የሚያቀርብ ነው። እነዚህ አገልግሎቶችን ለማስጀመር የአዋጪነት ጥናት መካሄዱን የሚያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፣ እንደ ማንኛውም የፋይናንስ አገልግሎት ስጋት ሊኖር እንደሚችል ታሳቢ መደረጉን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ይህ አገልግሎት የኢትዮጵያን ባህል ከግምት ውስጥ ማስገባቱን በማንሳት “ሁሉም ደንበኛ አይመለስም ብለን ልንወስድ አንችልም። . . . ተበድሮ አልመለሰም መባልን የማይፈልግው የማኅበረሰባችን ክፍል ሰፊ ነው። እርሱን እንደ ጥንካሬ ወስደነዋል።” አክለውም “ . . . አንዴ ብድሩን አልመለሰም ማለት በሚቀጥለው ብድር አያገኝም። ስለዚህ አንዴ ሁለት ሺህ ብር ተበድሮ ቢጠፋ ነው የሚሻለው ወይስ በዓመት ሁለቴም ሦስቴም ሁለት ሺህ፣ አራት ሺህ ቢበደር ነው የሚሻለው? ለማኅበረሰቡ የምናስረዳው ይህንን ነው። ይህ ይሆናል ብለን አንጠብቅም። ባለማወቅ ሊፈጠር ይችላል። ለዚያ ግን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እንሰራለን። ምንም ችግር አያጋጥመንም ግን አንልም። በፋይናንስ ሴክተር ያሉ እንደሚያውቁት በዋስትና የሚሰጠው ብድርም ላይመለስም ይችላል። ግን ከቁጥጥር ውጪ አይሆንብንም። እሱን አጥንተን ነው የገባነው” ብለዋል። ሥርዓቱ ላይ ይህ ችግር ሊያጋጥም ይችላል በሚል ይህንን ከመተግበር ወደ ኋላ አንልም የሚሉት ፍሬህይወት “60 በመቶ የኅበረተሰብ ክፍል የፋይናንስ አገልግሎት የማያገኝበት አገር ላይ ሆነን ሪስክ [ስጋት] አለ ብለን የገንዘብ ችግር ከመፍታት አንጻር ትልቅ አቅም የሆነውን አለመጀመር ደግሞ ተገቢ ነው ብለን አናስብም. . .” ስለዚህም ይህንን በአግባቡ ተጠቅመው ኑሯቸውን፣ ሕይወታቸውን፣ ቤተሰባቸውን ሊቀይሩ የሚችሉ ሚሊዮኖች ስላሉ የእነርሱን ዕድል ለማስፋት የተጀመረ ሥራ መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፣ “ሙሉ በሙሉ ስጋት (ሪስክ) የለውም ብለን ሳይሆን መልካም ጎኑን ይዘን ነው የተነሳነው” ሲሉም አክለዋል። ወደ አገልግሎት ከገባ 1 ዓመት ያለፈው ቴሌብር 22.2 ሚሊዮን ደንበኞችን ማፍራቱን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ያስረዳሉ። በእነዚህ ጊዜያትም 34.1 ቢሊዮን ብር የገንዘብ ዝውውር ተከናውኖበታል። ከዝውውሩ 18 በመቶ የሚሆነው ገንዘብ ማውጣት እና ማስገባት ሲሆን 40 በመቶ ደግሞ የአየር ሰዓት መሙላትን ነው። ገንዘብ መላላክ፣ የአገልግሎት ክፍያ እና ግብይት መፈጸም ደግሞ የተቀረውን ድርሻ ይይዛል። የግብር፣ የውሃ፣ የኤሌክትሪክ እና መሰል አግልግሎቶችን ከሚሰጡ በርካታ የመንግሥት ተቋማት፣ ከ13 ባንኮች እንዲሁም ከ22 ሺህ የንግድ ተቋማት ጋር የተሳሰረው ቴሌብር  በመላው አገሪቱ ከ79 ሺህ በላይ ወኪሎች እንዳሉትም ኃላፊዋ ጠቅሰዋል። “ይህንን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካታችንን እንደ ትልቅ ስኬት እንወስደዋለን” የሚሉት ኃላፊዋ ቴሌብር የገንዘብ ዝውውር እና ክፍያን ምቹ እና ቀልጣፋ ማድረግ፣ የክፍያ ሥርዓትን ማዘመን እና የዲጂታል ኢኮኖሚን በማስተዋወቅ በፋይናንስ አገልገሎት ያልተካተተውም ሕዝብ ተደራሽ ማድረግ ዋነኛ አላማው እንደሆነ አንስተዋል። እስካሁን ቴሌብር “የክፍያ ሥርዓቱን ሲያሳልጥ የቆየ” ሲሆን በፋይናንስ ሥርዓት ተደራሽ ያልሆኑ ሰዎችን ተደራሽ የማድረግ ቀዳሚ ዓላማውን ለማሰካት በቅርቡ ይፋ የሆኑት ዓላማዎች ወሳኙን ሚና እንደሚጫወቱ ጠቅሰዋል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cy0xj34y9l7o
amh
business
ቻይና ዝናብ ለማዝነብና የተፈጥሮ ሂደትን ለመቆጣጠር የምታደርገው ጥረት
እንደ ቻይናዋ ቤይጂንግ የአየር ብክለት የሚፈትነው ከተማ የለም። የቤይጂንግ ሰማይ በመጠኑም ቢሆን ጠርቶ ፀሐይ የምትታየው በከተማዋ የሚካሄድ ዓለም አቀፍ ውይይት ሲኖር ነው። ይህ የሚሆነው በተፈጥሯዊ ሂደት ሳይሆን መንግሥት በቀየሰው ስልት አማካይነት ነው። የቻይና መንግሥት የአገሪቱን የአየር ሁኔታ ለመለዋወጥ ሰው ሠራሽ መንገድ መጠቀም ጀምሯል። ይህ ሰው ሠራሽ ሂደት በጥቂት የቻይና ከተሞች ብቻ ይተገበር ነበር። ከጥቅምት ወዲህ ግን አገር አቀፍ እንደሚሆን ተነግሯል። ሂደቱ በሰው ሠራሽ መንገድ ዝናብ እንዲጥል ማድረግ፣ በረዶ ማዝነብ ወዘተ. . . ያካትታል። እአአ በ2015 ይህን ሂደት በቻይና 5.5 ሚሊዮን ስኩዌር ኪሎ ሜትር ማለትም የአገሪቱን 60 በመቶውን ለማዳረስ ታቅዷል። እቅዱ እንደ ሕንድ ላሉ ጎረቤት አገሮች አልተዋጠላቸውም። ቻይና እና ሕንድ ከድሮውም ውጥረት ውስጥ ናቸው። ቻይና የአየር ሁኔታን የምትለውጠው እንዴት ነው? በእንግሊዘኛው ክልውድ ሲዲንግ (cloud seeding) በሰው ሰራሽ መንገድ ዝናብ እንዲጥል የሚደረግበት ቴክኖሎጂ ነው። ለዚህም ሲልቨር አዮዳይድ የተባለ ንጥረ ነገር ወደ ደመና በመላክ የአየር ሁኔታ የሚለወጥበት ሂደት ነው። በሕንድ የአየር ሁኔታ ባለሙያው ዳናስሪ ጃይራም "ይህንን ቴክኖሎጂ ብዙ አገሮች ይጠቀሙበታል። ቻይናና ሕንድም ይጠቀሳሉ" ይላሉ። ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራትም ይህ ሂደት ይተገበራል። እንደ አውስትራሊያ ያሉ አገሮች ድርቅን ለመከላከል ይጠቀሙታል። ሂደቱ በተለይም በአሜሪካ ከ1940ዎቹ ወዲህ ነው እየታወቀ የመጣው። ውጤቱ ላይ ጥያቄ ያላቸው ባለሙያዎች ግን አሉ። በቤይጂንግ ዩኒቨርስቲ የሚሠሩት ጆን ሲ ሙር "ውጤታማነቱን የሚጠቁሙ ጥቂት ሳይንሳዊ ጽሑፎች ብቻ ናቸው ያሉት። ያለ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ የተተገበረ ሂደት ነው" ይላሉ። ሳይንቲስቱ እንደሚሉት፤ 50 ሺህ የቻይና ከተሞችና ወረዳዎች ይህንን መንገድ ተጠቅመው የእርሻ መሬታቸውን ለማዳን ይሞክራሉ። ዝናብን በማስቆም ማዕበል ሰብላቸውን እንዳያጠፋው ለመከላከል ይጥራሉ። ሆኖም ግን ተመራማሪዎች እንደሚሉት ይህ ሂደት ቻይና ውስጥ የሚሠራው ለአንድ ወይም ለሁለት ወራት ነው። ዝናብ የማነው? ቻይና የአየር ሁኔታን በመቆጣጠር ተፈጥሯዊ አደጋ እንዳይከሰት የመከላከል እቅድ እንዳላት አስታውቃለች። ሰብል እንዳይበላሽ፣ ሰደድ እሳት እንዳይስፋፋ፣ ከፍተኛ ሙቀትን ለመቆጣጠር፣ ድርቅን ለመግታት ወዘተ. . . ይውላል። ቤይጂንግ ውስጥ የምትሠራው ጋዜጠኛ ይትሲንግ ዋንግ እንደምትለው ቻይና የአየር ሁኔታን ለመቆጣጠር ያወጣችው መርሃ ግብር ሲተገበር ከግዛት ግዛት ይለያያል። ሂደቱ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች ቻይናን አላሳሰቧትም። የቻይና ውሳኔ ከጎረቤት አገሮቿ ጋር ያላትን የፖለቲካ ፍጥጫ ሊያባብሰው ይችላል። "የቻይና የአየር ሁኔታ የመለወጥ ሂደትደ የሕንድ የክረምት ዝናብ ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል የሚል ስጋት አለ" ሲሉ የሕንዱ ተመራማሪ ያስረዳሉ። በቻይና እና ሕንድ የድንበር ግጭት ሳቢያ ሕንድ ውስጥ ለቻይና ያለው አመለካከለት እየጠለሸ ነው። የአየር ሁኔታ ለውጡም ከዚሁ ጋር ተያይዞ ይታያል። በታይዋን ዩኒቨርስቲ በ2017 የተሠራ ጥናት እንደሚያሳየው፤ የአየር ሁኔታ ለውጥ ሲደረግ ከጎረቤት አገራት ጋር ውይይት ካልተደረገ ግጭት ሊነሳ ይችላል። የአንድ አገር የዝናብ መጠን ሲቀንስ ሌላውን አገር ተጠያቂ የማድረግ ሁኔታ ይፈጠራል። "ይህ ስጋት ሳይንሳዊ አይደለም። ሆኖም ግን የቲቤት ተራራ የአየር ሁኔታ የተለያየ መሆኑ ከግምት መግባት አለበት። ስለዚህ አንድ አካባቢ የአየር ንብረት ለውጥ ሲከሰት ሌላው ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩ አይቀርም" ሲሉ ሳይንቲስቱ ጆን ሲ ሙር ያስረዳሉ። ቻይና የተለጠጠ እቅድ በማንገብ ሌሎችም ዘርፎች ላይ ለውጥ ልታካሂድ እንደምትችል ባለሙያዎች ይሰጋሉ። ይህም በሰው ሠራሽ መንገድ የፀሐይ ጨረራን ለመቆጣጠር መሞከርን ያካትታል። እነዚህ ውሳኔዎች የሚተላለፉት ከጎረቤት አገሮች ጋር ባለው ውጥረት ሳቢያ ሊሆን ይችላል የሚል መላ ምትም አለ። ሳይንቲስቱ በበኩላቸው "ቴክኖሎጂው ችግር አለው እያልኩ አይደለም። ነገር ግን በቴክኖሎጂው አንዳች ችግር ቢከሰት በምን መንገድ ይፈታል? ኃላፊነቱንስ የሚወስደው ማን ነው? ለሚለው መልስ ሊኖር ይገባል" ይላሉ። በተጨማሪም የአየር ሁኔታን መለወጥን የመሰሉ ሂደቶች ዓለም አቀፍ ውይይት እና ስምምነት እንደሚፈልጉ ባለሙያው ያስረዳሉ። ሂደቱ የሚተገበርበት ወጥ አሠራር እንዲሁም ሂደቱን ተከትሎ ግጭት ቢነሳ በምን መንገድ መፈታት እንደሚችል አስቀድሞ መታሰብ አለበት ሲሉም ያክላሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-56099470
amh
business
ፓኪስታን ፡ በካርቱን ስዕል ምክንያት የፈረንሣይ ምርቶችን መጠቀም ልታቆም ነው
አንድ የፓኪስታን እስላማዊ ቡድን የጠራውን የፀረ-ፈረንሳይ ተቃውሞን የፓኪስታን መንግሥት የፈረንሳይ ምርቶችን ላለመጠቀም በመወሰኑ ማቋረጡን አሳወቀ። ሰልፎቹ የተጠሩት ፈረንሳይ የነቢዩ ሙሐመድን ካርቱን የማሳየት መብትን በመደገፏ ነበር። አንድ መምህር በክፍል ውስጥ በነበረ ውይይት ወቅት የነቢዩ መሐመድን ካርቱን ካሳዩ በኋላ መገደላቸውን ተከትሎ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን አገራቸው በሐይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አትገባም ሲሉ በጥብቅ ተከላክለዋል። ይህም በሙስሊሙ ዓለም ቁጣን ቀስቅሷል። የአክራሪው ተህሪክ ኢ-ላባይክ ፓኪስታን (ቲ.ኤል.ፒ) የተሰኘው ቡድን አባላት የፈረንሳይን ምርት ላለመግዛት የቀረበውን ውሳኔ የደገፉ ቢያንስ የሁለት ሚኒስትሮችን ፊርማ ያካተተ የስምምነት ቅጅዎችን አሳይተዋል። የፓኪስታን መንግስት በጉዳዩላይ በይፋ መግለጫ ካለመስጠቱም በላይ የፈረንሳይ ምርቶችን ያለመጠቀም አድማው እንዴት እንደሚተገበር አላሳወቀም። በፈረንሣይ እስልምናን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት ማክሮንን ከተቹ የፖለቲካ መሪዎች መካከል የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካን አንዱ ናቸው። ተቀዋሚዎቹ አሁንም ተጨማሪ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። ደጋፊዎች ከእሁድ ጀምሮ ወደ መዲናዋ ኢስላማባድ የሚወስደውን ቁልፍ መንገድ በመዝጋታቸው ከፍተኛ የእንቅስቃሴ መስተጓጎል አስከትሏል። የቲ.ኤል.ፒ አመራሮች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ መስጠቱን ከተናገሩ በኋላ ተቃውሞው እንዲቋረጥ ተጠይቋል። የቡድኑ ቃል አቀባይ የሆኑት ኢጃዝ አሽራፊ ለሮይተርስ እንደተናገሩት "የፈረንሳይ ምርቶችን እንደማይጠቀም መንግሥት በይፋ እንደሚደግፍ ስምምነት ከፈረመ በኋላ የተቃውሞ ሰልፎቻችንን እያቆምንው ነው" ብለዋል። ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ የተደረገው የስምምነት ሰነድ የሐይማኖታዊ ጉዳዮች ሚኒስትሩን እና የአገር ውስጥ ሚኒስትሩን ፊርማ ይዟል። የፈረንሣይ አምባሳደር ከአገር እንዲወጡ በማድረግ ዙሪያ ላይ ፓርላማው እንዲወስን መንግሥት ሐሳብ እንደሚያቀርብም ገልጿል። የፓኪስታን መንግሥት በስምምነቱ ላይ የሰጠው አስተያየት የለም። ቲ.ኤል.ፒ ቀደም ሲል ሐይማኖታዊ ስድብን ምክንያት በማድረግ ተቃውሞ ለማሰማት እጅግ ብዙ ሰዎችን በመሰብሰብ ይታወቃል። በፓኪስታን ሕግ መሠረት ነቢዩ ሙሐመድን በመሳደብ ጥፋተኛ የተባሉ ሰዎች የሞት ቅጣት ሊጣልባቸው ይችላል። በፈረንሳይ የመንግሥት በሐይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ ያለመግባት የአገሪቱ ዋነኛ መገለጫ ነው። በትምህርት ቤቶች እና በሌሎች ሕዝባዊ ቦታዎች ሀሳብን በነፃነት መግለጽም የዚህ አካል ሲሆን የአንድን የተወሰነ ሐይማኖት ስሜት ለመጠበቅ የሃሳብ ነጻነቱን መግታት ብሔራዊ መገለጫውን እንደሚያደፈርስ ተደርጎ ይወሰዳል። 'ቻርሊ ሄብዶ' የተሰኘው መጽሔት የነቢዩ ሙሐመድ ካርቱን ይዞ መውጣቱን ተከትሎ እ.አ.አ በ2015 በፓሪስ ውስጥ የጥቃት ዒላማ ቢሆንም የካቶሊክን እና የአይሁድን እምነት ጨምሮ ሌሎች ሐይማኖቶችም የሚያመለክቱ ስዕሎችን ይዞ ወጥቷል። የፈረንሣይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቀደም ሲል በበርካታ ሙስሊሞች በብዛት በሚገኙባቸው አገሮች ውስጥ የፈረንሳይ ሸቀጦችን ላለመጠቀም የሚደረጉ ጥሪዎችን "መሠረተ ቢስ" ብለው "በአፋጣኝ መቆም" እንዳለባቸውም ገልጸው ነበር። ባለፈው ወር ለተገደሉት መምህር ክብር የሰጡት ፕሬዝዳንት ማክሮን ፈረንሳይ "ካርቱኑን አታቆምም" ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54970898
amh
business
እየበረታ በመሄድ ላይ ያለው የዋጋ ንረት አዙሪት
ባለፉት ጥቂት ወራት የሸቀጦች የዋጋ ንረት እና አጠቃላይ የኑሮ ዋጋ መወደድ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ የብዙሃን መገናኛዎች ተደጋግመው የሚወሱ ጉዳዮች ሆነዋል። የመንግሥት ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶችም የችግሩን አሳሳቢነት ከመቀበል በዘለለ እየተወሰዱ ናቸው የሚሏቸውን እርምጃዎች ሲናገሩ ተስተውለዋል። በወርሃ ግንቦት 2011 ዓ.ም መገባደጃ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ኢንጂነር እንዳወቅ አብጤ በመዲናዋ በግንባታ ዕቃዎች፣ በእህል፣ በጥራጥሬ እና በአትክልት ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪዎች መከሰታቸውን ጠቅሰዋል። እንደመፍትሄም ችግሩን አባብሰዋል ያሏቸው ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊ መስመር ማምጣት፣ ፈቃደኛ ያልሆኑት ላይ ደግሞ ይህንን የሚከታተል ግብረ ኃይል በማቋቋም እርምጃ መውሰድ፣ እንዲሁም ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የአቀርቦት ሥርዓቱን ማሰተካከል የከተማዋ አስተዳደር የሚያከናውናቸው ተግባራት መሆናቸውን ገልፀው ነበር። • "ኢህአዴግ ነፃ ገበያም፣ ነፃ ፖለቲካም አላካሄደም" ፀደቀ ይሁኔ (ኢንጂነር ) • "መንግሥት የዋጋ ንረቱን ለመቆጣጠር መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦችን ያስገባል"ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ይሁንና ክረምቱ ሲገባ የዋጋ ንረቱ ከመርገብ ይልቅ ከፍ ብሎ ታይቶ የዋጋ ግሽበቱ ባለሁለት አሀዝ ሆኗል። በወርሃ ነሐሴ እንዲያውም ባለፉት ስድስት ዓመታት ከታየው የዋጋ ግሽበት መጠን ከፍተኛው ተመዝግቧል። የሸቀጦች የዋጋ ንረት ህይወታቸው ላይ ቀጥተኛ ጫና ካሳረፈባቸው የአዲስ አበባ ኗሪዎች መካከል ደግሞ የአርባ ዓመቱ ጎልማሳ ጋሹ መርከቡ አንዱ ነው። በአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሚኖረው ጋሹ ላለፉት ከአስራ ለሚልቁ ዓመታት በሚኒባስ ታክሲ ሾፌርነት ቤተሰቡን ሲያስተዳድር ኖሯል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን "የኑሮ መወደድ ከአቅሜ በላይ ሆኖ እያንገዳደገደኝ ነው" ይላል። "በዋጋ ላይ ያለውን ለውጥ ከቀን ወደ ቀን እያየሁት የመጣሁት ጉዳይ ነው፤ በእኔ [ህይወት] እንኳ ታክሲ ሠርቼ ብሩን ይዤ ብገባም ምንም የሚገዛው ነገር የለም" ይላል ከቢቢሲ ጋር በነበረው ቆይታ። "የልጆች ትምህርት ቤት፣ የእህሉ ውድነት፣ እንዲያውም ተስፋ ወደማስቆረጥ ደረጃ እየደረሰ ያለ ይመስለኛል" ይላል። መጪውን ፍራቻ ጋሹ የአራት ልጆች አባት ሲሆን ትልቋ የአስራ ሁለት ዓመት ልጁ የስድስተኛ ክፍል ተማሪ ናት። ሌሎቹ ሦስት ልጆቹም በመዋዕለ ሕፃናት እና በአንደኛ ደረጃ ትምርት ቤቶች ውስጥ ይማራሉ። ባለፉት ዓመታት ሁሉንም ልጆቹን በግል ትምህርት ቤቶች ያስተምር የነበረ ሲሆን አሁን ግን በኑሮ ውድነት ላይ በየጊዜው የሚጨምረውን የትምህርት ቤት ክፍያን መቋቋም ባለመቻሉ አንደኛውን ልጁን የመንግሥት ትምህርት ቤት፣ ሁለቱን ደግሞ በለጋሽ ድርጅቶች በሚደጎም እና በዚህም ምክንያት በአንፃራዊነት አነስተኛ ከፍያ ወደሚጠይቅ ትምህርት ቤት አስገብቷል። ለእያንዳንዳቸው በየወሩ ሦስት መቶ ብር በመደበኛነት ይከፍላል። • ኢትዮጵያዊያን ለምን ሥጋ አይመገቡም? • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማትን ሊያሸንፉ እንደሚችሉ ግምቶች አሉ አንደኛዋን ልጁን ብቻ በግል ትምህርት ቤት መማሯን እንድትቀጥል አድርጓል። ለብቸኛዋ የግል ትምህርት ቤት ተማሪ ልጁ መደበኛ ክፍያ ብቻ በዓመት ከአስር ሺህ ብር በላይ ያወጣል። ይህም የትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ፣ የአልባሳት፣ የምግብ ወጪዎች ሲደመሩበት "ናላን የሚያዞር" ሆኗል ይላል ጋሹ። በዚህ ላይ የቤት ኪራይ ወጪ ይታከልበታል። "ህይወታችንን ለማቆየት እየሰራን ነው እንጅ እየኖርን ነው ብዬ አላወራውም።" አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ መጪውን ጊዜ ይበልጥ እንዲፈራው እንዳደረገው ይናገራል ጋሹ፤ "ወደፊት እንዴት እንደማስተምራቸው ራሱ ግራ ግብት እያለኝ ነው" በማለት። ተስፋው ከዕለት ወደ ዕለት እንዲሟጠጥ አንድ ምክንያት የሆነው እርሱን ለመሰሉ ከኑሮ ጋር እልህ አስጨራሽ ግብግብ ለገጠሙ ሰዎች በፖለቲካ ልሂቃን ዘንድ ብዙም ትኩረት እየተሰጠ አይደለም ብሎ ማመኑ ነው። • ‹‹እነ ቴሌን ለግል ባለሀብት?›› ታሪካዊ ስህተት ወይንስ መልካም አጋጣሚ ? የፖለቲካ ልሂቃኑ "በብሔርም ጉዳይ፣ በምንም ጉዳይ የራሳቸውን ለማመቻቸት እንጂ የድሃውን [ጉዳይ] አንስቶ ልብህን [የሚነካ] ነገር ሲናገሩ እኔ እስካሁን ሰምቼም አላውቅም። የራሳቸውን ጉዳይ ከማስፈፀም በስተቀር ውስጥህን የሚነካ ነገር፣ ስለኑሮህ፣ ስለሽንኩርት የሚያወራ የለም" ይላል። ከጋሹ አስተያየት ጋር በሚስማማ መልኩ አጠቃላይ ምርጫ በሚከናወንበት ዓመት በፖለቲካዊ መድረኮች ላይ የዋጋ ንረት የሚገባውን ያህል ስፍራ ይዞ ያለመታየቱ እንደሚገርማቸው የሚያስረዱት የምጣኔ ሃብት የፖሊሲ ተንታኝ የሆኑት አሚን አብደላ ናቸው። "ምርጫ ኖረም አልኖረም፤ የማንኛውም አገር መንግሥት ፈተና የሚሆኑ ሁለት የማክሮኤኮኖሚ አመላካቾች አሉ፤ የሥራ አጥነት እና የዋጋ ንረት።"

በፖለቲካው መልክዐ ምድር ገኖ ያለው መንግሥታዊው ሥርዓት "የፌዴራል ይሁን አይሁን የሚል ዓይነት እንጅ የሥራ አጥነት እና የዋጋ ንረት ላይ ብዙም የፖለቲካ ልሂቃን ሲጨቃጨቁ አይቼ አላውቅም" ባይ ናቸው ተንታኙ። ለአንድ አገር መረጋጋት እና የምጣኔ ሃብት ዕድገት ወሳኝ ናቸው የሚሏቸው እነዚህ ጉዳዮች ብዙም ያለመነሳታቸው "ዋናው ነገር የተዘነጋ ይመስለኛል" አስብሏቸዋል። የምጣኔ ሃብት ፖሊሲ ተንታኙ አሚን አብደላ እንደሚሉት አጠቃላይ የዋጋ ንረት ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ እንዳለ መረጃዎች ያሳያሉ ይላሉ። በተሰናበተው 2011 ዓ.ም የሐምሌ ወር የዋጋ ግሽበቱ ከ15 በመቶ በላይ ደርሶ እንደነበረ የሚያስታውሱት አሚን በወርሃ ነሐሴ ደግሞ ይህ ቁጥር ወደ 18 በመቶ ከፍ ብሎ እንደነበርም ይጠቅሳሉ። ይህም ቁጥር በስድስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የታየው ትልቁ አሃዝ ነው። ለቁጥሩ ከፍ ማለት የምግብ ዋጋ፣ በተለይም የእህል ሰብል ዋጋ ንረት ምክንያት መሆኑን የስታትስቲክስ መረጃዎች ያመላክታሉ። • «አማካሪ አያስፈልገኝም ብሎ የሚያስብ መሪ አልገባውም ማለት ነው» ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ • በተሻሻለው የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ህግ ረቂቅ ጥፋተኛና አቃቤ ህግ ይደራደራሉ በዚህ ረገድ በአንዳንድ ትርፍ አምራች በሆኑ አካባቢዎች የነበረው የፀጥታ ሁኔታ፣ የመጓጓዣ አገልግሎት እንደልብ ያለመገኘት እና ከዚህም ጋር በተያያዘ ምርትን በተፈለገው ደረጃ ማቅረብ ያለመቻል ለችግሩ ምክንያት ሳይሆኑ እንዳልቀሩ ተንታኙ አሚን ያነሳሉ። እየናረ ያለውን የዋጋ ንረት ለማቃለል ሁለት የመፍትሄ እርምጃዎች ሊወሰዱ ይችላሉ የሚሉት ባለሙያው፤ "አንደኛው በአቅርቦት በኩል ሌላኛው ደግሞ በፍላጎት በኩል ያሉ ናቸው" እንደአሚን ገለፃ። "ከፍላጎት አንፃር የመንግሥት ወጪ የቀነሰበት ሁኔታ አለ። ያለፉትን ዓመታት ዓይነት እድገት ስለሌለ፤ ምጣኔ ሃብቱ ውስጥ የሚለቀቀው የገንዘብ መጠን ቀነስ ያለ ይመስላል። ይሁንና በአቅርቦት በኩል እምብዛም ለውጥ ያለ አይመስልም" ሲሉ ለቢቢሲ አስረድተዋል አቶ አሚን። የምርቶች በተገቢው መጠን አለመገኘት ለዋጋ መወደድ በአንዳንድ ሰዎች እንደምክንያት ተደጋግሞ የሚነሳ ሲሆን፤ ባለሙያውም በምርት እና በአቅርቦት መካከል ያለው ሰንሰለት ችግር እንደሚስተዋልበት ይናገራሉ። "ገበሬው አምርቶ ለምርቱ የሚያገኘው ዋጋ እና ከተማ ላይ መጥቶ የሚሸጥበት ዋጋ በጣም ከፍተኛ ልዩነት አለው። ገበሬው ከአንድ ኪሎ ሙዝ እያገኘ ያለው ገቢ እና አንድ ኪሎ ሙዝ ከተማ ውስጥ እየተሽጠበት ያለው ዋጋ ልዩነት አለው። "በዚህ መካከል ያለው የአገልግሎት፣ የደላላ፣ የመጓጓዣ፣ የቦታ ኪራይ እና የመሳሰሉት ወጪዎች ከፍተኛውን ድርሻ የሚወሰዱ ናቸው። ይህ የገበያ ሰንሰለት ሥርዓት እሰካልያዘ ድረስ፤ የምርቶች ዋጋ ከፍ እንዲል ማድረጉ አይቀሬ ነው" ለአሚን። • ሸማቹ በውጭ ምንዛሪ ለውጡ ማግስት • ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር ማዕድ የቀረቡት ምን ይላሉ? ከውጭ የሚመጣ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር የንግድ ውድድርን ማሳለጥ እንዲሁም የሸማቾችን ጥበቃ ማጠናከር ይገባል የሚሉት ባለሞያው፤ ከውጭ የሚመጡ ምርቶችን የሚያስመጡ ተቋማት እና ግለሰቦች በየተሰማሩበት ዘርፍ ጥቂት መሆናቸው ዋጋው ላይ ከሚገባው በላይ ጫና እንዲፈጠር መንገዱን ይጠርጋል ባይ ናቸው አቶ አሚን። ከውጭ የሚመጣ የዋጋ ንረት በውጭ ምንዛሬ እጥረት ምከንያትም ሊከሰት ቢችልም በእኛ አገር እየተስተዋለ ያለው እውነታ ግን በውጭ ምንዛሬው እጥረት መጠን ያህል መኖር ከሚገባው በላይ ጭማሪ ነው፤ ሲሉ የዋጋው ጭማሪ አሳሳቢ መሆኑን ይጠቅሳሉ። ባለሞያው አቶ አሚን አብደላ ለፖለቲካዊ ጉዳዮች እየተሰጠ ካለው ጋር የሚመጣጠን አትኩሮት የዋጋ ንረትን ለመሳሰሉ ምጣኔ ሃብታዊ ተግዳሮቶች መቸር አለበት ባይ ናቸው። በዚህ አስተያየታቸው ጋሹም የሚስማማ ይመስላል፤ "ይሄ ሁሉ እየታየ ቸል የሚባለው እስከመቼ እንደሆነ አይገባኝም።"
https://www.bbc.com/amharic/news-49922350
amh
business
የአንድ ቢትኮይን ዋጋ 2.4 ሚሊዮን ብር ገባ
የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ60 ሺህ ዶላር ወይም 2.4 ሚሊዮን ብር በላይ በመግባት ክብረ ወሰን ሰብሯል። ቢትኮይን መመንደግ የጀመረው በተለይ ደግሞ ከባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት መገባደጃ አንስቶ ነው። ይህንን የማይጨበጥ የማይዳሰስ መገበያያ ገንዘብ በርካታ ግዙፍ ድርጅቶች እንቀበለዋለን ማለታቸው ለዋጋው መናር ምክንያት ሆኗል ተብሏል። በዘርፉ ጥርስ የነቀሉ ግን የቦትኮይን ዋጋ እንዲህ ያሻቀበው የአሜሪካ መንግሥት በኮሮናቫይረስ ኪሳቸው ለተጎዳ ዜጎች የሰጠውን ድጎማ ተከትሎ ነው ይላሉ። የቢትኮይን ጠቅላላ የገበያ ዋጋ አሁን ከ1 ትሪሊየን በላይ ሆኗል። ቢሆንም ቢትኮይን ከተፈጠረበት የፈረንጆቹ 2009 ጀምሮ ዋጋው አንድ ጊዜ ሲያሻቅብ አንዴ ደግሞ ሲያሽቆለቁል ነው የከረመው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየታየ ያለው የቢትኮይን ማሻቀብ ከግዙፍ ኩባንያዎች ጋር ይያያዛል። ባለፈው ወር በኤሌክትሪክ የሚሠሩ መኪናዎች የሚያመርተው ተስላ የተሰኘው ድርጅት ባለቤት የሆነው ኢላን መስክ 1.5 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ቢትኮይን መግዛቱን ይፋ አድርጎ ነበር። አልፎም ድርጅቱ ተስላ ወደፊት ልክ እንደ ወረቀት ገንዘብ ለመገበያያነት እንደሚያውለው አስታውቆ ነበር። ቢትኮይን ምንድነው? ቢትኮይን ማለት በቀላል ቋንቋ፤ ዲጂታል ገንዘብ ወይም መገበያያ ነው ማለት ይቻላል። ይህ መገበያያ በኪሳችን ተሸክመን እንደምንዞረው የብር ኖት ወይም ሳንቲም ሳይሆን 'ኦንላይን' የሚቀመጥ ዲጂታል ገንዘብ ነው። ሌላው የቢትኮይንና የተቀሩት የክሪይፕቶከረንሲዎች ልዩ ባህሪ በመንግሥታት እና በባንኮች አለመታተማቸው እንዲሁም ቁጥጥር አለመደረጉ ነው። ቢትኮይን የሚፈጠረው 'ማይኒንግ' በሚባል ሂደት ነው። በመላው ዓለም በኔትወርክ በተሳሰሩ ኮምፒውተሮች ቁጥጥር ይደረግበታል። ለሚያቀርቡት ምርት እና አገልግሎት ቢትኮይንን በክፍያ መልክ የሚቀበሉ በርካቶች ድርጅቶች አሉ። ማይክሮሶፍት፣ የፈጣን ምግብ አቅራቢዎቹ ኬኤፍሲ እና ሰብዌይ፣ የጉዞ ወኪሉ ኤክስፔዲያን ከመሳሰሉ ባለብዙ ሚሊዮን ገንዘብ ኩባንያዎችን አንስቶ እስከ ሆቴሎች እና ካፊቴሪያዎች ቢትኮይንን በክፍያ መልክ ይቀበላሉ። ቢትኮይንን በመጠቀም የገዢው ማንነት ይፋ ሳይደረግ በየትኛውም ሰዓት እና በየትኛውም ስፍራ የቢትኮይን ዝውውር ማድረግ ይቻላል። ሕገ-ወጥ ቡድኖች የጦር መሳሪያዎች እና እጾችን ሊገዙ እና ሊሽጡ ይቻላሉ፣ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እና አሸባሪዎችን ለመደገፍ ያስችላል በማለት ቢትኮይንን ጨምሮ ሌሎች ክሪይፕቶከረንሲዎች ላይ ያላቸውን ስጋት የሚያነሱ በርካቶች ናቸው።
https://www.bbc.com/amharic/news-56391321
amh
business
ከኮሮናቫይረስ በኋላ ኢኮኖሚያቸው በቶሎ ሊያገግም የሚችል አምስት አገራት
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ አገራት ከበሽታ ጋር በሚያደርጉት ትግል በዓለም ምጣኔ ሃብት ላይ አለመረጋጋትን ፈጥሯል። ከዚህ አንጻር ከወረርሽኙ በኋላ የትኞቹ አገራት በተሻለ ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው እንደሚመለሱ ባለሙያዎች ለመገምገም ሞክረዋል። ይህንን በተሻለ ለመረዳት የኢንሹራንስ ኩባንያ የሆነው ኤፍ ኤም ግሎባል የ2019 ዓለም አገራት የምጣኔ ሃብት ፈተናን የመቋቋም አቅም አመላካች ደረጃን ተመለከትን። በዚህም አገራት ለቫይረሱ የሰጡትን የመጀመሪያ ምላሽ ከግምት በማስገባት ቀውሱን በተረጋጋ መንገድ የሚወጡበትን ሁኔታና የመቋቋም ዕድላቸው ተቃኝቷል። በደረጃ ጠቋሚው በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠችው ዴንማርክ ከቫይረሱ ስርጭት አንፃር ማኅበራዊ ርቀት እንዲተገበር በፍጥነት እርምጃ ወስዳለች። ጥቂት በበሽታው የተያዙ ሰዎች እንደተገኙ ነው ትምህርት ቤቶችን፣ አስፈላጊ ያልሆኑ ሥራዎችንና ድንበሯን በፍጥነት በመዝጋት ውሳኔዋ ውጤታማ መሆኑን ያረጋገጠችው። የዴንማርካዊያን ባህል የሆነው በመንግሥት ላይ እምነት ማሳደርና ለጋራ ዓላማ አብሮ የመቆም ፍላጎት በእርምጃዎቹ ውጤታማነት ላይ አውንታዊ ተጽዕኖ አሳድሯል። እናም ብዙ ሰዎች ለሕዝብ ጤና ሲሉ መስዋዕት የማድረግ የሞራል ግዴታ እንደሆነ ይሰማቸዋል። በዚህ ወቅት ዴንማርክ የሠራተኞችን ደመወዝ እስከ 90 በመቶ ድረስ ለመክፈል መወሰኗ እንደ ምሳሌ እንድትታይ አድርጓታል። ይህን ግን ቀላል አይደለም። እርምጃው ከጠቅላላው የአገሪቱ አጠቃላይ ምርት 13 በመቶውን ያህሉን ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ሲንጋፖር በጠንካራ ኢኮኖሚዋ፣ በአነስተኛ የፖለቲካ አደጋ፣ ጠንካራ መሠረተ ልማት እና ዝቅተኛ ሙስና በደረጃ ጠቋሚው 21ኛ እንድትሆን አድርጓታል። አገሪቱ ቫይረሱን ለመቆጣጠር በፍጥነት ከመንቀሳቀስ ባለፈ ስርጭቱም የተረጋጋ ነው። ቫይረሱን በመዋጋት ረገድ በግልጽነት በሚሰራው መንግሥት ላይ ሕዝቡ ከፍተኛ እምነት አለን። መንግሥት አንድ ውሳኔ ካስተላለፈ ሁሉም ተገዢ ሆኖ ተግባራዊ ያደርጋል። እንደ ትንሽ አገርነቷ የሲንጋፖር በጣም ስኬታማ መልሶ የማንሰራራት ውጤት ለማስመዝገብ በተቀረው ዓለም የማገገም ሂደት ላይ የተመሠረተ ነው። የዩናይትድ ስቴትስ ሰፊ ጂኦግራፊያዊ ቦታ መያዟ በደረጃ ጠቋሚው ላይ በሦስት የተከፈለች ሲሆን በአጠቃላይ ጥሩ ደረጃ ይዛለች። ቫይረሱ እንደ ኒው ዮርክ ባሉ ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ ፈታኝ ሲሆን፤ የሥራ አጥነት መጠኑም ታሪካዊ በሚባል ደረጃ ከፍ ብሏል። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ የተወሰደው አስገዳጅ የእንቅስቃሴ ገደብና ሌሎችም ለዚህ በምክንያትነት ተቀምጠዋል። ነገር ግን የአሜሪካ መንግሥት ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት የማነቃቂያ እርምጃዎችን በፍጥነት መውሰዱና ማኅበራዊ ርቀት መጠበቅ መተግበሩ ውጤት በማምጣት የቫይረሱ አጠቃላይ ተፅእኖን ሊቀንስና ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ማገገም ሊያስገኝ ያስችላል። 21 ትሪሊየን ዶላር የኢኮኖሚ ማበረታቻ ይፋ ያደረገችው አሜሪካ፤ ሩብ ያህሉን የዓለም አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርትን በመያዟ ወሳኝ የሚያደርጋት ሲሆን የዓለም ምጣኔ ሃብት ማገገም በአሜሪካ ውጤታማነት ላይ ጥገኛ እንደሆነ ይነገራል። በቅርብ በተደረጉት በኮርፖሬት አስተዳደር ማሻሻያዎች ምክንያት ሩዋንዳ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በደረጃ ጠቋሚዎች ውስጥ ትልቁን መሻሻል በማድረግ በዓለም ላይ የ77ኛ ደረጃን፣ ከአፍሪካ ደግሞ የአራተኛ ደረጃን ይዛለች። ከሁሉም በላይ ደግሞ በአውሮፓዊያኑ 2019 በጎረቤትዋ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ የተከሰተውን የኢቦላ ወረርሽኝ ድንበር ላይ በተሳካ ሁኔታ መቆጣጠር ከቻለች በኋላ እንደዚህ ዓይነቱን ቀውስ ለመከላከል በጥሩ ሁኔታ የተቀመጠች ይመስላል። ሁለን አቀፍ የጤና አጠባበቅ፣ የህክምና ቁሳቁስን በሚያደርሱ ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) እገዛ እና በድንበር ላይ የሙቀት ልየታ በማድረግ ሩዋንዳ በዚህ ቀውስ ወቅት ከሌሎች የአካባቢው አገራት አንጻር ጥንካሬዋን ጠብቃ ትቆያለች። ሩዋንዳ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ ዜጎች ቤት ለቤት ነፃ ምግብ እያሰራጨች የምትገኝ ሲሆን ይህም ከሰሃራ በታች ካሉ አገራት የመጀመሪያዋ ያደርጋታል። የቱሪዝም ዘርፉ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚገጥመው ይጠበቃል። ሩዋንዳም ለብዙ የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችና ኤግዚቢሽኖች ተወዳጅ መድረሻ ናት። አገሪቱ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ህይወታቸውን የሚያጡ ሰዎች ቁጥር አነስተኛ እንደሚሆኑ እና በፍጥነት ለማገገም የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንዳላት ይታመናል። ኒውዚላንድ በደረጃ ጠቋሚው የ12ኛ ቦታን ይዛለች። አገሪቱ ድንበሮችን ለዓለም አቀፍ ተጓዦች በመዝጋትና አስፈላጊ ያልሆኑ ሥራዎችን በፍጥነት በመዝጋት የቫይረሱ ስርጭትን ለመቆጣጠር መንቀሳቀስ ችላለች። ቱሪዝምና የወጪ ንግድ የምጣኔ ሃብቷ ዋና አካል ሲሆኑ ኒውዚላንድ በቅርብ ጊዜ ውስጥ አንዳንድ ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ያጋጥማታል ተብሎ ተሰግቷል። ነገር ግን ይህ የግድ መጥፎ ውጤት ላይኖረው ይችላል። ወረርሽኙ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳርፈው ጉዳት ቀላል የሚሆን ባይሆንም ኒወ ዚላንድ ግን ይህንን ተቋቁማ ለማገገም ብዙም እንደማትቸገር የምጣኔ ሃብት ሙያተኞች ያምናሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-52217125
amh
business
ላይቤሪያ 4 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ አሮጌ የገንዘብ ኖቶችን አቃጠለች
የላይቤሪያ ማዕከላዊ ባንክ ያረጁ እና የተበላሹ የገንዘብ ኖቶችን በአዲስ ለመተካት በሚል አራት ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ አሮጌ የገንዘብ ኖቶችን አቃጥሏል። በአገሬውም የመገበያያ ገንዘብም የተቃጠለው 600 ሚሊዮን የላይቤሪያ ዶላር ነው። የገንዘብ ኖቶቹ እንዲወገዱ የተደረጉትም መንግሥት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ አዳዲስ ኖቶችን ቢያትምም አሮጌዎቹ በስርጭት ላይ ይገኛሉ የሚለውን ስጋት ተከትሎ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በአውሮፓውያኑ 2018 ከፍተኛ መጠን ያለው የመንግሥት ገንዘብ ጠፍቷል የተባለ ሲሆን እንዲሁም ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚገመቱ አዲስ የታተሙ የላይቤሪያ የገንዘብ ኖቶች ጠፍተዋል የሚል ክስም እየቀረበ ይገኛል። ማዕከላዊ ባንኩ ይህንን አይቀበለውም የተባለው ገንዘብ በባንክ ካዝና ውስጥ መቀመጡን ገልጿል። የፕሬዚዳንት ጆርጅ ዊሃ መንግሥት አሮጌውን የላይቤሪያ ዶላር ለመተካት እና የሀገር ውስጥ ምንዛሬን ለማጠናከር በዚያው አመት ከሀገሪቱ የመጠባበቂያ ሂሳቦች ያወጣውን 25 ሚሊዮን ዶላር እስካሁን አልተካም። ይህንን ሊቀበሉ ያልቻሉ የተሟጋች ቡድኖች ማብራሪያ እና ተጠያቂነት እንዲኖር እየጠየቁ ነው። የላይቤሪያ ምጣኔ ኃብት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መንገዳገድ ቢያሳይም ነገር ግን ፕሬዚደንት ዊሃ በዚህ አይስማሙም በቅርቡ ለፓርላማ ባደረጉት አመታዊ ንግግር ኢኮኖሚው የተረጋጋና እያደገ ነው ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-60229480
amh
business
ምጣኔ ሐብት ፡ ከብር ለውጡ በኋላ የወርቅ ዋጋ ለምን ጨመረ?
ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ መደብሮች የወርቅ ዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን ነጋዴዎችና ገዢዎች ለቢቢሲ ገለጹ። ቢቢሲ በመሐል አዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ በሚገኙ የወርቅ መሸጫ መደብሮች ተዘዋውሮ እንደተረዳው የወርቅ መግዣ እና የመሸጫ ዋጋዎች ላይ ጭማሪዎች ታይተዋል። በተለይ ኢትዮጵያ የብር ኖቶቿን መቀየሯን ይፋ ካደረገችበት ከመስከረም ወር መጀመሪያ አንስቶ ጭማሪው በተለይ ከፍ ማለቱን በአዲስ አበባ ከተማ በወርቅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች እና ሠራተኞች ለቢቢሲ ተናግረዋል። ቢቢሲ አዲስ አበባ ውስጥ ዋነኛ የወርቅ መሸጫ መደብሮች በሚገኙበት በፒያሳ አካባቢ ቅኝት ባደረገበት በባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ 21 ካራት ወርቅ በግራም ከሦስት ሺህ ሰባት መቶ ብር እስከ አራት ሺህ ብር ይሸጣል መባሉን ከነጋዴዎቹ ለማረጋገጥ ችሏል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መስከረም አስራ ሰባት ቀን ያስቀመጠው የወርቅ የመግዣ ዋጋ ለሃያ አንድ ካራት 2012 ብር ከስድሳ አራት ሳንቲም ሲሆን፤ የጥራት ደረጃው ላቅ ላለው የሃያ አራት ካራት ወርቅ ደግሞ 2300 ብር ከአስራ ስድስት ሳንቲም ዋጋ ሆኖ ተቀምጦለታል። ባለፉት ጥቂት ወራት የወርቅ ዋጋ ጭማሪ ሲያሳይ መቆየቱን ቢቢሲ አግኝቶ ካናገራቸው የወርቅ መሸጫ መደብሮቹ ባለቤቶች እና ሠራተኞች ተረድቷል። ይሁንና የወርቅ ዋጋ ጭማሪው በተለይ የብር ኖቶች መቀየር ይፋ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ የበለጠ ከፍ ማለቱን በወርቅ ንግድ ላይ የተሰማሩት ነጋዴዎች ጨምረው ተናግረዋል። "ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ በግራም እስከ አምስት መቶ ብር ድረስ ጨምሯል" ስትል በአንድ የጌጣጌጥ መሸጫ መደብር ውስጥ የምትሰራ እንስት ለቢቢሲ ተናግራለች። ከግለሰቦች ቀለበት፣ ሃብል፣ የጆሮ ጉትቻና የመሳሰሉ የወርቅ ጌጣጌጦችን በመግዛት አትርፎ በመሸጥ የሚተዳደርና ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ አንድ ወጣት ደግሞ ጭማሪው ከሽያጭ በተጨማሪም በግዢም ላይ እየተስተዋለ እንደሚገኝ ተናግሯል።

"ከአንድ ወር በፊት አንድ ግራም የሃያ አንድ ካራት ወርቅ አንድ ሺህ ብር፤ ከፍ ሲል ደግሞ አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር ከሰው ላይ እገዛ ነበር" የሚለው ወጣት "ባለፈው አስራ አምስት ቀን ውስጥ ግን ብዙ ጭማሪ አሳይቷል" በማለት ባለፈው አርብ አንድ ግራም ወርቅ ሁለት ሺህ አንድ መቶ ሃምሳ ብር መግዛቱን ተናግሯል። ከሌላው ጊዜ በተለየ ወርቅ የሚገዙ ሰዎች ፍላጎት መጨመር ዋጋውን ማናሩን የሚናገረው ይህ ወጣት፤ ከብር ኖቶች ቅያሪው ጋር ተያይዞ የተከማቸ ገንዘብን ወደአስተማማኝ ውድ ዕቃ መቀየር የሚፈልጉ ሰዎች ሳይኖሩ እንደማይቀሩ ግምቱን አስቀምጧል። "የገንዘብ ኖቶች ለውጡ ሳይጠበቅ ዱብ ያለ በመሆኑ ውዥንብር እና እርግጠኛ ያለመሆን ስሜቶች ፈጥሯል" የሚሉት የምጣኔ ሐብት ጉዳዮች ተንታኙ አብዱልመናን መሃመድ ናቸው። ከዚህም ጋር ተያይዞ ገንዘብ በእጃቸው ላይ ያላቸው ሰዎች ደኅንነታቸው አስተማማኝ በሆኑ ንብረቶች ላይ ብራቸውን ለማዋል መፈለጋቸውን በወርቅ ግብይቱ ላይ የታየውን የዋጋ ለውጥ እንደምሳሌ በማንሳት ይገልፃሉ፤ "ይህም በእነዚህ ንብረቶች ዋጋ ላይ የመናር ምክንያት ሊሆን ይችላል" ባይ ናቸው። "መኪና እና ቤትን የመሳሰሉ ቋሚ ንብረቶችን እንዲሁም ወርቅን የመሳሰሉ ሌሎች ንብረቶች ላይ ገንዘብን ማዋል እንደአማራጭ ስለሚወሰድ ተፈላጊነታቸው መጨመሩ የሚጠበቅ ነው" ሲሉ ለቢቢሲ የተናገሩት አብዱልመናን፤ በሕገ ወጥ መልኩ የተገኘ ገንዘብን ለመሸሸግም ወርቅ ቀላል መንገድ ነው ይላሉ። 

"ስለዚህም የወርቅ የዋጋ ጭማሪን የፈጠረው የገንዘብ ኖት ለውጡ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም" ሲሉ እምነታቸውን ይገልጻሉ። ባለፈው ዓመት ወርሃ ግንቦት ላይ ብሔራዊ ባንክ ከ63 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት ወርቅ ወደ ገበያ መቅረቡን ገልፆ እንደነበር ይታወሳል። በወቅቱ የባንኩ ገዥ የሆኑት ይናገር ደሴ (ዶ/ር) ይህ የተጠቀሰው የወርቅ መጠን ከፍተኛ እንደነበርና ለመንፈቅ ዓመት ያህል የቁልቁል ይጓዝ የነበረው የወርቅ አቅርቦትን መጠን የቀየረ መሆኑን ተናግረው ነበር። ለወትሮውም ብሔራዊ ባንክ ወርቅን በሚገዛበት እና በነጋዴዎች ገበያ ላይ በሚሸጥበት ዋጋ መካከል ልዩነት መኖሩን የጠቀሱት ባለሞያው፤ ይህም ጌጣጌጥ ቤቶች ለንድፍ ሥራዎች፣ ለአገልግሎት ወጪዎች እና ለትርፍ በሚጨምሩት ገንዘብ ምክንያት ይመጣ እንደነበር ያስረዳሉ። በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት ወደ ውጭ በሚላክ ወርቅ መጠን ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ነበረው የሚሉት አብዱልመናን ይህንን ከግምንት ውስጥ በማስገባት በወርሃ ሐምሌ በብሔራዊ ባንክ የዋጋ ሽግሽግ ተደርጓል ብለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54333190
amh
business
የነዳጅ ድጎማ መነሳትና ሊያስከትል የሚችለው ጫና
የኢትዮጵያ መንግሥት የነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ ጭማሪ ማድረጉን አሳውቋል። በዚህም አስካሁን ከታዩት የዋጋ ጭማሪዎች ሁሉ ከፍተኛው እንደሆነ ተነግሯል። መንግሥት እንደሚለው የነዳጅ ምርቶችን ለመደጎም በወር በአማካይ 10 ቢሊዮን ብር ወጪ እንደሚደረግ በመግለጽ፣ በአሁኑ ወቅት 146 ቢሊየን 624 ሚሊየን 248 ሺህ 889 ብር የነዳጅ ድጎማ ዕዳ አለበት ተብሏል። ቀደም ሲል መንግሥት በየወሩ በሚያደርገው የነዳጅ ዋጋ ክለሳ ላይ ጭማሪው ከ10 በመቶ የሚበልጥ አልነበረም። አሁን ግን ይህንን የመንግሥት ድጎማውን ደረጃ በደረጃ ለማንሳት ባወጣ ዕቅድ መሠረት በቤንዚን ላይ ከ25 በመቶ በላይ፣ እንዲሁም በናፍጣ ላይ ከ35 በመቶ በላይ ጭማሪ ተደርጓል። መንግሥት እንደሚለው በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ዋጋ ቢሰላ የ1 ሊትር ናፍጣ የመሸጫ ዋጋ ብር 91 ከ23 ሳንቲም እና የቤንዚን ደግሞ በሊትር 82 ብር ከ07 ሳንቲም መሆን ነበረበት። በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ደግሞ ዋጋው ከዚህ ከፍ ይላል። ነገር ግን አሁንም መንግሥት 75 በመቶውን ጭማሪ እራሱ በመሸፈን 25 በመቶውን ብቻ ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ ማድረጉ ተገልጿል። የትኛውም የምርትና የአገለግሎት አቅርቦት በአንድም ሆነ በሌላ በኩል ከነዳጅ ዋጋ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ፣ ሕዝቡን ባስጨነቀው የኑሮ ውድነት ላይ ሌላ ጫናን ሊፈጥር ይችላል እየተባለ ነው። የአሁኑ የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ዋጋ ክለሳ እንዲሁም በቀጣይ የሚደረገው የዋጋ ማስተካከያ የሚያስከትለውን ውጤት በተመለከተ ከጥቂት ሳምንት በፊት ያዘጋጀነው ጥንቅር በዝርዝር ይዳስሳል። እነሆ . . . መንግሥት የውጭ ምንዛሬን በስስት ነው የሚያየው። እንደ ስእለት ልጅ። የዶላር ጥሪት እንደዋዛ አይቋጠርማ። በብዙ አበሳ፣ በብዙ የወጭ ንግድ፣ በብዙ ተጋድሎ ነው የሚመጣው። እንዲያም ኾኖ ጥሎበት ከአራት ቢሊዮን ዶላር አይዘልም። እሱም ቢኾን መጥቶ አይበረክትም፤ አብዛኛውን ነዳጅ ይጠጣዋል። ይሁን እንጂ፣ እስከዛሬ ድረስ ለነዳጅ የሚከፈለው ዶላር በወጭ ንግድ ከሚገኘው ዶላር በልጦ አያውቅም ነበር። አሁን ግን ታሪክ ተቀየረ፤ ነገሩ ከፋ። ይህ በይፋ የታወቀው ከኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ነው። ለ2015 ነዳጅ መግዣ የሚያስፈልግህ ስንት ነው ሲባል 5.6 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልገኛል አለ። እንዲህ ያለ አሃዝ ተሰምቶ አይታወቅም ነበር፤ ይህም የመርከብና የነዳጅ ዋጋ መናር ያመጣው ነው ይባላል። ታዲያ ይህ ገንዘብ ከየት ይመጣል? አንደኛ ከውጭ ንግድ እንዲህ ዓይነት ገቢ በጭራሽ ኖሮን አያውቅም። ቡናው፣ ሌጦው፣ ሰሊጡ ተረባርበው ከአገር ወጥተው እንኳ እንዲህ ዓይነት ገቢን አያመጡም። አሳሳቢው ይህ ብቻ በሆነ መልካም። ነዳጁ ከዚህም ከዚያም ዶላር ተፈልጎ ሊገዛ ይችላል። ከተገዛ በኋላም ግን መደጎም አለበት። ከተገዛበት ዋጋ በግማሽ ቀንሶ እንዲሸጥ መደጎም አለበት። ለዚህ ድጎማ ደግሞ አገሪቱ በወር በአማካይ 10 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋታል። አንድ የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ከሰሞኑ ለኢዜአ እንደተናገሩት ድጎማው መንግሥትን በጠቅላላው 132 ቢሊዮን ብር ለሚደርስ የዕዳ ክምችት ዳርጎታል። መንግሥት ይህን ህመሙን ለዓመታት ቻል አርጎት ቆየ። በኮቪድ ዘመን የዓለም የነዳጅ ዋጋ መሬት ሲነካ ህመሙን ለጊዜውም ቢኾን አስታግሶለት ይሆናል። ከኮቪድ በኋላ ግን የነዳጅ ዋጋ በድጋሚ ተቀጣጠለ። በእንቅርት ላይ. . . እንዲሉ የዩክሬን ጦርነት ተቀሰቀሰ። በዚህ ጊዜ በዓለም ነዳጅ ዋጋ ላይ ‘ሰደድ እሳት’ ተነሳ። ነዳጅ በዩክሬን ጦርነት ማግስት በበርሜል 140 ዶላር የደረሰበት ጊዜ ነበር። ይህ ዋጋ ሃብታም አገራትን ሳይቀር ሚዛናቸውን አስቷቸዋል። እዚህ ግባ የሚባል የተፈጥሮ ሃብት ለሌላት፣ የባሕር በር ለሌላትና ሰላም ለራቃት አገር ይህ ምን ማለት ሊሆን እንደሚችል ማብራሪያ አይሻውም። “የማይካደው ነገር በኢትዮጵያ የነዳጅ ዋጋ ከአንዳንድ የነዳጅ አምራች አገራት ጋር ሲነጻጸር እንኳ ርካሹ ነው” ይላሉ ተቀማጭነታቸውን በኩዌት ያደረጉት የምጣኔ ሃብት ተመራማሪው አየለ ገላን። “ከተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ጋር ቢነጻጸር እንኳ የኢትዮጵያ ነዳጅ ዋጋ በትንሹ አነስ ሳይል አይቀርም።” ይህን የሚሉት ድጎማው ምን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ለማስረዳት ነው። እኚህ ተመራማሪ ድጎማው ከፍተኛ መሆኑን ይግለጹ እንጂ መንግሥት ድጎማውን፣ በተለይ አሁን ላይ፣ ለማንሳት መወሰኑን በፍጹም አይስማሙም። “የነዳጅ ድጎማውን ማንሳት እየነደደ ያለ ቤት ላይ ነዳጅ ማርከፍከፍ ነው” ሲሉ የመንግሥትን ዕቅድ ይተቹታል። የነዳጅ ድጎማ በሂደት የተወለደ ሐሳብ ነው። የሕዝብ የመግዛት አቅም ሲያሽቆለቁል፣ የነዳጅ ዋጋ ሲያሻቅብ ድጎማ ተወለደ። ፖሊሲ ሳይሆን ሒደት ወለደው ማለቱ ይቀላል። “በመሠረቱ ይህ ድጎማ ሲጀመርም በፖሊሲ ተደግፎ አያውቅም” ይላሉ የነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር በቀለች ኩማ። “ነዳጅ እንዲሁ በቁጥጥር ሥርዓትና በዋጋ ማረጋጊያ ሰነድ የሚመራ እንጂ በፖሊሲ የተደገፈ የድጎማ ሥርዓት ኖሮት አያውቅም።” ለነዳጅ ሁነኛ መመሪያ የወጣለት ከሦስት ዐሥርታት በፊት ነው። በ1993 ዓ.ም. የነዳጅ ፈንድ ተመሠረተ። የነዳጅ ፈንድ ዋጋን የማረጋጋት ሚናን እንዲጫወት ነበር የታሰበው። ይህም ማለት መንግሥት ከዓለም ገበያ ነዳጅ ይገዛል። ከዚያ አገር ውስጥ ሲሸጥ ሽርፍራፊ ሳንቲሞችን ወደዚህ የነዳጅ ፈንድ እያስገባ ያጠራቅማል። ለምሳሌ ነዳጅ ተገዝቶ ተተምኖ ወደ ገበያ ሲወጣ 21 ብር ከ80 ሳንቲም ቢሆን መንግሥት 22 ብር ይሸጠውና 20 ሳንቲሟ ተጠራቅማ ለሚቀጥለው ድጎማ ትውላለች። በዚህ አሠራር የተወሰኑ ቢሊዮን ብሮች በዚህ የነዳጅ ፈንድ እየተጠራቀሙ ቆዩ። ኾኖም ነዳጅ የሚጨምርበት ፍጥነትና ይህ ፈንድ የሚለቃቅማቸው ሳንቲሞች ሊገናኙ አልቻሉም። የእርምጃና የ100 ሜትር ሩጫ ተወዳዳሪዎችን በአንድ መም የማሮጥ ነገር መሰለ። ይህ ሁኔታ በተለይ ከ2003 ዓ.ም. ወዲህ ጭራሽ ሊገናኝ አልቻለም። ከዚህ ወዲያ ነበር ከመንግሥት ካዝና ቢሊዮን ብሮች እየወጡ ነዳጅን በቀጥታ መደጎም የተያዘው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የነዳጅ ድጎማው በየወሩ እየተከለሰ ዋጋው ከዓለም ዋጋ ከፍና ዝቅ ጋር እየተነጻጸረ እንዲስተካከል ይደረግ ነበር። “ይሁንና ከ2009 ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ የተከለሰው ለ5 ጊዜ ብቻ ነው’’ ይላሉ በቀለች ጫናውን ምን ያህል መንግሥት ተሸክሞት እንደቆየ ለቢቢሲ ሲያስረዱ። ይህ ግን አሁን ካለው ዓለም አቀፋዊና አገራዊ ሁኔታ አንጻር የሚያስቀጥል አልሆነም። በዚህ የተነሳ አገሪቱ ከነዳጅ ጋር በተያያዘ በቀጣይ አካሄዷን ለማስተካከል ተገዳለች። የዓለም ዋጋን ያንጸባረቀ ዋጋን ከሕዝብ ጋር ለመጋራት ቆርጣለች። ሕመሜን አስታሙልኝ ነው ነገሩ። በዚህ ጊዜ ለምን እዚህ ውሳኔ ላይ ተደረሰ? ስንል የነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስትር መሥሪያ ቤትን ጠይቀናል። “በዚህ ኑሮ እሳት በሆነበት ጊዜ መሆኑ አደጋ የለውም ወይ?’’ ስንል የምጣኔ ሃብት አዋቂዎችን አወያይተናል። በቀለች ኩማ ድጎማውን በዚህ ወቅት ማንሳቱን የሚመለከቱት በተለየ መነጽር ነው። ነገሩን መንግሥት ላይ እያሳደረ ካለው የዕዳ ጫና ብርቱነት፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ መቀጣጠል እና ከሕገ ወጥ ንግድ መበራከት አንጻር መመልከትን ይመርጣሉ። “ድጎማው ከጥቅሙ ጉዳቱ በዛ” የሚሉት በቀለች በዋቢነት የሚያነሱት ሕገ ወጥ የኮንትሮባንድ ነዳጅ ንግድ መበራከትን ነው። ይህ አየር በአየር ሽያጭ አገሪቱን ለከፍተኛ ዕዳ ዳረጋት። በውድ የውጭ ምንዛሬ የሚደጎመው ነዳጅ እያከበረ ያለው ኮንትሮባንዲስቶችን ነው፤ ባለጸጎችን ነው፤ ሲሉ ያስረዳሉ። እርግጥ ሕዝብ ይደጉማል የተባለ ውድ ነዳጅ ማደያ ሳይደርስ ጎረቤት አገር ይቸበቸብ እንደነበር አገር ያወቀው፣ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። ቢሆንም ግን በዚህ ወቅት ቁጥጥርን ማጥበቅ እንጂ ድጎማን ማንሳት ያስኬዳል? ይህ ብቻ ግን አይደለም ድጎማ የማንሳቱ መንስኤ ይላሉ በቀለች፣ “ድጎማው በፖሊሲም ያልተደገፈ ከመሆኑ የተነሳ ጥቅል ድጎማ ነው የነበረው።’’ እርግጥ ድጎማው የጅምላ ድጎማ መሆኑን የምጣኔ ሃብት ባለሙያው አቶ ዋሲሁን በላይም አጥብቀው የሚኮንኑት ጉዳይ ነው። ጥቅል ድጎማ ሲባል ምን ማለት ነው? ሃብታምና ድሃን፣ ቤንትሌና ሃይገርን፣ ሊሞዚን፣ መርሴዲስን እና ‘ቅጥቅጥ አይሱዙን’ በእኩል መደጎም ማለት ነው። ኢኮኖሚስቱ አቶ ዋሲሁን፣ “መንግሥት የኤምባሲ መኪናንም የከተማ አውቶቡስንም በአንድ ሲደጉም ነው የኖረው” የሚሉት ለዚሁ ነው። የእስከዛሬው የነዳጅ ድጎማ ከመሠረታዊ የድጎማ (subsidy) ጽንሰ ሐሳብ ጋር የሚጻረር እንደነበር ቢቢሲ ያነጋገራቸው የምጣኔ ሃብት አዋቂዎች የሚስማሙበት ነጥብ ነው። ድጎማ በባህሪው የአጭር ጊዜ መፍትሄ ነው። የአጭር ጊዜ መሆን ብቻም ሳይሆን ማሳካት የፈለገው ግብ በውል ተለይቶ መቀመጥ አለበት። መቀመጥ ብቻም ሳይሆን ዓላማውን አሳክቷል ወይ ተብሎ መፈተሽ አለበት። ሁሉም ባለሙያዎች የሚሉት ይህንን ነው። በዚህ ሚዛን ላይ ሲቀመጥ ድጎማው ውሉን የሳተ ነበር ብለው ያምናሉ አቶ ዋሲሁን። እሳቸው መደጎም ያለበት የሚሉት በዋናነት ምርትን ማሳደግ የሚችለውን ዘርፍ ነው። ነዳጅ በኢትዮጵያ ሁለት ሚና አለው፤ አንዱ ለፋብሪካዎች የኃይል ምንጭ መሆን ነው፤ ሌላው ትራንስፖርት ነው። በኢትዮጵያ ብዙ አምራች ተቋማት የማምረት አቅማቸው 40 ከመቶ አይሞላም። አንዱ ምክንያታቸው ታዲያ በቂ ኃይል ስለማያገኙ ነው። ስለዚህ መብራት በጠፋ ጊዜ ጄኔሬተር ይለኩሳሉ። ጄኔሬተር ነዳጅ ይጠጣል። ለእነዚህ አምራቾች ቢቻል አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ ወይም መደጎም ምርታማነትን ይጨምራል። የኤምባሲ መኪናን ነዳጅ መደጎም ግን ምርታማነት አይጨምርም። ነዳጅን የምትደጉመው ኢትዮጵያ ብቻ ናት? ጥቂት የማይባሉ አገራት ነዳጅን ይደጉማሉ። ካልደጎሙም የኅብረተሰቡ የመግዛት አቅማቸው ከፍ ያለ ሊሆን ይችላል። ታዲያ ድጎማ ግቡ ምንድነው? “ማክሮ ኢኮኖሚ እንዳይዛባ፣ ምርትና ምርታማነት እንዳይጎዳ፣ ባለመደጎም የሚመጣ ውስብስብ ኢኮኖሚያዊ መዘዝ ሲኖር ድጎማ አግባብ ሆኖ ሊታይ ይችላል’’ ይላሉ አቶ ዋሲሁን። “ይሄ መንግሥት ግን ከአቅሙ በላይ ብዙ ነገር የሚደጉም መንግሥት ነው፤ ክፋቱ ደግሞ መደጎም የሌለበትንም ይደጉም ነበር።” ለነዳጅ ድጎማ የሚወጣው ከፍተኛ ገንዘብ የኢትዮጵያ መንግሥትን ጀርባው መጉበጡን የምጣኔ ሃብት አዋቂው አቶ አየለ ገላን ያምናሉ። ነዳጅ በኢትዮጰያ የሚሸጥበት ዋጋ አገሪቱን ነዳጅ አምራች እንዳስመሰላትም አልሸሸጉም። የእርሳቸው ልዩነት የሚነሳው ድጎማን በማንሳት ቅድመ ሁኔታዎች ላይ ነው። “የኢትዮጵያ ሸማች የመግዛት አቅም ደቃቃ ነው። ከሕዝብ አንጻር ስናየው እንዲያውም ድጎማው በቂ አልነበረም ልንል እንችላለን’’ ካሉ በኋላ መንግሥት ከድጎማ በፊት መሥራት የነበረበትን የቤት ሥራ አልሠራም ሲሉ ሂደቱን ክፉኛ ይተቻሉ። እነዚህ የቤት ሥራዎች ምን ነበሩ? “አንደኛ ኢኮኖሚው ተመሰቃቅሏል። ምርት አላደገም፣ የሕዝብ የመግዛት አቅም አልጨመረም። ጥቃቅን ኢንዱስትሪዎች በእግራቸው እንዲቆሙ አልተደረገም። የሕዝብ ደኅንነት አልተጠበቀም።...” መንግሥት እነዚህን መልከ ብዙ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ምስቅሎሽን ሳያስተካክል፤ ኢኮኖሚውን ጠንካራ መሠረት ላይ ሳያስቀምጥ ድጎማ ማንሳት (የእርሳቸው ቃል ለመጠቀም) “ኃላፊነት የጎደለው ውሳኔ ነው።’’ አቶ ዋሲሁን ከድጎማው መነሳት ማግስት ምን ሊፈጠር ይችላል የሚለውን ትንቢታዊ ጥያቄ በቀጥታ መጋፈጥን የመረጡ አይመስልም። ነገር ግን የመንግሥት ድጎማን የማንሳት ውሳኔን ከጥንቃቄ ጋር በአውንታዊ መልኩ ይረዱታል። “የድጎማ ሥርዓቱ (በአንድ ጥናት ላይ እንደታየው) 70 ከመቶ የሚሆነውን ድሃና 30 ከመቶ የሚሆነውን ሃብታም ነው ሲደጉም የኖረው። ስለዚህ ጤናማ ድጎማ አልበረም። ለድሃ የታሰበው ድጎማ ሃብታም ሲደጉም ነው የኖረው።’’ ስለዚህ በእሳቸው ዕይታ ከዚህ ወዲህ ድጎማው ለታሰበለት ሕዝብ ብቻ ስለመድረሱ እርግጠኛ መሆን ያሻል። “ድጎማ ዘዴኛና መለኛ (ታክቲካል) ካልሆነ ውሉን ሳተ ማለት ነው። ድሃው ነው የሚደጎመው ከተባለ ድጎማው ድሃው ጋር መድረሱን ማረጋገጥ ያስፈልጋል’’ የሚሉት አቶ ዋሲሁን ነዳጅ በሞያሌ እየወጣ ሲሸጥ፣ አውቶቡስና የኤምባሲ መኪና አብሮ ተሰልፎ በአንድ የዋጋ ተመን ነዳጅ ሲቀዳ ድጎማ ግብ እንደተሳተ ምልክቶች ሆነው ይታያሉ። በዚህ ሐሳብ የነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስትርም ባልደረባም ይስማማሉ። “የሚደጎምና የማይደጎምን በጥናት መለየት ያስፈለገውም ለዚሁ ነው ይላሉ” በቀለች ኩማ። ከድጎማ የተረፈው ገንዘብ ምን ላይ ይውል ይሆን? አቶ ዋሲሁን ከድጎማ መነሳቱ ይልቅ ከድጎማ የዳነው ገንዘብ የት እንደሚውል በእጅጉ ያሳስባቸዋል። “አሁን ያለው ኢኮኖሚ በግጭትና በጦርነት የቆሰለ ኢኮኖሚ ነው። ከፍተኛ ወጪዎች ይጠብቁታል። በወጪና ገቢ ልዩነት ማጥበብ ላይ ካልተሠራ የከፋ ሀኔታ ሊመጣ ይችላል” ይላሉ። ከፍተኛ የበጀት ጉድለት ደግሞ ወደ ገንዘብ ማተም ስለሚወስድ ለበለጠ የበጀት ቅርቃርና ኑሮ ውድነት ሊወስድ ይችላል የሚል ፍርሃት አላቸው። ስለዚህ መንግሥት ከድጎማ ወጪ ያዳነውን ገንዘብ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ሊያውለው ይገባል። “መንግሥት ማኅበረሰቡ ወጪውን እንዲጋራው መሞከሩ መጥፎ ነው ወይ? ብትለኝ እኔ መጥፎ ነው ብዬ አላስብም። ነገር ግን ገንዘቡ ለአበልና ለድግስ ከዋለ ነው ችግሩ።” አሁን በዓለም ገበያ ሰማይ የነካውን ነዳጅ መንግሥት በግማሽ ቀንሶ ነው ለሕዝብ የሚያደርሰው። ቀድም ባሉ ዓመታት በሊትር 5 እና 6 ብር ነበር የሚደጉመው። አሁን ያን ለማድረግ የሚያስችል አቅምን አጥቷል። በውስጣዊና ውጫዊ ዝርዝር ምክንያቶች። ምክንያቶቹን አቆይተን ነገር ግን መንግሥት በዚህ ድጎማ አሠራር ከሐምሌ ወዲያ መሻገር ይችል ነበር ወይ ብለን እንጠይቅ። በሌላ አነጋገር መንግሥት ደግ ሆኖ ልደጉም ቢልስ ይችላል ወይ? የብዙ ኢኮኖሚስቶች ምላሽ በአጭሩ ሲቀመጥ “አይችልም” የሚል ነው። ምክንያቱም፣ “...ሚያዝያ ወር ላይ ብቻ ዕዳው 124 ቢሊዮን ደርሰ” ይላሉ የነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባልደረባ በቀለች ኩማ። ምክንያቱም፣ “...561 ቢሊዮን ብር ይዞ የተነሳ ኢኮኖሚ ነው ያለው። በዚህ ዓመት በዘጠኝ ወር የተሰበሰበው 290 ቢሊዮን ብር ነው። ልዩነቱ ሰፊ ነው። ይህን የበጀት ጉድለት ይዞ ብዙ መጓዝ አይቻልም” ይላሉ አቶ ዋሲሁን። ይሁንና ነዳጅ ድጎማው የኑሮ ውድነቱን እንዳያባብስ ምን ማድረግ ይቻላል? አቶ ዋሲሁን የነዳጅ ድጎማው በኑሮ መወደድ ላይ የሚያስከትለውን ጣጣ ማንም አያጣውም ይላሉ። ነገር ግን ያን ማስቀረት በምጣኔ ሃብት ሳይንስ የሚቻልበትን ዕድል አይታያቸውም። “የትኛውም ፖሊሲ ሁሉን አስታርቆ መሄድ አይችልም። ሁሉንም ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ አስደስቶ የሚያቆይ የኢኮኖሚ ውሳኔ በምድር ላይ የለም።’’ ይልቅ በቀጥታ በድጎማ መነሳት ብቻ የሚፈጠር ዋጋ ንረት ሳይሆን ድጎማ የመነሳቱ ወሬ በራሱ የሚፈጥረው የገበያ ትኩሳት ይበልጥ ያሳስባቸዋል። “እኛ አገር ነጋዴው በአጋጣሚው እንዴት በአቋራጭ ልክበር ነው የሚለው፤ የድጎማውን ጭማሪ ብቻ ደምሮ ይሸጣል ብዬ አልገምትም” ይላሉ አቶ አየለ ገላን። ከሐምሌ ወዲህ የሕዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪ ማደያ ገብቶ ነዳጅ ሲቀዳ ጂፒኤስ ተገጥሞለት ነው። ነዳጅ አቅራቢዎች ለማደያዎች ደረሰኝ ይሰጣሉ። ባለታክሲው በታሪፍ የተቀመጠውን ዋጋ ከፍሎ ይሄዳል። ማደያው በደረሰኝ ቀሪውን ያወራርዳል። ይህ አሠራር በመተግበሪያ የሚሠሩት ታክሲዎችን አይጨምርም። የመንግሥት ሰርቪሶችንም አይጨምርም። “ከዚህ በኋላ በየትኛውም ማደያ ነዳጅ ሲራገፍ የኛ ተቆጣጣሪዎች በያንዳንዱ ማደያ ተገኝተው ነው” ይላሉ የነዳጅና ኢንርጂ ሚኒስቴር ባልደረባ በቀለች ኩማ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ሕዝብን ለማረጋጋት ይመስላል መንግሥት ድጎማ ማንሳቱ በኑሮ ላይ አንዳችም ጫናን አይፈጥርም የሚሉ ድምጾች እየተስተጋቡ ነው። ይህ ለምጣኔ ሃብት አዋቂዎችም ሆነ ለሰፊው ሕዝብ እምብዛምም ስሜት የሚሰጥ አይደለም። በቀለች ኩማ ግን “ድጎማ መነሳቱ በቀጥታ የሚባለውን ያህል የዋጋ ንረት አያስከትልም፤ ይህ በጥናት የተረጋገጠ ነው” ሲሉ የነገሩን ሀቅነት ይሞግታሉ። እሳቸው ጥናቱን ለቢቢሲ ለማጋራት ባይፈቅዱም የነዳጅ ድጎማ መነሳት በቀጥታ የሚያስከትለው የዋጋ ንረት እዚህ ግባ የሚባል እንዳይደለ ይጠቅሳሉ። “...ድጎማው ሲነሳ በእያንዳንዱ ሸቀጥ ላይ የሚያመጣው ጫና በሳንቲም ቤት እንደሆነ ተደርሶበታል” ይላሉ። ይሁንና ምጣኔ ሃብት ሙያተኞቹ አቶ ዋሲሁን እና አቶ አየለ ግን በዚህ ብዙም አይስማሙም። አንዱ ምክንያታቸው በኢትዮጵያ የንግድ ዘይቤ እንደታየው ዋጋ የሚወሰነው በቀጥታ በሚመጣ ጭማሪ ሳይሆን ገና በሥነ ልቦና በሚፈጠር ፍርሃትም ጭምር ስለሆነ ነው። ለብዙዎች አዲስ ዜና የሆነው ደግሞ የታለመላቸው የሚባሉት ተደጓሚዎችም ቢሆኑ ድጎማቸው ጊዜያዊ መሆኑ ነው። በቀለች ሁሉም ታክሲዎችና የሕዝብ አውቶቡሶች ሳይቀሩ በሂደት ከድጎማ ሥርዓት እንደሚወጡ ለቢቢሲ ተናግረዋል። “በአምስት ዓመት ውስጥ ከድጎማው ሙሉ በሙሉ ይወጣሉ። በየሦስት ወሩም ዋጋ ክለሳ ይደረግባቸዋል።” የሰዉ ስሜቱ የተዘበራረቀ ነው። ኑሮ መንደድ ያለበትን ያህል በመንደዱ ከዚህ በላይ ምን ሊመጣ? የሚል ስሜት ያላቸው አሉ። ነገን በፍርሃትና በሰቀቀን የሚጠብቁም አሉ። ድጎማው ሐምሌ ላይ ሲነሳ የዋጋ ጭማሪው እንደ ሐምሌ ዝናብ ዶፍ ሆኖ ሊወርድ የተሰናዳ ይመስላል። ሐምሌ አሳሳቢ ሆኖ የሚታየው ታዲያ ለተርታው ሕዝብ ብቻ አይደለም። ለጎምቱ ኢኮኖሚስቶችም ጭምር እንጂ። መቀመጫቸውን ኩዌት ያደረጉት አቶ አየለ ገላን፤ “በዚህ ጊዜ ድጎማን ማንሳት ለእኔ ስሜት የሚሰጥ አይደለም፤ ዚምባብዌ ወደ ገጠማት ኢኮኖሚ ሁኔታ የመንደርደር ያህል አድርጌ ነው የምመለከተው” ይላሉ። ምርትና ምርታማነት ፈቅ ሳይል፣ መሠረታዊ የኑሮ ደረጃ ኢምንት ሳይጨምር የገጠሩ የግብርና ኢኮኖሚ ሳያድግ አሁን ባለው ኢኮኖሚ ላይ የነዳጅ ድጎማን ማንሳት ከድጡ ወደ ማጡ ነው፤ ለእርሳቸው። በቀለች ኩማ ግን የተቀናጀ ቁጥጥርና በቂ ግንዛቤ ለኅብረተሰቡ ከደረሰ የከፋ ሁኔታ አይመጣም ባይ ናቸው። አቶ አየለ በፍጹም በዚህ አይስማሙም፤ በዚህ እሳት በሆነ ኑሮ ይህን መሠረታዊ  የነዳጅ ድጎማን ማንሳት “እየነደደ ባለ እሳት ላይ ነዳጅ ማርከፍከፍ ነው” ይሉታል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cyd3yjlr0rgo
amh
business
ሱዊዝ ቦይ በመዘጋቱ በየቀኑ የ9.6 ቢሊዮን ዶላር ምርት መተላለፍ አልቻለም
የግብጹ ሱዊዝ የባሕር ላይ ማቋረጫ ቦይ በመዘጋቱ በየቀኑ 9.6 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶች መተላለፍ እንዳልቻሉ ተገለጸ። በሱዊዝ መተላለፊያ ላይ አንድ ግዙፍ የጭነት መርከብ ባሕሩን ዘግቶ ከማክሰኞ ዕለት ጀምሮ በመቆሙ ምክንያት እንቅስቃሴ መገታቱ ይታወሳል። ሎይድስ ሊስት የተባለው የመርከብ ጉዞ ድርጅት እንደሚለው፤ በቀን ውስጥ ከምዕራብ አቅጣጫ ይመጡ የነበሩ 5.1 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶች መጓጓዝ አልቻሉም። ከምሥራቅ አቅጣጫ ይመጡ የነበሩና የተስተጓጎሉ ምርቶች ደግሞ 4.5 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ናቸው። የባሕሩን መተላለፊያ የዘጋው መርከብ እንቅስቃሴ እንዲጀምር ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ቢሆንም ሳምንታት ሊወስድ እንደሚችል ባለሙያዎች ተናግረዋል። በታይዋኑ ኤቨርግሪን ማሪን ሥር ያለው ኤቨር ጊቭን መርከብ በዓለም ትልቁ ኮንቴነር ጫኝ ሲሆን፤ 200,000 ቶን የሚመዝን እንዲሁም 20,000 ኮንቴነር ማጓጓዝ የሚችል ነው። መርከቡ በመቆሙ ሳቢያ ሌሎች መርከቦች ለቀናት መተላለፍ አልቻሉም። የባሕር ላይ ጉዞ አማካሪ ድርጅት ባለቤት ጆን ሞንሮይ ብዙ ወደቦች ላይ የሚገኙና መጓጓዝ ያልቻሉ ኮንቴነሮች እንዳሉ ይናገራል። መተላለፊያው በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ መካከል ምርቶች የሚተላለፉበት ሲሆን፤ የጦፈ ንግድ የሚካሄድበት መስመር ነው። ከመላው ዓለም የባሕር ንግድም 12 በመቶው የሚያልፈውም በዚሁ የግብጽ የባሕር ላይ ማቋረጫ መስመር በኩል ነው። ሎይድስ ሊስት ባወጣው አሃዝ መሠረት፤ በአሁኑ ጊዜ 160 መርከቦች በሱዊዝ ቦይ በኩል ለማለፍ እየጠበቁ ነው። ከእነዚህ መካከል 41 የሚሆኑት የተለያዩ ምርቶች ሲይዙ 24 ደግሞ ነዳጅ ጫኝ ናቸው። ቢአይኤምሲኦ የተባለው ዓለም አቀፍ የመርከበኞች ማኅበር እንደሚለው መተላለፊያው ተዘግቶ ከቆየ የምርት አቅርቦት ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩ አይቀርም። የሎጂስቲክስ ተቋሙ ኦኤል ዩኤስኤ ፕሬዘዳንት አለን ባይር "በእያንዳንዱ ቀን ያልተጓጓዙ ምርቶችን ለማሳለፍ ተጨማሪ ሁለት ቀናት ይጠይቃል" ብለዋል። እስካሁን ለሦስት ቀናት መተላለፍ ያልቻሉትን ምርቶች ለማጓጓዝ ስድስት ቀናት ገደማ ሊያስፈልግ እንደሚችልም ግምታቸውን አስቀምጠዋል። መተላለፊያው እስኪከፈት ድረስ ቀናት ወይም ሳምንታት ሊወስድ እንደሚችል የተጠቆመ ሲሆን፤ ይህ ደግሞ በመላው ዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ጫና ያሳድራል። የዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ይህ የግብጽ የባሕር ላይ መተላለፊያ ከመዘጋቱ በፊት በኮቪድ-19 ምክንያት መቀዛቀዝ አጋትሞት ነበር። አለን እንደሚሉት፤ መርከቦች ሌላ አማራጭ የጉዞ መስምር ከፈለጉ በምዕራብ አፍሪካ በኩል በመዞር ጉዟቸውን ሊቀጥሉ ብችሉም ይህ ጉዞ ግን ከሰባት እስከ ዘጠኝ ቀናት ሊፈጅ ይችላል። አንዳንድ ተቋሞች መተላለፍ ባልቻሉ ምርቶቻቸው ምትክ ሌሎች ምርቶችን በአውሮፕላን ወይም በባቡር መላክን እንደ አማራጭ ሊወስዱ ይችላሉ። እስካሁን ድረስ ሜርስክ እና ሀፓግ ሎይድ የተባሉ ተቋሞች ከሱዩዝ መተላለፊያ መስመር ውጪ ያሉ አማራጮችን እንደሚጠቀሙ አስታውቀዋል። የግብጹ የሱዊዝ መተላለፊያ ባለሥልጣን ባሕሩን የዘጋውን መርከብ ለማስነሳት የቻለውን ሁሉ እየሞከረ እንደሆነ አስታውቋል።
https://www.bbc.com/amharic/56534020
amh
End of preview. Expand in Data Studio

MasakhaNEWSClassification

An MTEB dataset
Massive Text Embedding Benchmark

MasakhaNEWS is the largest publicly available dataset for news topic classification in 16 languages widely spoken in Africa. The train/validation/test sets are available for all the 16 languages.

Task category t2c
Domains News, Written
Reference https://arxiv.org/abs/2304.09972

How to evaluate on this task

You can evaluate an embedding model on this dataset using the following code:

import mteb

task = mteb.get_tasks(["MasakhaNEWSClassification"])
evaluator = mteb.MTEB(task)

model = mteb.get_model(YOUR_MODEL)
evaluator.run(model)

To learn more about how to run models on mteb task check out the GitHub repitory.

Citation

If you use this dataset, please cite the dataset as well as mteb, as this dataset likely includes additional processing as a part of the MMTEB Contribution.


@misc{adelani2023masakhanews,
  archiveprefix = {arXiv},
  author = {David Ifeoluwa Adelani and Marek Masiak and Israel Abebe Azime and Jesujoba Alabi and Atnafu Lambebo Tonja and Christine Mwase and Odunayo Ogundepo and Bonaventure F. P. Dossou and Akintunde Oladipo and Doreen Nixdorf and Chris Chinenye Emezue and sana al-azzawi and Blessing Sibanda and Davis David and Lolwethu Ndolela and Jonathan Mukiibi and Tunde Ajayi and Tatiana Moteu and Brian Odhiambo and Abraham Owodunni and Nnaemeka Obiefuna and Muhidin Mohamed and Shamsuddeen Hassan Muhammad and Teshome Mulugeta Ababu and Saheed Abdullahi Salahudeen and Mesay Gemeda Yigezu and Tajuddeen Gwadabe and Idris Abdulmumin and Mahlet Taye and Oluwabusayo Awoyomi and Iyanuoluwa Shode and Tolulope Adelani and Habiba Abdulganiyu and Abdul-Hakeem Omotayo and Adetola Adeeko and Abeeb Afolabi and Anuoluwapo Aremu and Olanrewaju Samuel and Clemencia Siro and Wangari Kimotho and Onyekachi Ogbu and Chinedu Mbonu and Chiamaka Chukwuneke and Samuel Fanijo and Jessica Ojo and Oyinkansola Awosan and Tadesse Kebede and Toadoum Sari Sakayo and Pamela Nyatsine and Freedmore Sidume and Oreen Yousuf and Mardiyyah Oduwole and Tshinu Tshinu and Ussen Kimanuka and Thina Diko and Siyanda Nxakama and Sinodos Nigusse and Abdulmejid Johar and Shafie Mohamed and Fuad Mire Hassan and Moges Ahmed Mehamed and Evrard Ngabire and Jules Jules and Ivan Ssenkungu and Pontus Stenetorp},
  eprint = {2304.09972},
  primaryclass = {cs.CL},
  title = {MasakhaNEWS: News Topic Classification for African languages},
  year = {2023},
}


@article{enevoldsen2025mmtebmassivemultilingualtext,
  title={MMTEB: Massive Multilingual Text Embedding Benchmark},
  author={Kenneth Enevoldsen and Isaac Chung and Imene Kerboua and Márton Kardos and Ashwin Mathur and David Stap and Jay Gala and Wissam Siblini and Dominik Krzemiński and Genta Indra Winata and Saba Sturua and Saiteja Utpala and Mathieu Ciancone and Marion Schaeffer and Gabriel Sequeira and Diganta Misra and Shreeya Dhakal and Jonathan Rystrøm and Roman Solomatin and Ömer Çağatan and Akash Kundu and Martin Bernstorff and Shitao Xiao and Akshita Sukhlecha and Bhavish Pahwa and Rafał Poświata and Kranthi Kiran GV and Shawon Ashraf and Daniel Auras and Björn Plüster and Jan Philipp Harries and Loïc Magne and Isabelle Mohr and Mariya Hendriksen and Dawei Zhu and Hippolyte Gisserot-Boukhlef and Tom Aarsen and Jan Kostkan and Konrad Wojtasik and Taemin Lee and Marek Šuppa and Crystina Zhang and Roberta Rocca and Mohammed Hamdy and Andrianos Michail and John Yang and Manuel Faysse and Aleksei Vatolin and Nandan Thakur and Manan Dey and Dipam Vasani and Pranjal Chitale and Simone Tedeschi and Nguyen Tai and Artem Snegirev and Michael Günther and Mengzhou Xia and Weijia Shi and Xing Han Lù and Jordan Clive and Gayatri Krishnakumar and Anna Maksimova and Silvan Wehrli and Maria Tikhonova and Henil Panchal and Aleksandr Abramov and Malte Ostendorff and Zheng Liu and Simon Clematide and Lester James Miranda and Alena Fenogenova and Guangyu Song and Ruqiya Bin Safi and Wen-Ding Li and Alessia Borghini and Federico Cassano and Hongjin Su and Jimmy Lin and Howard Yen and Lasse Hansen and Sara Hooker and Chenghao Xiao and Vaibhav Adlakha and Orion Weller and Siva Reddy and Niklas Muennighoff},
  publisher = {arXiv},
  journal={arXiv preprint arXiv:2502.13595},
  year={2025},
  url={https://arxiv.org/abs/2502.13595},
  doi = {10.48550/arXiv.2502.13595},
}

@article{muennighoff2022mteb,
  author = {Muennighoff, Niklas and Tazi, Nouamane and Magne, Lo{\"\i}c and Reimers, Nils},
  title = {MTEB: Massive Text Embedding Benchmark},
  publisher = {arXiv},
  journal={arXiv preprint arXiv:2210.07316},
  year = {2022}
  url = {https://arxiv.org/abs/2210.07316},
  doi = {10.48550/ARXIV.2210.07316},
}

Dataset Statistics

Dataset Statistics

The following code contains the descriptive statistics from the task. These can also be obtained using:

import mteb

task = mteb.get_task("MasakhaNEWSClassification")

desc_stats = task.metadata.descriptive_stats
{
    "test": {
        "num_samples": 6242,
        "number_of_characters": 16946423,
        "number_texts_intersect_with_train": 66,
        "min_text_length": 1,
        "average_text_length": 2714.9027555270745,
        "max_text_length": 26369,
        "unique_text": 6234,
        "unique_labels": 7,
        "labels": {
            "business": {
                "count": 785
            },
            "health": {
                "count": 1258
            },
            "politics": {
                "count": 1589
            },
            "sports": {
                "count": 1265
            },
            "entertainment": {
                "count": 762
            },
            "technology": {
                "count": 297
            },
            "religion": {
                "count": 286
            }
        }
    },
    "train": {
        "num_samples": 21734,
        "number_of_characters": 58485151,
        "number_texts_intersect_with_train": null,
        "min_text_length": 1,
        "average_text_length": 2690.952010674519,
        "max_text_length": 46502,
        "unique_text": 21591,
        "unique_labels": 7,
        "labels": {
            "sports": {
                "count": 4401
            },
            "business": {
                "count": 2725
            },
            "health": {
                "count": 4384
            },
            "politics": {
                "count": 5555
            },
            "entertainment": {
                "count": 2654
            },
            "technology": {
                "count": 1029
            },
            "religion": {
                "count": 986
            }
        }
    }
}

This dataset card was automatically generated using MTEB

Downloads last month
173