query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
1
300
passage
stringlengths
78
13.7k
category
stringclasses
7 values
link
stringlengths
28
740
⌀
source_dataset
stringclasses
3 values
460e6bed89ae74e77469682001948a3a
c903306280bbc6d6cb8a2675f424191c
ማንም አልተረፈም
በበረራ ቁጥር ኢቲ 302 የተመዘገበው ቦይንግ 737 ማክስ ኤይት ጄት 149 መንገደኞችንና ስምንት የበረራ ቡድን አባላትን አሳፍሮ ወደ ናይሮቢ ለመብረር ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለምአቀፍ አይሮፕላን ጣቢያ የተነሣው ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ከ38 ደቂቃ ላይ ሲሆን መሬት ከለቀቀ ከስድስት ደቂቃ በኋላ ከምድር መቆጣጠሪያው ጋር የነበረው ግንኙነት መቋረጡ ተገልጿል።ከተሣፋሪዎቹ መካከል ሰላሣ ሁለት ኬንያዊያን፣ ስምንት ካናዳዊያን፣ ስምንቱን የበረራ ቡድኑን አባላት ሳይጨምር ዘጠኝ ኢትዮጵያዊያንና ስምንት አሜሪካዊያን መንገደኞች ይገኙበት እንደነበረ ታውቋል።ቦይንግ 737 ማክስ ኤይት ጄት አዲስና ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የደረሰው ባለፈው ኅዳር ሲሆን የዛሬው አደጋ ከመድረሱ በፊት አብራሪው የቴክኒክ ችግር እንደገጠመው አሳውቆ ወደ ቦሌ ለመመለስ ፍቃድ እንዲሰጠው ጠይቆ እንደነበር በአደጋው ሥፍራ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ለጋዜጠኞች መናገራቸው ተዘግቧል።አይሮፕላኑን ያበርሩ የነበሩት ካፕቴን የረዥም ጊዜ ልምድ የነበራቸው መሆኑን የአየር መንገዱ ቃል አቀባይ አቶ አሥራት በጋሻው ለቪኦኤ ተናግረው መንስዔውና የአደጋው ዓይነት እየተጣራ መሆኑን ገልፀዋል።አይሮፕላኑ ባለፈው ዕሁድ ከጆሃንስበርግ መንገደኞችን አሳፍሮ አዲስ አበባ አርፏል።የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት በመንግሥቱና በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ለተጎዱ ቤተሰቦች ጥልቅ ኀዘኑን በትዊተር ባሠራጨው መልዕክት አሳውቋል።ቦይንግ ኩባንያ ዛሬ ባወጣው ባለአንድ አረፍተ-ነገር መግለጫ ስለአደጋው ሪፖርት የደረሰው መሆኑንና ሁኔታውን በቅርብ እንደሚከታተል አስታውቋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ፤ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ለጋዜጠኞች የሰጡትን መግለጫ ከሥር ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። /እንግሊዝኛ/የሪፖርተሮቻችንን ተጨማሪ ዘገባዎችና ቃለ-ምልልሶችን በፌስ ቡክ ገፃችን @voaamharic ላይ ያገኛሉ። ሁኔታውን እየተከታተልን ማውጣት እንቀጥላለን።የኢቲ-302 ተሣፋሪዎች ቁጥርና ሃገሮቻቸው
ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/ethiopian-airlines-flight-et-302-boeing-737-max-8-crash-at-bishofu/4822249.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
13a9425dbd451b702e4ce4383f7c705e
0402e2304c04df9f64318c84f9fc1812
ጦማሪያኑ ከተመሠረተባቸው የሽብርተኝነት ድርጊት ወንጀል ክስ በነፃ ተሰናበቱ
ከሚያዝያ 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ላለፉት 18 ወራት በእስር ላይ የነበሩት ጦማሪያን፣ ጥቅምት 5 ቀን 2008 ዓ.ም. የተመሠረተባቸውን የሽብር ድርጊት ወንጀል ክስ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ተወሰነ፡፡ከታሰሩ ጀምሮ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የመሠረተባቸውን ክስ ሲመረምር የከረመው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት፣ በነፃ እንዲሰናበቱና በዕለቱ እንዲፈቱ ትዕዛዝ የሰጠው ጦማሪያን አቤል ዋበላ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አጥናፍ ብርሃኔና በሌለችበት የተከሰሰችው ሶሊያና ሽመልስ ናቸው፡፡ ጦማሪ በፈቃዱ ኃይሉ የተከሰሰበት የወንጀል ሕግ ተቀይሮ እንዲከላከል ብይን ተሰጥቷል፡፡ፍርድ ቤቱ በሰጠው ብይን እንደገለጸው፣ ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ ያቀረባቸው የሰውም ሆኑ የሰነድ፣ የኦዲዮና ቪዲዮ ማስረጃዎች እንደ ክሱ የሚያስረዱ ሆነው አልተገኙም፡፡ ወይም ምንም ዓይነት ቅርርብ የላቸውም፡፡ በመሆኑም መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ብይን ሰጥቷል፡፡ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ ግን ለፖሊስ በሰጠው የተከሳሽነት ቃል፣ ‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት (ኢሕአዴግ) በምርጫ ወይም በሰላማዊ ትግል የሚወገድ ስላልሆነ፣ በሁከትና በሕዝባዊ አመፅ መወገድ አለበት፡፡ አምኜ እንደ ግብፅ ሁከትና ብጥብጥ በኢትዮጵያም እንዲከሰት ቀስቃሽ ጽሑፎችን ጽፌያለሁ፤›› ብሎ የእምነት ቃል መስጠቱን ፍርድ ቤቱ በንባብ አሰምቷል፡፡ ዓቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ የሚያስረዱ ከኢንተርኔት ያቀረባቸው ጽሑፎችም፣ ተከሳሹ ለፖሊስ ከሰጠው ቃል ጋር ተያያዥነት እንዳላቸውና የሚደግፉ መሆናቸውን በመግለጽ እንዲከላከል ብይን ሰጥቷል፡፡ፍርድ ቤቱ ብይን ከሰማ በኋላ የተከሳሾች ጠበቃ አቶ አመሐ መኮንን ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ፣ ተከላከል የተባለው ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ ይከላከል የተባለበት የሕግ አንቀጽ ዋስትና ስለማይከለክለው፣ አቅሙን ያገናዘበ ዋስ እንዲፈቀድለት ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም በዋስትና ጉዳይ ላይ ተወያይቶ ለማሳወቅ ለጥቅምት 10 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ዓቃቤ ሕግ በብይኑ ላይ ይግባኝ ስለማለቱ ተጠይቆ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ብይን እርስ በርሱ እንደሚጋጭ በመጠቆምና የተሰጠው ብይን የቀረበውን ማስረጃ ያላገናዘበና በአግባቡ ያልተመዘነ መሆኑን በመግለጽ፣ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማለቱን አስታውቋል፡፡ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ብይን በሚመለከት አስተያየታቸውን የሰጡት ጠበቃ አመሐ መኮንን ‹‹ብይኑ ከግለሰብ ችሎታ አንፃር ከታየ በበለጠ በተሻለ ሁኔታ መተንተን ይቻል ነበር፡፡ ከፍርድ ቤቱ አቅም አንፃር ግን ብይኑ ሚዛናዊ ነው፡፡ መረጃዎቹን ከሕጉ ጋር በደንብ አገናዝበው ሠርተውታል፡፡ በአጠቃላይ ጥሩ ብይን ነው፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን ሥጋት እንዳላቸው የተናገሩት አቶ አመሐ፣ ሥጋታቸው ደግሞ ፍርድ ቤቱ በነፃ እንዲሰናበቱ የሰጠውን ትዕዛዝ፣ ቀደም ብሎ በሌሎች ደንበኞቻቸው (እነ ሀብታሙ አያሌው) ላይ የተፈጸመው ዓይነት ድርጊት ይፈጸማል የሚለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ በዕለቱ እንዲፈቱ ካዘዘ በኋላ፣ የማረሚያ ቤት ኦፊሰር የማስፈቻ ትዕዛዝ ወስዶ ለሚመለከታት የማረሚያ ቤቱ ሠራተኛ መስጠቱን መረጃ እንዳላቸው የተናገሩት አቶ አመሐ፣ የማረሚያ ቤቱ ሠራተኛ በተደጋጋሚ ስትጠየቅ ‹‹አልደረሰኝም›› ማለቷንም መስማታቸውን ተናግረዋል፡፡በመሆኑም በፍርድ ቤት የተገኘውን መብት እንደገና የሚነፈግበት ወይም ሊነጠቅ የሚችልበት ዕድል ሊኖር እንደማይገባም አቶ አመሐ አስረድተዋል፡፡ ከአራትና ከአምስት ለማይበልጡ ጉዳዮች የፍትሕ ሥርዓቱን በጠረባ እየመቱ መጣል ለማንም እንደማይጠቅምም አክለዋል፡፡ ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ጥቅምት 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ሌሊት ድረስ ጦማሪያኑ አለመፈታታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/9121
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
32daab06f86c9030e3b3d599aa7ff1c8
b11ebba52646ed81eba8c39ddf84e395
የቻይና መንግሥት በድርቅ ለተጋለጡ ሶማሊያውያን የ1 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ሠጠ
የቻይና መንግስት በድርቅ ለሚሰቃዩና ለተፈናቀሉ የሶማሊያ የህብረተሰብ ክፍሎች በእርዳታ የሚሰጥ የ 1 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ሰጠች።ጎረቤት ሃገር ሶማሊያ በየጊዜው የሚያጋጥማት የድርቅና የረሃብ ችግር ለመላቀቅ የአለም ሃገራት እርዳታ ስትሻ ቆታለች፡፡አሁን ካለችበት የድህነት አዘቅት ለመውጣትና ገፅታዋን ለመቀየርም እየጣረች እንደሆነ የተለያዩ የሚዲያ አውታሮች ሲዘግቡ እንደ ነበር የሚታወስ ነው፡፡ አሁንም ግን ከድርቅ መላቀቅ አልቻለችም፡፡ቻይና በሶማሊያ ለተፈናቀሉ እና ለችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመርዳት በአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በኩል የሚሰጥ የ 1 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገረገች፡፡ቻይና ወደ አለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) የላከችው ገንዘብ ኤጀንሲው የስደት ቀውሱን እንዲያስተካክል እና በሶማሊያ ውስጥ ለሚገኙ ስደተኞች መጠለያ እንዲሆን ይረዳል፡፡ በሶማሊያ የደረሰው ድርቅ እስካሁን ድረስ የቀጠለ ሲሆን ድርቅን ለመግታት ደግሞ ከሶማሊያ መንግስትና ከአለም አቀፍ ጋሮች ጋር ተባብረው በመስራት ላይ መሆናቸው ሽንዋ ዘግቧል፡፡የሶማሊያ መንግስት በበኩሉ ቻይና ድርቁን ለመታደግ ላደረገችው የገንዘብ ድጋፍ ምስጋናውና ገልጿል፡፡የተፈጥሮ አደጋ ቁጥጥር እና የሰብአዊ እርዳታ ሚኒስትር ዋና ፀሃፊ ሞሃመድ ሟይላም እንደተናደሩት ቻይና ለሶማሊያ ድጋፍ ከሚያደርጉ ሃገራት መካከል መሪ ናት፡፡ቻይና አሁን ባደረገችው እርዳታም ለ 2500 ቤተሰቦች ና ሞቃዲሾ የሚገኙ በረሃብ፣ በድርቅና በግጭት ምክንያት የተፈናቀሉ ከ ግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ተደራሽ እንደሚሆን ነው አክለው የገለፁት፡፡በሶማሊያ የቻይና አምባሳደር የሆኑት ኪን ጂያን በበኩላቸው የሃገራቸው መንግስት ሶማሊያን ለመደገፍና በሁለቱ ሃገራት ያለው ወዳጅነት ለማጎልበት በመስራት ላይ እንደሚገኙ በመግለፅ ቻይና በሶማሊያ የቤናዲር ሆስፒታልና የሞቃዲሾ ስቴዲየምን እንደገና ለመገንባት ከሃገሪቱ መንግስት ጋር የተስማማች ሲሆን ከዚህ በፊትም 89 ፕሮጀክቶችን በሶማሊያ አከናውናለች፡፡ ( ምንጭ: ዠንዋ)
ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/33369/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
6c3fa2cdf9e00b80488963c173f095e1
ac7f14d105040e73b3133472a70dd4f2
ለውጡና ውህደቱ በቀድሞ የኢህዴን ታጋዮች አንደበት
ስለ ዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ሲነሳ ለቀድሞ የኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲዊ ንቅናቄ /ኢህዴን / ታጋዮች ያበረከተው አስተዋጽኦ ይወሳል። ትግሉን የተቀላቀለው ብቻ ሳይሆን፣ በቀዬው ሆኖ ስንቅ በማቀበልና ልጁን ወደ ትግሉ እንዲቀላቀል ያደረገው ነዋሪ ሚና አይዘነጋም። ተራራዎቹም ባለታሪክ ናቸው። የያኔዎቹ ታጋዮች የአሁኖቹ ጡረተኞች ታጋይ ሰለሞን መሐመድ፣ ታዘበ ከፍያለው እና ከበደ ተገኝ ትግሉን በተቀላቀሉበትና ተወልደው ባደጉበት አካባቢ ማህበር መስርተው ጥቅሞቻቸውን ለማስከበር በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ። ያለፈውን የትግል ትውስታቸውንና ሁለተኛ ዓመቱን ስለያዘው ለውጥ ሀሳባቸውን አካፍለውናል። በሰቆጣ ከተማ ያገኘኋቸው የቀድሞ ታጋዮች እንዳጫወቱኝ በወጣትነት እድሜያቸው ነበር በ1970ዎቹ ኢህዴንን የተቀላቀሉት። ትግሉን የተቀላቀሉት በወቅቱ የዜጎችን ዴሞክራሲያዊ መብት በማፈን፣ ሰብዓዊ መብትን በመጣስ፣ በማሰር፣ በመደብደብ፣ በመረሸን ህዝብን ለስቃይና እንግልት ይዳርግ የነበረውን ጨቋኝ ሥርዓት ለመጣል ነው። ትግሉም ግቡን መቷል ይላሉ። በጨቋኙ መንግሥት ቦታ በህዝብ የተመረጠ መሪ መቀመጡንም ያስረዳሉ። እንደታሰበው የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበና ህዝብን ከድህነት ያላቀቀ የላቀ ውጤት ባይመዘገብም በልማቱና በፖለቲካው ሰፊ ሥራ መሰራቱን ይናገራሉ። ይሁን እንጂ በሂደት የታገሉለት ዓላማ ወደ ኋላ መመለሱን ካለው ነባራዊ ሁኔታ መገንዘባቸውንም ይገልጻሉ። ከህዝብ ጥቅም ይልቅ እራስን ማስቀደም እየሰፋ መምጣቱ፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና ሌሎችም በህዝብ የሚቀርቡ ቅሬታዎች እየበዙ መምጣታቸው ‹‹ለዚህ ነበር እንዴ የታገልነው›› እንዲሉ አድርጓቸዋል። አሁን የመጣው ለውጥም የዚሁ ውጤት እንደሆነ ይገልጻሉ። ታጋዮቹ ከሁለት ዓመት በፊት ሀገሪቷ ውስጥ የመጣውን ለውጥ ይደግፋሉ። የቀድሞ ታጋዮች ራስ አገዝ ማህበርን በአስተባባሪነት የሚመሩት ታጋይ ሰለሞን መሐመድ በሰጡት አስተያየት ለውጡን ቢደግፉም ሁለት ነገሮችን እንዲገነዘቡ አድርጓቸዋል። በአንድ በኩል የመረረው ህዝብ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ስልጣን የሚፈልግ አካል መኖሩ ይሰማቸዋል። ከዚህ ቀደም የሚያውቁት ኢህአዴግ የተፈጠረውን ችግር ይገመግማል። ጥፋተኛውንም ያስተካክላል። ያም ሆነ ይህ ‹‹ኢህአዴግ ጎዳን በደለን የሚል የህዝብ ቅሬታ በማየሉ›› ለውጡ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተውታል። የመስተካከል ዋና መርሁ ለውጥ እንደሆነና ህዝባዊ የሆኑ አሰራሮችን ማስፈን ጭምር ነው ይላሉ። የኢህአዴግ ስልጣን ላይ መቆየትም ዘላለማዊ መሆን እንደሌለበትና ስልጣን ማሸጋገር እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። በለውጡ የታዩት የእርስበርስ ግጭቶችና ዜጎችንም ከአካባቢያቸው እስከማፈናቀል መድረሱ አሳዝኗቸዋል። የኢትዮጵያ ህዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) አባል እና አጋር ድርጅቶች ውህደትን ታጋይ ሰለሞን ከኢትዮጵያ ሰላም፣ ከህዝቦች መረጋጋትና ፍቅር እንዲሁም ከኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ጥቅም አንጻር እንደሚያዩት ይናገራሉ። በዓላማ የሚተሳሰሩ የፖለቲካ ድርጅቶች ተዋህደው መንቀሳቀሳቸው ለኢትዮጵያ አማራጭና እፎይታ እንደሆነ ባይተዋርነትንም እንደሚያስቀር ገልጸዋል። ታጋይ ታዘበ እንዳሉት ታጋዩ ብቻ ሳይሆን፣ የዋግኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ነዋሪ በአጠቃላይ ለውጡን በድጋፍ ሰልፍ እንደተቀበለው በማስታወስ፣ ሰላማዊ ሰልፉ የድጋፍ መግለጫ እንደሆነም አስምረውበታል። ውህደቱንም በተመለከተ ለኢትዮጵያ ህዝቦች አንድነት፣ ማዕከላዊ መንግሥቱ እንዲጠናከር ለማድረግ፣ ሀገርንም በልማት ለማበልጸግና ዴሞክራሲን ለማስፈን ውህደቱ የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነ ያስረዳሉ። በድርጅት ደረጃም አማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) ለውጡን ተቀብሎ መንቀሳቀሱ ማሳያ እንደሆነና ታጋዮችም ከድርጅቱ የሚለዩ አለመሆናቸውን ይገልጻሉ። ከመነጣጠል በአንድ ሆኖ ሀገርን መምራት እንደሚጠቅም ተናግረዋል። ታጋይ ከበደ ተገኝ በበኩላቸው የለውጡን አስፈላጊነት ይደግፋሉ። ለውጡ ያስገኛቸውንም መካድ አይገባም ይላሉ። ነገር ግን ለውጥ ሰሞነኛ መሆን እንደሌለበት ያምናሉ። እርሳቸው እንዳሉት የደርግ ሥርዓት የተገረሰሰው ለውጥ በማስፈለጉ ነው። አሁንም የመጣው ለውጥ ይሄን የሚደግም እንዳይሆን ከሥር ከስር ማየት ይገባል። ችግሮች የማይደገሙበትና ወደ ህዝብ ጠብ የሚል ነገር ሲኖር ለውጡ ላይ እምነት መጣል ይቻላል ይላሉ። ውህደቱንም በተመለከተ ዘግይቷል ይላሉ። በተለይ አጋር ድርጅቶች እስከ መቼ በአጋርነት ይቀጥላሉ ለሚለው ምላሽ የሰጠም እንደሆነ ይገልጻሉ። መስማማት ለውጤት ያበቃል ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። አዲስ ዘመን ታህሳስ 2/2012 ለምለም መንግሥቱ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=24247
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
a13c722888f9cd48e89946f903f0a1a2
db1a9dde73735836a9394a4be9eec9d3
ኢትዮጵያ በብዝሃ ሕይወት ሃብት ከበለጸጉ አገራት ተርታ መሰለፏ ልዩ ድጋፍ ያስገኝላታል
ኢትዮጵያ ከሳምንታት በፊት ሜክሲኮ በተካሄደው የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት የብዝሃ ሕይወት  ጉባኤ ላይ  በብዝሃ ህይወት ከበለፀጉ አገራት  ተርታ እንድትሰለፍ መደረጉ ልዩ የቴክኒክና የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚያስገኝላት የአካባቢ ደንና የአየር ንብረት ለውጥ  ሚኒስቴር አስታወቀ ።   የአካባቢ ደንና  የአየር ንብረት ለውጥ ሚንስትር ዶክተር ገመዶ ዳሌ ዛሬ በሠጡት መግለጫ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በዓለም በብዝሃ ህይወት እውቅና ከተሠጣቸው አገራት መካከል በ19ኛነት መመዝገቧና እውቅና ማግኘቷ የብዝሃ ህይወት ሃብቷን ይበልጥ ለማልማት የሚያግዝ የፋይናንስና የቴክኒክ  ድጋፍ እንድታገኝ ያስችላታል ።   ኢትዮጵያ የተለየ የብዝሃ ሕይወት ክምችት ባለቤት በመሆኗ የያዘችው እምቅ ሃብት  እንዳይጠፋ  ልዩ  ቴክኒካዊና የፋይናንስ ድጋፍ የማግኘት መብት የሚሠጣት ከመሆኑ በተጨማሪ  ለአገሪቱ ገጽታ ግንባታና በዘርፉ ያላትን ተሰሚነት የሚያሳድግ መሆኑን ዶክተር ገመዶ ዳሌ አመልክተዋል ።   በሜክሲኮ ጉባኤ የኢትዮጵያ መብትና ጥቅም ከማስከበር  አኳያ በአገር ደረጃ ከጉባኤው ጎን ለጎን  የተለያዩ ድርድሮች መካሄዳቸውን  የገለጹት ዶክተር ገመዶ  ኢትዮጵያ በብዝሃ ህይወት ያላት ምርጥ  ተሞክሮ  በምሳሌነት ለሌሎች አገራት አቅርባለች ።ኢትዮጵያ 6ሺ 500  የእጽዋት ሃብት ፣  320 የእጥቢ እንስሳትና  926 የአዕዋፋት ሃብት ባለቤት  በመሆኗ  በብዝሃ  ህይወት  ከበለጸጉ አገራት መካከል አንዷ እንድትሆን ትልቅ ማሳመኛ ምክንያት  መሆኑን  ዶክተር ገመዶ አብራርተዋል ።ማህበረሰብ ዓቀፍ የሆኑ የብዝሃ ህይወት ማከማቻ ባንኮችና ማዕከላት በተለያዩ አገሪቱ  አካባቢዎች  መቋቋማቸውን ሌላው በጉባኤውን ቀልብ የሳበና  ኢትዮጵያም በብዝሃ ህይወት ከበለጸጉ አንዷ እንድትሆን እውቅና ያሠጣት ተግባር መሆኑን ዶክተር ገመዶ አያይዘው ገልጸዋል ።ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት በምታደርገው ጥረት  የተጎዱ አካባቢዎችን በብዝሃ ህይወት ማበልጸግ ወሳኝ  ሚና እንደሚጫወት በመግለጫው ተመልክቷል ።በቅርቡ  በሜክሲኮ ካንኩን  በተካሄደው  የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የብዝሃ ህይወት የሚኒስትሮች ጉባኤ “ ብዝሃነትን ማካተት ለሁሉም ድህንነት ” በሚል መሪ ቃል የተካሄደ  ሲሆን  37  ውሳኔዎች መተላላፉን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል ።        
ቢዝነስ
https://waltainfo.com/am/22944/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3edfa2fea86d5e0309aeef28648a8f9f
b5824201f1cc74afb01fe4e7d1134725
የአማራ ክልል መንግስት ፍንዳታው በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቋል
የፌደራል መንግስት ህወሓት በትናንትናው እለት በባህርዳርና ጎንደር ሮኬት መተኮሱንና በአውሮፕላን ማረፊያዎች አካባቢ ላይ መጠነኛ ጉዳት ማድረሱን አስታውቋል፡፡ ህወሓት “በእጁ ያሉትን የመጨረሻ መሳሪያዎች ጠጋግኖ” መሞከሩን የገለጸው መንግስት “ከመሞቱ በፊት የመጨረሻውን ዐቅሙን እየሞከረ መሆኑን ያመለክታል” ብሏል፡፡ የደረሰውን ጉዳት በሚመለከት መርማሪ ቡድን ተቋቁሞ እያጣራ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የአማራ ክልል መንግስት ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ በጎደርና በባህርዳር ፍንዳታ መከሰቱን አረጋግጦ፣ ሁኔታው በጸጥታ ሀይሎች በቀጥጥር ስር መዋሉን አስታውቆ ነበር፡፡ ህወሓት የፌደራል መንግስት በአየር ጥቃት የሚፈጽም ከሆነ አውሮፕላኖቹ በሚነሱባቸው አየርማረፊያዎች ላይ ጥቃት እንደሚሰነዝር ገልጾ ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጥቅምት 24 ምሽት ህወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ማድረሱን ከገለጹ በኃላ በፌደራል መንግስትና በህወሓት መካከል የነበረው የቆየ አለመግባባት ተባብሶ ወደ ጦርነት አምርቷል፡፡ ግጭቱ ከተጀመረ በኋላ የትግራይን ክልል የሚመራው ህወሓት ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲኖር ፍላጎቱን ቢገልጽም የፌደራል መንግስት “የህገወጡ የህወሓት” ቡድን ህግ ፊት ሳይቀርቡ ድርድር እንደማይኖር ገልጿል፡፡ የተወካዮች ምክርቤት  የክልሉን መሪ ዶ/ር ደብረጺዮን ገ/ብረሚካኤልን ጨምሮ የ39 የምክርቤት አባላትን ያለመከሰሰ መብት አንስቷል፡፡ ጠቅላይ አቃቤ ህግ በህወሓት መሪዎች ላይ የፍርድ ቤት የመያዣ ትእዛዝ አውጥቶባቸዋል፡፡ በፌደራል መንግስትና በትግራይ ክልል ያለው አለመግባባት የጀመረው ኢትዮጵያን ለ27 አመታት ሲመራ የነበረው ኢህአዴግ ፈርሶ ብልጽግና ፓርቲ ሲመሰረት፣ ከመስራቾቹ አንዱ የነበረው ህወሓት የውህደቱ አካል አልሆንም ባለበት ወቅት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ሃይሎች የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት እንዲጠብቁና ሰብአዊ መብትን እንዳይጥሱ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡
ፖለቲካ
https://am.al-ain.com/article/government-says-rocket-cause-damage-in-gondar-and-bahir-dar
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
6087940ba4d1c58722a8eb01f416f2b9
009658535179802a350c793c818b911f
በሽብር የተዘጋው የናይጀሪያው ዳፕቺ ትምህርት ቤት ተከፈተ
ናይጀሪያ ውስጥ ላለፉት ሦስት ወራት ተዘግቶ የቆየ አሸባሪዎች ጥቃት ያደረሱበትና 109 ተማሪዎች የተጠለፉበት ትምህርት ቤት ተከፈተ።ከተጠለፉት የሚበዙት ሴት ተማሪዎች ለቤተሰቦቻቸው የተመለሱ ቢሆንም ወደ ዳፕቺ ትምህርት ቤት ልጆቻቸውን ለመላክ የደህንነታቸው ጉዳይ እያሳሰባቸው መሆኑን ወላጆች እየተናገሩ ነው።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/nigerua-dapchi-girls-5-21-2018/4403292.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3f94eb536e699a276d0dd000189b92f8
7e6bac0d2718b15992b54d842888d060
ዶናልድ ትራምፕ - ስለ ጆን ሉዊስ
ኮንግሬስ ማን ሉዊስ “ወሬ ብቻ እንጂ እርምጃ መውሰድ ወይም ውጤት ማስመዝገብ አይሆንላቸውም” ሲሉም ትራምፕ ተችተዋል።እንደራሴ ጆን ሉዊስ “ወንጀል የበዛበትንና እየተፈረካከሰ ያለውን ወረዳቸውን ማስተካከል ሲገባቸው ስለ ምርጫው ውጤት በሀሰት ምሬት ያሰማሉ” በማለትም ወርፈዋቸዋል።ውዝግቡ ከተፈጠረ ወዲህ በተመራጩ ፕሬዚዳንት የቃለ መሃላ ስነ ሥርዓት ላይ እንደማይገኙ የሚገልፅ የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ቁጥር ከ50 በላይ ደርሰዋል።ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/democracy-in-action-1-18-2016/3681840.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
674b08f5ca6ba039837887c8abd628bb
a4e80bdf5c51d1597e11a9b6d6e0fd5a
የተጓዡ የሰላም ጥሪ
የሀገሪቱ አበይት ጉዳዮች መስተናገጃ፤ የመዲናይቱ ሁነቶች ማሳለጫ የሆነው መስቀል አደባባይ፤ ማለዳ ወደተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተጓዦችን ጭነው ለማድረስ የተዘጋጁ ሀገር አቋራጭ አውቶቡሶች ይሰባሰቡበታል። ሆዳቸው በሰው እስኪሞላ በራቸውን ክፍት አድርገው፤ የደንበኞቻቸውን ጓዝ ሸክፈው ፀሀይ ከመውጣትዋ በፊት ቦታውን ይለቅቃሉ። የበልግ ፀሀይ ከምስራቃዊ የመዲናዋ ክፍል ስትፈነጥቅ ሰርክ ሰዎችን የማያጣው አደባባይ ልዩ ፍካት ይጎናፀፋል። ከወትሮው በተለየ መልኩ ትልቅ ሀገራዊ ጉዳይ ያነገበ፤ የሀገሪቱ ወቅታዊ ሁናቴ ያሳሰበውና “የበኩሌን አስተዋፅዖ ላበርክት” ያለ፤ ሀገራዊ ሃላፊነቴን ልወጣ ብሎ ያሰበ አንድ ቤተሰብ አምባሳደሩን ወደተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሊሸኝ ተሰባስቦበታል። ይህ ቤተሰብ ስለ ሰላም ሊሰብክ፤ ስለ ፍቅር ሊመክር ያዘጋጀውን አባሉን “አላማህ ይሰካ” ብሎ ሊሰናበት እዚያ ቦታ ተገኝቷል። የሰላም ምልክት የሆነው የእርግብ ምስል በሙሉ ነጭ ባንዲራ ላይ ጎልቶ ይታያል። በመኪናው አራቱም ጎን ጠርዝ ላይ አርማው በአጫጭር ዘንጎች ተሰቅሎ ይውለበለባል። በመኪናው የተለያየ ጎኑ ስለ ሰላም የሚነግሩ መልዕክቶች ተለጥፈውበታል። ከፊት ለፊት የመኪናው አካል (ኮፈኑ) ላይ “እኔ ስለ ሰላም እጓዛለሁ! እናንተስ?” የሚልና የተመለከተውን ሁሉ ጠያቂ ጥቅስ በጉልህ ተፅፎ ተለጥፏል። በመኪናው ላይ በተሰቀለ የድምፅ ማጉያ የስመ ጥሩ አርቲስት ማህሙድ አህመድ “ሰላም በዓለም ዙሪያ ሁሉ…” የሚለው ዜማ ከተጓዡ የሰላም መልዕክቶች ጋር ተቀነባብሮ ይደመጣል። ነዋሪነታቸው አዲስ አበባ ነው። አቶ አዳሙ አምባቸው፤ በአገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የሚታየው የሰላም እጦት አሳስቧቸው በመላው ኢትዮጵያ በመዞር ስለ ሰላም አስፈላጊነት ለመስበክና መልዕክት ለማስተላለፍ ማክሰኞ የካቲት 17 ቀን 2012 ዓ.ም በግል መኪናቸው የሰላም ጉዞ ጀምረዋል። “ለሀገሬ ሰላም የድርሻዬን እወጣለሁ” በሚል መርህ ሀገር አቀፍ የሰላም ጉዞ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን የሚገልፁት በጎ ፈቃደኛውና የሰላም ተጓዡ አቶ አዳሙ አምባቸው፤ በቀጣይ ለአምስት ተከታታይ ሳምንታት ለሚያደርጉት የሰላም ጉዞ መኪናቸውንና ሙሉ ወጪያቸውን በግል በመሸፈን “አገራዊ ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የበኩሌን አስተዋፅዖ ማበርከት አለብኝ” በሚል ዓላማ እንደተነሱ አስረድተዋል። አቶ አዳሙ በአገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚስተዋለው የእርስ በእርስ ግጭትና አለመግባባት ማህበረሰቡን የሰላም ስጋት ውስጥ ጥሎታል። በመሆኑም እኔ ስለ ሰላም ጠቀሜታ መልዕክት በማስተላለፍና ስለ ፍቅር በመንገር ሃላፊነቴን ለመወጣት እጥራለሁ በማለት የያዙትን ዓላማ ያስረዳሉ። “ስለ ሰላም በጉዞዬ የሚገጥመኝን ሁሉ ለመጋፈጥና መስዋዕትነት ቢሆንም ለመክፈል እራሴን አዘጋጅቻለሁ” የሚሉት አቶ አዳሙ፤ ሰላም ለሰው ልጅ ህይወት እና ደህንነት የሚያስፈልግ፤ ሁሉም ሊጠብቀው የሚገባ መሆኑን ይናገራሉ። በተለያዩ የክልል ከተሞች፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የገበያ ቦታዎች፣ ህዝብ በሚሰበሰብባቸው አደባባዮችና መድረኮች ስለ ሰላም በመናገር መልዕክት በማስተላለፍ የሰላም ጠቀሜታ ለማስረዳት ሙሉ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ይገልፃሉ። የአቶ አዳሙ ባለቤት ወይዘሮ የምስራች ፍቅሩ፤ ሰላም ለሀገር ህልውና መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን አስታውሰው፤ ባለቤታቸው የሰላም ጉዞ ማድረግ ከፈለጉበት ጊዜ ጀምሮ ለጉዞው ስኬት ድጋፍ ማድረጋቸውን ይገልፃሉ። “ለሰላም መስፈን ሁሉም በጋራ ሊሰራ ይገባል” ያሉት ወይዘሮ የምስራች፤ ለሁለንተናዊ ለውጥና እድገት ሰላም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ለህብረተሰቡ የሰላምን ጠቀሜታ መንገር፤ ሰላም እንዲሰፍን መጣር ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑንም አክለዋል። የሰላም ተጓዡ የአቶ አዳሙ ቤተሰብና ወንድም የሆኑት አቶ ግርማ ሸዋፈራው “ስለ ሰላም መረጋገጥ ሁሉም የራሱን ሚና ሊጫወት ይገባል” ይላሉ። “ከግጭት የሚገኘው እልቂትና መለያየት በመሆኑ ቀድሞ የነበረውን አብሮነት ማስቀጠል ተገቢ ነው፤ ለመጪው ትውልድ ሰላሟ የተረጋገጠች ኢትዮጵያን ማውረስ ይገባል” በማለት ምክረ ሃሳባቸውን ይለግሳሉ። ሁሉም ህብረተሰብ የሰላምን አስፈላጊነት በመረዳት ነገሮችን በሰከነ መንገድ በውይይት ሊፈታ እንደሚገባውም ይመክራሉ። የሰላም ተጓዡ አቶ አዳሙ ሰላም ካለ የማይፈታ ችግር አለመኖሩን ተረድተው ፖለቲከኞች ከፖለቲካዊ ፍላጎታቸው በፊት ህዝብንና ሀገርን ሊያስቡ እንደሚገባም ይናገራሉ። “እኔ ለሀገሬ የሰላም መስፈን የድርሻዬን ለመወጣጥ ዝግጁ ነኝ። ሰላም ህይወት ነውና ለህይወት መረጋገጥ እተጋለሁ” በማለት ለሰላም ሊያደርጉት ያሰቡትን የግል ጥረትና ዝግጅት ያስረዳሉ። ከዚህ ቀደም በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ስራዎች ላይ ሲሳተፉ መቆየታቸውን የሚናገሩት አቶ አዳሙ የሰላም ጥሪ ለማድረግ በሚያደርጉት ጉዞ መላ ኢትዮጵያውያን ስለ ሰላም በማሰብና የሰላምን ጠቀሜታ በመገንዘብ ቀና ትብብርና አድማጭ የሆነ ጆሮ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።አዲስ ዘመን የካቲት 18/2012ተገኝ ብሩ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=27881
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
78384839099da7b17fa966a55ee3916f
6479c0a2308ac7189b5975118b44a447
የኢንተርኔት ማቆም፣ መዝጋትና መረጃን አጣርቶ መልቀቅ የሚያስችል ህግ ሊወጣ ነው
አዲስ አበባ፡- የኢንተርኔት ማቆም፣ መረጃን አጣርቶ ማውጣትና መዝጋት በተመለከተ በአገር ደረጃ የወጣ ህግ ባለመኖሩ ተገቢው መረጃ ለተገቢው አካል እንዳይደርስ ሆኗል። በዚህም ይህንን ለማረም በኮምፒውተር ወንጀሎች አዋጅ ለማካተት ረቂቅ እየተዘጋጀ መሆኑን የብሔራዊ ህግና ፍትህ አማካሪ ምክርቤት አስታወቀ።በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት መምህርና በጠቅላይ አቃቤ ህግ የተቋቋመው የህግና ፍትህ አማካሪ ምክርቤት አባል ረዳት ፕሮፌሰር መሰንበት አሰፋ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ መንግስት ኢንተርኔትን በማቆም፣ በመዝጋትና መረጃ አጣርቶ በማውጣቱ ዙሪያ ሊከተላቸው የሚገቡ ህጎች በአገር ደረጃ አልተቀመጡም። በዚህም በተለያየ መንገድ እነዚህ ክዋኔዎች ተግባራዊ እየሆኑ መጥተዋል። ይህ ደግሞ ተጠቃሚዎችንም ሆነ ህዝቡን መረጃ በትክክል እንዳያገኝ አድርጎታል። በሚዲያ የመረጃ ነጻነትና በኮምፒውተር ወንጀሎች ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ አሁን ባለው ደረጃ ምክር ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ህግ ለማውጣት እየሰራ እንደሆነ የሚገልጹት ረዳት ፕሮፌሰሩ፤ የህጉ መውጣት በህግ አግባብ የተቃኘ መረጃ ለህዝብ እንዲደርስ እድል ይሰጣል ብለዋል። የኢንተርኔት አጠቃቀም ሁኔታውም ሥርዓት እንዲኖረው ያደርጋል። ከዚያ ባሻገር መንግስት ምን ምን አስገዳጅ ሁኔታ ሲገጥመው ኢንተርኔትን ማቆም፣ መዝጋትና ትክክለኛ መረጃ አውጥቶ  ማሰራጨት እንዳለበትም ያመላክታል። ከዚያ ውጪ ከተሰራ ደግሞ ተጠያቂነት እንዲኖርበት ያደርጋል። በተመሳሳይ ተጠቃሚ አካላትም የህግ አግባብን ተከትለው አቤቱታቸውን እንዲያቀርቡ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል። በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት የመገናኛ ብዙሃን ህግ መምህርና በኔቶርክ ፎር ዲጅታል ራይት አባል ዮሐንስ እንየው በበኩላቸው፤ አገሪቱ በተለያየ መልኩ በቴክኖሎጂ እያደገች ከመምጣቷ ጋር ተያይዞ ብዙ ወንጀሎች ይፈጸማሉ። በዚህም ይህ ህግ አለመኖሩ ወንጀሉ እንዲበራከት ያደርጋልና ህጉ እንዲወጣ መታሰቡ የመረጃ ትክክለኛነትን ከማረጋገጥ አኳያ የማይተካ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። በኮምፒውተር ወንጀሎች አዋጅ ውስጥ ተካቶ ተጠያቂነት እንዲኖር መደረጉ ግን አጠያያቂ እንደሆነ የሚጠቅሱት መምህር ዮሐንስ፤ ኢንተርኔት ከለውጥ በፊትም ሆነ በኋላ እየተዘጋ ነው። አሁንም ዝግ የሆነባቸው ቦታዎች አሉ። ስለሆነም ለምን ተዘጋ የሚለውን በደንብ ግልጽ ማድረግና ከኮምፒውተር ወንጀል አዋጁ ጋር ማገናኘት ያስፈልጋል ብለዋል። ተፈጻሚነቱንም ማፋጠን እንደሚገባ አሳስበዋል። ምክንያታቸውም በቅርብ በወጣው የኢትዮ ቴሌኮም መረጃ 22 ነጥብ 74 ሚሊዮን ህዝብ ኢንተርኔት ይጠቀማል። በዚህ አዋጅ ውስጥ የሚካተቱ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ጥርት ባለ መልኩ መጻፍና መተግበር እንዳለባቸው የሚናገሩት መምህር ዮሐንስ፤ ሁኔታው በፍጥነት ተጠናቆ በህግና መመሪያ ታስሮ ወደ ትግበራ መግባት እንዳለበት አስረድተዋል።አዲስ ዘመን ጥር 24/2012ጽጌረዳ ጫንያለው
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=26518
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9fa8548b4c0f8c2f8dccf9c20a32cb1b
3e85aae8839d691fc26a90946c5b8084
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ለኮቪድ መከላከያ ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ለኮቪድ መከላከያ ከ100 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።ድጋፉ በተለያዩ የዓለም አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም የኢፌዲሪ ሚሲዮኖች ኮቪድ 19 ለመከላከል የተደረገ መሆኑን የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤቱ ባወጣው መረጃ አስታውቋል። ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!ከዚህ በተጨማሪም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ሰራተኞች ለወረርሽኙ መከላከል የ4 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውም ተገልጿል።ድጋፉ በብሔራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ስር የተቋቋመው የውጭ ድጋፍ አሰባሰቢ ንኡስ ኮሚቴ አስተባባሪነት መሰብሰቡም ነው የተገለጸው።በዚህም በምስራቅ አውስትራሊያ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ያደረገችውን የገንዘብ ድጋፍ በመወከል የማዕከላዊ እና የምዕራበ ጎንደር ሊቀ ዻዻስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ዮሀንስ፣ አገር ውስጥ የሚገኘው የኦሮሚያ ዳያስፖራ ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱላዚዝ ኢብራሂም እንዲሁም የዩኤስ ኮሌጅ ባለቤት አቶ ቶላ ገዳ ተገኝተው ለንኡስ ኮሚቴው ድጋፋቸውን በቼክ አስረክበዋል።ኮሚቴው ባለፉት ሳምንታት ከተለያዩ ሃገራት ሃብት የማሰባሰብ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።በተለያዩ የዓለም አገራት የተቋቋሙ 60 የኢፌዲሪ ሚሲዮኖች የኮሚቴውን እቅድ መነሻ በማድረግ በልዩ ልዩ ደረጃዎች ተሳትፎ እያደረጉ እንደሚገኙም ነው የተገልጸው።በፕሮግራሙ ላይ የተገኙ ሚኒስትሮች በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን፣ የኢትዮጵያ ወዳጀች እና ዲፕሎማቶች ራሳቸውን ከኮሮና ቫይረስ በመጠበቅ ለወገን እያደረጉ ላለው ያልተቋረጠ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።የኮሮና ቫይረስ የደቀነውን ስጋት መቋቀም የሚቻለው ሁሉም አካል በሚችለው አቅሙ ሲረዳዳ እና ሲተባበር በመሆኑ ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ሚኒስትሮቹ ጥሪ አቅርበዋል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%8b%8d%e1%8c%ad-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8a%96%e1%88%a9-%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab%e1%8a%95%e1%8a%93-%e1%89%b5%e1%8b%8d%e1%88%8d%e1%8b%b0-%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
ca3eeb1657d36c7daa6927eafc3cd62c
b8bd363f0ebf6459c1ba9ff26cc2cbbb
ሪፖርት | መቐለ ከሜዳው ውጪ ጣፋጭ ሙሉ ነጥብ ጨበጠ
በአራተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሲዳማ ቡና በመጀመሪያው አጋማሽ በተቆጠሩበት ግቦች በመቐለ 70 እንደርታ 2-1 ተሸንፏል፡፡ባለሜዳው ሲዳማ ቡና ባሳለፍነው ሳምንት ጅማ አባ ጅፋርን ሲረታ ከተጠቀመው የመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ ዮሴፍ ዮሃንስን በአበባየው ዮሃንስ የለወጠ ሲሆን በተመሳሳይ መቐለ 70 እንደርታ በሜዳው ከኢትዮጵያ ቡና ጋር 1-1 በተለያየበት ጨዋታ የተሰለፈው አስናቀ ሞገስን በአምበሉ አንተነህ ገብረክርስቶስ ተክቶ የዛሬውን ጨዋታ ጀምሯል፡፡ፌዴራል ዳኛ አሸብር ሰቦቃ በመሩት በዚህ ጨዋታ የመጀመሪያው አጋማሽ ሁለቱም ቡድኖች ተመሳሳይ የአጨዋወት መንገድን ይዘው የገቡ ቢሆንም አዋጪ የማጥቃት ኃይላቸውን ግን በግልፅ መመልከት ያልቻልበት ነበር። ይሁንና ሲዳማ ቡና እንደ ወትሮው በዳዊት ተፈራ ይመራ የነበረው የአማካይ ክፍሉ ያለመረጋጋት ይታይበት የነበረ በመሆኑ በመልሶ ማጥቃት ወደ አማኑኤል ገብረሚካኤል እና ኦኪኪ አፎላቢ ላዘነበለው ምዓም አናብስት በቀላሉ ተጋላጭ ሆኗል፡፡ አጀማመራቸው በእንቅስቃሴ በተወሰነ መልኩ ያመረላቸው ሲዳማ ቡናዎች በቀኝ በኩል ሀብታሙ ገዛኸኝ በ7ኛው እና 10ኛው ደቂቃ በፈጣን ሽግግር የተገኙ ሁለት አጋጣሚዎችን ሞክሮ ግብ ጠባቂው ፊሊፕ ኦቮኖ አዳነበት እንጂ በመጀመሪያዎቹ አስር ደቂቃዎች መሪ ለመሆን ተቃርበው ነበር።የጨዋታው ደቂቃ እየገፋ ሲመጣ የሲዳማን የአጨዋወት መንገድ በሚገባ የተረዱት መቐለዎች 20ኛው ደቂቃ ላይ ግብ አስቆጥረዋል፡፡ በመሀል ሜዳ የሲዳማ ቡና ተጫዋቾች ኳስ በሚቀባበሉበት ወቅት ኦኪኪ አፎላቢ በፍጥነት ከኃላ ደርሶ የነጠቃትን ኳስ በግራ አቅጣጫ አመቺ ቦታ ላይ የሲዳማ ቡና ተከላካዮችን የአቋቋም ስህተት በመጠቀም ለአማኑኤል ገብረሚካኤል አሳልፎለት አጥቂው በሚታወቅበት የማስቆጠር ብቃት ኳሷን እየነዳ ወደ ሳጥን በመግባት ግብ አድርጓታል፡፡ግብ ካገቡ በኃላ አሁንም ሌላ ግብ ፍለጋ አፋጣኝ የመልሶ ማጥቃት አደረጃጀትን ለመጠቀም ያሰቡትን መቐለ 70 እንደርታዎች በድጋሚ የሲዳማ ቡናን ስህተት ተጠቅመዋል፡፡ 44ኛው ደቂቃ ያሬድ ከበደ መሀል ሜዳው ጨረር ላይ ከሀብታሙ ገዛኸኝ ላይ ኳስን ነጥቆ ጥቂት ከገፋት በኋላ ለአማኑኤል ሰጥቶት አማኑኤል የሲዳማን የተከላካይ መስመር መዘናጋት ተመልክቶ በድጋሚ ነፃ ቦታ ላይ ለቆመው ያሬድ አሳልፎለት ያሬድም ወደ ግብነት ለውጧት በሁለት ግቦች ልዩነት የመቐለን መሪነት አስተማማኝ አድርጓል፡፡ሁለት ግብ በራሳቸው ግልፅ ስህተት ለማስተናገድ የተገደዱት ሲዳማ ቡናዎች የዕረፍት መውጫ ጭማሪ ደቂቃዎች ላይ በከፈቱት ማጥቃት በግራ የመቐለ የግብ ክልል ወደ ኃላ በተጠጋ ቦታ ላይ አንተነህ ገብረክርስቶስ በሀብታሙ ገዛኸኝ ላይ በሰራው ጥፋት የተገኘውን ቅጣት ምት ዳዊት ተፈራ በረጅሙ ሲያሻማ አበባየው ዮሐንስ በግንባሩ ጨረፍ አድርጎ ግብ በማስቆጠር ሲዳማን ወደ ጨዋታው መመለስ የቻለች ግብ አግብቶ 2-1 በሆነ ውጤት መልበሻ ክፍል አምርተዋል፡፡በእረፍት ሰዓት የቡድኖቹ አባላት ወደ መልበሻ ክፍል በሚያመሩበት ወቅት የመቐለ 70 እንደርታ የአሰልጣኞች ቡድን አባላት ከእለቱ ዳኞች ጋር እሰጣ ገባ ውስጥ የገቡ ሲሆን የቃላት ምልልሶችንም አስተውለናል።ከዕረፍት ሲመለሱ እየተመሩ ከሜዳ የወጡት ሲዳማ ቡናዎች የተጫዋቾቻቸውን የጨዋታ ቦታ ከመለወጥ ባለፈ ቅያሪዎችንም አድርገው ገብተዋል፡፡ ተከላካዩ ሰንደይ ሙቱኩን አውጥተው በመሀል ሜዳ የነበረባቸውን ክፍተት ለመድፈን ብርሀኑ አሻሞን በማስገባት በተከላካይ አማካይ ቦታ ላይ ሲጫወት የነበረው ግርማ በቀለን ወደ መሀል ተከላካይነት መልሰዋል፡፡ በአንፃሩ መቐለ 70 እንደርታዎች በመከላከሉ ቀዝቀዝ ብሎ የታየውን ቢያድግልኝ ኤልያስን አስወጥተው ጋናዊውን ተከላካይ ላውረንስ ኢድዋርድን ወደ ሜዳ ማስገባታቸው እና የመከላከል ቁጥራቸውን ከአማካይ ክፍሉ አሚኑ ነስሩን ወደ ኃላ በማስጠጋት ከፍ ማድረጋቸው አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ውጤቱን አስጠብቀው ለመውጣት ማቀዳቸውን የሚያሳይ ነበር። የሲዳማ ቡና የበላይነት አመዝኖ በታየበት በዚሁ አጋማሽ የብርሀኑ አሻሞን መግባት ተከትሎ በረጅሙ ወደ አዲስ እና ሀብታሙ የሚጣሉ ኳሶች በተደጋጋሚ ይታዩ ነበር።የመቐለ 70 እንደርታ አጥቂዎች እጅጉን ቀዝቅዘው በታዩበት ሁለተኛው አጋማሽ ኦኪኪ አፎላቢ በግል ጥረቱ አግኝቶ መጠቀም ካልቻለባት አንድ አጋጣሚ ውጪ አብዛኞቹ ተጫዋቾች አፈግፍገው በመጫወት እና ሰዓት ለማባከን በተደጋጋሚ በመውደቅ አሳልፈዋል። በተቃራኒው ተደጋጋሚ የግብ ዕድሎችን የፈጠሩት ሲዳማዎች ደግሞ ኳስ እና መረብን ማገናኘት ቸግሯቸዋል።ከነዚህም ውስጥ በ59ኛው ደቂቃ አዲስ ግደይ በቀኝ በኩል በረጅሙ የጣለለትን ይገዙ ቦጋለ በግንባር መትቶ ኦቮኖ የያዘበት የሚጠቀስ ሲሆን ግብ ጠባቂው በዳዊት ተፈራ ተቀይሮ ከገባ በኃላ ኳስን ለመያዝ ጥረት ሲያደርግ የነበረው ሚካኤል ሀሲሳ ክፍተቶችን እየጠበቀ ከርቀት ያደረጋቸው ሦስት ኢላማቸውን የጠበቁ ሙከራዎችንም አምክኗል። በተጨማሪም 69ኛው ደቂቃ ላይ በቀኝ በኩል ከቅጣት ምት አዲስ ግደይ መትቶት ፊሊፕ ኦቮኖ እንደምንም ያወጣበት ኳስ ሲዳማ ቡናን አቻ ለማድረግ የተቃረበ ነበር፡፡በቀሪዎቹ ደቂቃዎች ሲዳማ ቡና ፍፁም ብልጫን ወስዶ ቢጫወትም ጥቅጥቅ ብሎ መከላከልን አማራጩ ያደረገው የገብረመድህን ኃይሌ ቡድን 2ለ1 በማሸነፍ ከሜዳው ውጪ ወሳኝ ሙሉ ነጥብን ይዞ ወጥቷል፡፡
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/53212
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8409fb7b34c69c671cbefa2e81787d75
44bdb55b3f790c85c7f487d2439a470e
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ ላልወሰነ ጊዜ ተቋረጠ
አራተኛ ሳምንት ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ላልወሰነ ጊዜ እንደሚቋርጥ ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።የፌዴሬሽኑ መረጃ ይህንን ይመስላል፡-የኢትዮጵያ ከ17 እና ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድኖች በቀጣይ ከዩጋንዳ እና ከቡሩንዲ አቻዎቻቸው ባለባቸው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ምክንያት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም መደረጉን የሴቶች እግር ኳስ ልማት እና ውድድር ኮሚቴ ዛሬ ታህሳስ 21 ባካሄደው ሳምንታዊ ስብሰባ አሳወቀ፡፡ውድድሩ ለመራዘሙ ምክንያት በመሆን የቀረበው በርካታ ተጫዋቾች ለብሄራዊ ቡድኑ በየእድሜ ደረጃው በመመረጣቸው መሆኑ ታውቋል፡፡ ባሳለፍነው ቅዳሜ ታህሳስ 18/2012ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዲቪዚዮን ውድድር ጨዋታዎች ለ17 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ሴት ብሄራዊ ቡድን 6ተጫዋቾችን ካስመረጠው የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ቡድን በስተቀር ውድድሮቹ በተያዘላቸው የጨዋታ ፕሮግራም መሰረት እንዲካሄዱ ተወስኗል፡፡
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/53355
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
6a6d2d3eda1b5298c91dbf1822c27300
5bbb1aa7bf3820a6f614597d0efc858f
ባንግላዲሽ፡ ፆታዊ ትንኮሳ ደርሶብኛል በማለቷ ተቃጥላ እንድትሞት የተደረገችው ወጣት
ኑስራት ጃሃን የ19 ዓመት ወጣት ነበረች። ባንግላዴሽ ውስጥ ፌኒ በምትሰኝ አነስተኛ ከተማ ውስጥ የእስልምና ትምህርት ቤት ውስጥ ትምህርቷን ስትከታተል ቆይታለች። መጋቢት 18 2011 ዓ.ም የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ኑስራትን ወደ ቢሮው ያስጠራታል። ከዚያም ኑስራት እንደምትለው ርዕሰ መምህሩ ባልተገባ ሁኔታ ይነካካት ጀመረ። ከዚያም ከቢሮው ሮጣ አመለጠች። የባንግላዴሽ ሴቶች ከማህብረሰቡ እና ከቤተሰቦቻቸው የሚደርስባቸውን መገለል እና ሃፍረት በመፍራት የሚፈፀምባቸውን ፆታዊ ትንኮሳዎች አይናገሩም። ኑስራት ግን ርዕሰ መምህሩ የፈፀመባትን መናገር ብቻ ሳይሆን በቤተሰቦቿ እርዳታ ጉዳዩን ፖሊስ ጋር ወሰደችው። ፖሊስ ግን ቃሏን ተቀብሎ ጉዳዩን እያጣራ ከለላ ማድረግ ሲገባው ኑስራትን ማብጠልጠል ጀመረ። በዕለቱ ተረኛ የነበረው ፖሊስ ኑስራት ቃሏን ስትሰጥ ቪዲዮ እየቀረፃት ነበር። ኑስራት ቃሏን እየሰጠች በፖሊሱ መቀረፅ አላስደሰታትም። በተቀረፀው ቪዲዮ በግልፅ እንደሚታየው ኑስራት በእጇ ፊቷን ለመሸፈን ጥረት ታደርግ ነበር። በተንቀሳቃሽ ምስሉም ፖሊሱ የኑስራትን ቅሬታ ''ይህ ትልቅ ጉዳይ'' አይደለም እያለ ሲያጣጥል ይሰማል። ይህ ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት ተሰራጭቷል። ኑስራት ላይ የተፈፀመው አስከፊ ተግባር በርካቶችን አስቆጥቷል። ወደ ፖሊስ ጣቢያው ሄዳ ቃሏን ከሰጠች በኋላ፤ ርዕሰ መምህሩ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ተደረገ። ይህ ግን ለኑስራት ችግርት ፈጠረ። በቡድን የተደራጁ ወንዶች ርዕሰ መምህሩ ከእስር እንዲለቀቁ ሰልፍ ማድረግ ጀመሩ። ተቃውሞ ሰልፉን ሲያስተባብሩ ከነበሩት መካከል ኑስራት የምትማርበት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆኑ ሁለት ወንዶች ይገኙበታል። የአከባቢው ፖለቲከኞችም የተቃውሞ ሰልፉ ተሳታፊ ሆነዋል። በርካቶች ለርዕሰ መምህሩ መታሰር ኑስራትን ተጠያቂ ማድረግ ጀመሩ። ወላጆቿም የልጃቸው ደህንነት ያሰጋቸው ጀመር። ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ ለፖሊስ ቃሏን ከሰጠች ከ11 ቀናት በኋላ ኑስራት ማጠቃለያ ፈተና ለመፈተን ወደ ትምህርት ቤቷ ሄደች። ''ደህንነቷ ስላሰጋን ትምህርት ቤት ድረስ ይዣት ሄድኩ። ወደ ትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ እንዳልገባ ግን ተከለከልኩ።'' ይላል የኑስራት ወንድም መሃሙዱል ሃሰን ኖማን። "እንዳልገባ ባይከለክሉኝ ኖሮ፤ ይህን መሰል ተግባር በእህቴ ላይ አይፈፅሙም ነበር'' ሲል ጨምሮ ይናገራል። የኑስራት ወንድም መሃሙዱል ሃሰን ኖማን በኑስራት የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ሃዘኑን ሲገልጽ። ኑስራት በሰጠችው ቃል መሠረት አንድ የክፍል ጓደኛዋ፣ ጓደኛቸው እየተደበደበች እንደሆነ በመንገር ኑስራትን የትምህርት ቤቱ ሕንፃ ጣሪያ ላይ ይዛት ትወጣለች። ጣሪያው ላይ የጠበቃት ግን ሴት ለመምሰል ዓይነ እርግብ የለበሱ (ዓይናቸው ብቻ የሚያሳይ ሂጃብ) አምስት የሚሆኑ ወንዶች ነበሩ። ከዚያም ኑስራትን በመክበብ በርዕሰ መምህሩ ላይ ያቀረበችውን ክስ እንድታነሳ ያስፈራሯታል። ኑስራት ግን እንደማታደርገው ትናገራለች። ከዚያም ነዳጅ አርከፍክፈውባት እሳት ለኩሰው አቃጠሏት። የመርማሪ ፖሊሶች ኃላፊ ባንድ ኩማር ማጁመደር እንዳሉት ተጠርጣሪዎቹ ''ኑስራት እራሷን ያጠፋች ለማስመሰል አስበው ነበር'' ሃሳባቸው ሳይሳካ የቀረው ተጠርጣሪዎቹ ኑስራት ሕይወቷ ያለፈ መስሏቸው አካባቢውን ጥለው ከሄዱ በኋላ ኑስራት እስተንፋሷ ሳይወጣ ቃሏን በመስጠቷ ነው። ''አንደኛው ተጠርጣሪ የኑስራትን ጭንቅላት በእጆቹ ወጥሮ ከመሬት አጣብቆ ይዞ ስለነበረና ጭነቅላቷ ላይ ነዳጅ ስላላፈሰሱ ከአንገቷ በላይ አልተቃጠለችም። በዚህም ሕይወቷ ሊቆይ ችሏል'' ሲሉ የፖሊስ አዛዡ ለቢቢሲ ቤንጋሊ ቋንቋ አገልግሎት ተናግረዋል። ኑስራት አካባቢው ወደሚገኝ ሆስፒታል ስትወሰድ 80 በመቶ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
b3b7e503de6b8a3181fedd8a7d763e49
1704e3762144be620a3eea43c615a07e
ዛሬ በመቀሌ ሊካሄድ የነበረ ሠላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ
ይህ ሠላማዊ ሰልፍ የተጠራው የትግራይ ክልል የከፍተኛ የትምህርት ተቋም ተማሪዎች ችግር ያጋጥማቸዋል ወደተባሉ ቦታዎች እንዲሄዱ እንዳይደረግ በክልሉ መንግሥት ላይ ግፊት ለማድረግ እንደነበረ ተነግሯል። ሠላማዊ ሰልፉን የጠራው ማህበር ሊቀ መንበር መሃሪ ዮሐንስ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ስለሰልፉ ለማሳወቅ ለመቀሌ ከተማ ከንቲባ ጸሐፊ ደብዳቤ ማስገባታቸውንና ግልባጩንም ለዞኑ ፖሊስ ለማስገባት ሙከራ ባደረጉበት ወቅት አንቀበልም መባላቸውን ተናግረዋል። • በመቀሌ ከተማ ፆታዊ ጥቃትን በመቃወም ሊደረግ የነበረው ሰልፍ ተከለከለ • የትግራይ ክልል አዲስ ገቢ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ወደ አማራ ክልል አንደማይልክ አስታወቀ ሊቀ መንበሩ በተጨማሪ ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ መንግሥት ሁኔታዎችን እንዲያመቻች ማሳወቅ እንጂ የመፍቀድና የመከልከል ህጋዊ መብት የለውም ብለዋል። ዛሬ ጠዋት ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ሮማናት ተብሎ በሚጠራው የመቀሌ ከተማ አደባባይ መሰባሰብ በጀመሩበት ጊዜ ፖሊሶች ወደ ስፍራው መጥተው ሰልፉ ህጋዊ ስላልሆነ በመግለጽ እንዲያስቆሙ መታዘዛቸውን በመግለጽ ሰልፈኞቹ እንዲበተኑ ማድረጋቸውን የሰልፉ አስተባባሪዎች ተናግረዋል። አስተባባሪዎቹም ከፖሊስ ጋር ግብግብ መፍጠር ተገቢ ባለመሆኑ ሰልፉን ለማካሄድ ለሁለተኛ ጊዜ ለፖሊስ የማሳወቂያ ደብዳቤ እንደሚያስገቡ ተናግረዋል። • "ሰልፍ የዜጎች መሰረታዊ መብት ነው" መስፍን ነጋሽ • ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርስቲ ብቻ ነው መማር የሚችሉት- የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የመቀሌ ከተማ ምክትል ከንቲባ ስለተከለከለው ሠላማዊ ሰልፍ ተጠይቀው "ሰልፉ ሊከለከል አይገባም። ቢሆንም የጸጥታውን ሥራ በተመለከተ ማን ተጠይቆ ምን መልስ ተሰጠ? የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ ይገባል" ብለዋል። የሠላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ደብዳቤውን ተቀብሎ ወደሚመለከተው አካል ያላቀረበ ግለሰብ ካለ እንቀጣለን" ያሉት አቶ አቶ ብርሐነ፤ ለፖሊስ ቀርቦ ነበር የሚለው ቅሬታን ተከትሎ ፖሊስ የመከልከል መብት ስለሌለው ተቀባይነት እንደሌለው ገልጸዋል። ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተጠይቆ ሲከለከል በዚህ ሳምንት ውስጥ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ከቀናት በፊት በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጾታዊ ጥቃትን ለማውገዝ በተመሳሳይ መቀሌ ውስጥ ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ጥያቄ ቀርቦ እንደተከለከለ መዘገባችን ይታወሳል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
7fe3b2689ab2d3a28a75a8db9ce0c74c
b7ca9f7eb563d479961f2c974e921262
ፊንላንድ ለአባቶች የእናቶችን ያህል የሥራ ፈቃድ ልትሰጥ ነው
የጾታ እኩልነትንና ደህንነትን ለማበረታታት በሚል የሚሰጥው እረፍ ክፍያንም እንደሚጨምር ታውቋል። የፊንላንድ ጎረቤረት የሆነችው ስዊድን ወላጆች ልጅ ከወለዱ በኋላ ለእያንዳንዳቸው 240 የወላጆች የእረፍት ፈቃድን በመስጠት በአውሮፓ ውስጥ ለጋስ የሆነ የተደነቀ ሥርዓትን በመዘርጋት ትታወቃለች። የፊንላንድ የጤናና ማኅበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር የሆኑት አይኖ-ካይሳ ፔኮነን ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ከመጀመሪያው አንስቶ የወላጆችን ግንኙነት ለማጠናከር ባለመ ሁኔታ "ቤተሰቦች በሚያገኙት ጥቅማጥቅሞች ላይ መሰረታዊ ለውጥ" ተደርጓል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ፊንላንድ ለወለዱ እናቶች ከአራት ወራት በላይ የወሊድ ፈቃድ የምትሰጥ ሲሆን ለአባቶች ደግሞ ከሁለት ወር በላይ ፈቃድ ይሰጣል። ነገር ግን በአማካይ ከአራት ወንዶች አንዱ ብቻ ነው የተሰጠውን ፈቃድ የሚጠቀምበት። አሁን የታቀደው የፈቃድ አይነት የወላጆች ፈቃድን ብቻ የሚመለከት ነው ተብሏል። ወላጆች ከሚሰጣቸው ፈቃድ ውስጥ 69 ቀኑን ወደ ሌላ ጊዜ ማስተላለፍ ይችላሉ፤ በተጨማሪም ነፍሰጡር እናቶች አንድ የወር ደሞዝን ያህል ክፍያን ያገኛሉ ተብሏል። የፊንላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳና ማሪና ባለፈው ወር እንዳሉት አገራቸው የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የሚቀሯት ሥራዎች እንዳሉና ልጆቻቸው ታዳጊ እያሉ አብረዋቸው ጊዜ የሚያሳልፉ አባቶች ቁጥር በጣም ውስን ነው ሲሉ ወቅሰዋል። በኦስሎ ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ሊሲ ኢሊንግሳትር ለቢቢሲ እንደተናገሩት ፊንላንድ የምትገኝበት የኖርዲክ አካባቢ አገራት ወደ እናቶች የማይዘዋወር የወላጅነት የሥራ ፈቃድ በመስጠት በኩል ቀዳሚ ሆነው ቆይተዋል። የአውሮፓ ኅብረትም ተመሳሳይ ውሳኔን እየተከተለ ሲሆን ባለፈው የፈረንጆች ዓመት አባል አገራት ለእያንዳንዱ ወላጅ የአራት ወር ፍቃድ እንዲሰጡና ከዚህም ውስጥ ሁለቱ ወር ወደ ሌላ ጊዜ የማይተላለፍ እንዲሆን የሚያስገድድ ነው። ፖርቱጋል የትኛውንም ጾታ የማይለይ ሁሉን አቀፍ ሥርዓት ያላት አገር ናት። በዚህም ለሁለቱም ወላጆች የአራት የሥራ ፈቃድና ሙሉ ደሞዝ እንዲሁም የሚፈልጉ ከሆነ ተጨማሪ አንድ ወር ፈቃድና የደሞዛቸውን 80 በመቶ እንዲያገኙ ይፈቀዳል። ከታኅሳስ ወር ጀምሮ ፊንላንድ በአራት ፓርቲዎች ጥምረት እየተመራች ሲሆን እያንዳንዱን ፓርቲም የሚመሩት ሴቶች ናቸው። ለወላጆች በሚሰጠው የሥራ ፈቃድ ላይ የሚደረገው ለውጥ የፊንላንድ መንግሥትን ተጨማሪ 110 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስወጣው ተገምቷል። ስዊዲን፣ ኖርዌይ፣ አይስላንድ፣ ኢስቶኒያና ፖርቱጋል ለቤተሰብ ተስማሚ የሆነ ፖሊሲ በማውጣት ባለፈው ዓመት በዩኒሴፍ አድናቆትን አግኝተዋል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
f77747d1f84381569bee5eac76449590
0e0c3db9aabdf2ded4e7cad800579b3e
በምዕራብ ኦሮሚያ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የጦር መሪ የሆነው ኩምሳ ዲሪባ ወይም መሮ፤ በምዕራቡ ክፍል የሚገኘው የኦነግ ጦር የትጥቅ ትግል ማድረጉን እንደሚቀጥል ለቢቢሲ ተናገረ።
ኩምሳ ዲሪባ (መሮ)፡ የኦነግ ጦር መሪ በትግላችን እንቀጥላለን አለ\nየምዕራብ ኦሮሚያ የኦነግ ጦር መሪ መሮ (ግራ) እና የኦነግ ሊቀመንበር ዳውድ ኢብሳ (ቀኝ)። መንግሥትን እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባርን ለማስታረቅ ተዋቅሮ የነበረው ኮሚቴ ትናንት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት መድረክ ላይ የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ከአሁን በኋላ ኦነግ ታጥቆ የሚንቀሳቀስ የጦር ኃይል አይኖረውም ማለታቸውን ተከትሎ ነው የጦሩ መሪ ይህን የተናገረው። • በምዕራብ ኦሮሚያ ስድስት ሰዎች መገደላቸው ተሰማ በምዕራብ ኦሮሚያ የጦር መሪ የሆነው ኩምሳ ዲሪባ ወይም መሮ፤ ''የተለወጠ ነገር የለም'' በማለት ከኦነግ ሊቀ መንበር በተለየ መልኩ የኦነግ ጦር የትጥቅ ትግል ማድረጉን እንደሚቀጥል ለቢቢሲ ተናግሯል። መሮ መከላከያው፣ ፖሊስ እና የደህንነት አካሉ ሙሉ በሙሉ የፓርቲ ወገንተኝነቱን አቁሞ የሕዝብ ወገንተኝነቱን እስካላረጋገጠ ድረስ የመንግሥትን ጥሪ አንቀበልም ብሏል። ''እኛ ለፓርቲ ወግኖ ሕዝብን የሚጎዳ የመከላከያ አካል መሆን አንሻም'' ሲል ከዚህ በፊት ከመንግሥት ጋር በተደረሰው ስምምነት የግንባሩ ታጣቂዎች ከመንግሥት የጸጥታና የመከላከያ ኃይል ጋር ለማካተት የቀረበውን ሃሳብ መሮ ውድቅ አድርጎታል። • በጦላይ የኦነግ ሠራዊት አባላት ላይ የተከሰተው ምንድን ነው ? ጨምሮም ''ለጊዜያዊ ጥቅም ተብሎ በንግግር ተሸፋፍኖ የሚያልፍ ነገር አያዛልቅም። ነገ እሳት መነሳቱ አይቀርም። ዘላቂ መፍትሄ በሚሰጡ ምክክሮች ላይ ለመወያየት ግን ዝግጁ ነን'' በማለት ለድርድር ዝግጁ መሆኑን ጠቁሟል። መንግሥትን እና ኦነግን ለማስታረቅ ተዋቅሮ የነበረው ኮሚቴም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት መሣሪያ አንገበው ጫካ ገብተው የነበሩ የኦነግ ወታደሮች በሰላማዊ መንገድ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ወይም ወደሚዘጋጅላቸው ስፍራ ለስልጠና እንዲገቡ ጥረት ሲያደርግ እንደቆየ አስታውሷል። ኮሚቴው የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በተገኙበት ነው ሪፖርቱን ያቀረበው። • «ኦነግ ሀገር ለመገንጠል ነው የምሠራው ብሎ አያውቅም» ሽጉጥ ገለታ (ዶ/ር) ሪፖርቱ በቀረበበት ወቅት የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ፤ ኦነግ ከአሁን በኋላ ጦር አንግቦ የሚንቀሳቀስ ሠራዊት አይኖረውም፤ መንግሥት ሕግ ለማስከበር የሚወስደውን እርምጃም እንደግፋለን ብለዋል። የኮሚቴው ሪፖርት ቁልፍ ነጥቦች የአስታራቂ ኮሚቴውን ሪፖርት ያቀረቡት አቶ በቀለ ገርባ ሲሆኑ፤ ባቀረቡት ሪፖርት ውስጥ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል። ኦነግ ከአሁን በኋላ ታጥቆ የሚንቀሳቀስ ጦር ስለማይኖረው ኮሚቴው የተቋቋመበትን ዓላማ ማሳካቱን ጠቅሰው፤ ኮሚቴው በኦነግ እና በመንግሥት መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ምክንያት ታስረው የነበሩ ሰዎች ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቋል። • ከተገደሉት አንዱ የማዕድን ኩባንያው ባለቤት ነበር በተጨማሪውም ኮሚቴው ኦነግ በሰላማዊ መንገድ ፖለቲካዊ ትግሉን ለመቀጠል በሚያደርገው እንቅስቃሴ የመንግሥት ድጋፍ እንዳይለይ እና የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ወደተዘጋጀላቸው ስፍራ የገቡ የኦነግ ጦር አባላት ቃል የተገባላቸው ሁሉ ተፈጻሚነት እንዲኖረው ኮሚቴው ጠይቋል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
3229af0f7bddbac561380a46b16e67e9
a9776eb5efd212efd630e0cd578a2ec8
በችግር ላይ የሚገኙ የወረገኑ ተፈናቃዮች የስደተኞችን ያህል ዕርዳታ እንዲፈቀድላቸው ጠየቁ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ ባካሄደው ሕገወጥ ያላቸውን ቤቶች የማፍረስ ዘመቻ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ የወረገኑ አካባቢ ነዋሪዎች፣ ከውጭ አገር ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ ስደተኞች እንደሚደረገው ሁሉ ለእነሱም ዕርዳታ የሚያገኙበት መንገድ እንዲመቻች ጠየቁ፡፡ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉት እነዚህ ወገኖች ባቋቋሙት ኮሚቴ አማካይነት ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በጻፉት ደብዳቤ፣ ቤተሰቦቻቸውን ይዘው ጎዳና ላይ መውደቃቸውን ገልጸዋል፡፡‹‹የምንኖረው ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ ነው፡፡ በድንገት ቤታችን በመፍረሱ ጭራሹኑ የኑሮ መሠረታችን ተናግቷል፤›› በማለት ለከተማው ምክር ቤት በጻፉት ደብዳቤ የገለጹት እነዚህ ተፈናቃዮች፣ ‹‹ወቅቱ ክረምት በመሆኑ ከልጆቻችን ጋር ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገናል፤›› ሲሉም መንግሥት እንዲደርስላቸው ተማፅነዋል፡፡እነዚህ ተፈናቃይ ወገኖች በጻፉት መማፀኛ ደብዳቤ ሌሎች አማራጮች ባይኖሩ እንኳን፣ ቢያንስ መንግሥት ችግራቸውን ተረድቶ ለደቡብ ሱዳን፣ ለሶማሊያና ለኤርትራ ስደተኞች እንዳደረገው ላስቲክ ወጥረው የሚኖሩበትን መንገድ እንዲያመቻች ጠይቀዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪ ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው ያስከተለባቸው የከፋ ችግር ባለበት ወቅት ቀጣዩ የትምህርት ዘመን እየቀረበ በመሆኑ፣ ልጆቻቸውን በቋሚነት ለማስተማር ለመወሰንም እንደተቸገሩ ተፈናቃዮቹ በጻፉት ደብዳቤ ገልጸዋል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ዶ/ር ታቦር ገብረ መድኅን የተፈናቃዮቹን ጥያቄ ከተመለከቱ በኋላ፣ ሊደረግ የሚችል ድጋፍ ካለ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት እንዲመለከተው ጠይቀዋል፡፡‹‹የከተማው አስተዳደር ምንም መጠለያ ለሌላቸው መፍትሔ ለመሻት ባለው ዕቅድ መሠረት የሚሰጥ ምላሽ ካለ እንዲመለከተው›› በማለት ዶ/ር ታቦር ተፈናቃይ ወገኖች የጻፉትን መማፀኛ ደብዳቤ አባሪ በማድረግ ለከንቲባ ጽሕፈት ቤት መርተዋል፡፡ነገር ግን ተፈናቃይ ወገኖች ያቋቋሙት ኮሚቴ አባላት በተደጋጋሚ ወደተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ቢመላለሱም መፍትሔ ማጣታቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ‹‹ከዚህ የባሰ ችግር የለም፤›› ያሉት ስማቸውን ቢገልፁ ሌላ ያልጠበቁት ችግር ሊገጥማቸው እንደሚችል የሰጉ የኮሚቴው አባላት መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ‹‹መንግሥት ባለበት አገር እንዲህ ዓይነት ስቃይ ሊገጥመን አይገባም፡፡ ቢያንስ ላስቲክ ወጥረን የዕለት ኑሯችንን የምንገፋበት መንገድ ይመቻች፤›› በማለትም ተማፅነዋል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚያዝያ 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረገኑና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሃና ማርያም አካባቢዎች ሕገወጥ ያላቸውን ግንባታዎች ማፍረሱ ይታወሳል፡፡በወረገኑ አካባቢ 4,800 ቤቶች ፈርሰዋል፡፡ በአጠቃላይ እነዚህ ቤቶች በመፍረሳቸው ከአምስት ሺሕ በላይ የሚቆጠሩ ዜጎች እንደተፈናቀሉ የኮሚቴ አባላቱ ይናገራሉ፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ1988 እስከ 1997 ዓ.ም. ድረስ ከተገነቡት በስተቀር፣ የተቀሩት በተለይ ከ1997 ዓ.ም. ወዲህ የተገነቡት ‹‹ሕገወጥ›› በመሆናቸው መፍረስ እንደሚኖርባቸው ይገልጻል፡፡የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታምራት አስናቀ እንደሚሉት፣ እስከ 1997 ዓ.ም. ከተገነባው ‹‹ሕገወጥ›› ግንባታ በስተቀር አግባብ ባልሆነ መንገድ የተያዘን መሬት መንግሥት ሕጋዊ አያደርግም፡፡ተፈናቃዮቹ እንደሚሉት ግን የፈረሱባቸውን ቤቶች ሲገዙም ሆነ ሲገነቡ መንግሥት ያውቅ ነበር፡፡ በኮብልስቶን፣ በድልድይ ግንባታ፣ በኮሙዩኒቲ ፖሊሲንግ፣ እንዲሁም በአካባቢው በተካሄዱ የልማት ሥራዎች ከገንዘብ መዋጮ ጀምሮ ተሳታፊ እንደነበሩ ያስታውሳሉ፡፡‹‹ይህ ሁሉ ቀርቶ አሁን የምንፈልገው የላስቲክ መጠለያ ነው፤›› በማለት የኮሚቴ አባላቱ በተለይ የመጠለያ ችግር የተፈናቃዮችን ሕይወት እያናጋ መሆኑን አፅንኦት በመስጠት ተማፅነዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%89%A0%E1%89%BD%E1%8C%8D%E1%88%AD-%E1%88%8B%E1%8B%AD-%E1%8B%A8%E1%88%9A%E1%8C%88%E1%8A%99-%E1%8B%A8%E1%8B%88%E1%88%A8%E1%8C%88%E1%8A%91-%E1%89%B0%E1%8D%88%E1%8A%93%E1%89%83%E1%8B%AE%E1%89%BD-%E1%8B%A8%E1%88%B5%E1%8B%B0%E1%89%B0%E1%8A%9E%E1%89%BD%E1%8A%95-%E1%8B%AB%E1%88%85%E1%88%8D-%E1%8B%95%E1%88%AD%E1%8B%B3%E1%89%B3-%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B2%E1%8D%88%E1%89%80%E1%8B%B5%E1%88%8B%E1%89%B8%E1%8B%8D-%E1%8C%A0%E1%8B%A8%E1%89%81
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f216913f849de6138461f4bf002aede6
42547809e4b5ed7f701ad67abb73054f
የብሔር ጥቃት የሚፈፅሙ ባለስልጣናት ለፍርድ እንዲቀርቡ ተጠየቀ
በሃገሪቱ ማንነትን መሠረት አድርገው የሚፈፀሙ ኢ-ሠብአዊ ድርጊቶችና መፈናቀሎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ያሳሰበው ሠማያዊ ፓርቲ፤ መንግስት ኃላፊነቱንም እንዲወስድ የጠየቀ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን በበኩሉ፤ ከቤኒሻንጉል ተፈናቅለው ለወራት በባህርዳር ተጠልለው የሚገኙ ዜጎችን ሁኔታ እመረምራለሁ ብሏል፡፡ጥቅምት 17 ቀን 2010 ዓ.ም ከ30 ዓመታት በላይ ከኖሩበት ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለጋንፎ ወረዳ የሠው ህይወት በጠፋበት ሁኔታ በሃይል የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆችን አስመልክቶ መግለጫ ያወጣው ሠማያዊ ፓርቲ፤ ማንነትን መሰረት አድርጎ የሚፈፀም በደል በአስቸኳይ እንዲቆም ለመንግስት ጥሪ አቅርቧል፡፡ በህዝቡ ላይ በደል ያደረሱ፣ ግድያ የፈፀሙና ያስፈፀሙ አካላትም ተጣርተው ተገቢውን ፍርድ እንዲያገኙ የጠየቀው ፓርቲው፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተፈፀመው መፈናቀል በመንግስት ባለስልጣናት ትዕዛዝ ነው የሚል ጥርጣሬ እንዳለውና መንግስት በባለስልጣናት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡ በመንግስት ሃላፊዎች ትዕዛዝ በተደጋጋሚ ማንነትን መሠረት አድርጎ የሚፈፀም ጥቃት አሣሣቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ያለው ፓርቲው፤ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እየተፈፀመባቸው ያሉ ማህበረሠቦችን አስፈላጊውን ከለላ በመስጠት መንግስት ከጥቃት የመከላከል ሃላፊነት አለበት ብሏል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=21843:%E1%8B%A8%E1%89%A5%E1%88%94%E1%88%AD-%E1%8C%A5%E1%89%83%E1%89%B5-%E1%8B%A8%E1%88%9A%E1%8D%88%E1%8D%85%E1%88%99-%E1%89%A3%E1%88%88%E1%88%B5%E1%88%8D%E1%8C%A3%E1%8A%93%E1%89%B5-%E1%88%88%E1%8D%8D%E1%88%AD%E1%8B%B5-%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B2%E1%89%80%E1%88%AD%E1%89%A1-%E1%89%B0%E1%8C%A0%E1%8B%A8%E1%89%80&Itemid=180
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3bddf0eac5527066c820513d3635385a
47cc888c1d94b58b09b61390f54c8224
ካንበራ
ካንቤራ የአውስትራሊያ ዋና ከተማ ነው። የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 339,900 ሆኖ ይገመታል። በዚህም በሀገሪቱ ካሉት የየብስ ከተሞች ትልቁ ሲሆን በአጠቃላይ ደግሞ ፰ኛው ከፍተኛ የህዝብ ብዛት የሚገኝበት ከተማ ነው። ካምቤራ ላይ ተቀምጦ ይገኛል። ነጮች መጀመርያ የሠፈሩበት በ1818 ዓ.ም. ገደማ ነው። ዋና ከተሞች የአውስትራልያ ከተሞች
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
2520d489819f4487aa3a8793f152b1c6
bb57e6a79cab6576e3afb645bd10a0bc
በአንዋር መስጊድ በደረሰ የእሳት ቃጠሎ በርካታ መደብሮች ወደሙ
የንብረት ግምት ገና እየተጣራ ነው ተብሏል መርካቶ በአንዋር መስጊድ በከለላቸው የንግድ መደብሮች ላይ በደረሰ የእሳት ቃጠሎ፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ንብረት መውደሙን የንብረቶቹ ባለቤቶች ገለጹ፡፡ የአንዋር መስጊድ አስተዳደር ካከራያቸው 300 ያህል መደብሮች ውስጥ 50 ያህሉ መቃጠላቸውን የተገለጸ ቢሆንም፣ ንብረቶቻቸው የእሳቱ ሰለባ የሆኑባቸው ባለንብረቶች ግን የሱቆቹ ብዛት ከ163 በላይ መሆናቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡       አቶ ከድር መሐመድ የተባሉ የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች መሸጫ መደብር ባለቤት እንደተናገሩት፣ መርካቶ ውስጥ ሦስት በአራት የሆነ ክፍል ሰባትና ስምንት ሱቆችን አካቶ እንደሚይዝ ገልጸው፣ የእሳቸው ሱቅ በውስጡ ከ200 ሺሕ ብር በላይ የሚገመት ንብረት ነበረው ብለዋል፡፡ ስፋቱ ግን ሁለት በሁለት ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል፡፡      በመሆኑም ሃምሳም ይሁኑ መቶ መደብሮችን የመስጊዱ አስተዳደር ማከራየቱን ቢገልጽም፣ በነፍስ ወከፍ ተይዘው ይሠራባቸው የነበሩ ሱቆች ግን ሁለት መቶ ሊደርሱ እንደሚችሉ አቶ መሐመድ ጠቁመዋል፡፡      ረቡዕ ሰኔ 20 ቀን 2010 ዓ.ም. ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት አካባቢ እሳቱ መነሳቱን የገለጹት ባለመደብሮቹ፣ በወቅቱ ሁሉም መደብሮች ዝግ ነበሩ ብለዋል፡፡ የተወሰነ እንኳን ማትረፍ እንዳይችሉ ተደውሎላቸው የደረሱት ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓትና ከዚያ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ምንም ዓይነት ንብረት ማትረፍ አለመቻሉን፣ አንዳንዶቹ አዳዲስ ግዥ ፈጽመው መደብሮቻቸውን የሞሉ በመሆናቸው ማካካሻ እንኳን እንደሌላቸው አስረድተዋል፡፡       የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መቆጣጠር ባለሥልጣን ተደውሎለት ከሌሊቱ 7፡30 ሰዓት በቦታው መገኘቱን፣ ከ15 በላይ የአደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎችና 112 ሠራተኞቹን በማሠማራት እሳቱ ወደ ሌላ እንዳይዛመት ባለበት ለመቆጣጠር መቻሉን አስታውቋል፡፡      የባለሥልጣኑ የኮሙዩኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ሰለሞን መኮንን ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ በመስጊዱ አስተዳደር መረጃ መሠረት የተቃጠሉት 50 መደብሮች ናቸው፡፡ መደብሮቹ በተቀጣጣይ ሸቀጣ ሸቀጦች የተሞሉ በመሆናቸው እሳቱ በቀላሉ ስለሚዛመት፣ ወደ ሌላ እንዳይስፋፋ በመከላከል እዚያው እንዲቀር ተደርጓል፡፡ በሕዝቡ ትብብር እስከ ንጋት ድረስ በተደረገው ርብርብ እሳቱ ሳይዛመት ለመቆጣጠር ቢቻልም፣ መደብሮቹን ማዳን አለመቻሉን አስረድተዋል፡፡      የደረሰውን የጉዳት መጠን ለማወቅ ባለሥልጣኑ ከፖሊስ ጋር በመተባበር እየሠራ በመሆኑ፣ ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰ መግለጽ እንደማይቻልም ተናግረዋል፡፡       የእሳቱ መንስዔም ምን እንደሆነ ለማወቅ ጥረት እየተደረገ ነው ሲሉ አቶ ሰለሞን አክለዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/article/11575
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
d510f0a33881dec680a6af2c61e6c2b3
d2dbbf004e0e605c9c6ccda6b83ce802
ሃያ ሺ የሚጠጉ አባወራዎች ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ተጠቃሚ መሆናቸው ተጠቆመ
አዲስ አበባ፡- በ2011 በጀት ዓመት 19 ሺ 739 አባወራዎች ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ቅጥያ ተሰርቶላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ በተያዘው በጀት ዓመትም 12 ሺ 201 አባወራዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩንም አመልክቷል፡፡የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን የሥራ ሂደት መሪ ወይዘሮ ሰርካለም ጌታቸው በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ከሚሰራቸው ሥራዎች መካከል ፍሳሾችን ከህብረተሰቡ ሰብስቦ በማጣራት መልሶ የመጠቀም ሥራ አንዱ ነው፡፡ በዚህም በ2011 ዓ.ም ላይ 19 ሺ 739 አባወራዎች ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ቅጥያ ተሰርቶላቸው ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ እንደ ወይዘሮ ሰርካለም ገለፃ፤ ህብረተሰቡ የቤት ለቤት ቅጥያ በስፋት ያለመሳተፍ ችግር ቢኖርም በተያዘው በጀት ዓመት በዋነኝነት ትኩረት በማድረግ 12 ሺ 201 አባ ወራዎችን የቅጥያ ተጠቃሚ ለማድረግ እቅድ ተይዟል፡፡ ባለፉት አራት ወራትም የክረምት ወቅት በመሆኑ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ሲከናወን ነበር:: በቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ውስጥ 689 አባወራዎች ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ በቀጣይ በመካኒሳ፣ በንፋስ ስልክ ላፍቶና በአዲስ ከተማ ቅርንጫፎች ሰፊ ሥራ ለመስራት እቅድ መያዙን የጠቆሙት ወይዘሮ ሰርካለም፤ ከዚህ ቀደም ሶስት ሺ 460 ተሰርቶ ህብረተሰቡ ደጃፍ ላይ ቢደርስም ቅጥያ ያልተሰራላቸውን ማጠናቀቅ እንዲሁም በፕሮጀክት ጽህፈት ቤቶች እየተሰሩ የሚገኙ አምስት ሺ 526 ቅጥዎች ለማጠናቀቅ ይሰራል ብለዋል፡፡ ህብረተሰቡ ሴፍቲ ታንከሩን ላለማፍረስ የፍሳሽ ማስወገጃ ቅጥያ ደጃፋቸው ደርሶ የማይጠቀሙበት ሁኔታ መኖር፣ የመስመር ክዳን ስርቆት፣ በመስመሮች ውስጥ የፕላስቲክ ጠርሙሶች እና የጫት ገረባና ቆሻሻዎችን መክተት እንዲሁም በህገወጥ መንገድ የፍሳሽ ማስወገጃ ቅጥያ የሚያደርጉ ግለሰቦች ለሥራው ተግዳሮት መሆናቸውን የገለፁት ወይዘሮ ሰርካለም ዘመናዊ የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓት ወጪ ቆጣቢ በመሆኑ ህብረተሰቡ በአግባቡ መጠቀም እንዳበትም አሳስበዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 22/2012 መርድ ክፍሉ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=23454
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c8500c38a9d9b3bf759725be0d65727e
dbb917ac36cb75ef848fd91968bd6f58
ጠጥቶ ማሽከርከርን ለማስቆም ዘመቻ ተጀመረ
በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ ለሚከሰቱ 1.2 ሚሊዮን አደጋዎች አምስት ምክንያቶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ በተለይ ሁለቱ በፍጥነት ማሽከርከርና ጠጥቶ ማሽከርከር ናቸው፡፡ እነዚህም በተጠናቀቀው 2008 ዓ.ም. በመላ አገሪቱ ለ4,358 ሰዎች ሕይወት መጥፋት ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው፡፡ በተለይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመሆን በሚቀጥሉት ሳምንታት ጠጥቶ ማሽከርከርን ለማስቆም ዘመቻ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል፡፡ ባለፈው ዓርብ መስከረም 13 ቀን 2009 ዓ.ም. ጠጥቶ ማሽከርከር ለማስቆም ዘመቻ ለመጀመር ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ በመግለጫው ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው፣ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዶ/ር ሰሎሞን ኪዳኔ፣ በአጋርነት የሚሠራው የቫይታል ስትራቴጂ ፕሬዚዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማስተር ሆዙ ሉዋ ካስትሮን ጨምሮ በርካታ የባለድርሻ አካላት ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%8C%A0%E1%8C%A5%E1%89%B6-%E1%88%9B%E1%88%BD%E1%8A%A8%E1%88%AD%E1%8A%A8%E1%88%AD%E1%8A%95-%E1%88%88%E1%88%9B%E1%88%B5%E1%89%86%E1%88%9D-%E1%8B%98%E1%88%98%E1%89%BB-%E1%89%B0%E1%8C%80%E1%88%98%E1%88%A8
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
24dd8b5e4b76f4146900d6ecbe18f74b
b6c311197a51bb87c1777fb774d322c6
ሲዳማ ቡና በረከት አዲሱን ለሁለት አመት አገደ
ሶከር ኢትዮጵያ ባረጋገጠችው መረጃ መሰረት በረከት አዲሱ ለሌሎች የክለቡ ተጨዋቾች አርአያ የማይሆን የክለቡን ስምና ክብር የሚያጎድፍ ተግባር ሲፈፅም ደርሼበታለው በማለት ለሁለት አመት ምንም አይነት ግልጋሎት እንዳይሰጥ የዲሲፒሊን ቅጣት አስተላልፎበታል፡፡ከእግር ኳስ ህይወቱ በስተጀርባ ከባድ ጉዳቶች እና ውዝግቦች የማያጡት የቀድሞው የንግድ ባንክ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና አዳማ ከተማ አጥቂ ባለፈው የውድድር ዘመንም ከአሰልጣኙ ጋር በተፈጠረ ልዩነት ለክለቡ እምብዛም ግልጋሎት መስጠት አልቻለም ነበር፡፡
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/22121
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9a8d5064bfd25ad07950e629381f8e3f
7cb3bce30691349b73e4687b7229e1c2
ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፖብሊክ በ2017
የመጀመሪያው የአዲሱ ብሔራዊ ጦር ልምምድ ተጠናቆ የፊታችን ጥር ወር ሥራውን ይጀምራል፤ የአውሮፓ ሕብረት ወታደራዊ አሰልጣኞች በቀጣዩቹ ሁለት ዓመት ውስጥ እስከ 2ሺሕ ወታደሮችን አሰልጥነው ያወጣሉ ተብሎም ይጠበቃል። የማዕከላዊ አፍሪካ ሠራዊት፣ በማካሄድ ላይ ባለው የነፍስ-አድን ልምምድ፤ የተራቀቀ ትርዒት በማሳየት ላይ ይገኛል።ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/car-eu-army-12-27-2016/3653023.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e0bc551a236af24b8bc89df9249d8c7c
8d46cd29e49ff07603a65f2c8682b34b
የሰው ልጅ ከሚበላቸው ምግቦች መካከል እጅግ ፍጹም የሆነውን ማግኘት ከባድ ሊሆን ይችላል፤ እንቁላል ግን ለፍጹምነት የቀረበ የምግብ አይነት እንደሆነ ይነገርለታል።
ለሰው ልጅ ምርጡ ምግብ እንቁላል ይሆን?\nእንቁላል በቀላሉ መገኘት ይችላል፣ በቀላሉ መብሰል ይችላል፣ ዋጋውም ርካሽ የሚባል ሲሆን ለሰውነታችን በጣም አስፈላጊ የሆነው ፕሮቲንንም በብዛት ይዟል። በዩኒቨርሲቲ ኦፈ ከነቲከት የሥነ ምግብ ሳይንስ ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ክሪስቶፈር ብሌሶ እንደሚሉት እንቁላል ሁሉም አይነት አስፈላጊ ንጥረ ነገሮች ያሉት ሲሆን፤ አንድን ፍጥረት በተገቢው ሁኔታ ለማሳደግ ብቻውን በቂ ሊሆን እንደሚችል ይናገራሉ። • ቁርስ የቀኑ እጅግ አስፈላጊ ምግብ ነውን? ከዚህ በተጨማሪ እንቁላልን ከሌሎች ምግቦች ጋር ቀላቅሎ መመገብ ሰውነታችን ቫይታሚኖችን በቀላሉ ለመሰብሰብ ያስችለዋል። ለምሳሌ አንድ ጥናት እንደጠቆመው እንቁላልን ከአትክልት ጋር መመገብ በአትክልቱ ውስጥ ያለውን ቫይታሚን ኢ የመሰብሰብ ሥራን ቀላል ያደርገዋል። ነገር ግን በእንቁላል ውስጥ ያለው የኮሌስትሮል መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ለብዙ ዓመታት መከራከሪያ ሆኖ ቆይቷል። ከፍተኛ የኮሌስትሮል መጠን ደግሞ ለልብ በሽታዎች ያጋልጣል። በእንቁላል ውስጥ የሚገኘው አስኳል እስከ 185 ሚሊግራም የሚደርስ ኮሌስትሮል በውስጡ ይይዛል። ይህ ማለት እንቁላል ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል ማለት ነው? ኮሌስትሮል በጉበታችንና በጨጓራችን ውስጥ የሚመረት ቢጫ ቀለም ያለው 'ፋት' (ጮማ) ሲሆን በእያንዳንዱ የሰውነታችን ሴሎች ውስጥ ይገኛል። ብዙዎቻችን መጥፎ ነገር እንደሆነ እናስባለን። ነገር ግን ኮሌስትሮል ሴሎቻችንን ሸፍኖ ከተለያዩ ነገሮች ይጠብቃቸዋል። ከዚህ ባለፈም ቫይታሚን ዲ ለማምረትና እንደ ቴስቴስትሮን እና ኦስትሮጅን ያሉ ሆርሞኖችን ለማማንጨት ይረዳል። ምንም እንኳን ሰውነታችን ኮሌስትሮልን በራሱ ማማረት ቢችልም ከተለያዩ የእንስሳት ምርቶችም ሊያገኝ ይችላል። ለምሳሌ የበሬ ሥጋ፣ እንቁላል፣ አይብ እና ቅቤን መጥቀስ ይቻላል። • ምግብ ወሲብን የተሻለ ያደርጋል? መርሳት የሌለብን እንደ ልብ በሽታ ላሉ ከፍተኛ የጤና እክሎች የሚያጋልጠን ኮሌስትሮል በተፈጥሯዊ መንገድ የሚመረተው ሳይሆን፤ ሰው ሰራሽ የሆነው በተጠበሱ ምግቦች፣ ኬኮችና ሌሎችም ውስጥ የሚገኙት ናቸው። በእንቁላል ውስጥ የሚገኘው የኮሌስትሮል መጠን ከተለያዩ የእንስሳት ምርቶች የበለጠ ቢሆንም የስብ (ፋት) ክምችቱ ግን በጣም አነስተኛ ነው። ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ደግሞ ይህ የስብ ክምችት የደም ቧንቧችንን በመድፈን ለልብ በሽታ ሊያጋልጠን ይችላል። በቦስተን ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ኤሊዛቤት ጆንሰን እና ባልደረቦቻቸው በሰሩት ጥናት መሰረት ከቀጥተኛ የእንስሳት ተዋጽኦ የምናገኘው ኮሌስትሮል ለልብ ህመም እንደሚያጋልጥ ማረጋገጫ ማግኘት አልተቻለም። ሰውነታችን ኮሌስትሮልን እንደ እንቁላል ካሉ ምግቦች ማግኘት ከቻለ በራሱ የሚያመርተውን መጠን መቀነስ ይችላል። ይህ ማለት ደግሞ ተፈጥሯዊው ኮሌስትሮል መቼም ቢሆን በሰውነታችን ውስጥ መኖር ካለበት መጠን አያልፍም ማለት ነው። • እውን እንጀራ ሱስ ያስይዛል? የምርምርና ስርፀት ሥራዎች በኢትዮጵያ የዘርፉ ባለሙያዎች በቅርቡ በሰሩት ጥናት እንቁላል ምንም አይነት የጤና እክል እንደማያስከትል አረጋግጠናል እያሉ ነው። ተመራማሪዎቹ ባለፉት 17 ዓመታት 30 ሺህ ሰዎች ስለተመገቧቸው ምግቦች የሚያትቱ መረጃዎችን ሲያሰባስቡ ነበር። በጥናቱም መሰረት በየቀኑ እንቁላል የሚመገቡ ሰዎች በተለያዩ የልብ በሽታዎች የመሞት እድላቸው 18 በመቶ የቀነሰ መሆኑን የደረሱበት ሲሆን በደም ግፊት የመያዝ እድል ደግሞ እንቁላል ከማይመገቡት ጋር ሲነጻጸር 28 በመቶ የቀነሰ ነው። ምንም አንኳን እርግጠኛ ሆኖ መደምደም ባይቻልም እንቁላል ከጉዳቱ ጥቅሙ እንደሚጎላ መገመት ቀላል ነው። በእንቁላል ውስጥ የሚገኘው ኮላይን የተባለው ንጥረ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
8a7181e288a3f72a4ab97db2a901f8ab
e646ff0e6fde77ced2c9c53bf6448cd8
ጃፓን ለምግብ እርዳታና ሌሎች ለኢትዮጵያ የ30 ሚሊዮን እርዳታ ሰጠች
የዓለም ምግብ ፕሮግራም በበኩሉ የሚፈለገዉ እርዳታ ካልደረሰ አስከፊ ችግር ሊከሰት ይችላል አለ የጃፓን መንግስት ለኢትዮጵያ በድርቅ ለተጎዱና ለሌሎችም ምላሽ የሚሆን የ 30 ሚሊዮን እርዳታ ዛሬ ይፋ አድርጓል።የምግብ እስርዳታ የሚያስፈልጋቸዉ ዜጎችን ፍላጎት ለማሟላት የሚያስፈልገዉ የገንዘብ መጠን በአስቸኩዋይ ካልደረሰ አስከፊ ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስታዉቋል።የድምጽ ፋይሉን በመጫን የእስክንድር ፍሬዉን ዘገባ ያድምጡ።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/japan-food-aid-to-ethiopia-due-to-drought/3261906.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
96cffe7025da574a58c487052e874c45
0582cb850cd400216914d5dcbaf313df
ኢንጂነር ይልቃል ሰማያዊ ፓርቲን በድጋሚ ለመምራት ይወዳደራሉ
ሰማያዊ ፓርቲን ከምሥረታው ጀምሮ ላለፉት ሦስት ዓመታት በፕሬዚዳንትነት ሲመሩት የነበሩት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት፣ ፓርቲውን ዳግም ለመምራት ራሳቸውን ዕጩ ማድረጋቸውን አስታወቁ፡፡ፓርቲው ከተመሠረተ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደው ጠቅላላ ጉባዔ በመጪው ነሐሴ 16 እና 17 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚካሄድ ሲሆን፣ በወቅቱ በሚካሄደው የአዳዲስ አመራር ምርጫ ላይም በአሁኑ ጊዜ ፓርቲውን በፕሬዚዳንትነት እያገለገሉ የሚገኙት ኢንጂነር ይልቃል፣ ፓርቲውን ለቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት በመሪነት ለማገልገል በዕጩነት እንደሚቀርቡ አረጋግጠዋል፡፡በሰማያዊ ፓርቲ መተዳደርያ ደንብ መሠረት አንድ አባል ፓርቲውን ለመምራት ሁለት ጊዜ እንዲወዳደር ይፈቅዳል፡፡ ኢንጂነር ይልቃልም በዚህ ደንብ መሠረት ዳግም ፓርቲውን ለማገልገል እንደሚወዳደሩ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪም ስለሚኖረው ውድድርና እነማን ተፎካካሪዎቻቸው ሊሆኑ እንደሚችሉ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹እስካሁን ድረስ በግልጽ ራሱን ለፕሬዚዳንትነት ዕጩ አድርጐ ያቀረበ ተወዳዳሪ አባል የለም፡፡ እኔ ግን ለምክር ቤቱም ሆነ ለሚመለከታቸው አካላት ለፕሬዚዳንትነት እንደምወዳደር ይፋ አድርጌያለሁ፡፡ ተወዳዳሪዎች እንደሚኖሩ ጥርጥር የለውም፡፡ እስካሁን ይፋ ያደረገ ግን የለም፤›› ብለዋል፡፡በፓርቲው መተዳደርያ ደንብ ላይ ጠቅላላ ጉባዔ በየአንድ ዓመቱ እንደሚሰበሰብ ይደነግጋል፡፡ ይሁንና እስካሁን ድረስ ጠቅላላ ጉባዔ ተጠርቶ አያውቅም፡፡ ያልጠራችሁት ለምንድነው ለሚለው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹በየዓመቱ የሚለው እንደ ሁኔታው ነው የሚወሰነው፡፡ ፓርቲው በራሱ አስፈላጊ ነገሮች ሲኖሩና ጉባዔው ቢያያቸው ጥሩ ነው በሚል እሳቤ በየዓመቱ ጠቅላላ ጉባዔ ሊያካሂድ ይችላል እንጂ፣ በአስገዳጅነት በየዓመቱ መካሄድ አለበት የሚል ነገር የለም፡፡ በአስገዳጅነት መካሄድ አለበት የሚለው የሦስት ዓመቱ ነው፤›› ብለዋል፡፡‹‹የጠቅላላ ጉባዔ ሥልጣን ትልቅ ነው ይባላል፡፡ ነገር ግን በተግባር ደረጃ ሲታይ ግን በሦስት ዓመት አንዴ ነው የሚሰበሰበው፡፡ ያንን ለምን አንቀይረውም በማለት በዚያ መሠረት ነው ደንባችን ውስጥ ያካተትነው እንጂ፣ የጠቅላላ ጉባዔው የሥልጣን ዘመን ለሦስት ዓመት ጊዜ ነው፤›› በማለት ጨምረው አስረድተዋል፡፡የፓርቲው መተዳደርያ ደንብ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሥልጣንና ተግባር በሚመለከት የሚደነግገው አንቀጽ 13 ንዑስ አንቀጽ 13፣ ‹‹የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በድጋሚ ካልተመረጡ በስተቀር የሥራ ጊዜያቸው ሦስት ዓመት ይሆናል፡፡ በሊቀመንበርነት የኃላፊነት ቦታ ማገልገል የሚቻለው ለሁለት ተከታታይ ዙሮች ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ከአንድ የሥራ ዘመን ዕረፍት በኋላ ተመልሶ ለዚያው ቦታ ሊመረጥ ይችላል፤›› ይላል፡፡ ይሁን እንጂ ጠቅላላ ጉባዔው መደበኛ ጉባዔውን በዓመት አንድ ጊዜ ማካሄድ እንዳለበት ደንቡ በአንቀጽ 24 ላይ ይደነግጋል፡፡ ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ቢያጋጥምም ማራዘም የሚቻለው ለሦስት ወራት ብቻ እንደሆነ ያሰፍራል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ያሉት አስገዳጅ የሆነ የጉባዔው ስብሰባ በየሦስት ዓመቱ እንደሆነ የሚገልጽ አንቀጽ ግን የለም፡፡የፊታችን ቅዳሜና እሑድ በሚካሄደው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ በአጠቃላይ የነበረውን የፓርቲውን ጉዞ እንደሚገመገም የተገለጸ ሲሆን፣ በተጨማሪም ፓርቲው አሁን ካለበት ተነስቶ ምን ማድረግ አለበት የሚሉትን ጉዳዮች፣ እንዲሁም አጠቃላይ የአገሪቱንና የቀጣናውን የፖለቲካ ሁኔታ በመዳሰስ አቋም እንደሚወሰድ ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል፡፡በጠቅላላ ጉባዔው ለመሳተፍ ከመላው አገሪቱ የተውጣጡ 250 ያህል የፓርቲው አባላት እንደሚወከሉ ገልጸው፣ ‹‹ጠቅላላ ጉባዔውም ጠንካራ የትግል መንፈስ ለመፍጠርና ፓርቲው የነበሩትን ጠንካራና ደካማ ጐኖችን ገምግሞ፣ በጠንካራዎቹ ላይ የበለጠ ለመሥራት፣ ደካማ ጐኖችን ደግሞ እየቀረፈ በመሄድ ተጠናክሮ ለመሥራት አቅጣጫ ይቀመጣል፤›› በማለት ኢንጂነር ይልቃል የጠቅላላ ጉባዔው ውጤት ምን ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ሰማያዊ ፓርቲ በይፋ መመሥረቱን ያወጀው ታኅሳስ 2004 ዓ.ም. ላይ የነበረ ቢሆንም፣ በምሥረታው ወቅት ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባቱ የሚታወስ ነው፡፡ፓርቲውንና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን አወዛግቦ የነበረው ጉዳይ ደግሞ ፓርቲው ያቀርበው የነበረ የሕግ አግባብ ነው፡፡ ይህም አንድ ፓርቲ የምሥረታ ጥያቄውን ለምርጫ ቦርድ ባቀረበ ሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ ምላሽ ካልተሰጠው ዕውቅና እንደተሰጠው ይቆጠራል የሚለው ነው፡፡ በዚህም መሠረት ፓርቲው በታኅሳስ 2004 ዓ.ም. በሰጠው መግለጫ መመሥረቱን ይፋ ሲያደርግ፣ ከምርጫ ቦርድ ዕውቅና አግኝቶ መንቀሳቀስ የጀመረው ግን ከሐምሌ 3 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ነው፡፡
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/8404
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
1ace737574924851bdee90f05c5f39e5
6f25bfd8796fda2ea66336238251826f
የ40/60 ቤቶችን ብረት በመዝረፍ የተጠረጠሩ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተጠየቀባቸው
የቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ እየገነባቸው ለሚገኙት የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ የተገዙ ብረቶችን በመዝረፍ ለግል ጥቅማቸው በማዋል ተጠርጥረው በታሰሩ ሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ፣ ለተጨማሪ ምርመራ የ14 ቀናት ጊዜ ተጠየቀባቸው፡፡ተጠርጣሪዎቹ የኢንተርፕራይዙ የንብረት አስተዳደር ሠራተኛ መብራቱ ካሳሁን፣ የንብረት ክፍል ሠራተኛ ሔኖክ ነጋሳ፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ሥራ አስኪያጅ ዳዊት ገብረ እግዚአብሔር፣ ነጋዴዎች ታከለ ግርማ፣ ይስሀቅ ለማ፣ ጌታቸው ዩሱፍና የገልባጭ ተሽከርካሪ ሾፌር ዕቁባይ ገብረ ጊዮርጊስ መሆናቸውን፣ በአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ መርማሪ ፖሊስ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት አስረድቷል፡፡ከሦስት ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለውን ባለስድትና ባለ ስምንት ስታፋ ብረቶች ከመጋዘን በሐሰተኛ ሰነድ ዘርፈው መውሰዳቸውንና በተለያዩ ቦታዎች በመበታተን፣ በመሸጥና በመሸሸግ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸውን መርማሪ ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስረድቷል፡፡ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ባደረገው ምርመራ የተለያዩ ሰነዶችን መሰብሰቡን ገልጾ ያልተያዙ ተጠርጣሪዎች መኖራቸውን፣ የጣት አሻራ መወሰድ እንደሚቀረውና የተወሰኑ ብረቶችን ማስመለስ እንደሚቀረው በማስረዳት፣ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡ ተከሳሾቹ የተጠረጠሩበት ጉዳይ ዋስትና እንደማያስከለክል አስረድተው ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡ነገር ግን መርማሪ ፖሊስ ጥያቄውን በመቃወም በዋስ ቢለቀቁ ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን ሊያስጠፉ እንደሚችሉ፣ ሥልጣን ያላቸው የመንግሥት ሠራተኞች በመሆናቸው ሰነዶችን ሊያጠፉ እንደሚችሉ አስረድቶ፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ለመርማሪው የሰባት ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ሰጥቶ የዋስትና ጥያቄውን በማለፍ፣ ለታኅሳስ 11 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡      
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%8B%A84060-%E1%89%A4%E1%89%B6%E1%89%BD%E1%8A%95-%E1%89%A5%E1%88%A8%E1%89%B5-%E1%89%A0%E1%88%98%E1%8B%9D%E1%88%A8%E1%8D%8D-%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%8C%A0%E1%88%A8%E1%8C%A0%E1%88%A9-%E1%89%B0%E1%8C%A8%E1%88%9B%E1%88%AA-%E1%8B%A8%E1%88%9D%E1%88%AD%E1%88%98%E1%88%AB-%E1%8C%8A%E1%8B%9C-%E1%89%B0%E1%8C%A0%E1%8B%A8%E1%89%80%E1%89%A3%E1%89%B8%E1%8B%8D
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
41f642ab30376bab5e96da540d7788ed
5ac262c14313da8274724eb2022a9e70
በግጭት የተሳተፉ አመራሮች ሰሞኑን በቁጥጥር ሥር እንደሚውሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ
በአገሪቱ ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት ውሳኔ መሠረት በአገሪቱ የፖለቲካ ቀውስ የፈጠሩ ኃይሎችንና አመራሮችን በሕግ መጠየቅ እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ጥቅምት 30 ቀን 2010 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤታቸው ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ አብዛኞቹ የግጭት ፈጣሪዎች በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ሥር የዋሉ መሆኑንና ቀሪዎቹን በዚህ ሳምንት ውስጥ በቁጥጥር ሥር እንደሚውሉ አረጋግጠዋል፡፡ ከፀረ ሰላምና አሸባሪ ኃይሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር በቅርቡ በአገሪቷ የተከሰተውን አለመረጋጋት ለራሳቸው የፖለቲካ ፍላጎት በመጠቀም እየሠሩ የነበሩና የሚገኙ አመራሮች ይጠየቃሉ ብለዋል፡፡ በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት የኪራይ ሰብሳቢዎችና የኢሕአዴግ አመራሮች ተሳትፎ እንደነበረበት ያስታወቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በአወዳይ ላይ ዜጎች መቀላታቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ የኦሮሚያ ፖሊስ ፈጥኖ ባይደርስ ኖሮ እልቂቱ የከፋ ነበር ብለዋል፡፡ ‹‹የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ንፁህ ፖሊስ ነው፤ ሕዝባዊም ነው፤›› ሲሉ አወድሰዋል፡፡
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/2712
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
02d5980b1d59aab9c8bab857fea39533
ca6a82752dbf21da5639127483d9baa8
በኡጋንዳ 30 ባለስልጣናት በመፈንቅለ መንግስት ሴራ መታሰራቸው ውጥረት ፈጥሯል
የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዮሪ ሙሴቬኒ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣኔን ለመቀማት ሲያሴሩ ደርሼባቸዋለሁ ያሏቸውን 30 ያህል የአገሪቱ ከፍተኛ የጦር መሪዎችና ባለስልጣናት ማሳሰራቸውን ተከትሎ በአገሪቱ ውጥረት መንገሱ ተዘገበ፡፡ከአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በመተባበር በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት ለመጣል አሲረዋል የተባሉት የጦር መሪዎችና ባለስልጣናቱ፣ ባለፈው ሳምንት መታሰራቸውን ያስታወሰው አሶሼትድ ፕሬስ፤ ይህን ተከትሎም ድርጊቱን የተቃወሙ ታጣቂዎች በመንግስት ፖሊሶች ላይ ተኩስ መክፈታቸውንና ውጥረት መንገሱን ገልጧል፡፡የአገሪቱ ፖሊስ ከመፈንቅለ መንግስት ሴራው ጋር ንክኪ አላቸው ያላቸውን በርካታ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትንና ደጋፊዎችን ማሰር መቀጠሉን የጠቀሰው ዘገባው፤ 12 ያህል የተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊ ታጣቂዎች፣ ኡጋንዳ ፒዩፕልስ ኮንግረስ የተባለው ፓርቲ አባል የሆኑትንና በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉትን ዳን ኦላ ኦዲያ የተባሉ ግለሰብ ለማስለቀቅ፣ባለፈው እሁድ በፖሊስ ላይ ተኩስ በመክፈት ብጥብጥ መፍጠራቸውን ጠቁሟል፡፡  ባለፈው የካቲት ወር በተካሄደው የአገሪቱ ምርጫ የሙሴቬኒ ተፎካካሪ ሆነው የቀረቡትና የምርጫውን ውጤት በመቃወም ብጥብጥ አስነስተዋል በሚል ወደ ወህኒ የተወረወሩት ፎረም ፎር ቼንጅ የተባለው ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ዶ/ር ኪዛ ቢሲጂ፤ባለፈው ረቡዕ በአገር ክህደት ተከሰው በናካዋ ከተማ ፍርድ ቤት በቀረቡበት ወቅት፣ በአካባቢው ከፍተኛ ውጥረት ነግሶ እንደነበር ዘገባው አመልክቷል፡፡ መፈንቅለ መንግስቱን የጠነሰሱት ኪዛ ቢሲጄ የተባሉ የአንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር እንደሆኑ መነገሩን የጠቆመው ዘገባው፣ ግለሰቡ በአገር ክህደት ከተከሰሱት ቢሲጂ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት እንዳላቸው ገልጾ፣ ቢሲጂ በመንፈንቅለ መንግስቱ ሴራ እጃቸው ሊኖርበት እንደሚችል መጠርጠሩን አስታውቋል፡፡ቪኦኤ በበኩሉ፤ የአገሪቱ መንግስት ባለስልጣናቱን በመፈንቅለ መንግስት ሴራ ጠርጥሮ ማሰሩ በቀጣይም ከፍተኛ ብጥብጥ ሊፈጥርና አገሪቱን ወደ ከፋ ቀውስ ሊከታት እንደሚችል እየተነገረ እንደሚገኝ ዘግቧል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=18385:%E1%89%A0%E1%8A%A1%E1%8C%8B%E1%8A%95%E1%8B%B3-30-%E1%89%A3%E1%88%88%E1%88%B5%E1%88%8D%E1%8C%A3%E1%8A%93%E1%89%B5-%E1%89%A0%E1%88%98%E1%8D%88%E1%8A%95%E1%89%85%E1%88%88-%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%B5%E1%89%B5-%E1%88%B4%E1%88%AB-%E1%88%98%E1%89%B3%E1%88%B0%E1%88%AB%E1%89%B8%E1%8B%8D-%E1%8B%8D%E1%8C%A5%E1%88%A8%E1%89%B5-%E1%8D%88%E1%8C%A5%E1%88%AF%E1%88%8D&Itemid=212
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f733ada59b037dc0071da0cf52db94fd
c56a445992ccb830fb5712a2f1493ca0
በባሕር ዳር ከተማ በርካታ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ
የአማራ ክልል አድማ ብተና 2ኛ ሻለቃ 1ኛ ሻምበል ምክትል ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ታለማ ዳኛ ለአብመድ እንደተናሩት፤ በ20 ጆንያዎች የተቋጠረ 497 ሽጉጥ እና ወደ 46 ሺህ የሚገመት ጥይት በባሕር ዳር ከተማ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነትና ከኅብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሠረት ከነዳጅ ጋር ተቀላቅሎ ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ በገባ የነዳጅ ማመላለሻ ቦቴ ውስጥ ሲጓጓዝ ነው ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያው በቁጥጥር ስር የዋለው፡፡ከትናንት ምሽት ጀምሮ በተደረገ ክትትል ነው ባሕር ዳር ከተማ ጣና ክፍለ ከተማ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያው በቁጥጥር ስር የዋለው፡፡አሽከርካሪው ለማምለጥ ሙከራ አድርጎ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ያስታወቁት ምክትል ኢንስፔክተር ታለማ ነዳጁ ከባሕር ዳር አልፎ የሚሄድ እንደነበርና ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያውን ከቦቴው ለማውጣት የሚያገለግል ብረት ከተሽከርካሪው መገኘቱን አመልክተዋል፡፡
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/31352/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
beddd20d92ba7652a1d49b684b99db0b
eb18a57edcb010752485d227ad86b8f8
ባሕር ዳር በጣና ላይ የጀልባ ትርኢትና በሌሎች መሰናዶዎች እንግዶችን ለማስተናገድ ተዘጋጅታለች፡፡
ባሕር ዳር ጥር 7/2012ዓ.ም (አብመድ) ሆቴሎችና አስጎብኚ ድርጅቶች ለጥምቀት በዓል የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ተዘጋጅተዋል፡፡ለእንግዶች አቀባበል ያደረጉትን ዝግጅት በተመለከተ አብመድ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳድር የሚገኙ የሆቴል ሥራ አስኪያጅ እና አስጎብኚ ድርጅቶችን አነጋግሯል፡፡ የዩኒሰን ሆቴል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ አክሊሉ ባለፈው የልደት በዓል ጥሩ ዝግጅት እና አፈጻጸም እንደነበራቸው ተናግረዋል፡፡ ለጥምቀትም ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ሃገር ለሚመጡ እንግዶች እንደየ ባህላቸው አገልግሎት ለመስጠት ሆቴሉ በቂ ዝግጅት አድርጓል ነው ያሉት፡፡የባሕር ዳር ከተማ የአስጎብኚዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት አቶ ማስተዋል ዘለቀ ደግሞ ለጥምቀት በዓል የበጎ ፈቃድ አግልግሎት የሚሰጡ 28 ወጣቶች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ የጎንደርን የጥምቀት በዓል ለመታደም የሚመጡ እንግዶች በባሕር ዳር የሚኖራቸውን ቆይታ ያማረ እና አይረሴ ለማድረግ ማኅበሩ መዘጋጀቱንም ነው የተናገሩት፡፡ ከዝግጅቶች መካከልም ጥር 14/2012 ዓ.ም በጣና ሐይቅ ላይ የሚካሄደው የጀልባ ትዕይንት ይጠቀሳል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%89%a3%e1%88%95%e1%88%ad-%e1%8b%b3%e1%88%ad-%e1%89%a0%e1%8c%a3%e1%8a%93-%e1%88%8b%e1%8b%ad-%e1%8b%a8%e1%8c%80%e1%88%8d%e1%89%a3-%e1%89%b5%e1%88%ad%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8a%93-%e1%89%a0%e1%88%8c/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
516ba357e3695520a652c2b3725371f8
afd67eb9614d258a9386d57081f69c9e
ባለፉት 24 ሰአታት ለ4 ሺህ 225 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 11 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 9 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 24 ሰአታት ለ4 ሺህ 225 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 11 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።ሚኒስትሯ በፌስቡክ ገጻቸው እንዳስታወቁት ቫይረሱ የተገኘባቸው 5 ወንድ እና 6 ሴት ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ከ17 እስከ 45 አመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው።ከእነዚህ ውስጥ አራቱ ከአዲስ አበባ ሲሆኑ፥ 6 ከሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ለይቶ ማቆያ ፣አንድ ሰው ከአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አጣዬ ከተማ ለይቶ ማቆያ ናቸው፡፡ቫይረሱ ከተገኘባቸው ውስጥ ሰባቱ የውጭ ሃገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ሲሆኑ ሶስቱ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያላቸው እንዲሁም አንደኛው ንክኪም ሆነ የውጭ ሃገር ጉዞ የሌለው ነው ብለዋል።በዚህም አሁን ላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች  ቁጥር 317 ደርሷል፡፡እስካሁን 113 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት 197 ሰዎች ደግሞ በህክምና ላይ ይገኛል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a3%e1%88%88%e1%8d%89%e1%89%b5-24-%e1%88%b0%e1%8a%a0%e1%89%b3%e1%89%b5-%e1%88%884-%e1%88%ba%e1%88%85-225-%e1%88%b0%e1%8b%8e%e1%89%bd-%e1%8b%a8%e1%88%8b%e1%89%a6%e1%88%ab%e1%89%b6%e1%88%aa/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f785875b8b9a38373c834c49d11b36d1
9b895abb338607b96935805ce73b361d
በጎንደር ከተማ የሽብር ተግባር ሊፈፅሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በጎንደር ከተማ የሽብር ተግባር ሊፈፅሙ በዝግጅት ላይ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ ።በከተማዋ ማራኪ ክፍለ ከተማ ብጥብጥና የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ሲቀሰቅሱ የነበሩ ሶስት የባጃጅ አሽከርካሪዎች እና በመድሃኒዓለም ክፍለ ከተማ ደግሞ ለአድማ የሚያነሳሳ መልዕክት የያዘ ወረቀት ሲበትኑ የነበሩ አምስት የፀረ ሠላም ኃይሎች ናቸው የተያዙት።ግለሰቦቹ በከተማዋ ነዎሪዎችና በፀጥታ ኃይሎች የተቀናጀ ስራ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ ተመልክቷል። በተጨማሪም ከሶስት ቀን በፊት በከተማዋ ላይ የሽብር ተግባር ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሁለት የፀረ ሠላም ሀይሎች ከያዙት ቦምብ ጋር በፀጥታ ሀይሎች አማካኝነት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ቢሮው አስታውሷል።በሌላ በኩል ነሃሴ 6 2009 ምሽት 1 ሰአት ከ50 በባህር ዳር ሰፈነ ሰላም ክፍለ ከተማ አካባቢ ቦምብ በመወርወር ለሁለት ሰዎች መቁሰል ምክንያት ሆነዋል የተባሉ ሁለት ተጠርጣሪዎች በደቡብ ጎንደር ዞን ሊቦ ከምከም ወረዳ አምቦ ቀበሌ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል(ኤፍ.ቢ.ሲ) ።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/29306/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
4acd70377521db08843aa6de4cccd4ff
01daa25af9657e855e41766969e5368e
የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው ዓለም ለቆመችለት መርህ ያላትን ታማኝነት ያረጋገጠ ነው – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ ) የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው ዓለም ለቆመችለት መርህ ያላትን ታማኝነት ያረጋገጠ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በህዳሴ ግድብና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡በመግለጫቸውም የግድቡ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው ዓለም ለቆመችለት መርህ ያላትን ታማኝነት ያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ከዚህ ባለፈም ኢትዮጵያውያን ያቀዱትን የሚያሳኩ ሀዝቦች መሆናቸውን ለዓለም ያስመሰከሩበት መሆኑንም አውስተዋል፡፡በህዳሴ ግድብ ላይ እየተካሄደ ያለው የሶስትዮሽ ድርድር በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት መመራቱ ለኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ድል መሆኑንም አስረድተዋል።በመግለጫው የውሃ ሙሌቱ በድል መጠናቀቁ ኢትዮጵያውያንን በዓለም መድረክ ከፍ አድርጓልም ነው ያሉት።በሌላ በኩል በባህር ማዶ በችግር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተም ከዓለም አቀፉ ፍልሰተኞች ድርጅት እና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡እስካሁንም ከሳዑዲ ዓረቢያ፣ ኩዌት፣ ቤሩት እና ከሌሎች ሃገራት 30 ሺህ 87 ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ከዚህ ባለፈም ወደ ሃገር ቤት የሚመለሱትን ዜጎች የማቋቋም ስራ እንደሚሰራም አስታውቀዋል፡፡በሌላ በኩል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኮቪድ19 ሳቢያ ችግር ውስጥ ለገቡ ዜጎች ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ቃል አቀባዩ ገልጸዋል፡፡በምስክር ስናፍቅ እና ስላባት ማናዬ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%88%85%e1%8b%b3%e1%88%b4-%e1%8c%8d%e1%8b%b5%e1%89%a5-%e1%8b%a8%e1%88%98%e1%8c%80%e1%88%98%e1%88%aa%e1%8b%ab-%e1%8b%99%e1%88%ad-%e1%8b%a8%e1%8b%8d%e1%88%83-%e1%88%99%e1%88%8c%e1%89%b5-2/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e896557d4200fe016b437761f05f6739
5219b0a1422ea8c6be13e00f1e4eaffc
የሰላም ኮንፈረንስ በይርጋለም ከተማ
የአገር ሸማግሌዎች ፣ የሀይማኖት አባቶችና ወጣቶች የተገኙበት የሰላም ኮንፈረንስ በይርጋለም ከተማ ተካሂዷል፡፡ወጣቶች ጥያቄያቸው ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ የሲዳማ "ሃላሌ" ባህላዊ ስርዓት ተከትለው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠይቁ የሲዳማ አገር ሸማግሌዎች አሳስበዋል፡፡"ኤጄቶዎች" ወይም የሲዳማ ወጣቶችና አገር ሸማግሌዎች የጋራ የሰላም ኮንፈረንስ ማካሄድ ከጀመሩ በኋላ ለውጥ መታየቱን የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ አስታውቋል፡፡"ኤጄቶዎች" የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ የሚረጋገጥበትን ህዝበ ውሣኔ እንዲያስፈፅም የክልሉ ምክር ቤት ለምርጫ ኮሚሽን ቢስታውቅም ዘግይቷል ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/yergalem-peace-conference-1-30-2019/4765690.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
41fca0cb804a9b7883787d6f4463dd42
8703949006519fc8763580785a0eb18e
የጋዜጠኛ መሃመድ ስራጅ አጭር የህይወት ታሪክ
• ሙሉ ስም ከነአያት፡___መሃመድ ስራጅ ዋበላ • እምነት፡- ሙስሊም • ዕድሜ፡__38 • ጾታ፡__ወንድ • ዜግነት፡- ኢትዮጵያዊ • አሁን የሚሰራው ሥራ (መስሪያ ቤት)፡- የማስታወቂያ ባለሙያ፤ደራሲ፤የማህበረሰብ አንቂና ጋዜጠኛ ሲሆን በአዋሽ 90.7 ኤፍ ኤም ራዲዮ ጣቢያ በዋና ስራ አስኪያጅነት እየሰራ ይገኛል፡፡ የት/ ደረጃ፡- የመጀመሪያ ድግሪ በቋንቋና ስነ-ጽሁፍ ፤በሁለተኛ ድግሪ በማህበረሰብ ጥናት (Sociology) በአሁን ሰአት ደግሞ በሚችጋን ዩኒቨርሲቲ Leadership and Management (Leading People and Teams Specialization) Masters Program From University of Michigan. የስራ ልምድ፡_ ከ19/97 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁኗ ሰአት ድረስ 18 አመት በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት ከባለሙያ እስከ ከፍተኛ ሃላፊነት፤በግል ስራ ድርጅት አስተዳደር፤በጋዜጠኝነትና በማህበረሰብ አንቂነት እየሰራ ሲሆን በአሁን ሰአትም በአለም አቀፍ ተደማጭነት ባለው ተወዳጅና ተመራጭ የራዲዮ ጣቢያ አዋሽ 90.7 ኤፍ ኤም ራዲዮ በስራ አስኪያጅነት እየሰራ የሚገኝ ሲሆን በአመራሩም በሃገራችን ካሉ ሚዲያዎች በዚሁ አመት በኢትጵ ብዙሃን መገናኛ ተሸላሚ እንዲሆን አድርጓል፡፡ • ጋዜጠኛ መሃመድ ስራጅ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁኗ ሰአት ድረስ ሃገሩን በተሰማራባቸው ዘርፎች በታማኝነት፤በቅንነትና ያለ አድሎ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ በጋዜጠኝነትና በተለያዩ የስራ ዘርፎች ከ18 አመታት በላይ ያገለገለ ሲሆን በዋናነት ከሰራባቸው የሚደያ ተቋማቶች መካከል የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቭዥን፤በፋና፤ በዋልታ፤በኢ.ቢ.ኤስ፤በኤፍ.ኤም.አዲስ 97.1፤በአሐዱ ኤፍ.ኤም.94.3፤በአሁኑ ሰአት ደግሞ በአዋሽ 90.7 ኤፍ.ኤም በስራ አስኪያጅነት እየሰራ ይገኛል፡፡ • ጋዜጠኛ መሃመድ ሃገሩን በተለያዩ ዘርፎች ማለትም በተለያዩ ከዝቅተኛ እስከ ከፍተኛ የሃላፊነት ቦታዎች ሰርቷል፤በማህበረሰብ አንቂነት፤በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች፤ከግለሰብ አስከ ክልልና ብሔሮች መካከል በእርቅና በሰላም፤በባህልና በቱሪዝም፤በሐይማኖት አብሮነት፤በዲሞክራሲና ኢኮኖሚ ግንባታ፤በስራ ባህል መዳበር፤ • የኢትዮጵያ ኩላሊት ህሙማን እጥበት ማህበርን በመመስረት፤ገንዘብ በማሰባሰብና በመደገፍ፣ የብሔራዊ ደም ባንክ አገልግሎትን በመደገፍና ደም በማሰባሰብ፣ በጎዳና ላይ ህጻናቶች በበርካታ የህብረተሰባዊ ድጋፍ አገልግሎቶች ላይ ተሳትፎ በማድረግ እና በማህበራዊ ጉዳዮች በመንቀሳቀስ አመርቂ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በተለይ የህጻናት ማሳደጊያዎችን ገቢ በማሰባሰብ፤በመደገፍና በማስተባበር የጎዳና ተዳዳሪዎችን በመመገብና ከሱሰኝነት እንዲላቀቁ በማድረግ፤ በትምህርት፣ በጤና፣ በጋብቻ እና በኢንተርፕርነሮች ዘርፎች ባለሞያዎችን በማስተባበር በነጻ ስልጠና ለተለያዩ ተቋማትና ግለሰቦች እየሰጠም እያሰጠም ይገኛል፡፡ • ጋዜጠኛና ደራሲ መሃመድ ስራጅ በተለያየ ጊዜያት ከ500,000 ሰው በላይ ጊዜያዊ የስራ እድል ፈጠራ፤በአወንታዊና ሀገራዊ አስተሳሰብ፤በተለያዩ ሃገር በቀል ፕሮጀክቶች፤በሀገርና በስብእና ገጽታ ግንባታ፤በህዳሴ ግድብ ገቢ ማሰባሰብ፤በ6ተኛው ሃገር አቀፍ ምርጫ፤በሰሜኑ አካባቢ በተከሰተው ጦርነት ከገቢ ማሰባሰብ እስከ የጦር ዘገባ፤ • ለተከታታይ 10 አመታት በተለያዩ በክልልና በማህበረሰብ ራዲዮ፤በሚኒ-ሚዲያና በተለያዩ ክበባት በተግባቦት፤በመሰራዊ ጋዜጠኝነት፤በራስ ማሰተዳደር እና በሌሎች የህይወትና የስራ ክህሎቶች ከ1,5000 ሰው በላይ በነጻ ስልጠና በመስጠት፤በኮቪድ-19 የግንዛቤ ፈጠራና ገቢ ማሰባሰብ፤የየክልል ልማት ማህበሮች ገቢ ማሰባሰብ፤በህገ-ወጥ ስደት፤በአረንጓዴ አሻራ፤በዲፕሎማሲ፤በአዳዲስ ፈጠራና በቴክኖሎጂ፤በሃገራዊ መግባባትና የተለያዩ የአስተሳሰብ ከፍታን የሚያሳዩ ሃገር የሚያሻግሩ በራሱ ወጪ ስድስት(6)ታትመው ለንባብ የበቁ መጽሐፎች ‹‹ከሰማይ ውስጥ››፤‹‹ከፍታ››፤ ‹‹ጋብቻና ፍቅር››፤‹‹መሪ››፤‹‹ይመለከተኛል ኢትዮጵያ›› የተሰኙ መጽሃፎችን ለሃገሩ አንባቢዎች ያበረከተና ሌሎች በአሁን ሰአት ለህትመት የተዘጋጁ ከስምንት (8) በላይ እጅግ ትውልድን የሚቀይሩ አወንታዊ አስተሳሰብን፤የስራ ባህልን፤የቁጠባ ባህልን፤የንባብ ባህልንና የአብሮነት እሴትን የሚያዳብሩና ለጥናትና ምርምር መነሻ የሚሆኑ ዝግጅትና አርትኦት ስራቸው ጥንቅቅ ያሉ አእምሮን የሚለሙ መጽሃፎቶች በእጁ ላይ ይገኛሉ፡፡ ለነዚህም ስራዎቹ ምስክርነት መንግታዊና መንግታዊ ካልሆኑ ተቋማት ከመቶ ሰማንያ (180) በላይ የምስጋናና የምስክር ወረቀቶች በማህደሩ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከ500,000 (ከአምስት መቶ ሺ) በላይ ተከታይ ባለው የግል ማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም አነቃቂና ሃገራዊ ሃሳቦችን በማንሳት ማህበረሰቡን በሃገር ፍቅር፤በመልካም ስነ ምግባር በማሳወቅ፤በመቀስቀስና ተአማኝ መረጃ በመስጠት ሃገሩ በፈለገችው ቦታዎች ሁሉ በፍትሃዊነት፤በታማኝነትና በልማታዊ አስተሳሰብ እስካሁኗ ሰአት ድረስ ሃገሩን በቁርጠኝነት እያገለገለ ይገኛል፡፡ • ጋዜጠኛና ደራሲ መሃመድ ስራጅ በአሁን ሰአትም በአዋሽ 90.7 ኤፍ.ኤም ከስራ አስኪያጅነት በተጨማሪ ተወዳጅና ትውልድ ገንቢ የሆኑ ‹‹ከአባይ ጓዳ››፤ ‹‹ይመለከተኛል ኢትዮጵያ››፤ ‹‹አዋሽ ስፔሻል›› ፤ “አዋሽ ወቅታዊ”ና ሌሎችንም ፕሮግራሞችን በዋና አዘጋጅነት እየሰራ ይገኛል፡፡
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
a1e289c3d18e2f8acae5f4c85ef5cc79
5be0f5a37a03c78cfb5a8e3cf943f928
አራት ሜክሲኳውያን ተማሪዎች ከጾታዊ ጥቃት የሚከላከል ካፖርት ፈልስፈዋል። የካፖርቱ እጀታ የተሰራው ከሚነዝር ኤሌክትሪክ ሲሆን፤ ጥቃት የሚሰነዝር ሰው ካፖርቱን የለበሰን ሰው ክንድ ሲይዝ እንዲነዝረው ያደርጋል።
የሜክሲኮ ተማሪዎች ወሲባዊ ትንኮሳን የሚከላከል ካፖርት ፈለሰፉ\nየካፖርቱ እጀታ ከነዛሪ ኤሌክትረክ የተሰራ ነው ተማሪዎቹ ካፖርቱን የፈለሰፉት ሀገራቸው ውስጥ የተንሰራፋውን ወሲባዊ ትንኮሳ ለመከላከል ሲሆን፤ "ውሜን ዌረብል"ወይም "እንስቶች የሚለብሱት" የተሰኘ ስያሜ ተሰጥቶታል። • ሴቶች እንዲደፈሩ ያበረታታው ግብጻዊ የህግ ባለሙያ ተፈረደበት • ካይሮ፡ ለሴቶች በጣም አደገኛ ከሆኑ ከተሞች አንዷ ከአራቱ ተማሪዎች ሁለቱ አናይድ ፓራ ኮሬዝ እና ኤስቴላ ጎሜዝ የሜካትሮኒክስ ኢንጅነሪንግ ተማሪዎች ናቸው። የሮቦቲክስ ተማሪዋ ግዌን ፓርክ እንዲሁም የህግ ተማሪ ጉዋዱልፔ ማርቲኔዝም ተሳትፈዋል። አራቱ የካፖርቱ ፈልሳፊዎች ፈልሳፊዎቹ የፈጠራ ኃሳቡ ብልጭ ያለላቸው ለአንድ የትምህርት ክፍለ ጊዜ ፕሮጀክት ሲያውጠነጥኑ ነበር። አናይድ ፓራ "ብዙ ሴት ጓደኞቻችን የሀይል ጥቃት ይደርስባቸዋል። ጾታን መሰረት ስላደረገ ጥቃት ጥናት ከሰራን በኃላ ካፖርቱን ለመስራት ወሰንን" ትላለች። በሚኖሩበት የሜክሲኮዋ ፑቤላ ግዛት በየቀኑ ወሲባዊ ትንኮሳ ይደርሳል። ካፖርቱ የተሰራው ከጥጥ ሲሆን፤ ዘጠኝ ቮልት የኤሌክትሪክ ሀይል የሚያመነጭ ባትሪ ውስጡ ተቀብሯል። የኤሌክትሪክ ገመዱ በካፖርቱ ውስጥ ለውስጥ ይዘዋወራል። ካፖርቱ ኤሌክትሪክ እንዲያመነጭ መዝጊያው (ዚፕ) ላይ ማብሪያና ማጥፊያ ተገጥሞለታል። ካፖርቱ የሚሰራው ቀልፉን በመጫን ነው አንድ ሰው ካፓርቱን የለበሰ ሰውን ለማጥቃት አስቦ የተጠቂውን ክንድ ቢይዝ የኤሌክትሪክ ንዝረት ይከተላል። አጥቂው በኤሌክትሪክ ንዝረቱ ሲንዘፈዘፍ ተጠቂው ከአካባቢው ርቆ ለመሸሽ ጊዜ ያገኛል። የህግ ተማሪው ጉዋዱልፔ ማርቲኔዝ፤ ካፖርቱን ጥቅም ላይ ማዋል የህግ ጥያቄ እንደማያስነሳ ሲያስረግጥ "አላማው ራስን መከላከል ብቻ ነው" በማለት ነው። ካፖርቱ የሚያመነጨው የኤሌክትሪክ ንዝረት ለህይወት ስለማያሰጋ እንደ መሳሪያ ሊቆጠር እንደማይቻልም ያስረዳል። • ሞርጋን ፍሪማን በፆታዊ ትንኮሳ ለቀረበባቸው ውንጀላ ይቅርታ ጠየቁ • ቢል ኮዝቢና ፖላንስኪ ከኦስካር አካዳሚ ተባረሩ የካፖርቱን ንድፈ ሀሳብ የሚያሳይ የሙከታ ስራ (ፕሮቶታይፕ) ለማጠናቀቅ ሶስት ወር ወስዶባቸወሰል። በቀጣይ የኤሌክትሪክ ኃይሉን ከካፖርቱ እጀታ በዘለለ በሌሎች የካፖርቱ ክፍሎችም የመግጠም እቅድ አላቸው። ተማሪዎቹ ተመሳሳይ መንገድ በመጠቀም ነዛሪ ካናቴራ፣ ቀሚስና ሱሪም ለመስራት አስበዋል። ካፖርቱ ገበያ ላይ ከዋለ 50 ዶላር የሚሸጥ ይሆናል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
3277fc6d984bc7a4f40c4d8700ba6534
e8448e3362bf4c1a7797852c4f299444
ሰርከም ሚኒራል በአፋር ፖታሽ እንዲያወጣ ፈቃድ ተሰጠው
ሰርከም ሚኒራል የተባለው የእንግሊዝ የማዕድን ኩባንያ፣ የፖታሽ ማዕድን በአፋር ለማውጣት የሚያስችለውን ስምምነት ከማዕድን፣ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር ጋር ተፈራረመ፡፡ስምምነቱን ሚኒስትሩ አቶ ሞቱማ መቃሳና የሰርከም ሚኒራል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብራድ ሚልስ በሚኒስቴሩ ቅጥር ግቢ ዓርብ መጋቢት 29 ቀን 2009 ዓ.ም ከቀትር በኋላ ተፈራርመዋል፡፡ከፊርማው ሥነ ሥርዓት በኋላ ኩባንያው ሥራውን በሁለት ወራት ውስጥ ይጀምራል ተብሏል፡፡ ለኩባንያው የተሰጠው የከፍተኛ ደረጃ የማዕድን የማውጣት ፈቃድ ለሃያ ዓመት ፀንቶ የሚቆይ ሲሆን፣ በባለፈቃዱ ጥያቄ መሠረት የፈቃድ ዕድሳት ጊዜ ከአሥር ዓመታት ላልበለጠ ጊዜ ሊታደስ ይችላል፡፡ይህ የማዕድን የማውጣት ፈቃድ ኩባንያው በአፋር ክልል ዳሎል አካባቢ በ365 ኪሎ ሜትር ካሬ ውስጥ የሚገኝ 4.9 ቢሊዮን ቶን የፖታሽ ማዕድን ላይ መብት እንዲኖረው ያደርጋል፡፡ከፖታሽ ማዕድን ጋር በተያያዘ ሰርከም ሚኒራል ማዕድኑን የማውጣት ፈቃድ ያገኘ ሁለተኛው ኩባንያ ሆኗል፡፡ ከአሁን ቀደም አላና ፖታሽ የተባለው የካናዳ ኩባንያ ፈቃዱን አግኝቶ ነበር፡፡ በቅርቡም ያራ የተባለው ዓለም አቀፍ ኩባንያ የፖታሽ ማዕድን ለማውጣት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ጥያቄውም በመንግሥት እየታየ እንደሆን ተገልጿል፡፡ ያራ ኢትዮጵያ ወደ አገር ውስጥ የምታስገባቸውን ማዳበሪያዎች ለብዙ ዓመታት ሲያቀርብ እንደነበር ይታወሳል፡፡በፖታሽ ላይ የተጠኑ ጥናቶች እንደሚያሳዩት በዳሎል ብቻ 12 ቢሊዮን እስከ 14 ቢሊዮን ቶን የሚጠጋ የፖታሽ ማዕድን አለ፡፡ሰርከም ሚኒራል ከዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ በፖታሽ ፍለጋ ላይ ነበረ፡፡ ከአራት ዓመት በፊት በዳሎል ጥናት እንዲያደርግ ፈቃድ አግኝቷል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት በአካባቢው ላይ ማዕድኑን ማግኝት እንዳቻለ አሳውቆ ነበር፡፡እስካሁን ባለው ቆይታ ኩባንያው ወደ 65 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጉ ታውቋል፡፡ ከአሁን በኋላ በአምስት ዓመት ውስጥ ፖታሽ ማምረት ይጀምራል ተብሏል፡፡በአጠቃላይ ወደ 2.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚያወጣ ተገልጿል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ባለሀብቶች ኢንቨስት እንዲያደርጉ እየተነጋገረ እንደሆነ ኩባንያው ለሪፖርተር ገልጿል፡፡ሰርከም ሚኒራል በዓመት 2.75 ሚሊዮን ቶን ፖታሽ እንደሚያመርት፣ ከዚህ ውስጥ ሁለት ሚሊዮን የሚጠጋው ፖታሽ እንደሆነና ቀሪውን ፖታሽየም ሰልፌት ዳሎል ከሚገኘው ፕሮጀክቱ ያመርታል ተብሏል፡፡ከቅርብ ዓመታት ጀምሮ የፖታሽ ዋጋ በዓለም አቀፍ ገበያ መቀነሱ ይታወሳል፡፡ ከአራት ዓመት በፊት 570 ዶላር በቶን ሲሸጥ የነበረው በአሁኑ ጊዜ ወደ 214 ዶላር ወርዷል፡፡ሰርከም ሚኒራል የሚያከናውነው ፕሮጀክት ከታጁራ ወደብ በ600 ኪሎ ሜትር ርቀት ይገኛል፡፡ ከፕሮጀክቱ እስከ ወደቡ የሚያገናኙ መንገዶችን ለመገንባት መንግሥት እየሠራበት አንደሆነ፣ በፊርማው ላይ የተገኙት የማዕድን፣ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ቴዎድሮስ ገብረ እግዚአብሔር ተናግረዋል፡፡ከፕሮጀክቱ ጋራ የሚያገናኙ መንገዶችን ለመገንባት በቅርቡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የግንባታ ውል እንደተፈራረመ ይታወሳል፡፡በዋናነት ኩባንያው የውጭ ገበያ ላይ የሚያተኩር ሲሆን፣ በአገር ውስጥ ሊገነቡ ለታቀዱ የማዳበሪያ ፋብሪካዎችም ፖታሽ ማቅረብ እንደሚፈልግ ገልጿል፡፡በቅርቡ የሞሮኮ መንግሥት በኢትዮጵያ የማደበሪያ ፋብሪካ በ3.7 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያቋቁም መግለጹ ይታወሳል፡፡ ፋብሪካው ሲጠናቀቅ በዓመት 3.7 ሚሊዮን ቶን ማዳበሪያ ያመርታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡በተጨማሪም ያዩ የተባለው የማዳበሪያ ፋብሪካ በብረታ ብረት ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ሥር በግል ኩባንያዎች እየተገነባ ነው፡፡ ይህ ፋብሪካ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 300 ሺሕ ቶን ዩሪያ ማዳበሪያ ያመርታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ወደ አገር ውስጥ ተገዝተው በሚገቡ ማዳበሪያዎች ጥገኛ ለሆነው የኢትዮጵያ ገበያ፣ በመንግሥት በሺዎች ቶን መጠን ይቀርብለታል፡፡ 
ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%88%B0%E1%88%AD%E1%8A%A8%E1%88%9D-%E1%88%9A%E1%8A%92%E1%88%AB%E1%88%8D-%E1%89%A0%E1%8A%A0%E1%8D%8B%E1%88%AD-%E1%8D%96%E1%89%B3%E1%88%BD-%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B2%E1%8B%AB%E1%8B%88%E1%8C%A3-%E1%8D%88%E1%89%83%E1%8B%B5-%E1%89%B0%E1%88%B0%E1%8C%A0%E1%8B%8D
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8027a1fd917d94f6787d9b11bda25a8d
28afc57ca782158a223abb5b84bc0307
ግዙፉ ኤሌክትሮኒክስ አምራቹ ፎክስኮን ኮሮናቫይረሰን ለመከላከል ወይም በቀዶ ህክምና ወቅት ሊደረግ የሚችል የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ ወይም ጭምብል ሊያመርት መሆኑ ተነግሯል።
የአይፎን ስልክ አምራቹ ኩባንያ ኮሮናቫይረስ መከላከያ ጭምብል ማምረት ሊጀምር ነው\nየአይፎን ስልክ አምራች ጭምር የሆነው ኩባንያው በኮሮናቫይረስ ምክንያት በቻይና ለመዝጋት የተገደደውን ማምረቻ ጣቢያዎቹን ለመክፍት ጥረት እያደረገ ይገኛል። የኮሮናቫይረስ መከሰት በመላው ዓለም የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ 'ማስክ' እጥረት እንዲያጋጥም አድርጓል። ፎክስኮን በዚህ ወር መጨረሻ ላይ በቀን ሁለት ሚሊዮን የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛዎችን ለማምረት ማቀዱን አስታውቋል። "ይህን ወረርሽኝ ስንዋጋ እያንዳንዷ ሰከንድ ትርጉም አላት" ሲል ኩባንያው 'ዊቻት' በተሰኘው ማህብራዊ ሚዲያ ላይ አስፍሯል። "የመከላከል እርምጃ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ያስችላል። የሰዎችን ህይወት መታደግ መቻል ማለት በፍጥነት ቫይረሱን ማሸነፍ ማለት ነው" ብሏል አይፎን አምራቹ ኩባንያ። ይህ ኩባንያ የዓለማችን ግዙፉ የኤሌክትሮኒክስ አምራች ሲሆን፤ ከአይፎን በተጨማሪ፣ አይፓድ፣ የአማዞን ኪንድል እና ፕለይስቴሽኖችን ያመርታል። ኩባንያው በቅድሚያ የሚያመርታቸው የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ምርቶች ለሠራተኞቹ እንደሚያድል ከዚያ በኋላ ምርቶቹን ለገበያ እንደሚያቀርብ አስታውቋል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
4536cf379e0915b2d4495d3ea9c493f0
3d6165bd9a3dfbab25c33de4c8dec1f1
በዘንድሮ ዓመት አገሪቱ ካለፈው አመት ጋር ተመሳሳይ የሆነ የኢኮኖሚ እድገት ታስመዝግባለች- ብሔራዊ ባንክ
በተያዘው ዓመት አገሪቱ ካለፈው የበጀት ዓመት ከተመዘገበው  የ7ነጥብ7 በመቶ የሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት ጋር ተቀራራቢነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ታስመዘግባለች ተብሎ እንደሚጠበቅ  የብሔራዊ ባንክ  ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ ከ1996 – 2007 ዓ.ም ባሉት  ዓመታት በአማካይ 10 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቧን ያስታወሱት ዶክተር ይናገር ከ2008 ዓም አንስቶ እድገቱ መቀዛቀዙን አስረድተዋል፡፡ለዚህ ደግሞ የወጪ ንግድ መቀነስ፤ በሃገሪቱ የነበረው የፖለቲካ ሁኔታ፤ የኮንትሮባንድ ንግድ መስፋፋት፤ የዓለም ኢኮኖሚ በተለይም የቻይና መቀዛቀዝ በምክንያትነት እንደሚጠቀሱ ገልጸዋል፡፡በተለይ የወጪ ንግዱ መቀዛቀዝ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እንዲከሰት በማድረጉ ኢኮኖሚውን በከፍተኛ ሁኔታ ጎድቶታል፡፡የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብ የወጭ ንግዱን ማሳደግና ኮንትሮባንድን መቆጣጠር እንደሚገባ ዶክተር ይናገር ገልጸዋል፡፡የኮንትሮባንድ ንግዱን ለመቆጣጠር የፖሊሲ ማሻሻያ ማድረግ እንዲሁም አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መውሰድ ይገባልም ብለዋል፡፡የውጭ ብድርን በተመለከተ ሃገሪቱ 26 ቢሊዬን ዶላር እዳ እንዳለባት ዶክተር ይናገር ጠቁመው ከዚህም ውስጥ 85 በመቶ የሚሆነው የቻይና እንደሆነ ተናግረዋል፡፡23 ሚሊዮን ሰዎች ከድህነት ወለል በታች ሲሆኑ 8 ሚሊዮኑ ደግሞ ከመንግስት የምግብ ድጋፍ የሚጠብቁ መሆናቸውን የብሄራዊ ባንክ ገዢ ተናግረዋል፡፡
ቢዝነስ
https://waltainfo.com/am/23724/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
674569196d8be6f73eb4d2edecefe6c9
78387e74002fab6840d3331083544a5a
የትራምፕ ደጋፊዎች የአሜሪካ – ሜክሲኮ ድንበር ግንብ መገንባት ጀመሩ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎች አሜሪካ እና ሜክሲኮን ድንበር የሚለያየውን ግንብ ባገኙት የገንዘብ ድጋፍ መገንባት መጀመራቸውን አስታውቀዋል።የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋም የቀድሞ አባል ብሬን ኮልፋጅ በኒው ሜክሲኮ ግዛት የተጀመረውን ግንባታ የሚያሳይ ፎቶግራፍ ያጋሩ ሲሆን፣ የግንባታውን መሠረት የያዙት ብረቶች የቆሙት በእርዳታ በተገኘ 22 ሚሊየን ዶላር እንደሆነና ገንዘቡን በበይነመረብ አማካኝነት ባካሄዱት ዘመቻ እንደሰበሰቡት ተናግረዋል።ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግንቡን ለመገንባት ያቀረቡትን ሃሳብ ምክር ቤቱ ውድቅ ካደረገባቸው በኋላ ገንዘብ የማሰባሰብ ሥራውን እንደጀመሩ ገልፀዋል።ባለፈው እሁድ የቀድሞው የአየር ኃይል አባል ኮልፋግ አዲስ እየተገነባ ያለውን ግንብ ተንቀሳቃሽ ምስልና ፎቶግራፍ በትዊተር ገፃቸው ላይ ለቀውታል ነው የተባለው።"ታሪክ ሰርተናል! በመጀመሪያው የተሰበሰበው ገንዘብ ዓለም አቀፉን ድንበር ለመገንባት ውሏል" ሲሉ ኮልፋግ በትዊተር ገፃቸው ላይ ደስታቸውን ገልፀዋል።ግንቡ የሚሰራው 'ዊ ቢዩልድ ዘ ዎል ኢንክ' በተሰኘ ለትርፍ ባልተቋቋመው ድርጅታቸው ሲሆን ድርጅቱ የተመሰረተው ከገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻው በኋላ ነው።የቀድሞ የዋይት ሃውስ ባለሥልጣን ስቴቭ ባነን የዚህ ድርጅት አማካሪ ቦርድ ኃላፊ ናቸውም ተብሏል።የቦርዱ ኃላፊ ባነን ለሲ ኤን ኤን እንደተናገሩት አዲስ እየተገነባ ያለው 21 ማይል ርዝመት ካላቸው ሁለት ግንቦች ጋር የሚያያዝ ነው ብለዋል።የቀድሞ ካንሳስ ሃገረ ገዢ የነበሩትና በአሁኑ ሰዓት የድርጅቱ አማካሪ ክሪስ ኮባች በበኩላቸው ግንባታው 8 ሚሊየን ዶላር ገንዘብ እንደሚፈጅ ገልፀዋል።ግንባታውን እያካሄዱ ያሉት ቡድኖች በሰሜን ዳኮታ ግዛት የዓሳ አምራቾች ተቀጥረው የሚሰሩ ተቋራጮች ሲሆኑ ፕሬዚደንት ትራምፕ ግንባታውን እንዲያካሂዱ አሳስበዋቸው ነበር።ከትራምፕ ደጋፊዎች አንዱ የሆነው የ56 ዓመቱ ጄፍ አለን ግንቡ የተገነባው በሰን ላንድ ፓርክ በኒው ሜክሲኮ ግዛት ሲሆን ከሜክሲኮ ሲዩዳድ ጁዋሬዝ በተቃራኒው አቅጣጫ የሚገኝ ነው።ጄፍ አለን እንዳለው ግማሽ ማይል የሚሆነው የግንቡ ክፍል በዚህ ሳምንት መጨረሻ ይጠናቀቃል ተብሏል።"ግንቡን ራሳችን እንገነባዋለን፤ ይህ አውሮፓ አይደለም፤ ይህ አሜሪካ ነው፤ ድንበራችችንን ራሳችን እንጠብቃለን" ሲልም ለኤ ኤፍ ፒ ተናግሯል።ይሁን እንጂ ይህንን የሚያደርጉት ስደተኞችን በመጥላት እንዳልሆነ በመናገር ሚስቱ ሜክሲኳዊት ስትሆን ሴት ልጁም የተወለደችው ሲዩዳድ ጁዋሬዝ ውስጥ መሆኑን ጠቅሷል።ውሳኔው ላይ የደረሰው ዘረኛ ስለሆነ ሳይሆን ራሱንና አሜሪካን ለመጠበቅ ደህንነቱ የተረጋገጠ ድንበር እንዲኖራት ስለሚፈልግ እንደሆነም አክሏል።"ሰዎች አገራቸውን ትተው ለመሰደድ ካሰቡም በቀጥታ በመሄድ ማመልከት ይችላሉ" ብሏል ጄፍ አለን።በመጨረሻም ግንባታውን እያካሄደ ያለው ድርጅት "ይህ ጅምር ነው፤ በአሜሪካ ደቡባዊ ክፍል ያለውን ድንበር መጠበቅ ዓላማችን ነው"ሲል አስታውቋል።ባለፈው ሳምንት የአሜሪካ ፍርድ ቤት የትራምፕ አስተዳደር ግንቡን ለመስራት ያቀረበውን የገንዘብ ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ የሚታወስ ነው። (ምንጭ፡-ቢቢሲ) 
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/33940/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
40f7c404c3925890db033fd5b07d80a6
282e54e8400f259eaef39b0edfcd8196
በደቡብ ክልል፤ ከፋ ዞን፤ ቦንጋ ከተማ ሠርግ አስደግሶ "የሙሽራዬ ቤት ጠፋኝ" ያለው ግለሰብ ከእስር መለቀቁን የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ክፍሌ ተካ ለቢቢሲ ገለፁ። ነገሩ እንዲህ ነው. . .
ከፋ ዞን፡ በቦንጋ ሠርግ አስደግሶ "የሙሽራዬ ቤት ጠፋኝ" ያለው ግለሰብ የእስር ጊዜውን አጠናቀቀ\nግለሰቡ በቦንጋ ከተማ ቤት ተከራይቶ ይኖር ነበር። ዕድሜው አሁን ወደ 30 ይጠጋል። የኑሮ ሁኔታውም ዝቅተኛ ደረጃ የሚባል ዓይነት ነው ይላሉ የሚያውቁት። ታዲያ አንድ ቀን ለሠፈሩ ሰዎች "ላገባ ነው" ሲል ያበስራቸዋል። መቼም አንድ ሰው በሕይወቱ ወደ መልካም ምዕራፍ ሲሸጋገር ደስ ያሰኛልና እነርሱም ደስታቸውን ይገልፃሉ። "አበጀህ የእኛ ልጅ" ይሉታል። • 'ወንድ ያገቡት' ኡጋንዳዊ ኢማም ከኃላፊነታቸው ታገዱ • የቴክሳስ ፖሊስ ልማደኛዋን ድንኳን ሰባሪ እየፈለገ ነው ሁሉም ባቅሙ እያዋጣ እርሱም ካመጣው ጋር እየተጨማመረ ድግሱ በትብብር ተዘጋጀ። የሠርጉ ቀን ሲደርስም ሸራ ተወጥሮ፣ ወንበር ተሰባስቦ ለእንግዶች ተሰናዳ። ዳሱም በአበባ እና በዘንባባ ተጌጠ። ጎረቤቱም እንደ ባህሉ ተሰባስቦ በአቅማቸው ድግሱን ሲያስተናብሩ ዋሉ። ሁሉም ተሰናድቶ ካለቀ በኋላ ሙሽራው ከአጃቢዎቹ ጋር [6 ወንድ እና ሁለት ሴት] እየጨፈሩ፣ እየዘፈኑ ሙሽሪትን ለማምጣት ዴቻ ወረዳ፤ ሻፓ ወደ የሚባል ቀበሌ አመሩ። ሻፓ በእግር ቢያንስ 1 ሰዓት ይወስዳል። ሚዜዎቹና አጃቢዎቹ "ደስታህ ደስታችን ነው" ብለው ይህንን ሁሉ ርቀት ተጉዘው ሥፍራው ደረሱ። ይሁን እንጂ ሙሽራው አንዳች ነገር እንደጠፋው ሁሉ መንደሩን መዟዟር ጀመረ። በድካም የዛሉት ሚዜዎቹ "ቤቱ አንደርስም ወይ? ሙሽራዋ የታለች?" ብለው መጠየቃቸው አልቀረም። ግን መዳረሻው አልታወቅ አለ። በአካባቢው የሚታይም ሆነ የሚሰማ የሠርግ ሁናቴ የለም። ግራ የተጋቡት አጃቢዎች "የታለች?" ሲሉ ሙሽራውን ወጥረው ይይዙታል። "ልጅቷ ያለችበት ቤት ጠፋብኝ " ይላቸዋል። 'ሙሽራዋ ጠፋች'። በነገሩ ግራ የተጋቡት አጃቢዎቹ የሚያደርጉት መላ ቅጡ ጠፋቸው። ዳስ ውስጥ ሆነው እየዘፈኑ ሙሽራዋን የሚጠባበቁት ሠርገኞች ፊት እንዴት ባዶ እጃቸውን እንደሚገቡ ጭንቅ ያዛቸው። በዚህ መሃል አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው። ከአጃቢዎቹ አንዱን ጫማው እንዲያወልቅ አድርገው በነጠላ በመሸፋፈን ሙሽራ አስመስለው እየዘፈኑ፣ እየጨፈሩ ይዘው መግባት። በሃሳቡ ተስማሙ፤ እንዳሰቡት አደረጉ። ቤቱ እንደደረሱም "በእግሯ ረዥም ሰዓት ስለተጓዘች በጣም ደክሟታል።" ብለው ወደ ጫጉላው ቤት አዝለው ያስገቧታል። የሆነውን ማንም የገመተ የለም። ትንሽ ቆይቶ "ሙሽራዋ ትውጣና ራት ይበላ" ሲሉ ደጋሽ ጎረቤቶች ይጠይቃሉ። ምላሹ አሁንም "ደክሟታል" የሚል ነበር። አቶ ሙሉጌታ ገ/ሚካኤል ሠርግ ተጠርተው ከተገኙት ጎረቤቶች መካከል አንዱ ነበሩ። "ከሌላ ቦታ መጥቶ እኛ ሠፈር ቤት ተከራይቶ ይኖር ነበር። 'ላገባ ነው' ብሎ የተወሰኑ ጎረቤቶቹን ሠርግ ጠራ። እኔም ተጠርቼ ስለነበር ሠርጉ ላይ ተገኘሁ። ሙሽራዋን እንቀባለለን ብለን ሽር ጉድ ስንል ዋልን። በ'ጂ ፓስ' የሠርግ ሙዚቃ ተከፍቶ እየተጠባበቅን ነበር። በኋላ ላይ አምሽተው መጡ። ነገር ግን ብንጠብቅ ብንጠብቅ ሙሽራዋ አትመጣም። ወሬ አይቀርምና ሴት አስመስለው ይዘው የገቡት ወንድ ነው ተባለ። እንግዶችም ድግሱን ሳይቀምሱ ወዲያው ነበር በብስጭትና በእፍረት የተበታተኑት" ሲሉ አጋጣሚውን ያስታውሱታል። ሚስጢሩ ከጫጉላ ቤቱ ወጥቶ ወደ ዳሱ ሲዛመት ግን አፍታም አልቆየ። "ሴት አይደለም ወንድ ነው" የሚል። 'ጉድ' ተባለ። የሆነውን ባለማመን እያጉመተመቱ ወደየመጡበት የሄዱ እንዳሉ ሁሉ ጉዳዩን ለሕግ አካል ለማሳወቅም ያሰቡ አልጠፉም። ለፖሊስ ጥቆማ ተሰጠ። ፖሊስም በሥፍራው ተገኝቶ 'ሙሽራውን' በቁጥጥር ሥር አዋለ። " እኔ እንዲህ ዓይነት ነገር ሰምቼም አላውቅም።" የሚሉት አቶ ሙሉጌታ፤ በአካባቢው ባህል መሠረት በሠርግ ወቅት ገንዘብ ስለሚሰጥ ግለሰቡ ይህን ያደረገው ገንዘብ ለማግኘት መሆኑን የተረዳነው በኋላ ነው ይላሉ። ቆይተው...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
f1a6b31bea5ada9d52d3cf135c5ccc34
2f055e82b5e4485b0a7c6697c31cb997
“ጠላት” የነበሩ ሴቶች ዳግም ዕውቅና ማግኘት የሴቶቹ ሹመት ሕዝባዊ ፋይዳ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከመጡ ወዲህ በታየው የለውጥ ሒደት ውስጥ በተለያዩ የመንግሥት ኃላፊነቶች ላይ ሴቶችን የማስቀመጥ ጅምሩ ጉልሕ ድርሻ ካላቸው ለውጦች አንዱ ነው። ይህንን በማስመልከት ቤተልሔም ነጋሽ ፋይዳውን ይነግሩናል።  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የዛሬ ሰባት ወራት ገደማ ወደ ሥልጣን ሲመጡ፣ ያንን ተከትሎ የመጀመሪያውን አነቃቂና ተስፋ ሰጪ የተባለ ንግግራቸውን ፓርላማው ፊት ሲያደርጉ፣ በሴቶች መብቶች ዙሪያ ያገባናል ለምንል ትንሽ የተስፋ ጭላንጭል ታይቶን ነበር። ይኸውም መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ ሴቶች ትንሽም ቢሆን የተሻለ ይሆናል የሚል ነበር። እንደ እኔ ቢያንስ ያለፉትን ዐሥርት ዓመታት የኢትዮጵያ ሴቶችን ጉዳይ ጉዳዬ ብሎ የተከታተለ ሰው እንደሚረዳው፣ ቢያንስ በመንግሥት ደረጃ ገዢው ኢሕአዴግ ‹የሴቶች ጥያቄ ተመልሷል› ብሎ ያምን ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይህን ሽረው ከከፈሉት መስዋዕትነትና በአገሪቱ እያደረጉት ካሉት ከፍተኛ አስተዋፅዖበተቃራኒ የኢትዮጵያ ሴቶች ዕውቅና ተነፍገው መክረማቸውን ጠቀሱ።በግላቸው የባለቤታቸውንና የወላጅ እናታቸውን አስተዋጽኦ ተናግረው በይፋ አመሰገኑ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደሥልጣን ከመጡ በኋላ ቃል የገቡትን የለውጥ እርምጃ ተከትሎ በተለያዩ አካላት “ይህን ቢያደርጉ” ተብለው ከሚሰነዘሩ የፖሊሲና ተያያዥ ለውጥ ሐሳቦች መካከል የሴቶችን ጉዳይ የሚመለከቱ ሐሳቦችም ነበሩበት። በሴቶች መብት ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚሠሩ ተቋማት በጋራ ለጽ/ቤቱ ካስገቡት ይፋዊ ደብዳቤ ሌላ በግለሰብም ደረጃ የሚሰነዘሩ፣ ይህ ቢደረግ በሴቶች ሕይወት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ይመጣል የሚባሉ አስተያየትና ጥቆማዎችን በተለያዩ አጋጣሚዎች ስንሰማ ነበር። የሴቶች እኩልነት ላይ በሚሠሩ ተቋማትና በግላቸውም አቀንቃኝ በሆኑት ሰዊት ኃይለስላሴ እና ቢልለኔ ሥዩም (በአሁኑ ሰዓት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የፕሬስ ሴክሪታሪ ሆነው በመሥራት ላይ የሚገኙት) የጻፉትና በተለያዩ ድረ-ገጾች ያጋሩት “ግልጽ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ” የሚለው የጥያቄዎች ስብስብ ምናልባትም በዚህ ዘርፍ ከቀረቡት ሐሳቦች መካከል በድረ ገፆች በመታተምና በተለይ አንደኛዋ ጸሐፊ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በማኅበራዊ ሚዲያ በመዘዋወር ተጠቃሽ ነው። በደብዳቤው ላይ በግልጽ ከተቀመጡት ጥያቄዎች መካከል በካቢኔ የሴቶች ቁጥር ጨምሮ ሃምሳ-ሃምሳ የፆታ ተዋፅዖ እንዲኖር በተጨማሪም የወንዶች ግዛት ተደርገው ሚወሰዱት እንደ ንግድ፣ መከላከያ፣ ፋይናንስ እና ኢንዱስትሪ በሴቶች ቢያዙ የሚል ነበር። ጥቅምት 6፣ 2011 ጠቅላይ ሚኒስትሩ 20 አባላት ያሉት አዲሱን ካቢኔያቸውን ሲያስተዋውቁ የሆነው ግን ከተስፋውና ከጥያቄው ጋር ቢሔድም በፍፁም ያልተጠበቀ ነበር። በመጨረሻ የኢትዮጵያ ሴቶች ጊዜ መጣ እስኪባል ደስታ ሆኖ ነበር። በሳምንቱ የቀድሞዋ አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ፣ ቀጥላ ታዋቂዋ የሴቶች መብት ተሟጋችና ሴቶች ላይ አድልዎ ያደረጉ በርካታ ሕጎች እንዲቀየሩ ምክንት የሆነው የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር መሥራች መዓዛ አሸናፊ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆና ስትሾም እንደ ካቢኔው የፆታ ተዋፅዖ መመጣጠን ዜና ሁሉ አገራችን በዓለም በአዎንታዊ መልኩ ሥሟ ተነሳ። ለዘመናት ትርጉም ያለው የሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት እንዲረጋገጥ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ፣ የሴቶች ውክልና ሊረጋገጥ ይገባል ብለው ባገኙት መድረክ ሲሟገቱ የከረሙ ጥረታቸው ፍሬ አፈራ። ለእኔ በተለይ በሴቶች መብቶች ዙሪያ ድምፃችንን ለምናሰማና በዚህ ጥላሥር ለተሰባሰብን ድሉን የበለጠ ጣፋጭ የሚያደርገው የሴቶችን መብቶች ጥየቃ መንግሥትን አላግባብ ተዳፈራችሁ ተብለው ድርጅታቸው የተዘጋው እነ መዓዛ አሸናፊ ይገባችኋል ተብለው ለቁልፍ ሼል መታጨታቸው ነው። አሸባሪ ተብለው በእስር ቤት መከራ ከማየት እስከመሰደድ የደረሱት እነ ብርቱካን ሚደቅሳ መብታቸውን የነሳቸው ተቋም ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ነው። በብዙ የሴቶች መብት መሸራረፍ ዘልማድ ሆኖ እንዲቀጥል ፈላጊዎች እንደ ፅንፈኛ የሚታየውን ፌሚኒዝም በይፋ የሚያቀነቅኑ ሌሎች እንደ ፕሬስ ሴክሪታሪዋ ያሉ ፖለቲከኛ ያልሆኑ ዋነኛ የሴት መብት ተሟጋቾች በመንግሥት ከፍተኛ ቦታዎች መግባታቸው ነው። ያሁኑን ውጤት ጣፋጭ የሚያደርገው በመንግሥት ሳይቀር የነበረውን አሠራር በመገዳደራቸው ድርጅቶቻቸው እስኪዘጉ ‹ጠላት› ተደርገው የተቆጠሩ ዕውቅና ሲሰጣቸው ብቻ ሳይሆን ‹ታውቃላችሁ፣ ትችላላችሁ፣ ኑ ምሩ!› ሲባሉ ማየቱ ነው። ለዚህም ነው ይህ እውን እንዲሆን በአገራችን የመጀመሪያ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ቡድን (ሴቶች) የከፍተኛውን ሥልጣን ግማሹን እንዲይዙ ላደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ብቻ ሳይሆን እንደ መዓዛ ያሉ ከእሷ ጋር የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበርን የመሠረቱ፣ ያለምንም ማወላወል የተጋፈጡ ለቆሙለት ዓላማ “ትዳር አፋቺ” እና ሌላ ሥያሜ ተለጥፎባቸው ቢጠሉም ወደኋላ ያላሉ፣ በብዙ ሺዎች ለሚቆጠሩ ሴቶች መከታ የሆኑ በፍርድ ቤት በነፃ እየቆሙ አንገታቸውን ቀና አድርገው እንዲሔዱ ያደረጉ ዛሬ ለመጣው ለውጥ ለከፈሉት ዋጋ የምናመሰግናቸው።የሹመቱ ፋይዳ የሴቶች ወደ ሥልጣን መውጣት ለምን ያስፈልጋል የሚለውን ተመልክቼ ጽሁፌን ልቋጭ። ግሎሪያ ስቴነም ባለፈው ሰሞን የአሜሪካ ‹የሚድ ተርም› ምርጫን አስመልክቶ በርካታ ሴቶች በእጩነት ስለመቅረባቸው ስትጠየቅ ለሲኤንኤንዋ ክርስቲያን አማንፑር እንደተናገረችው ‹የመጀመሪያው በዲሞክራሲ መርሖ መሠረት ሥልጣን ላይ የሚወጡት ሰዎች በፆታም፣ በዘርም፣ በሃይማኖትም በአመለካከትም አጠቃላዩን ሕዝብ የሚመስሉ መሆን አለባቸው› ብላለች። በስፋት ተቀባይነት ካገኙ የዲሞክራሲ ፅንሰ ሐሳቦች መካከል አንዱ የፖለቲካ እኩልነት ሲሆን ሁሉም ዜጎች እኩል የፖለቲካ ተሳትፎ መብት አላቸው የሚለው ሐሳብ የዲሞክራሲ ዋና መሠረት ነው። ይህ የዜጎች እኩል ተሳትፎ መረጋገጥ የሚለው ብቻ በቂ ላለመሆኑ ግን ከጥቂቶች በስተቀር በብዙ የዓለም አገራት የሴቶች ውክልና አናሳ መሆን ምስክር ነው። ለዚህም ነው የአውሮፓ አገራትን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ባሉ ፓርላማዎች ጥናት ያደረጉ ምሁራን ከእኩል ውክልና (Equal representation) ይልቅ ገላጭ ውክልና(Descriptive Representation)ተገቢ የዲሞክራሲ ማረጋገጫ መንገድ መሆን አለበት ሲሉ የሚከራከሩት።ገላጭ ውክልና ማለት በፓርላማና በሌላውም የፖለቲካ ሥልጣን ላይ የሚሆነው አካል የሕዝቡን ብዝኃነት ያካተተ ሲሆን ማለት ነው። ሕዝቡ በትክክል ተወከልኩ የሚለው እያንዳንዱ እሱን የሚመስል ሰው በፓርላማም በቀበሌም በሚኒስትር ደረጃም ሥልጣን ይዞ ማየት ሲችል፣ ድምፁ በሚመስሉትና ኑሮን እሱ በሚያየውና በሚያልፍበት መንገድ ያለፉ ሰዎችን ማየት ሲችል ነው። ይህ በምላሹ ፖለቲካ የተወሰኑ ሰዎች ፍላጎት ወይም ርስት ሳይሆን ብቃትና ዕውቀት ያላቸው ሰዎች በፍላጎት ተነሳስተው የሚገቡበት እንዲሆን ያበረታታል።፡ ከሁሉም በላይ የሴቶች ወደከፍተኛው የሥልጣን እርከን መምጣት ዋጋ የሚኖረው ደግሞ በተለይ ለሴት ሕፃናት ነው። እነሱን የሚመስሉ ሴቶችን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሲመለከቱ ወደፊት በፖለቲካ ለመሳተፍ፣ እነኛን ቦታዎች ለመያዝ የማለም ዕድል ይኖራቸዋል። ከዚህ ሌላ ሴቶች ለፓርላማውም ይሁን ከታች ጀምሮ እስከላይኛው የሥልጣን እርከን ሲመጡ ይዘው የሚመጡት የተለየ እይታ አለ። ሴቶች ከዕለት ተዕለት ኑሮ ፣ ወደ ፖለቲካ ከመግባት አንስቶ ሥልጣን ላይ እስከመውጣት ባለው ሂደት የሚያልፏቸው ተግዳሮቶች ከወንዶች የተለዩ ናቸው። ይህን ነገሮችን በተለየ መነፅር የመመልከት ይህንና የተለየ የህይወት ልምዳቸውን ለአመራር ዘይቤያቸው ሲጠቀሙ አመራሩና ሂደቱ የተሟላ እይታና ልምድ የሚጠቀም እንዲሆን ይረዳል። በተጨማሪም ፖለቲከኞች የወከሉትን ብቻ ሳይሆን የወጡበትን ማኅበረሰብ ችግር የመፍታት አዝማሚያ አላቸው። ሴት ባለሥልጣናት ሲበዙ ፖሊሲዎች ሲወጡ የሴቶች ድምፅ እንዲካተት ያደርጋሉ የሚል ነው እሳቤው። ደግሞም የፕሬዚዳንትነትም ሆነ የግማሽ ካቢኔው እንዲሁም አሁንም በሌሎች ቦታዎች እስከ ቀበሌ ድረስ ይቀጥላል ብለን በምናምነው ሹመት የሚካተቱ ሴቶች በችሮታ የተሰጣቸው ሳይሆን በመብታቸውም፣ በትግላቸው ያገኙትም ጭምር ነው። በመጨረሻም“አሁንማ መከላከያ ሚኒስቴር ሆናችሁ፤ ከዚህ በላይ ምን ትፈልጋላችሁ?” የሚል አስተያየት ለሚሰነዝሩ የሚከተለውን መልስ መስጠት አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁ። ሕገ መንግሥቱን ጨምሮ ለሴቶች መብቶችን የሚያጎናፅፉ መልካም የሕግ ማዕቀፎች ቢኖሩም፣ በሴቶች ላይ የሚፈፀም ጥቃት እየጨመረ መጥቷል። ታዳጊ ሕፃናትና ወጣት ሴቶች ሊጠብቋቸው፣ ከለላ ሊያደርጉላቸው በሚገባ የቅርብ በሚሏቸው ሰዎች ሳይቀር ይደፈራሉ። ትምህርት ቤቶች ለሴቶች አመቺ አይደሉም። ሴቶች ዕለት ተዕለት ኑሯቸውአሁንም በሥጋት የተሞላ ነው። ለብዙ ሴቶች በሠላም ወጥቶ መግባት አሁንም ምኞት ነው። በሥራ ቦታዎች ሴቶች አሁንም ሴት በመሆናቸው ብቻ አድልዎና በደል ይፈፀምባቸዋል። ዛሬም “ፈልጌሻለሁ” ያለ ወንድ እንቢ በማለታቸው አሲድ የሚደፋባቸው ሴቶች አሉ። የድህነት ከባድ ጫና ዋነኛ ተሸካሚ ሴቶች ናቸው። ተስፋችን ይህ ይቀየራል የሚል ነው። የሴቶች ቁጥር በዛ ብሎ በውሳኔ ሰጪነት ላይ መሳተፍ ትርጉም ኖሮት፣ በየዘርፉ ሴቶች ያሉበትን ሁኔታ አይቶ ሆን ብሎ ያንን ለመቀየር የሚሠራ መንግሥት እንዲኖረን ያደርጋል የሚል ነው።ቤተልሔም ነጋሽ የፖለቲካ ተግባቦት ባለሙያ ናቸው። በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ሊገኙ ይችላሉ።
ፖለቲካ
https://addismaleda.com/archives/2043
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
5c975fe8ddd874f5595e76d4edcaa501
a10f8d4b2d57cb29119f43024c86731d
እነ አቶ ጃዋር መሐመድ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ በቅርቡ በሰጡት መግለጫ ላይ ነጻ ሆነን የመታየት መብታችንን የሚቃረን አስተያየት በመስጠታቸው ፍርድ ቤቱ እንዲጠይቅላቸው አቤቱታ አቀረቡ።
ጃዋር መሐመድ፡ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተጠየቀ\nአቶ በቀለ ገርባና ጀዋር መሐመድ የጠቅላይ አቃቤ ሕጉ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት በመገኘት ለጋዜጠኞች የሰጡት መግለጫ ነጻ ሆኖ የመታየት መብታቸውን የሚጻረር መሆኑን እና ለህይወታቸው አስጊ እንደሆነ ዛሬ ለተሰየመው ፍርድ ቤቱ ገልፀዋል። "እኛ ላይ ምስክሮች እንኳ ሳይሰሙ፣ የፖለቲካ ባለስልጣናት፣ በተለይም ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ፍርድ ቤቱ እኛ ላይ ውሳኔ እንዳስተላለፈ አድርገው ነበር የተናገሩት" ያሉት አቶ ጃዋር መሐመድ የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ መግለጫ ለህይወታቸው አስጊ መሆኑን ተናግረዋል። "ጽንፈኞች ተብለናል፤ እንዲሁም ግርግር እንደፈጠርን እና ሰው እንደገደልን ወስነዋል" በማለት የጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞትዮስ ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲጠየቁ አቤቱታቸውን አሰምተዋል። አቶ በቀለ ገርባም " ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ እኛ መከላከል በማንችልበት ሁኔታ ለውጪ አገር ሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል። ይህም የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ገለልተኛ መሆን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው" በማለት ዶ/ር ጌዲዮን ፍርድ ቤት ቀርበው መጠየቅ አለባቸው ሲሉ ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱም በበኩሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በሚቀጥለው ቀጠሮ ላይ በጽሑፍ ምላሽ እንዲሰጡ ትዕዛዝ አስተላልፏል። የዛሬ ችሎት ውሎ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ ጃዋር መሐመድን ጨምሮ በ24 ሰዎች ላይ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የከፈተውን ክስ ለተከሳሾች አንብቧል። ፍርድ ቤቱም ከተራ ቁጥር 1 እስከ 15 ድረስ ያሉ ተከሳሾችን ብሔርን እና ሐይማኖትን መሰረት ያደረገ ሁከት በመፍጠር በአዲስ አበባ ከተማ የ13፣ በኦሮሚያ ክልል ደግሞ 167 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ 360 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት እና 4.6 ቢሊዮን ብር በላይ የተገመተ ንብረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውን አንብቧል። ከዚህም ውጪ ያለፈቃድ የጦር መሳሪያዎችን ይዘው በመገኘትና የቴሌኮም ማጭበርበርን መፈፀም የሚሉ ጉዳዮች ክሱ ውስጥ የተካተቱ ጉዳዮች ናቸው። 18ኛ ፣ 21ኛ፣ 6ኛ፣ 8ኛ፣ 9ኛ፣20፣7ኛ ተከሳሾች አማርኛ የማይሰሙ መሆናቸው ተገልጾ እነርሱ ላይ የቀረበውን ክስ አለመረዳታቸውን ለፍርድ ቤቱ አስታውቀዋል። ጠበቆቻቸው ደግሞ በደንበኞቻቸው ላይ የተከፈተውን ክስ ማረሚያ ቤት በመገኘት ማሳወቅ እንደሚችሉ ለፍርድ ቤቱ ገልፀዋል። ፍርድ ቤቱም የተከሳሽ ጠበቆችን ሁሉንም በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ አግኝተዋቸው እንዲወያዩ ማረሚያ ቤት ሁኔታውን እንዲያመቻች ትዕዛዝ ሰትቷል። አቤቱታና የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በዛሬ የፍርድ ቤት ውሎ ተከሳሾችና ጠበቆቻቸው እንዲሁም ዐቃቤ ሕግ የተለያዩ አቤቱታቸውን ለፍርድ ቤት በማቅረብ ፍርድ ቤቱም ትዕዛዝ ሰጥቶባቸዋል። ተከሳሾች እጃቸው በካቴና ታስሮ ረዥም ሰዓት መቆየታቸውንና እንዲፈታ ጠይቀው እምቢ መባላቸውን፤ እንዲሁም ጠዋት ቁርስ ሳይበሉ ወደ ፍርድ ቤት መወሰዳቸውን በመግለጽ አቤቱታ ያቀረቡ ሲሆን፤ ፍርድ ቤቱ ለምን በካቴና እንደታሰሩ ማረሚያ ቤቱ በጽሁፍ ምላሽ እንዲሰጥ ትዕዛዝ ሰጥቷል። ከዚህ በተጨማሪ ተከሳሾች ማለዳ ወደ ፍርድ ቤት ሲወሰዱ እስር ቤቱ ቁርስ እንዲያቀርበላቸው ፍርድ ቤቱ አዟል። የተከሳሽ ጠበቆች ሸምሰዲን ጠሃ የኢሬቻ በዓል ላይ እንዲገኝ ያቀረበውን ጥያቄ ትዕዛዝ ይሰጥልን በማለት ጠይቀዋል። ከዚህም በተጨማሪ ተከሳሾች የባህል ልብስ እንዲገባላቸውና የኢሬቻን በዓል እስር ቤት በጋራ እንድናከብር ይፈቀድልን ሲሉ ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱም ሸምሰዲን ጠሃ ኢሬቻ ላይ ተገኝቶ በዓሉን እንዲያከብር ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ ያደረገ ሲሆን፤ ተከሳሾች ግን የባህል ልብስ ገብቶላቸው ከዚህ በፊት የተለያዩ የእምነት በዓላት ሲከበሩ እንደቆየው እንዲያከብሩ ሁኔታዎች እንዲመቻችላቸው ትዕዛዝ ሰጥቷል። በተጨማሪም ባህር ማዶ ቤተሰብ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
761e877e874553633a7d31ad21c9c034
2b464374c357fa2e0311f20fa9c79baf
ባለፉት 24 ሰዓታት 890 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው 3 ሰዎች ህይወት አልፏል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 6 ሺህ 916 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 890 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።በዚህም በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 76 ሺህ 988 ደርሷል።በሌላ በኩል ባለፉት 24 ሰዓታት ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ የ 3 ሰዎች ህይወት አልፏል።በዚህም በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎቸ ቁጥር 1 ሺህ 208 መድረሱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት መረጃ ያመለክታል።በ24 ሰዓታት ውስጥ 247 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ እስካሁን ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 31 ሺህ 677 ደርሷል።እንዲሁም 296 ፅኑ ህሙማን የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ተብሏል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a3%e1%88%88%e1%8d%89%e1%89%b5-24-%e1%88%b0%e1%8b%93%e1%89%b3%e1%89%b5-890-%e1%88%b0%e1%8b%8e%e1%89%bd-%e1%8b%a8%e1%8a%ae%e1%88%ae%e1%8a%93-%e1%89%ab%e1%8b%ad%e1%88%a8%e1%88%b5-%e1%88%b2/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
054cd0177bc68a0ba1981ca6e5b15a83
3899ca19ab42c77d93f35d142ca79538
የኦሎምፒክ ችቦ ዘንድሮ ውድድሮቹን ወደ ምታስተናግደው ወደ ሪዮ ዲ ጃኔሮ የብራዚል ከተማ ጉዞ ጀምሯል
የኦሎምፒክ ችቦ ዘንድሮ ውድድሮቹን ወደ ምታስተናግደው ወደ ሪዮ ዲ ጃኔሮ (Rio De Janero) የብራዚል ከተማ ጉዞ ጀምሯል። ችብው ትናንት አጠር ያላ የማብራት ሥነ ሥርዓት ተደርጎለት ጉዞውን የጀመረው የኦሎምፒክ ውድድሮች ከተጀመሩባት ከግሪክ ከተማ ከኦሎምፒያ (Olympia) ነው። ችቦውን በርካታ የግሪክ ከተሞችን ለስድስት ቀናት አቋርጦ በሚያልፍበት ወቅት አንድ የዚያችን ሃገር ጥገኝነት የጠየቀውን ሦሪያዊ ስደተኛ ጨምሮ፥ 450 ሰዎች ይቀባበሉታል። በግንቦት ወር መጀመሪያ ላይ አስተናጋጇ ብራዚል ከገባ በሁዋላም፥ በ 83 ትላልቅና በ 500 አነስተኛ ከተሞቿ ሲያልፍ 12 ሺህ ሰዎች ይቀባበሉታል። የመጨረሻው ሰው በኦሎምፒክ መክፈቻው እለት በሚደረገው ሥነ ሥርዓት ላይ ችቦውን ማራካና (Maracana) ስታዲየም በተዘጋጀለት ልዩ ሥፍራ ላይ ያኖራል።በነገራችን ላይ ኦሊምፒክ በአንድ የላቲን አሜሪካ ሃገር ውስጥ ሲዘጋጅ የ 2016ቱ በታሪክ የመጀመሪያው ነው።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/the-olympic-in-rio-de-janero-started-on-thursday-in-olympia/3298531.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
043833e6a0b94cb363dde1e9324b20ed
b09ccd2c0b349000c1bd2dd386c29ba5
ኢትዮጵያ ዓለምአቀፍ የግልግል ዳኝነቶችን በግዛቷ ከማስፈጸም ምን ታተርፋለች?
በውጭ ሀገራት የሚሰጡ የግልግል ዳኝነቶችን ዕውቅና መስጠት እና ማስፈጸምን በተመለከተ የተደረሰው ስምምነት ይፋ ከተደረገ 60 ዓመታት አልፈዋል።በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ የራሷን አሰራር ከመዘርጋት ውጪ የስምምነቱ ፈራሚ ሆና አልታየችም ነበር።አሁን ላይ ግን ኢትዮጵያ በውጭ ሀገራት የተሰጡ የግልግል ዳኝነቶችን በሀገር ውስጥ ያለ ተጨማሪ ስነ-ስርዓት እና ቅድመ -ሁኔታ ለማስፈጸም የሚያስችላትን ሰነድ ለማጽደቅ እየተዘጋጀች ስለመሆኑ ተሰምቷል። የተሰኘው ይሄንን ሰነድ ለመቀበል የሚኒስትሮች ምክር ቤት የወሰነ ሲሆን ፣ገዥነቱን ለማጽደቅ ደግሞ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀጠሮ እንደያዘለት ተሰምቷል።ለመሆኑ የሰነዱ ዓላማ ምንድነው? ኢትዮጵያ ሰነዱን በመፈረሟ የምትጠቀማቸው እና የምትጎዳባቸው ጎኖች አሉ ወይ? የሚሉ ጥያቄዎችን አንስቶ ሀብታሙ ስዩም ከባህርዳር ዩኒቨርሰቲው የግብር እና ኢንቨስትመንት ህግ መምህር ምስጋናው ጋሻው ጋር አጨር ቆይታ አድርጓል። አቶ ምስጋናው የሰነዱን ምንነት እና ይዘት በማስረዳት ይጀምራሉ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB-%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D%E1%8A%A0%E1%89%80%E1%8D%8D-%E1%8B%A8%E1%8C%8D%E1%88%8D%E1%8C%8D%E1%88%8D-%E1%8B%B3%E1%8A%9D%E1%8A%90%E1%89%B6%E1%89%BD%E1%8A%95-%E1%89%A0%E1%8C%8D%E1%8B%9B%E1%89%B7-%E1%88%88%E1%88%9B%E1%88%B5%E1%8D%88%E1%8C%B8%E1%88%9D-%E1%8A%A5%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%88%B0%E1%8A%93%E1%8B%B3%E1%89%BD-%E1%8A%90%E1%8B%8D-%E1%8A%A8%E1%8B%9A%E1%88%85-%E1%8A%A5%E1%88%AD%E1%88%9D%E1%8C%83-%E1%88%9D%E1%8A%95-%E1%89%B5%E1%8C%A0%E1%89%80%E1%88%9B%E1%88%88%E1%89%BD-/5217061.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
330bf35c55443c58f49c5604c9d28fb5
1db0f3f26cdbc17b162d23030687f2ea
በቅማንት አካባቢ ግጭቱ እንደገና ያገረሸው ባለፈው ዓመት ጳጉሜ 3/2011 ዓ.ም እንደሆነ በአካባቢው ነዋሪ የሆኑት መምህር መካሻው ለቢቢሲ ተናግረዋል።
"ታጣቂዎች ሰላማዊ ዜጎች መኪና አስቁመው ተገድለዋል" አቶ አገኘሁ - "ሰላማዊ ሰዎች በአማራ ልዩ ኃይል ጥቃት ደርሶባቸዋል" የአካባቢው ነዋሪ\nየነዋሪውን ሀሳብ የሚያጠናክሩት የቅማንት የማንነትና የራስ አስተዳደር ይከበርልኝ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ከፍአለ ማሞ በበኩላቸው ከጳጉሜ 3 ጀምሮ በአካባቢው ጦር መዝመቱን የይናገራሉ። የአማራ ክልል የሰላምና ሕዝብ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ተሻገር በበኩላቸው የክልሉ ልዩ ኃይል ሕግ ለማስከበር ወደ ስፍራው መንቀሳቀሱን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ከጳጉሜ 3 ጀምሮ የክልሉ የፀጥታ ኃይል ወደ አካባቢው አንቀሳቅሶ ወደ ቀበሌዎች በመግባት፣ ሰላማዊ መንደርን ከብቦ ጥቃት ማድረሱን የተናገሩት መምህር መካሻው የፀጥታ ኃይሉ ለተኩሱ ምክንያት የሰጠው በአካባቢው ሽፍታ አለ የሚል መሆኑን ያስረዳሉ። • የዛሬዋን ኤርትራ የሚገልጹ አስደናቂ እውነታዎች • የጤፍ ቢራ አሜሪካ ውስጥ ገበያ ላይ ዋለ • ቻይና ኮሚዩኒስት ፓርቲ የተመሰረተበትን 70ኛ አመት እያከበረች ነው መምህር መካሻው በስፍራው ሽፍታ እንደሌለና፣ ሰላማዊ ሰዎች የሚኖሩበት አካባቢ በልዩ ኃይሉ ጥቃት እንደተፈጸመ ይናገራሉ። "በሕዝብ ይሁንታ የቅማንት የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄን ለማስተባበር የተቋቋመው ኮሚቴ አባላትን ለመያዝ ሆን ብሎ የተደረገ ነው" የሚሉት መምህር መካሻው ሕዝቡ ኮሚቴዎቻችንን አትንኩ እያለ ስለሆነ "ሽፍታ ልንይዝ ነው" በሚል ሰበብ መጥተዋል ሲሉም ያስረዳሉ። አቶ ከፍአለ ማሞ በበኩላቸው በ2012 ዓ.ም ከመስከረም 10 ጀምሮ በአካባቢው የልዩ ኃይል ጥቃት እያደረሰ ነው ሲሉም ይከስሳሉ። መስከረም 11 ወደ መንደር ገብተው ወጣቶች ላይ ተኩስ መክፈታቸውን ከዚያም ገበሬውም ላይ መተኮስ መጀመሩን ያስረዳሉ። በአሁኑ ሰዓት ወደ ስፍራው ከፍተኛ ጦር እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ይናገራሉ። መምህር መካሻው መስከረም 11 የልዩ ኃይል አባላት በድጋሚ መጥተው መንደሩን ማሰሳቸውን፣ የደረሰውን ሰብልም ሲያጠፉ ውለዋል ሲሉ ምሬታቸውን ይገልፃሉ። "የፀጥታ ኃይሉ በእግሩ የደረሰውን ሰብል ሲረመርም ገበሬዎች ተኩስ መጀመራቸውን" የሚናገሩት መምህር መካሻው "በጥቃቱ ምክንያት ንብረት ወድሟል፣ ሰዎች ከቀያቸውና ከአካባቢያቸው ተፈናቅለዋል" ሲሉም ያለውን ሁኔታ ያስረዳሉ። ከዚህ በኋላም ከመስከረም 16 ጀምሮ ባሉ ተከታታይ ቀናት ጥቃት እየደረሰባቸው እንዳለ የተናገሩት ግለሰቡ በዚህም የተነሳ አንድ ሰው ጨንቾ አካባቢ መሞቱን ተናግረዋል። አይከል ከተማ አካባቢም የሞቱ ሰዎች መኖራቸውን የሚናገሩት ግለሰቡ በወና ከተማ ሰው መገደሉን በመግለፅ በቁጥር በርከት ያሉ ሰላማዊ ዜጎች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ያብራራሉ። አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የአማራ ክልል የሰላምና ሕዝብ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ የቅማንት የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄ በአግባቡ እንዲፈታ ክልሉ ውሳኔዎችን ማሳለፉን በማስታወስ "የአማራ ክልል ውስጥ የተረጋጋ ሁኔታ እንዳይፈጠር የሚፈልጉ ኃይሎች" ያሏቸውን ለተፈጠረው ግጭት ተጠያቂ ያደርጋሉ። እነዚህን ኃይሎችን በስም ባይጠቅሱም፤ የግጭቱ ዓላማ ነው ያሉትን ሲያስረዱም "በአካባቢው አለመረጋጋት እንዲኖር፣ ወደ መተማ የሚሄደውን መንገድ መዝጋት፣ በዚህም የተነሳ የአማራ አርሶ አደርና ባለ ሀብት ምርቱን እንዳይሰበስብ ሆን ተብሎ፣ ታቅዶ እየተሰራ ያለ ሥራ ነው" ይላሉ። • ከልጁ ስድስት ልጆች የወለደው አባት በአካባቢው በታጣቂዎች ደረሰ ያሉትን ጥቃት ሲዘረዝሩም "ሰላማዊ ዜጎች በመኪና ሲንቀሳቀሱ መኪናውን አስቁመው በማንነታቸው ብቻ ተገድለዋል፤ ከዚህ በተጨማሪም የሚኒባስ ሾፌር ተገድሏል" የሚሉት ኃላፊው የነዳጅ ቦቴ ሾፌሮች መታገታቸውንና ቦቴውን ማቃጠላቸውንም ጨምረው አስረድተዋል። የሰሞኑ ግጭት የተቀሰቀሰው የፀጥታ አካላት አንድ በወንጀል የሚጠረጠር ግለሰብ ይዘው ከአንድ ቀበሌ ወደ ሌላ ቀበሌ ሲንቀሳቀሱ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
5e2978fa4d3907c4141e723394858c29
eb6d95a3059a18b71f6c71701037b370
ኮቪድ19 - ክትባት ለወራት ላይደርስ ይችላል
ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረ ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ ዘጠኝ መቶ ሃምሣ ሰው ለኮሮናቫይረስ መጋለጡ መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር ባወጣው የክትትል ሪፖርት አስታውቋል።ዝርዝሩ እንደሚያሳየው ከፍተኛው ቁጥር በተመዘገበባት አዲስ አበባ 324 ሰው፣ በኦሮምያ 249፣ በትግራይ 101 ተጋልጧል።ከመቶ ያነሰም ቢሆን ከፍተኛ ቁጥሮች በደቡብ፣ በአማራ፣ በሲዳማ፣ በአፋር፣ በጋምቤላ፣ በሃረሪ፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በሶማሌ ክልሎችና ድሬ ዳዋ ውስጥ ተመዝግበዋል።ኢትዮጵያ ውስጥ በአጠቃላይ 35 ሺህ 791 ሰው ኮቪድ 19 ህመም ላይ እንደሚገኝና 21 ሺህ 102 ሰው ከህመሙ ማገገሙ ተገልጿል።ኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ያለፉ 17 ህይወቶችን ጨምሮ እስካሁን 897 ሰው በኮቪድ 19 ምክንያት መሞቱን የጤና ሚኒስቴሩ የዛሬ ሪፖርት አመልክቷል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ህንድ ውስጥ ቁጥሩ ወደ 86 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰው ዛሬ ብቻ ለኮሮናቫይረስ መጋለጡ ተዘግቧል። በዚህም መሠረት የህንድ የኮቪድ 19 ተጋላጭ ቁጥር ከአራት ሚሊየን በላይ መሆኑን የጃንስ ሃፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ የኮሮናቫይረስ መረጃ ማዕከል አስታውቋል።አሁን ባለው ሁኔታ ከህንድ የበለጠ የኮሮናቫይረስ ተጋላጭ ቁጥር ያላቸው ዩናይትድ ስቴትስና ብራዚል ሲሆኑ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ 6 ሚሊየን 2 መቶ ሺህ ሰው ኮሮናቫይረስ ተላልፎበታል።ሜክሲኮ ውስጥ ኮቪድ 19 እያደረሰ ባለው የከፋ ጥፋትና ሞት ምክንያት በአንዳንድ አካባቢዎች ቫይታል ስታቲስቲክስ መዝጋቢ ቢሮዎች የሞት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት መጨረሳቸው ተነግሯል።በኮቪድ 19 ምክንያት ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ 187 ሺህ 768 ሰው፣ ብራዚል ውስጥ 125 ሺህ 502 ሰው ህንድ ውስጥ 69 ሺህ 561 ሰው ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት መሞቱን ጃንስ ሃፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል።በዓለም ዙሪያ በኮቪድ 19 ሰባት ሺህ የሚሆኑ የጤና ሠራተኞችና ባለሙያዎች መሞታቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታውቋል።በሌላ በኩል ደግሞ ለኮሮናቫይረስ መከላከያ የሚሆን ደኅንነቱ የተረጋገጠና ውጤታማ ክትባት በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል እስከመጭው የአውሮፓ ዓመት አጋማሽ ላይደርስ እንደሚችል የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል።ከድርጅቱ ዋና መቀመጫ ጄኔቫ የተጠናቀረው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል።ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡት።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/who-covid-vaccine-09-05-2020/5572229.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
0d934e245d767e45cdcab078c41f5fa9
9b05fe4fb4a7b47055a72cc4d08dfdf0
"እልም ያለ ሥርዓት አልበኝነት ሊፈጠር ይችላል" ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌ.)
ዛሬ በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የሚከሰቱ አለመረጋጋቶች፣ ግጭቶችና ከዕለት ወደ ዕለት አሳሳቢ እየሆነ የመጣው የሰላም ዕጦት፣ ነገ ደግሞ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን? የሚል ስጋት/ጭንቀት መኖሩን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለፁ።ብርሀኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የለውጡን ሂደት፣ በዚህ ዓመት ማጠናቀቂያ ላይ የሚካሄደውን ምርጫ ፋይዳ እና በኢትዮጵያ ላይ የተደቀኑ አደጋዎችን በሚመለከት ባቀረቡት ግምገማና ጥሪ ላይ ነው ይህንን የተናገሩት።በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚከሰቱ ግጭቶችና አለመረጋጋቶች አሳሳቢ እየሆነ የመጣው የሠላም ዕጦት ኢዜማን እንደሚያሳስበው ፕሮፌሰሩ ገልጸዋል።ኢዜማ ከአባላቱና ከተለያዩ አካላት ያገኘውን መረጃ በመሰብሰብ፣ ኢትዮጵያ ያለችበትን ሁኔታ በመገምገም የጋራ አገራዊ ግንዛቤ ለመፍጠርና፣ ውይይት ለመክፈት በማለት በትናንትናው ዕለት አገራዊ ጥሪ ለሚመለከታቸው አካላት በሙሉ በመሪው በኩል አቅርቧል።• ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት አገረ መንግሥት ግንባታ ያለፈችባቸውን ለውጦች ዘርዝረው፣ በእነዚህ ለውጦች ውስጥ የታዩት ተግዳሮቶች ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ከመገንባት ይልቅ ማኅበረሰብን በጠባብ የዘውግ መለኪያ ብቻ የሚመለከት የአድሎ ሥርዓት መፍጠሩን በትንታኔያቸው ላይ ጠቅሰዋል።ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ለሦስተኛ ጊዜ ትልቅ የለውጥ ሂደት ውስት ገብታለች ያሉት ፕሮፌሰሩ፤ "ነገር ግን ይህ ለውጥ ወደምንፈልገው የተረጋጋ ዲሞክራሲያዊ መንገድ ይውሰደን አይውሰደን ገና የታወቀ ነገር የለም" ሲሉ ይገልፃሉ።ለዚህም እንደምክንያት ያነሱት በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚከሰቱ ግጭቶች፣ መፈናቀሎችና ሥርዓት አልበኝነቶችን ሲሆን በሕዝቡ ዘንድም ቀጣዩ ምርጫ ያጫረውን ስጋት በዋቢነት ጠቅሰዋል።ፕሮፌሰር እንዳሉት በአሁኑ ሰዓት ያለው ለውጥ የተጀመረው በፊት የነበረውን መዋቅር ሙሉ በሙሉ በማፈራረስ ሳይሆን ቀስ በቀስ የነበሩ ህፀጾችን እየቀነሱ ባለው መልካም ሁኔታ ላይ እየጨመሩ መሄድ በሚል መሆኑን ይጠቅሳሉ።ነገር ግን የተለያየ ዓላማ ይዘው ለለውጥ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች እና ለውጡን እንደግፋለን ብለው ወደ አገር ቤት የገቡ፣ በመንግሥትም ሆነ በተለያየ የሥልጣን እርከን ውስጥ ያሉ ግለሰቦች ከለውጡ አላማ ውጪ መንቀሳቀስ የጀመሩት ወዲያውኑ መሆኑን ያነሳሉ።በዚህም የተነሳ ይላሉ ፕሮፌሰሩ ማዕከላዊው መንግሥት ሰላም የማስጠበቅ አቅሙን ከመገንባቱ በፊት ማኅበረሰቡ፣ በለውጡና በለውጡ ኃይሎች ተስፋ እንዲቆርጥ "መንግሥት የለም" ብሎ ሥርዓት አልበኝነት በአገሪቱ እየነገሰ ነው ብሎ እንዲሰጋና ለደህንነቱ ሲል ሁሉም ወደ ዘውጌ ምሽግ እንዲገባ እና የጣለውን ዘውጌ ሥርዓት እንዲናፍቅ ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት ማድረጋቸውን ይጠቅሳሉ።ይህንን እንቅስቀሳሴ ሦስት አካላት ይሳተፉበታል በማለትም ሲዘረዝሯቸው የቀድሞ ሥርዓት ዋነኛ ተጠቃሚዎች፣ ለውጡን የሚፈልግና በባለተራ ዘውጌነት ክልሉን መግዛት የሚፈልግ፣ እንዲሁም የለውጥ ኃይሉን በፍፁም የማያምን ናቸው በማለት ያስቀምጧቸዋል።እንደ ፕሮፌሰሩ ማብራሪያ ከሆነ "ይህ ሦስተኛው ኃይል የለውጥ ኃይሉ በደንብ ከመደላደሉ በፊት በመቃወም፣ የህዝብ ተቀባይነት እንዳያገኝ በማድረግና ለውጡን ለማስኬድ ብቃትም ሆነ ተአማኒነት የለውም በማለት የተጀመረውን ለውጥ ከግቡ ለማድረስ ከሁሉም የተውጣጣ የሽግግር መንግሥት ይፈጠር በሚል የራሱን አጀንዳ ለማራመድ የሚሞክር ኃይል ነው።"የሦስቱ ኃይሎች የጋራ ፍላጎት መንግሥትን ማዳከም ሲሆን በጋራ ላይሰሩ ይችላሉ ይላሉ። ፕሮፌሰሩ በዚሁ ጥሪ ባቀረቡበት ዘለግ ያለጽሑፍ ላይ እንዳስቀመጡት ሕዝቡ ይወክለኛል ያለውን ያለመሳቀቅ እና ፍርሃት መምረጥ ካልቻለ ባለፉት 18 ወራት ያየናቸውና ማኅበረሰባችንን ጭንቀት ውስጥ የከተቱት ችግሮች እጅግ በጣም በገዘፈ መልኩ የሚከሰቱበትና ወደ አጠቃላይ ቀውስ የምንገባበት ሁኔታ መፈጠሩ አይቀሬ ይሆናል ይላሉ። ውክልናቸው በህዝብ ያልተረጋገጠላቸው "ወኪል ነን" ባይ ድርጅቶች "ውክልናቸውን ለማረጋገጥ" ሊሄዱበት የሚችሉት ብቸኛ መንገድ ጉልበትና አመጽ ብቻ ይሆናል ሲሉም ይገልጻሉ።ይህ አመጽ ደግሞ አንድ ኃይል ወይም አንድ ወገን ብቻ የሚያካሂደው አመጽ ሳይሆን ሁሉም ሁሉንም የሚፈራበት፤ ሁሉም ከፍርሀቱ ለመውጣት ሳልቀደም ልቅደም በሚል ራሱን ለአመጽ የሚያዘጋጅበት፤ ተዘጋጅቶም "ጠላቴ" የሚለውን ኃይል ለማጥፋት የሚንቀሳቀስበት ነው።የዘውጌ ክልሎች አንዱ ካንዱ ጋር ለውጊያ የሚነሳሱበት፣ በዘውጌ ክልሎችም ውስጥ፤ በየአካባቢው ባሉ 'ጊዜው የኛ ነው' ባይ ጉልበተኞች (የጦር አበጋዞች) የሚመሩ ቡድኖች የበላይነት ለማግኘት የዕርስ በዕርስ ጦርነት ውስጥ የሚገቡበት እልም ያለ ሥርዓት አልበኝነት የሚነግስበት ሁኔታ መፈጠሩ አይቀሬ ነው ሲሉ ስጋታቸውን ያስቀምጣሉ።አክለውም ይህ የተያያዝነው የለውጥ ሂደት ከዚህ በፊት እንደነበሩት የለውጥ ሙከራዎች ከስሞ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሌሎች ማኅበረሰቦች የደረሱበት ስልጣኔ ሂደት አካል ከመሆን ይልቅ ከመቶዎች ዓመታት በፊት ወደነበርንበት የጨለማ ዘመን መልሶ የሚከተን ከሆነ አደጋው ወደኋላ መመለስ ብቻ ሳይሆን እንደ አገር መቀጠል አለመቻልም ሊሆን ይችላል ብለዋል።ህዝብ በሚኖርበት የአስተዳደር እርከን ሁሉ እራሱን በራሱ ማስተዳደር አለበት የሚለውን መሰረተ ሃሳብ በግልጽ የሚቃወም የፖለቲካ ኃይል በዛሬይቱ ኢትዮጵያ የለም የሚሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ልዩነት ያለው ያልተማከለ ፌደራላዊ አስተዳደር ሲባል በተጨባጭ ምን ማለት ነው የሚለው ጥያቄ ላይ እንደሆነ ይጠቅሳሉ።አክለውም በፌደራላዊ የመንግሥት አደረጃጀት ውስጥ ከታችኛው እርከን ጀምሮ ያሉ የመንግሥት አስተዳደሮች ሁሉ በአካባቢው ነዋሪ በተመረጡ መሪዎች ይተዳደራሉ ወይም አካባቢውን የሚመለከቱ አስተዳደራዊም ሆነ የልማት ውሳኔዎችን በህዝብ በተመረጡ መሪዎች ይወሰናሉ ብለዋል።"ኢትዮጵያ ውስጥ ግን በብሔር የተደራጁ ኃይሎች ይህንን ለዘመናት "ታግለንለታል" የሚሉትን መርህ እንኳን በተግባር ለማዋል ፈቃደኞች አይደሉም" በማለት ከክልላቸው ውጪ ያሉ ዜጎች ምንም አይነት የዜግነት መብት የሌላቸው እንደሆኑ ተደርጎ የመቁጠር ሁኔታ እንዳለ ምሳሌ ጠቅሰው አስረድተዋል። በማስከተልም "እንዲህ አይነት አስተሳሰብ በነገሰበት አገር ውስጥ የተለያየ የዘውግ ማንነት ያላቸው ህዝቦች አገራዊ አንድነት ፈጥረው በሰላም አብሮ መኖር ይችላሉ?" በማለት "ዜጎች በሚኖሩበት አካባቢ ሰርተውና ያፈሩትን ሃብትና ከሚኖሩበት አካባቢ ነዋሪዎች ጋር ተጋብተው ወልደው የመሰረቱት ኑሮ ዋስትና ከሌለው እንዴት እራሳቸውን የዚህ አገር ዜጋ ነኝ ብለው ይጠራሉ?" ብለው ይጠይቃሉ ፕሮፌሰር ብርሃኑ። ቀጣዩ አገራዊ ምርጫ የችግሮቻችን መፍቻ መነሻ ነው የሚሉት ፕሮፌሰሩ ምርጫው ተዓማኒ እንዲሆንና፣ የሕዝብ እውነተኛ ፍላጎት መገለጫ እንዲታይ መሟላት ያለባቸው ጉዳዮችን ይዘረዝራሉ።ከእነዚህም መካከል አማራጭ አለን የሚሉ ድርጅቶች በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል ተንቀሳቅሰው፣ ያለምንም ችግር ማኅበረሰቡን ሰብስበው ማናገር መቻል አለባቸው የሚለው ቀዳሚው ነው። መራጩም የሚፈልገውን ስለመረጠ ምንም ዓይነት የደህንንት አደጋ አይደርስብኝም ብሎ መተማመን ደረጃ ላይ መድረስ አለበት ይላሉ።በማስከተልም ሌሎች በምርጫው ወቅትና ከምርጫው በኋላ መሆን አለባቸው ያሏቸውን ከዘረዘሩ በኋላ ለምርጫው ሳንካዎች ናቸው ያሏቸውን ፓርቲያቸው በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀስ የገጠሙትን ችግሮች በመንቀስ ያስረዳሉ።ይህ ጉዳይ ከቀጠለ ለበለጠ ግጭት ሊዳርግና ምርጫውን ተዓማኒነት ጥያቄ ውስጥ ይጥለዋልም ብለዋል።በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ውስጥ በተለይ በታችኛው እርከን ያሉ የመንግሥት አስተዳዳሪዎችና የፀጥታ ኃይሎች ከፖለቲካ ኃይሎችና ኢ-መደበኛ ከሆኑ የወጣት አደረጃጀቶች ጋር ህዝባዊ ስብሰባዎችን የማሰናከል፣ የተፎካካሪ ድርጅት አባሎችን ማሰርና ማንገላታት በተደጋጋሚ እያጋጠሙ ያሉ ፈተናዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ፕሮፌ. ብርሃኑ ለገዢው ፓርቲ ማስመረጫ ገንዘብ ማሰባሰብ በሚል እየተደረገ ነው በሚል በምሳሌ አስደግፈው ያቀረቡት ክስ ላይ "የመንግሥት ኃላፊነት ያለባቸው የገቢዎች ባለስልጣን ኃላፊዎች የሚቆጣጠሩትን የንግድ ማህበረሰብ ለብልጽግና ፓርቲ ገንዘብ እንዲያወጣ ሲጠይቁ፤ ባንዳንድ ቦታ የገቢዎች ባለስልጣን ማህተም ባለበት ደብዳቤ ነጋዴዎች ለብልጽግና ፓርቲ ገንዘብ እንዲያስገቡ ሲጠየቁ" እንደነበር አመልክተዋል። "ይህ እየተሄደበት ያለው መንገድ የምርጫውን የመወዳደሪያ ሜዳ እጅጉን ሚዛናዊነት የጎደለው እንዲሆን ከማድረጉም በላይ ከምርጫው በኋላ ሊመጣ የሚችለውን የሙስና አካሄድ የሚያሳይ ነውና ካሁኑ ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል" በማለት የመግሥትና የፓርቲ ኃላፊነቶችን የሚያደበላልቁ ሁኔታዎች ማየታቸው እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘም "የምርጫውን ተአማኒነት የሚያሳጡና ሀሳቦች በነጻነትና እንዳይንሸራሸሩ የሚያሰናክሉ ተግባራት፤ ወይም ምርጫው በፍትሃዊነት እንዳይካሄድና ወደ ገዥው ፓርቲ እንዲያደላ የመንግሥት ሃብትና መዋቅርን እራሱን ለማስመረጥ በሚል በየትኛውም መልክ ከተጠቀመበትና ምርጫው ተአማኒነት ካጣ፤ በሽግግሩ ሂደቶች ለሠራቸው ጥሩ ሥራዎች የምናመሰግነውን ያህል ዋናውን የመዳረሻ ሂደት ካበላሸው የለውጥ ኃይሉን በግልጽ ከመኮነንና ተጠያቂ ከማድረግ በፍጹም ወደኋላ እንልም!" ሲሉ በአጽኖት ተናግረዋል። በአጠቃላይ ግን ይህ ምርጫ እውነትም የህዝብ ውክልና የሚገለጥበት እንዲሆን ከተፈለገ እነኝህን በየክልሉ በተለይም በታችኛው እርከን ላይ የሚገኙ የመንግሥት ጉልበተኞች በአስቸኳይ መቆጣጠር ካልተቻለ ይህ ምርጫ ከፍተኛ የተአማኒነት ችግር ውስጥ እንደሚገባ ግልጽ ነው በማለት ጠቁመዋል።የጠቀሷቸው ችግሮች በዚሁ የሚቀጥሉ ከሆነም የምርጫው አካሄድ ክፉኛ ሊያበላሽና "አስፈሪ" ወዳሉት ሥርዓት አልበኝነት ወይንም "አዲስ ዓይነት አምባገነናዊ ሥርዓት" አገሪቱን ሊወስድ እንደሚችል ጠቁመዋል። አክለውም "ይህ የሽግግር ሂደት የለውጥ ኃይል እየተባለ ሲሞካሽ በነበረው ኃይል አጋዥነት ከተቀለበሰ የበለጠ ወደ አሳፋሪና አስፈሪ አደጋ አገራችንን መውሰዱ አይቀሬ ነው" በማለት አስጠንቅቀዋል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.bbc.com/amharic/51657331
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9895301a1818d7c52775bfcb1c5952e9
531ffedbbc157525cf8444f0044eae80
ህብረቱ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሀገራት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከላከያዎች በማሰራጨቱ እየተወጣች ላለችው ሚና ምስጋና አቀረበ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)  የአፍሪካ ህብረት ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ – ጃክ ማ ኢንሽዬቲቭ አማካኝነት ለአፍሪካ ሀገራት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከላከያዎች በማሰራጨቱ እየተወጣች ላለችው ሚና ምስጋና አቀረበ።የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊመቀመንበር ሙሳ ፋኪ መኸመት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በላኩት ደብዳቤ፥ ቁሳቁሶቹን በመረከብ እና ለሁሉም አባል ሀገራት በፍጥነት ለማድረስ ለሰጡት አመራር ምስጋናቸውን አቅርበዋል።ቁሳቁሶቹ በፍጥነት እንዲሰራጩ የህብረቱ አካል ለሆነው የአፍሪካ በሽታ መከላከል ማዕከል /ሲ ዲ ሲ/  ለሰጡት አመራር እና ምክርም ሊቀመንበሩ አመስግነዋል።እነዚህ ቁሳቁሶች በፍጥነት እንዲደርሱም ሁሉም አባል ሀገራት የዓየር ክልላቸውን እንዲከፍቱ እና አስፈላጊውን ሁኔታዎች እንዲያሟሉ ማስታወሻ ለሀገራቱ እንደሚልኩም ገልፀዋል።የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ቻይናዊው ባለሃብት ጃክ ማ በጋራ በወሰዱት ኢኒሼቲቭ አማካኝነት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን በአፍሪካ ለመከላከል የሚያግዙ የሕክምና መርጃ ቁሳቁሶች ወደ ተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በመድረስ ላይ ናቸው።ለእያንዳንዱ የአፍሪካ ሃገርም ቫይረሱን ለመለየት የሚረዱ 20 ሺህ መመርመሪያዎች፣ 100 ሺህ የፊት ጭምብል እና የህክምና ባለሙያዎች የሚለብሷቸው 1 ሺህ መከላከያ ልብሶች በመሰራጨት ላይ ይገኛሉ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%88%85%e1%89%a5%e1%88%a8%e1%89%b1-%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab-%e1%88%88%e1%8a%a0%e1%8d%8d%e1%88%aa%e1%8a%ab-%e1%88%80%e1%8c%88%e1%88%ab%e1%89%b5-%e1%8b%a8%e1%8a%ae%e1%88%ae/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
d8d5f6458f24ca4f63967657423469bb
6a06b01484cf84e4c2f33f065ae30fb4
የ16 አመት ሱዳናዊ ስደተኛ አስከሬን በፈረንሳይ ባህር ዳርቻ ተገኝቷል።
የታዳጊው ሱዳናዊ ስደተኛ አስከሬን በፈረንሳይ ባህር ዳርቻ ተገኘ\nታዳጊው ከፈረንሳይ ወደ እንግሊዝ በትንሽ ጀልባ ሊያቋርጥ ሲል ጠፍቶ የነበረ ሲሆን የስደተኞች መናኸሪያ በሆነው ካላይስ መገኘቱንም ባለስልጣናቱ አስታውቀዋል። ሌላ ስደተኛ በዚሁ ዳርቻ መገኘቱንም ተከትሎ ነው ፍለጋው የተጀመረው። ይኸው ግለሰብ መዋኘት የማይችለው ጓደኛው መጥፋቱን ተናግሯል። ትንሿ ጀልባ በስደተኞች ታጭቃ የነበረ በመሆኑም ወደ ጎን አጋድላ የተወሰኑት ውሃው ውስጥ መግባታቸው ተገልጿል። የፈረንሳይ ሚኒስትር ማርሊን ሺያፓ የታዳጊው አስከሬን በዛሬው ዕለት መገኘቱን የገለፁ ሲሆን ሰጥሞም በውሃው እየተገፋ ወደዳርቻው ተገፍቷል ብለዋል። በታዳጊውም መሞት በርካቶች ኃዘናቸውን የገለፁ ሲሆን ቻሪቲ ኬር ፎር ካላይስ የተባለው ድርጅት ተወካይ ክሌር ሞስሌይ የታዳጊውን ሞት "በጣም አሳዛኝና ተስፋ አስቆራጭ" ብለውታል። "ምን ያህል ፈርቶ ይሆን? በጣም ያሳዝናል፤ ለቤተሰቦቹም መፅናናትን እንመኛለን" ብለዋል። ድርጅታቸው የሚደግፋቸው ታዳጊዎቹ ስደተኞች በርካቶዎቹ በትምህርታቸው ጎበዝ፣ አንዳንዶቹ እግር ኳስ የሚወዱ፣ መፅሃፍ የሚያነቡና ያለፉበትን ሰቆቃና መከራ ረስተው ነገን በተስፋ የሚያዩ ናቸው ይላሉ። "ማንም ቢሆን በእንዲህ አይነት መንገድ ብቻን በባህር መሞት አይገባውም" ብለዋል። የእንግሊዙ ቀይ መስቀል ዋና ስራ አስፈፃሚ ማይክ አዳምሰን በበኩላቸው "ሰዎች አማራጭ አጥተው እንዲህ አደገኛ የሆኑ ጉዞዎችን ለማድረግና ጥበቃ ለመፈለግ ይህን ያህል መስዋዕትነት ሊከፍሉ መገደድ የለባቸውም" ሲሉ አስረድተዋል። የእንግሊዝ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ፕሪቲ እንዳሉት የታዳጊው ስደተኛ ሞቶ መገኘት "ህገ ወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች ምን ያህል ተጋላጭ ማህበረሰቦችን እንደሚበዘብዙ በሚያሳዝን መልኩ የሚያስታውስ ነው" ብለዋል። የእንግሊዝ ባለስልጣናት ታዳጊው ወደ እንግሊዝ ለመድረስ እየተጓዘ ነው ከማለት ተቆጥበዋል። በዚህ አመት 4 ሺህ 800 ስደተኞችን የያዙ 360 ትንንሽ ጀልባዎች ወደ እንግሊዝ ገብተዋል። የሌበር ፓርቲ ፓርላማ አባል ቶማስ ስይሞንድስ በበኩላቸው በጀልባ ለሚያቋርጡ ስደተኞች የመንግሥታቸው ምላሽ "ኃዘኔታን ያጣና በቂ አይደለም" ሲሉ ተችተዋል። በርካታ ስደተኞችም ህይወታቸውን እያጡም እንደሆነም ገልፀዋል። እየተከሰተ ላለው ቀውስም ሰብዓአዊ መፍትሄ ለማምጣት ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር እንዲሰሩም ለሚኒስትሮች ጥሪ አቅርበዋል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
9d500ec4d2526a74bbf7268a3e94b664
997a81e7da7d4441905978d44f5001cf
በአሰቃቂው የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደ ቅጠል ረግፈዋል። በርካቶች ተደፍረዋል፣ አካል ጉዳተኛ ሆነዋል።
በሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ የተሳተፉ ሴቶች የተዘነጋ ታሪክ\nፎርቹኔት ሙካንኩራንጋቨ የማያቋርጥ ዋይታ፣ ለቅሶ የተሰሙባቸው መራር መቶ ቀናት። የዘር እልቂቱ ሁለት አስርት ዓመታትን ቢያስቆጥርም ከመራር ሃዘን ጋር ለመኖር የተገደዱ፣ ከማይሽር ጠባሳ ጋር እየተጋፈጡ የሚኖሩ ጥቂት አይደሉም። ያው ህይወት መቀጠል አለባት። ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት በሩዋንዳው የዘር እልቂት ተሳትፈዋል የሚባሉት ታዋቂ ስሞች በተደጋጋሚ ይነሳሉ። ብዙዎቹም ወንዶች ናቸው። ከእልቂቱ ጀርባ ግን በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ሴቶች ቢሳተፉም ታሪክ ዘንግቷቸዋል። ጋዜጠኛዋ ናታሊያ ኦጄውስካ በጭፍጨፋው ተሳታፊ ከነበሩት መካከል በእስር ላይ የሚገኙትን የተወሰኑትን አናግራቸዋለች። ቀኑ ምንም የተለየ ነገር አልነበረውም። ፎርቹኔት ሙካንኩራንጋ ሌላ ጊዜ እንደምታደርገው ከቤቷ የወጣችው ቁርስ ለማዘጋጀት በሚል ውሃ ልትቀዳ ነበር። ነገር ግን በዚያኑ ዕለት ውሃ ብቻ አይደለም የቀዳችው፤ የሰው ህይወትም ነበር ያጠፋችው። እንዴት? የእስር ቤቱን ብርቱካናማ ቀለም ያለው መለያ ልብስ ለብሳ፣ ረጋ ባለ ድምጿ ከሃያ ስድስት ዓመት በፊት የነበረውን ሁኔታ እንዲህ ታስታውሰዋለች። ጊዜው ሚያዝያ 2/1986 ዓ.ም (በጎርጎሳውያኑ ሚያዝያ 10/1994)፤ እለቱም እሁድ ነበር። ቁርስ ለማዘጋጀት የሚያስፈልጋትን ውሃ ልትቀዳ ከቤቷ ወጣች። በመንገዷ ላይም በርካታ ሰዎች ተሰባስበው ሁለት ወንዶችን ክፉኛ ሲደበድቧቸው አየች። በጥላቻ የተሞላ ጊዜ፤ ርህራሄም ሆነ ሃዘን በመጀመሪያ አልተሰማትም። "ግለሰቦቹ ድብደባው ሲበዛባቸው መሬት ላይ ተዝለፍልፈው ሲወድቁ እንጨት አነሳሁና ቱትሲዎች መሞት አለባቸው እያልኩ አብሬ መደብደብ ጀመርኩ . . . ሰዎቹ በድብደባውም ሞቱ። ከገዳዮቻቸውም መካከል አንዷ እኔ ነኝ" ትላለች የ70 ዓመቷ እስረኛ። የሞቱት ድምፅ ይጣራል እነዚህ በጭካኔ መንገድ ላይ የተገደሉት ሁለቱ ሰዎች በመቶ ቀናት ውስጥ ከተገደሉት 800 ሺህ ቱትሲዎችና፣ ለዘብተኛ ከተባሉ ሁቱዎች መካከል ናቸው። ከሁቱ ጎሳ የሆነችው ፎርቹኔት በግድያው ከተሳተፈች በኋላ ለሰባት ልጆቿ ቁርስ ልትሰራ ወደቤቷ፣ ወደኑሮዋ ተመለሰች። ወደ ቤቷ ስትመለስ ግን ሌላ ሰው ሆና ነው የተመለሰችው። ቤት ስትደርስ ተሸማቀቀች። ውስጧ ተፀፀተ። የተገደሉት ሁለት ሰዎች ተማፅኖ፣ አሰቃቂ ድብደባም ፊቷ ላይ ድቅን ይልባታል። እረፍትም ነሳት። "እናት ነኝ። የሌሎች ህፃናት ወላጆችን ግን ገደልኩ" ብላለች። ከጥቂት ቀናትም በኋላ ወላጆቻቸው በቆንጨራ የተገደሉባቸው ሁለት የቱትሲ ህፃናት እየተንቀጠቀጡ ቤቷ መጡ። የሚደበቁበት የጠፋቸው፤ የሚሄዱበት የጨነቃቸው ልጆች መጠለያን ፈልገው ነበር ደጃፏ የደረሱት። ከምትጠላው ጎሳ ቢሆኑም የእናትነት አንጀቷ አላስቻላትም። አስገብታ ደበቀቻቸው። ከጭፍጨፋውም ሊተርፉ ቻሉ። "ሁለቱን ልጆች ባድናቸውም በሁለት ሰዎች ግድያ ተሳትፌያለሁ። ምንም ቢሆን ካደረስኩት ጥፋት ነፃ ሊያወጣኝ አይችልም" ብላለች ፎርቹኔት። በዘር ጭፍጨፋው ውስጥ ተሳትፈዋል በሚል ክስ ከተመሰረተባቸው 96 ሺህ ሴቶች መካከል ፎርቹኔት አንዷ ናት። እንደ ፎርቹኔት በርካታ ሰዎችን በመግደል እስር ቤት የገቡ እንዳሉ፤ ብዙዎችም ቱትሲ ሴት ህፃናትን ጨፍጭፈዋል እንዲሁም ቱትሲ ሴቶች እንዲደፈሩ ተባብረዋል። ከምሽቱ ሚያዝያ 2/ 1986 ዓ.ም በጊዜው ፕሬዚዳንት የነበሩት ጁቬናል ሃብያሪማና ተሳፍረውበት የነበረው አውሮፕላን መዲናዋ ኪጋሊ በሚገኘው አየር ማረፊያ አካባቢ ተመትቶ ወደቀ። ከሁቱ ጎሳ የሆኑት ፕሬዚዳንት ጁቬናልም ህይወታቸው አለፈ። ፕሬዚዳንቱን የገደላቸው ማን እንደሆነ ባይታወቅም የሁቱ ፅንፈኞች ግን የቱትሲ አማፂ ቡድን ነው ጥቃቱን የፈፀመው በሚል ወሬ መንዛት ጀመሩ። ምንም እንኳን ይሄ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
b86c8a241ae961c0edef15ba681e2a32
4c1bcb11a0ad2894343dd12163513515
የሱዳን መንግስት 1 ሺ 400 ኢትዮጵያዊያን እስረኞችን መፍታቱ ተገለጸ
የሱዳን መንግስት በተለያዩ እስር ቤቶች የሚገኙ 1ሺ 400 ኢትዮጵያዊያንን መፍታቱ ተገልጿል።ይህ የሆነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በሱዳን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት በሱዳን የታሰሩ ኢትዮጵያዊያንን እንደሚፈቱ ፕሬዝዳንት ኦማር ሐሰን አልበሽር  ቃል በገቡት መሰረት ነው።ዶክተር አብይ አህመድ በሱዳን ሚያዚያ 24 እና 25 ቀን 2010 ዓ.ም ይፋዊ ስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል።በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በተለያዩ ምክንያቶች በሱዳን በእስር ላይ ያሉ ኢትዮጵያዊያን እንዲፈቱ ለፕሬዚዳንት ኦማር ሐሰን አልበሽር ጥያቄ አቅርበዋል።ፕሬዝዳንት አልበሽርም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ጥያቄ መሰረት ኢትዮጵያዊያኑን እንደሚፈቱ ቃል በገቡት መሰረትም 1 ሺ 400 እስረኞች መፈታታቸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/29885/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
333778a43a6ea6523f774c5844d63f84
941ea0ec54a22e8f6301817c58eb1277
እህል በአፏ የማይዞረው ታዋቂዋ ምግብ አብሳይ
ሎሬታ የምትሠራው ምግብ ጨው ይብዛው ይነሰው መቅመስ ባትችልም በኢንስታግራም መድረክ በርካታ ወዳጆች አፍርታለች። ሎሬታ ቀቅላ የጠበሰችውን ድንች በሹካ እየፈረካከሰች እንፋሎቱን ትምጋለች። ሎሬታና እናቷ ጁሊ ይህን ማዕድ በጥንቃቄ ያበሰሉት ምናልባትም ይህ የመጨረሻዋ ይሆናል ብለው አስበው ነው። በደቂቃዎች ውስጥ አንድ ከበድ ያለ ስቃይ ሆዷን እየቦረቦረ እንደሚገባ ታውቀዋለች። ይህን ለምዳዋለች። እህልና ፈሳሽ ወደ አፏ ሄዱ ማለት ስቃይ ነው ትርፉ። ነገር ግን የመጣው ይምጣ ብላ ስቃይዋን ተቀብላ በቤተሰቦቿ ኩችና ወንበር ላይ ትውላለች። ኩችናው ማብሰል የተማረችበት አስኳላ ነው። "ከእናቴና እህቴ ጋር አንድ አፍታ ቁጭ ብሎ መመገብ የሚሰጠው ደስታ ለየት ያለ ነው።" ጊዜው በፈረንጆቹ 2015 ነበር። የ23 ዓመቷ ሎሬታ ለዓመታት በፈሳሽ መልክ በሚሰጣት ምግብ ነው የምትንቀሳቀሰው። ቤተሰቦቿ ለእራት ጠረጴዛ ሲከቡ እሷ ተለይታ ክፍሏ ውስጥ ከመቀመጥ ያለፈ ዕጣ አልነበራትም። በነጭ ሽንኩርትና ሎሚ ያበደውን የዶሮ ሥጋ አንስቶ መግመጥ ይቅርና ቢላና ሹካ ማንሳት ራሱ ብርቅ ነው የሚሆንባት። ነገር ግን ይኸው ዛሬ አንድ ጊዜ እንኳ ከቀረበላት ማዕድ ላይ ምግብ አንስታ እንድትበላ ሆነች። ይህን ያደረገው አንድ ባለሙያ ነው። ባለሙያው ሎሬታ ለምን ምግብ ስትበላ እንደሚያማት፣ ለምንስ ሽንት ቤት መጎብኘት እንደማትችል ለመመርመር ነው ዕቅዱ። ሎሬታ የዚያን ቀን ጠዋት ለንደን ወደ ሚገኘው ቅዱስ ማርቆስ ሆስፒታል አቅንታ በአፍንጫዋ ወደታች በተላከ አንድ ቀጭን ቱቦ የትንሹ አንጀቷን ጤንነት ተመርምራ መጥታለች። ሎሬታ ጨቅላ ሳለች በቴሌቪዥን መስኮት የሚታዩ የምግብ ዝግጅት ቅንብሮችን አስመስላ ለቤተሰቦቿ ታቀርብ ነበር። ምግብ ማብሰል መክሊቷ ነው ብንል ማጋነን አይሆንም። የ11 ዓመት ታዳጊ ሳለች ዘወትር ማክሰኞ እናቷ ከሥራ አምሽታ እንደምትመጣ ስለምታውቅ እራት አሰናድታ ትጠብቃት ነበር። እናቷ ጁሊ እንደምትለው ሎሬታ ማብሰል የጀመረችው በቲማቲም ስልስ የተቀመመ ፓስታ በመሥራት ነው። ነገር ግን ትንሽ ቆይታ ከበድ ያሉ ምግቦችን ማሰናዳት ተያያዘችው። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን እየተከታተለች ሳለ የምግብ ማብሰል ውድድር ላይ ተሳትፋ አሸንፋለች። ከትምህርት ቤት አልፋ በሌሎች ውድድሮች ላይ ታላላቆቹን ሳይቀር ረትታ ዋንጫ ይዛ መጥታለች። "የሎሬታ ትልቁ ብቃቷ ኩችና ውስጥ ባለው ነገር የሆነ ምግብ መሥራት መቻሏ ነው" ትላለች እናቷ ጁሊ። 15 ዓመት ሲሞላት የምግብ መብላት መመሰቃቀል የሚያስከትለው 'ኢቲንግ ዲስኦርደር' የተሰኘው በሽታ አገኛት። ነገር ግን እሷ እንደምትለው በሽታው ከአንድ ዓመት በላይ አልቆየም። ቢሆንም በታዳጊነት ዘመኗ የምግብ አለመፈጨት በጣም ያስቸግራት እንደነበር ታስውሳለች። ይህ ምግብ በበላች ቁጥር የሚጎረብጣት ስሜት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰ መጣ። የሆነ ሆኖ ይህን ስሜት እየታገለች ምግብ ማብሰሏንና መመገቧን ቀጠለች። ሎሬታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን እንደጨረሰች ለንደን ውስጥ ያለ አንድ ትልቅ የምግብ ዝግጅት ጥበብ ኮሌጅን ተቀላቀለች። ነገር ግን የሦስቱን ዓመት ኮርስ መማር የቻለችው ለአንድ ዓመት ብቻ ነው። ለዚህ ተጠያቂው ደግሞ የጤናዋ ሁኔታ ነበር። በ19 ዓመቷ ትምህርቷን አቋርጣ፣ ከምትወደው ኩችና ተነጥላ አልጋዋ ላይ ስቃይዋን እያስታመመች መኖር ሆነ ሥራዋ። በሽታው ሥጋዋን መጦ ከሰውነት ተራ እንድትወጣ አደረጋት። አልፎም የአእምሮ ጤናዋ ተቃወሰ። ሎሬታ በአንድ ወቅት ክብደቷ ሲለካ መመዘኛው ላይ የሚታየውን ብዙዎች ማመን አልቻሉም። 25 ኪሎ ይላል። ይህ ደግሞ ለሕይወቷ ጭምር አስጊ እንደሆነ ዶክተሯ በተደጋጋሚ አስጠንቅቀዋል። ምንም እንኳ ስቃዩ ለጠላቷ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
944036ceab8417805897d0c094b67ff5
bd377903ee795adc49c663cc1287497f
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ወራት 83 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ ገብተዋል
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 13 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ወራት 83 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 4 ሺህ 359 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን በኦሮሚያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አዲሱ አረጋ አስታወቁ።ከእነዚህ ውስጥ 3 ሺህ 519 ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮች ሲሆኑ 316ቱ ወጣቶች መሆናቸውን ገልፀዋል።450ዎቹ ሀገር በቀል ባለሀብቶች እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እና 74 የማስፋፊያ ጥያቄ ያቀረቡ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ለእነዚህ አልሚዎች 35 ሺህ 920 ሄክታር መሬት ተላልፏል ያሉት አቶ አዲሱ ፕሮጀክቶቹ በሙሉ አቅም ወደ ስራ ሲገቡ ለ313 ሺህ 566 ወጣቶች የስራ ዕድል ይፈጥራሉ ብለዋል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
ቢዝነስ
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%8a%a6%e1%88%ae%e1%88%9a%e1%8b%ab-%e1%8a%ad%e1%88%8d%e1%88%8d-%e1%89%a3%e1%88%88%e1%8d%89%e1%89%b5-%e1%8a%a0%e1%88%9d%e1%88%b5%e1%89%b5-%e1%8b%88%e1%88%ab%e1%89%b5-83-%e1%89%a2%e1%88%8a/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
09054b725ba417b69cde8136e942dac1
2beb381f477c9bde7e1b16b4e9a2efd8
ም/ጠ/ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከጣሊያን የህግ መወሰኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ
የኢትዮጵያ ም/ጠ/ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከጣሊያን የህግ መወሰኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ።ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በሮም በሚካሄደው የኢትዮ ጣሊያን የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ለመሳተፍ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሓላፊዎችና የንግዱ ማህበረሰብ ልዑካን ቡድንን በመምራት ጣሊያን ተገኝተዋል፡፡በዚህም ሀገራቱ ያላቸውን ዲፕሎማሲና የልማት ትብብሮቻቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከጣሊያን ሴኔት ፕሬዝዳንት ማሪያ ኤልዛቤታ አልበርቲ ጋር በሮም ተወያይተዋል፡፡ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ በተለይም ከኤርትራ ጋር የቆየውን የሻከረ ግንኙነት የተሻለ ለማድረግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተጫወቱት ሚና ለሌሎች ሀገራት በተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ የ2019ኙን የዓለም የኖቤል ሽልማት በማሸነፋቸው ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክም አስተላልፈዋል፡፡ጣሊያንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት መስክ አብረው በጋራ እንደሚሰሩም በነበረው ውይይት ላይ ተነስቷል፡፡ከዚህ በተጨማሪም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅት ፋኦ ዋና ዳይሬክተር ጄነራል ኩን ዶንግ ዩን ጋር ተወያይተዋል፡፡በውይይቱ ወቅትም ዓለም አቀፉ የምግብና የእርሻ ድርጅት ፋኦ በኢትዮጵያ ያለውን የለውጥ ሂደትና ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስራዎችን እንደሚደግፍ ነው ያረጋገጡት፡፡ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ዛሬ በሚከፈተው የኢትዮ ጣሊያን የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ተገኝተው ፣ከተለያዩ ተቋማት መሪች ጋርም ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል፡፡
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/31413/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9fcc9dcb602b883e48a1400861c42a26
94710418ad1c9f7c85bc2f9f40004b02
የሴቶች ንፅህና መጠበቂያ (ሞዴስ) በምትሰራ አንዲት ወጣት ሴት ህይወት ላይ ያተኮረው ዘጋቢ ፊልም ኦስካር አሸንፏል።
'አስጸያፊ' ከመባል ኦስካር ወደማሸነፍ\nየንጽህና መጠበቂያው ሞዴስ ሲሠራ ትላንት ባልተለመደ ሁኔታ ያለ አስተዋዋቂ የተካሄደው የኦስካር የሽልማት ሥነ ሥርዐት በርካታ ጥቁር ፊልም ሠሪዎች ጎልተው የወጡበት ነበር። 'ብላክ ፓንተር' በምርጥ ኦሪጅናል ስኮር፣ በፕሮዳክሽን ዲዛይንና በኮስቲውም ዲዛይን ሦስት ሽልማቶች አግኝቷል። በተጨማሪም ዛንዚባር የተወለደው የሮክ ኤንድ ሮል ሙዚቀኛ ህይወትና ሥራ የሚዳስሰው ፊልም እንዲሁም፣ ለበርካታ ዓመታት ሽልማት ሳይገኝ የቆየው ስፓይክ ሊ ተሸልሟል። ሌላው ተሸላሚ የጽህና መጠበቂያ ሞዴስ ላይ የሚያተኩረው ዘጋቢ ፊልም ነው። በሥራው ከተሳተፉት አንዷ ደግሞ ስኔህ ትባላለች። ስኔህ የወር አበባ ያየችው በ15 አመቷ ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ የወር አበባዋ ሲመጣ ምን እየተፈጠረ እንደሆነ አላወቀችም ነበር። "በጣም ደንግጬ ነበር። ከባድ በሽታ የያዘኝ መስሎኝ ማልቀስ ጀመርኩ" በማለት ትናገራለች። • "በወንድሜ ለአምስት ዓመታት ተደፍሬአለሁ" • በፍቅረኞች ቀን የፍቅር ስጦታ ለሴት ተማሪዎች "ለእናቴ ለመናገር ስለፈራሁ ለአክስቴ ነበር የነገርኳት። አክስቴ 'አሁን አድገሻል ማለት ነው። አታልቅሺ፤ ተፈጥሯዊ ነው።' በማለት አስረዳቺኝ። ለእናቴ የነገረቻት እሷ ናት" ስኔህ አሁን 22 አመቷ ነው። በመንደሯ በሚገኝ የንፅህና መጠበቂያ (ሞዴስ) በሚያመርት አነስተኛ ድርጅት ውስጥ ትሠራች። ስለ ወር አበባ ለህብረተሰቡ ታስተምራለች። ስኔህ ስለ ወር አበባ የተዛባ አመለካከት እንዳለ ትናገራለች 'ኢንድ ኦፍ ሴንቴንስ' (የአረፍተ ነገር መጨረሻ) የተባለው ዘጋቢ ፊልም ኦስካር ሲያሸንፍ፤ ስኔህ የኦስካር ዝግጅትን ለመታደም ወደ ሎስ አንጀለስ አቅንታለች። ዘጋቢ ፊልሙ የተሠራው በሰሜን ሆሊውድ አንድ የተማሪዎች ቡድን ባሰባሰበው ገንዘብ ንፅህና መጠበቂያ (ሞዴስ) የሚሰራ ማሽን እና ኢራናዊ አሜሪካዊ ፊልም ሠሪ ራይካ ዜህታብቺን ወደ ስኔህ መንደር በመላክ ነው። ፊልሙ የተቀረፀው በካቲክሄታ መንደር ባሉ የእርሻ ቦታዎች፣ ሜዳዎች እና የትምህርት ክፍሎች ነው። እንደ ሌሎቹ የሕንድ አካባቢዎች ሁሉ በካቲክሄራ መንደርም የወር አበባ የመነጋገሪያ ርዕስ አይደለም። • ሴቶች የተቆጣጠሩት የስፔን ካቢኔ • ታሪክ እየቀየሩ ያሉት ሴቶች ሴቶች በወር አበባ ወቅት እንደቆሸሹ ስለሚታሰብ ከሀይማኖት ቦታዎች እና ሌሎች ማኅበራው ክንውኖችም ይታገዳሉ። ስለ ወር አበባ ብዙ የተዛቡ አመለካከቶች ስላሉም ሰኔህ የወር አበባ ከማየቷ በፊት ስለ ወር አበባ ምንነት አለማወቋ አይገርምም። "የወር አበባ የመነጋገሪያ ነጥብ አልነበረም፤ በሴቶች መካከልም መወያያ ርዕስ አልነበረም" ትላለች። እንደ አውሮፓውያኑ በ2017 'አክሽን ኢንዲ' ውስጥ የሚሠራ ሱማን የተባለ ጎረቤቷ ንፅህና መጠበቂያ (ሞዴስ) የሚሠራ አነስተኛ ድርጅት ውስጥ ለመሥራት ፈቃደኛ እንደሆነች ጠየቃት። የኮሌጅ ተመራቂ የሆነችው እና አንድ ቀን ለደልሂ ፖሊስ መሥራትን የምታልመው ሰኔህ ጥያቄውን በደስታ ተቀበለች። በመንደሩም "ሌላ ምንም አይነት የሥራ እድል" አልነበረም። 'ፍላይ' የተባለው ንጽህና መጠበቂያ ሞዴስ "እናቴን ፍቃድ ስጠይቃት 'አባትሽን ጠይቂ አለችኝ'። በቤታችን ሁሉም ከባድ ውሳኔዎች በወንዶች ነው የሚወሰኑት" ስኔህ ለአባቷ ስለ ሥራው ለመናገር በጣም አፍራ ስለነበረ የህፃናት መፀዳጃ እንደምትሰራ ነበር የነገረችው። "ሥራውን ከጀመርኩ ሁለት ወር በኋላ ነው እናቴ ለአባቴ የሴቶች መፀዳጃ (ሞዴስ) እንደምሠራ የነገረችው" ትላለች ሰኔህ። እድለኛ ሆና አባቷ " ችግር የለውም፤ ሥራ ሥራ ነው" አለ። • ሴቶች በሰሜን ኮሪያ ሠራዊት ውስጥ • መጠጥ የ130 ሰው ህይወት ቀጠፈ ዛሬ አነስተኛ ድርጅታቸው ከ18 እስከ 31 ዓመት የሆኑ ሰባት ሴት ሠራተኞች...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
3147e89bfc7022fb0e61258cf40f1ef7
f4b22a37cce72c981d1c75bfcad4bcf1
የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በሳምንቱ መጨረሻ በውህደት ላይ ለመወሰን ይሰበሰባል
በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የሚመራው የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ፣ በዚህ ሳምንት መጨረሻ እንደሚሰበሰብና በግንባሩ ውህደት ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፍ ዋነኛው አጀንዳ እንደሚሆን ከግንባሩ ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ስብሰባ እንዲካሄድ የሚጠበቀው በሳምንቱ መጨረሻ እንደሆነ ጊዜያዊ ፕሮግራም መያዙን ከመረጃው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የመወያያ አጀንዳ ከሚሆኑት ወሳኝ ጉዳዮች መካከል የግንባሩን ቀጣይ አደረጃጃት መወሰን ነው፡፡ በዚህም መሠረት ግንባሩን አንድ ወጥ አገር አቀፍ ፓርቲ ለማድረግ ሲካሄድ የነበረውን ጥናት መነሻ በማድረግ ተወያይቶ የውሳኔ ሐሳብ ማሳለፍ አንዱ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ በግንባሩ ሦስት ፓርቲዎች በውህደቱ ላይ ተመሳሳይ አቋም መያዙ የተሰማ ሲሆን፣ የግንባሩ መሥራች የሆነው ሕወሓት ግን በግንባሩ አባል ፓርቲዎች መካከል የሐሳብ አንድነት የሌለ በመሆኑ ውህደትን በአሁኑ ወቅት ለመቀበል ፍላጎት እንደሌለው አቋሙን ይፋ አድርጓል፡፡ አዴፓ፣ ኦዴፓና ደኢሕዴን በግልጽ ወደ አገር አቀፍ ፓርቲ ለማምራት የሚያስችለውን ውህደት ደግፈዋል፡፡የአዴፓ፣ የኦዴፓና የደኢሕዴን አመራሮች እስካሁን ያለው የኢሕአዴግ አደረጃጀት አጋር ፓርቲዎች የሚመሯቸውን ክልሎች ያገለለና በአጠቃላይ ኢትዮጵያን ለመወከል የማያስችለው በመሆኑ፣ ኢሕአዴግ ከግንባርነት ወደ አገር አቀፍ ፓርቲነት መሸጋገሩ የግድ መሆኑ እንደታመነበትና ይህም በጠቅላላ ጉባዔ ተወስኖ ጥናት ሲደረግበት እንደነበር አስታውቀዋል፡፡ በጥናቱ ላይም ውይይቶች መደረጋቸውንና ስምምነት ላይ መደረሱን ገልጸዋል፡፡የኢሕአዴግ ውህደት ኢትዮጵያዊነትንና አንድነትን ከማንነት ጋር በማስተሳሰር ማስኬድ እንደሚቻል፣ ውህደት ለመፍጠርም በብሔራዊ ድርጅቶችና በኢሕአዴግ ደረጃም ውይይቶች መደረጋቸውንና ቀጣይ ውይይቶች እንደሚኖሩም አስረድተዋል፡፡የውህደት ሐሳቡ አስፈላጊነትን በተመለከተ ግንባር ቀደም ሚና የሚያራምዱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ የሚመሩት የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዴፓ) ማዕከላዊ ኮሚቴ በቅርቡ በአዲስ አበባ አድርጎት የነበረውን ስብሰባ አጠናቆ ባወጣው መግለጫ፣ አሁን ያለው የኢሕአዴግ አደረጃጀት የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ ለመመለስ የማያስችል እንደሆነ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡የኦዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባወጣው በዚህ መግለጫ የኢሕአዴግ አደረጃጀትን በማዘመን በዘመናዊ አሠራር የሚመራ ፓርቲ ለመመሥረት የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ሐሳብን በመደመር ሐሳብ ለመተካት ውይይት ሲደረግበት መቆየቱን ገልጾ፣ የመደመር ሐሳብ ከዚህ ቀደም የነበሩት ስኬቶችን ይበልጥ ለማጠናከር፣ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታትና የአዲሱን ትውልድ መብትና ጥቅም ያስከብራል ብሎ እንደሚያምን አስታውቋል፡፡በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች፣ ቋንቋዎችና ባህሎች ባሉበት አገር ውስጥ የፌዴራሊዝም ሥርዓት አማራጭ የሌለው ስለሆነ፣ ኦዴፓ ብዝኃነትን ማዕከል ያደረገ እውነተኛ ፌዴራሊዝም እንዲገነባና የኢትዮጵያ ሕዝቦች እኩልነትና ነፃነት እንዲከበር የማያወላዳ አቋም እንዳለው ገልጿል፡፡ በሳምንቱ መጨረሻ ላይ የሚሰበሰበው የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በግንባሩ ውህደት ጉዳይ ላይ ተወያይቶ ግንባር የፈጠሩት ፓርቲዎች እንዲዋሀዱ የሚፈቅድ የውሳኔ ሐሳብ የሚያሳልፍ ከሆነ፣ የውሳኔ ሐሳቡ በቀጣይ ለኢሕአዴግ ጠቅላላ ጉባዔ ቀርቦ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥበት ይደረጋል፡፡ ይህንን ሒደት ማጠናቀቅ ከቻለ ኢሕአዴግ ግንባርነቱን አፍርሶ ለመዋሀድ መወሰኑን የሚገልጹ ማስረጃዎችን በማቅረብ፣ አዲሱን ውህድ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ እንዲመዘገብ ያደርጋል፡፡ በአዲሱ የምርጫና የፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ መሠረት ውህድ ፓርቲውን ለማስመዝገብ ከሚቀርቡ ሰነዶች መካከል፣ የሚዋሀዱት ፓርቲዎች በተናጠል ጠቅላላ ጉባዔያቸው ውህደቱን ተቀብለው መወሰናቸውንና የግንባሩ ጠቅላላ ጉባዔ ውህደቱን ፈቅዶ ስለመወሰኑ የሚያስረዱ ሰነዶች ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ በውህደቱ ያልተስማማ የግንባሩ አባል ፓርቲ የራሱን ሕጋዊ ሰውነት ይዞ መቀጠል የሚችል ሲሆን፣ ውህደቱን ከተቀበሉ ፓርቲዎች ውስጥ በውህደቱ የማይስማሙ የፓርላማ ተመራጭ የሆኑ አባላት ቀሪ የምርጫ ዘመናቸውን የግል ተመራጭ እንደሚሆኑ አዋጁ ይደነግጋል፡፡ምርጫ በሚደረግበት ወቅት ውህደት የሚፈጽሙ ፓርቲዎች ውህደቱን በማስመዝገብ ዕውቅና ለማግኘት ማመልከት የሚጠበቅባቸው፣ የዕጩዎች ምዝገባ ከመጀመሩ ከ90 ቀናት በፊት መሆን እንዳለበትም አዋጁ ይደነግጋል፡፡
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/17273
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8ef337766f31c8cc1e946f0af5ec6ed6
9841a4fbd81bbf7c97a951562bb2dc6b
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ እጩ ተወዳዳሪዎች የመጀመርያው ዙር ክርክር አካሄዱ
ሁለቱ እጩዎች ለፕሬዘዳንትነት በሚያደርጉት በዚህ በትላንቱ የ 90 ደቂቃ ጠንካራ ክርክር፥ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች፥ በምጣኔ ሃብትና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተከራክረዋል።የትላንት ማታው ክርክር፥ በ 2016ቱ የዩናይትድ ስቴትስ ምርጫ ዘመቻቸው ላይ ትልቅ ልዩነት ሊያመጣ ይችላል ተብሎ የታመነበት ነው።ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/usa-first-presidential-candidates-debate-/3527238.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
aa853403280da7c7aed0e25371c59b68
c9e91727f74d9d9722020188c1072e1a
የዓለም ጤና ድርጅት ለአዳዲሶቹ የኮቪድ-19 ዝርያዎች ስም ለመስጠት የሚያስችል ስርአት ማዘጋጀቱን አስታወቀ።
ኮሮናቫይረስ፡ የዓለም ጤና ድርጅት ለአዲሶቹ የኮቪድ ዝርያዎች የግሪክ ስያሜዎችን ሰጠ\nከዚህ በኋላም ድርጅቱ የቫይረሱን አይነቶች ለመለየት የግሪክ ፊደላትን የሚጠቀም ሲሆን በዩናይትድ ኪንግደም፣ ደቡብ አፍሪካና ሕንድ ውስጥ የታዩት አዳዲስ ዝርያዎች መጀመሪያ ስያሜ ይሰጣቸዋል። ለምሳሌም በዩናይትድ ኪንግደም የታየው አዲሱ ቫይረስ ዝርያ 'አልፋ' የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። የደቡቡ አፍሪካው 'ቤታ' የተባለ ሲሆን በሕንድ በርካቶችን ያጠቃው የቫይረስ አይነት ደግሞ 'ዴልታ' ተብሎ እንደሚጠራ የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። የዓለም ጤና ድርጅት ስያሜዎቹን ያስተዋወቅኩት አንደኛ በንግግር ወቅት ቀላል ለማድረግና በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በቫይረሱ ዙሪያ የሚኖሩ የተለያዩ ማግለሎችን ለማስቀረት ነው ብሏል። ባሳለፍነው የፈረንጆቹ ወር መጀመሪያ አካባቢ የሕንድ መንግሥት በአገሪቱ የተገኘውን የኮቪድ-19 አዲስ ቫይረስ 'ቢ.1.617.2' የሚል ስያሜ መስጠቱን ተከትሎ በርካታ ትችቶችን አስተናግዶ ነበር። ''የትኛውም አገር አዲስ የቫይረሱ አይነቶችን ሪፖርት በማድረጉ መገለል ሊደርስበት አይገባም'' ብለዋል የዓለም ጤና ደርጅት ቴክኒካል መሪ የሆኑት ማሪያ ቫን ኬርኮቭ። አክለውም አገራት አዲሶቹ ቫይረሶች ላይ ጠበቅ ያለ የክትትልና የምርመራ ስራ እንዲያከናውኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። አዲሱ የቫይረሶቹ ስያሜ ከተለያዩ ነገሮች አንጻር ከግምት ውስጥ እንደገባ የተገለጸ ሲሆን የሁሉም ቫይረሶች ስም ዝርዝር በዓለም ጤና ድርጅት ድረገጽ ላይ ይፋ ተደርጓል። እነኚህ የግሪክ ፊደላት አሁን በጥቅም ላይ እየዋሉ የሚገኙትን ሳይንሳዊ ስሞች የሚተኩ አይደለም። አዲሶቹ የኮሮናቫይረስ አይነቶች ከ24 የሚበልጡ ከሆነ የተዘጋጀው ስርአት ፊደላት ያልቁበታል። በዚህም መሰረት አዲስ ስያሜ የመስጠት ስርአት ይዘረጋል ብለዋል ማሪያ ቫን ኬርኮቭ። ''እኛ እያልን ያለነው እንደ ቢ.1.617.2 ያሉ ሳይንሳዊ ስያሜዎችን ሙሉ በሙሉ መቀየር ሳይሆን ሁሉም ሰው የሚረዳው አይነት ስያሜ እንስጠው ነው። ስያሜው ቀለል ሲል ማህበረሰቡ በዕለት ተዕለት ግንኙነቱ ይጠቀማቸዋል'' ብለዋል። ሰኞ ዕለት የዩናይትድ ኪንግደም መንግስትን የሚያማክሩ ተመራማሪዎች አገሪቱ በሶስተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የመጀመሪያ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል። በዋነኛነት ሰዎችን እያጠቃ የሚገኘውም 'ዴልታ' የሚል ስያሜ የተሰጠው የሕንዱ ዝርያ ነው። ይህ ዝርያ 'አልፋ' የሚል ስያሜ ከተሰጠው የዩኬው ዝርያ በበለጠ መልኩ በቶሎ መሰራጨት የሚችል ሲሆን በዩኬ ለጨመረው በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ምክንያት ነው። በሌላ በኩል በቬትናም የተስተዋለው አዲሱ የቫይረስ አይነት በሕንድ እና ዩናይትድ ኪንግደም ከታዩት የቫይረሱ ዝርያዎች የተቀላቀለ ሲሆን በቀላሉ በአየር መተላለፍ የሚችል ነው።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
5276b4d43be70c3e76236238c32acc4a
b735dac0cb300f0fda03f273eddf4723
በአማራ ክልል የካናቢስ አምራች ኩባንያና በነዋሪዎች መካከል ተደረገ የተባለው ውይይት ወዝግብ አስነሳ
አፍሪካና ካናቢስ የተሰኘ በአገር ውስጥና በውጭ ባለሀብቶች የተቋቋመ ኩባንያ፣ በአማራ ክልል ደምበጫ ወረዳ የካናቢስ ማምረቻ ፋብሪካ ለመክፈት ከነዋሪዎች ጋር አደረገው የተባለው ውይይት ውዝግብ አስነሳ፡፡ ኩባንያው ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ በክልሉ ለመድኃኒትነት የሚውል የካናቢስ ማምረቻ ፋብሪካ ለመክፈት ጥያቄ ቢያቀርብም፣ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሳይሰጠው ቆይቷል፡፡የኩባንያው ባለሀብቶች ባለፈው ሳምንት ደንበጫ ወረዳ በመሄድ የወረዳው አመራሮች በተገኙበት ለነዋሪዎች የካናቢስ (ዕፀ ፋሪስ) ፋብሪካ ማቋቋም እንደሚፈልጉ፣ በሚገነባው ፋብሪካም አምስት ሺሕ ለሚሆኑ ነዋሪዎች ሥራ መፍጠር እንደሚችሉ ማብራርያ መስጠታቸው ታውቋል፡፡ ባለሀብቶቹ ባቀረቡት ሐሳብ ላይ ተሰብሳቢዎች ይሁንታ ሰጥተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡‹‹በዋናነት ወደ ወረዳው የሄድነው የኩባንያው አንደኛው ባለሀብት የአካባቢው ተወላጅ ስለሆነ ማኅበረሰቡን ለማሳመን ነው፤›› ሲሉ፣ የአፍሪካና ካናቢስ ኩባንያ ተወካይ አቶ ደረጀ ነጋሽ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ነገር ግን ጉዳዩ በማኅበራዊ ትስስር ድረ ገጾች በተለይም በፌስቡክ ከተለቀቀ በኋላ ውዝግብ ተነስቷል፡፡የጤና ጥበቃ ሚኒስቴሩ ዶ/ር አሚን አማን ካናቢስን ለመድኃኒትነት ለማዋል ተብሎ የተሰጠ ፈቃድ እንደሌለ በትዊተር ገጻቸው ይፋ አድርገዋል፡፡የአማራ ክልል የኮሙዩኒኬሽን ቢሮም ተመሳሳይ መልዕክት አስተላልፏል፡፡ ‹‹ክልላችን ምንም ዓይነት ፈቅድ አልሰጠም፤›› በማለት፣ የቢሮው ኃላፊ አቶ አሰማኸኝ አስረስ ለሪፖርተር አስታውቀዋል፡፡ ነገር ግን ስብሰባው መካሄዱን ገልጸዋል፡፡‹‹ባለሀብቶቹ ስብሰባውን ያደረጉት ሆን ብለው ማኅበረሰቡን አሳምነው ፈቃድ ለማግኘት በማሰብ ሳይሆን አይቀርም፤›› ሲሉ፣ የአማራ ክልል የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የፕሮሞሽን ኃላፊ አቶ ይኼኔው ዓለም ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡ኩባንያው ከኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ቁጥጥርና አስተዳደር ባለሥልጣን ፈቃድ ጠይቆ መከልከሉን፣ ከባለሥልጣኑ አንድ ኃላፊ ለመረዳት ተችሏል፡፡ከአፍሪካና በተጨማሪ ካነቦ ሪሰርች የተባለ የእስራኤል ኩባንያም ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርቦ እንደነበር የሪፖርተር ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/article/15086
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
de6909640161979801ac5b3811540973
219273f0ebbbdbef73905880074e1db9
በመዲናዋ ከ120 ሺ በላይ ሠራተኞች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሊሰጡ ነው
አዲስ አበባ:- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር ተቀጥረው የሚሠሩ ከ120 ሺ በላይ የመንግሥት ሠራተኞች የፐብሊክ ሰረቪስ ሳምንት በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለመዲናዋ ነዋሪዎች ሊሰጡ ነው። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፍሬህይወት ገብረህይወት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የፐብሊክ ሰርቪስ ሳምንትን በመዲናዋ በተያዘው ዓመት ለስድስተኛ ጊዜ ይከበራል፡፡ ከአሁን በፊት የከተማ አስተዳደር ሠራተኞች በዓሉን ሲያከብሩ የነበረው የተለያዩ ግምገማዎችን፣ ውይይቶችን እንዲሁም ስብሰባዎችን በማድረግ ሲሆን፤ ዘንድሮ ግን ሥራ በማይኖርበት ቅዳሜ ዕለት ለከተማዋ ነዋሪ አገልግሎት በመስጠት አክብረው የሚውሉ ይሆናል፡፡ በዓሉን የበጎ ፍቃድ አገልግሎትን ለማበረታታትና የሥራን ክቡርነትን ለማሳየት በማሰብ ነገ በመዲናዋ ከ120 ሺ በላይ የመንግሥት ሠራተኞች በሥራ ገበታቸው ተገኝተው በመደበኛው የሥራ ቀናት የሚሰጡትን አገልግሎት በበጎ ፈቃደኝነት ለመዲናዋ ማህበረሰብ አገልግሎቱን ለመስጠት እንደተዘጋጁ ገልፀዋል። ዓላማው የመንግሥት ሠራተኛው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ባህሉን ለማሳደግ እንደሆነ የሚናገሩት ዶክተሯ፤ ባለፈው ዓመት በዚህ ወቅት ሰኔ 16 ቀን የመዲናዋ ህዝብ በራሱ ተነሳሽነት <<ሆ>> ብሎ በመውጣት ለውጡን እንደሚደግፍ ያሳየበት ጊዜ እንደነበር አስታውሰው፤ ስለዚህ የዛሬ ዓመት በዚህ ወቅት የመዲናዋ ህዝብ ለውጡን ደግፎ ላሳየው አንድነት የፐብሊክ ሠራተኛው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በመስጠት ምስጋና ለማቅረብ ታሳቢ የተደርገ ነው ብለዋል።አዲስ ዘመን ሰኔ 14/2011
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=12882
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f8550737d2383fe15f97e0f64e00aee9
df829dcb2f13ee94a028c875634ade79
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን አስመረቀ
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሐግብሮች ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎቹን አስመረቀ፡፡ዩኒቨርሲቲው በዛሬው እለት ያስመረቃቸው ተማሪዎች ቁጥር 1 ሺህ 300 ተማሪዎች ናቸው፡፡ከዚህ ውስጥ 1 ሺህ 228 በመጀመሪያ ዲግሪ ሲሆን 70 በሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም ሁለት ተመራቂዎችን በሶስተኛ ዲግሪ አስመርቋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%8a%a0%e1%8b%b3%e1%88%9b-%e1%88%b3%e1%8b%ad%e1%8a%95%e1%88%b5%e1%8a%93-%e1%89%b4%e1%8a%ad%e1%8a%96%e1%88%8e%e1%8c%82-%e1%8b%a9%e1%8a%92%e1%89%a8%e1%88%ad%e1%88%b2%e1%89%b2-%e1%89%b0/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
6e7ced5f0f35154cdef363976d1d199f
e46f6252e2b95e3ebf83da8b8cd5c454
የኢትዮጵያ አየር መንገድ መቀሌና ላልይበላ ጨምሮ በሰሜናዊ የአገሪቱ ክፍሎች ዛሬ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎችን ባጋጠመው አስቸጋሪ የአየር ጠባይ ምክንያት መሰረዙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መቀሌና ላልይበላ በረራዎችን ሰረዘ\nአየር መንገዱ ጨምሮም በተመሳሳይ ወደ ጎንደር፣ አክሱምና ሽሬ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎችም ዛሬ ጠዋት በነበረው አመቺ ያልሆነ የአየር ሁኔታ ሳቢያ መስተጓጎሉን አመልክቷል። በዛሬው ዕለት የተሰረዙትን በረራዎች ያለው የአየር ሁኔታ መሻሻሉን በተመለከተ ከብሔራዊ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት የሚገኝን መረጃ መሰረት በማድረግ እንዲቀጥል የሚደረግ መሆኑን ገልጿል። ነገር ግን አሁን ከብሔራዊ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በረራዎችን ያስተጓጎለው የአየር ሁኔታ በቀጣዮቹ ሁለት ቀናት ውስጥም ሊቀጥል እንደሚችል አመልክቷል። በተያያዘ ዜና ከአርብ ከሰዓት ጀምሮ ቅዳሜ ዕለትም የባህር ዳር ከተማ ሰማይ በአቧራ ጭጋግ ተሸፍኖ እንደነበር ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገልጸዋል። ይህንን ክስተት በተመለከተ የምዕራብ አማራ የሜቲዮሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል የትንተናና ትንበያ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት አቶ ጥላሁን ውቡ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት "ጠንካራ የአቧራ ጭጋግ ተከስቷል።" ይህ የአቧራ ጭጋግ የሚከሰተው በደረቅ አካባቢዎች የሚከሰትን አውሎ ነፋስ ተከትሎ ነው የሚሉት ባለሙያው፤ በባህር ዳር ላይ የታየው የአቧራ አውሎ ነፋስ ሱዳን ላይ በተከሰተ ዝቅተኛ የአየር ግፊት ምክንያት መሆኑን ይናገራሉ። ይህ የአቧራ ጭጋግ የተከሰተው በባህር ዳር ከተማ ብቻ አለመሆኑን የሚናገሩት ባለሙያው ጎንደር ላይም መታየቱን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ክስተቱ ብዙ ጊዜ ለረዥም ሰዓት አይቆይም የሚሉት አቶ ጥላሁን ቶሎ ሊጠፋ እንደሚችል ያስረዳሉ። ነገር ግን በእንዲህ ዓይነት የአየር ሁኔታ አውሮፕላኖች ለመነሳትም ሆነ ለማረፍ እይታን ስለሚጋርድ ለበረራ አስቸጋሪ እንደሚሆን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ላይ ግን በረራዎች ከተስተጓጎሉባቸው ከተሞች ውስጥ የአቧራ ጭጋጉ የተከሰተባት የባህር ዳር ከተማ የለችበትም። ባለሙያው ጨምረውም እንዲህ አይነት አቧራ ጭጋግ የመተንፈሻ አካል ችግር በተለይ አስም ላለባቸው ሰዎች አስቸጋሪ እንደሚሆን አስታውሰው፤ እንዲሁም ክስተቱ የማጅራት ገትር በሽታ መንስዔም ሊሆን እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። ባህር ዳር የሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ እንዳረጋገጠው የአቧራ ጭጋጉ ዛሬ በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ቢሆንም የተወሰኑ ምልክቶች ግን እንዳሉ አመልክቷል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
16ffe9dd86c0fbe3b35e77d22d048ac9
1e88300a3d79e7acbcf5d0a2df4cdcde
የሲአን ዓለም አቀፍ ድጋፍ ምክር ቤት የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ እንደሚደግፍ አስታወቀ
የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ሲዳማ ዞን ራሱን በራሱ እንዲያስተዳድር ላለፉት 40 ዓመታት የታገልኩለት ዓላማ በመሆኑ የምደግፈው ዕርምጃ ነው ሲል አስታወቀ፡፡ የሲአን አመራሮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በውጭ አገር የሚገኙ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡና እንዲታገሉ ጥሪ ካቀረቡ በኋላ ወደ አገር ውስጥ መግባቱን በማስታወቅ፣ ሲዳማ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖረው አስተዋፅኦ የጎላ እንዲሆን ለማድረግም እሠራለሁ ሲል አስታውቋል፡፡‹‹የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ በተለየ መንገድ የሚረዱ ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ይሁንና የብሔር ማንነትና ኢትዮጵያዊነት አብረው የሚሄዱ ናቸው ብለን ስለምናምን፣ ለዚህ ጥያቄ መልስ በመሰጠቱ ከማንም በላይ ዘብ የምንቆምላት ኢትዮጵያ ነች የምትኖረው፤›› ሲሉ፣ የንቅናቄው ዓለም አቀፍ ድጋፍ ምክር ቤት ሰብሳቢ በዛብህ በራሳ (ዶ/ር) ለሪፖርተር አስታውቀዋል፡፡ስለዚህ ይህ ውሳኔ ወደ ተግባር እንዲገባ በፍጥነት ሕዝበ ውሳኔ ተደራጅቶ ሲዳማ ራሱን በራሱ ማስተዳደሩ ዕውን እንዲሆን ጥሪ በማቅረብ፣ ‹‹ሲዳማ የኢትዮጵያ አካል ሆኖ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ያለባት ኢትዮጵያ እንድትኖር፣ የበኩላችንን አስተዋፅኦ ለማድረግ ዝግጁ ነን፤›› ብለዋል፡፡የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ደጀኔ ወልደ አማኑኤል የብሔር ግጭቶችን በተለይም የወላይታና የሲዳማ ብሔር ግጭቶችን በማነሳሳት የሲዳማን ጥያቄ ሌላ መልክ ለማስያዝ ጥረት የሚያደርጉ አካላት አሉ ካሉ በኋላ፣ ‹‹በመሠረቱ የሲዳማና የወላይታ ፍላጎት ምንም የሚያጋጭ አይደለም፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡ ‹‹ሁለቱም የራሳቸው አስተዳደር ተሰጥቷቸው በሰላም እንድንኖር ነው የምንፈልገው፤›› ብለዋል፡፡በቀጣይ ምርጫ ብቁ ተወዳዳሪ ለመሆን ፓርቲያቸው ብቁ ዝግጅት ማድረጉን፣ እንደ ካሁን ቀደሙ አንድ ፓርቲ በበላይነት የሚመራት አገር ስለማትሆን ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ጥምረት ፈጥረው ለመሥራት ዓላማ እንዳላቸው፣ ለዚህም ለቀጣዩ ምርጫ እየተዘጋጁ እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ የመድረክ አባል የሆነው ሲአን መሥራች የሆኑ ስድስት አባላት ኅዳር 3 ቀን 2011 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ያስታወቁት የድጋፍ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ፣ በተለያዩ አገሮች ያሉና እስካሁን በፖለቲካው በንቃት ሊሳተፉ ያልቻሉ አባላትን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት እየሠሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡‹‹አሁን በአገሪቱ እያታየ ያለው ለውጥ እንዳይጨናገፍና ዘላቂ እንዲሆን ያለምንም ማለሳለስ የምንደግፈው ነው፤›› ያሉት አቶ ደጀኔ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይና ለመንግሥታቸው ምሥጋና አቅርበዋል፡፡በተጨማሪም ‹ኤጀቶ› በመባል የሚታወቁት የሲዳማ ወጣቶችን በለውጡ ተጫውተዋል ላሉት ሚናም አመሥግነዋል፡፡
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/13919
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
68540015b25e36f8dba522fe8f69c920
f77f3db07148be3a141502bce2707633
ኒው ዚላንድ
ኒው ዚላንድ በደቡብ ምዕራብ ፓሲፊክ ውቅያኖስ የምትገኝ የደሴት ሀገር ናት። ቋንቋዎች በኒው ዚላንድ በዋንነት የሚነገረው መደበኛ ቋንቋ እንግሊዝኛ ነው። ማዖሪኛ በተለይ በማዖሪ ብሔር ይነገራል፣ በ1979 ዓ.ም. ደግሞ ይፋዊ ቋንቋ ሆነ። ከ1998 ዓ.ም. ጀምሮ የአገሩ ሦስተኛው ይፋዊ ቋንቋ የኒው ዚላንድ እጅ ምልክት ቋንቋ ሆኗል። ባህል ከኒው ዚላንድ ሕዝቦች መካከል የማዖሪ ብሔር ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን በደሴቶቹ ላይ ኑረዋል። ማዖሪዎች «ሃካ» ስለ ተባለው ባህላዊ የውግያ ጭፈራ ታውቀዋል። በኒው ዚላንድ ባሕል ደግሞ የአገሩ ስፖርት (በተለይ የራግቢ) ቡድኖች ጨዋታ ሳይጀምሩ ሁልጊዜ «ሃካ» ይጨፍራሉ። አንዳንዴ በቀልድ የኒው ዚላንድ ባህል ዓምዶች «ሦስቱ Rዎች» ይባላሉ - እነሱም «Rugby Racing እና beeR» (ራግቢ፥ እሽቅድድምና ቢራ) ናቸው። እንዲያውም የፈረስ እሽቅድድም አሁን እንደ ቀድሞ ደረጃ የተወደደ አልቆየም፣ ራግቢ እና ቢራ ግን ዛሬውንም በኒው ዚላንድ ሕዝብ በኩል በጣም የሚወደዱ ሆነው ቀርተዋል። የኒው ዚላንድ ሰዎች አንዳንዴ በመጫወት ሲሆን በራሳቸውም ሆነ በሌሎች ዘንድ «ኪዊዎች» ይባላሉ። «ኪዊዎች» በተለመደው (በጅምላ አመለካከት) ተጨባጭ ያልሆነ ኀልዮ ወይም አሣብ ሳይሆን ተግባራዊ ጉብዝና እና ሙያ ይመርጣሉ። ኒው ዚላንድ ለረጅም ዘመን በክፍሎች ያልተመደበ ሕብረተሰብ ይቆጠር ነበር - ከሃብታሞችና ደሃዎች ኒው ዚላንድ ኗሪዎች መካከል የነበረው ልዩነት ያንስ ነበር ማለት ነው። በቅርቡ ባለፉት አሥርታት ግን ይሄው ሁናቴ ተቀይሯል። ብዙ የዚው ዚላንድ ኗሪዎች አድገው ወደ ውጭ አገሮች ይጎበኛሉ፣ ብዙዎቹም የባህላዊ ልውውጥ ፕሮግራሞች ይጠቅማሉ፣ ስለዚህ በዓለም ዙሪያ ይገኛሉ፣ በተለይም በአውስትራሊያ፣ ብሪታንያ፣ አውሮፓና እስያ ይጓዛሉ።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
ec79f3691904312fc89b349adc593cc9
6e002244634011733706037bb4dd7ed5
ፌዴሬሽኑ በወልዋሎ እና ሶስት ተጫዋቾች ውዝግብ ዙርያ ውሳኔ አስተላለፈ
በወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል የነበራቸው የወልዋሎ ተጫዋቾች አታክልቲ ፀጋዬ፣ ወግደረስ ታዬ እና መኩሪያ ደሱ ከክለቡ ጋር ኮንትራት እያላቸው አሰናብቷቸዋል በሚል ከዚህ ቀደም በዲሲፕሊን ኮሚቴ የተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንዲያደርግ በፌዴሬሽኑ ውሳኔ ተላልፎበታል።ተጫዋቾቹ በክረምቱ ክለቡ ቀሪ የአንድ ዓመት የውል ኮንትራት ቢኖራቸውም ከክለቡ ጋር እንደማይቀጥሉ በተሰጣቸው ደብዳቤ ክለቡን እንዲለቁ ቢወስንም ዘንድሮ የሚያጫውት ውል ያላቸው ሶስቱ ተጫዋቾች ለፌድሬሽኑ ቅሬታቸውን በማሰማታቸው ፌድሬሽኑ ተጫዋቾቹ ጥያቄያቸው ተገቢ ነው በማለት የወልዋሎን ውሳኔ በመሻር ወደ ስራቸው እንዲመለሱ እና ያልተከፈለ ደሞዛቸው በ10 ቀናት ውስጥ እንዲከፈል ማሳሰቡ የሚታወስ ነው። ሆኖም ክለቡ ውሳኔውን ተግባራዊ ባለማድረጉ ምክንያት የፌዴሬሽኑን ውሳኔ ተግባራዊ እስኪያደርግ ድረስ ማንኛውንም አገልግሎት ከፌዴሬሽኑ እንደማያገኝ በተከታዩ ደብዳቤ ገልጿል፡፡
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/41451
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
69f2ecb56632e59deb021bd495b5b6fc
ece1fa2e08e11ef74b2087677b390468
አክሰስ ሪል ስቴት ለሁለት ዓመታት ያቆመውን ሥራ ጀመረ
መሥራችና የቦርድ ሊቀመንበሩ የነበሩት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ከሁለት ዓመታት በፊት በድንገት ከአገር በመውጣታቸው፣ ሥራውን አቋርጦ የነበረውና በተለይ በቤት ገዢዎች ከፍተኛ ተቃውሞ የቀረበበት አክሰስ ሪል ስቴት፣ ከየካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ መደበኛ ሥራውን መጀመሩ ተገለጸ፡፡አክሰስ ሪል ስቴት ሥራውን መጀመሩን ይፋ ያደረገው አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ከመንግሥት ጋር ባደረጉት ድርድር በሕግ ያለመጠየቅ ዋስትና ተሰጥቷቸው፣ በስደት ለሁለት ዓመታት ከቆዩበት የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ የካቲት 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ በተመለሱ በ15ኛ ቀናቸው፣ ከንግድ ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን በሰጡት ቁጥብ ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡አቶ ኤርሚያስ የቦርድ ሊቀመንበር ሆነው ይመሩት የነበረው አክሰስ ሪል ስቴት፣ ከ2,000 በላይ የሚሆኑ ቤት ገዢዎች ሙሉ ክፍያ፣ ግማሽና የተወሰኑ ክፍያዎችን ተቀብሏል፡፡ ለቤት ገዢዎቹ በገቡት ውል መሠረት ቤታቸውን ገንብቶ ለማስረከብ ውል የፈጸመ ቢሆንም፣ የገባውን የውል ግዴታ በወቅቱ ሊወጣ አልቻለም፡፡ በመሆኑም ከአስገንቢዎቹ በተፈጠረ ጫና ምክንያት አቶ ኤርሚያስ ከአገር በመውጣታቸው ምክንያት፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ትዕዛዝ አማካይነት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ያሉበት ዓብይና የቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ የአክሲዮን ማኅበሩን ችግር ለመፍታት ሲንቀሳቀስ እንደነበር፣ የቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢና የንግድ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ኑረዲን መሐመድ አስታውሰዋል፡፡በመሆኑም አክሲዮን ማኅበሩ ወደተፈለገው የሥራ እንቅስቃሴ እንዲገባና ወደ ውጤት እንዲመለስ ለማድረግ፣ ከአገር ወጥተው ከነበሩት የማኅበሩ የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ኤርሚያስ ጋር የቀጥታ ድርድር በማድረግ፣ በሕግና በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ፖሊሲ የተቀመጡ ጉዳዮች ላይ በመነጋገርና ሕጉ የሚፈቅደውን በሕግ አግባብ በማድረግ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን አቶ ኑረዲን ገልጸዋል፡፡አቶ ኤርሚያስ የካቲት 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ አገር ቤት ከተመለሱ በኋላ፣ ተቋቁሞ ለነበረው ዓብይና ቴክኒክ ኮሚቴ (ከቤት ገዢዎች፣ ከውጭ ጉዳይ፣ ከንግድ፣ ከከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች፣ ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የተወከሉ ናቸው) የሥራ ዕቅዳቸውን እንዲያቀርቡ ተጠይቀው፣ አሥር ገጽ ጥቅል ዕቅድ ማቅረባቸውንም አቶ ኑረዲን አስረድተዋል፡፡ ከየካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮም መደበኛ ሥራ መጀመራቸውንም አረጋግጠዋል፡፡እሳቸው ይመሩት በነበረው አክሰስ ሪል ስቴት ላይ የተፈጠረው ችግር ለባለጉዳዮቹ፣ ከውጭ ሆኖ ለሚመለከተውም ሆነ ለራሳቸው ሊታሰብ የማይችልና ግራ የሚያጋባ መሆኑን የገለጹት አቶ ኤርሚያስ፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ብዙ ነገር መባሉ ትክክል መሆኑንና ነገር ግን ለምን እንደተፈጠረ፣ ማን ችግሩ እንዲፈጠር እንዳደረገና ሌሎች እውነታዎችን ጊዜውን ጠብቀው እንደሚናገሩ ቃል ከመግባት ባለፈ በወቅቱ ከመናገር ተቆጥበዋል፡፡‹‹አክሰስ ሪል ስቴት አክሲዮን ማኅበር ትልቅ ሀብት ይዟል፡፡ ከችግርም የሚያድነው ይኸው ትልቅ ሀብት ነው፡፡ መንግሥትም አምኖበት የገባው ትልቅ ሀብት ያለው ድርጅት በመሆኑ ነው፤›› ያሉት አቶ ኤርሚያስ፣ አክሲዮን ማኅበሩ ሥራውን ሊያቆም የቻለው ሀብት አጥቶ ሳይሆን እምነት በመጥፋቱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ እምነት ከሌለ ሁሉም ነገር እንደሚሸረሸርና እንደሚሸሽ የጠቆሙት አቶ ኤርሚያስ ቤት ገዢው፣ ባለድርሻው፣ ሕዝቡና መንግሥት እምነት ካላቸው ድርጅቱ ሊፈርስ እንደማይችል ደጋግመው ተናግረዋል፡፡ አሁን ትልቁ ዓላማቸው እምነት መገንባት እንደሆነም አክለዋል፡፡ ድርጅቱ እንዳይፈርስ መንግሥት እጁን አስገብቶ ውሳኔ ማሳለፉ ሊያስመሰግነው እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡በአክሰስ ሪል ስቴት ያለው ሥራ ያንን ያህል የሚያስጨንቅና የሚያስቸግር ባለመሆኑ በቀላሉ እንደሚከናወን የገለጹት አቶ ኤርሚያስ፣ ቤት የገዛም ሆነ የአክሲዮኑ ባለድርሻ የሆነ ሰው ቤቱን ከፈለገ ቤቱን፣ ወይም የከፈለውን ገንዘብ ከነወለዱ እንደሚያገኝ ገልጸዋል፡፡ እሳቸው፣ ድርጅቱና መንግሥት በአጭር ጊዜ የሚፈጽሙት ተግባር መሆኑንም አክለዋል፡፡ባለፉት ሁለት ዓመታት መብታቸውን በሕግ ለማስከበር ወደ ፍርድ ቤት ከሄዱ ቤት ገዢዎችና ድርጅቶች የተወሰኑት በሒደት ላይ ቢሆኑም፣ የተወሰኑት ውሳኔ አሰጥተው በአፈጻጸም ላይ መሆናቸው በሚመለከት ለተነሳው ጥያቄ የኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ኑረዲንና አቶ ኤርሚያስ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት የወሰዱ በሕግ አግባብ ማግኘት የሚገባቸውን ማግኘት መብታቸው መሆኑን፣ ኮሚቴውም ሆነ መንግሥት በሕግ የተያዙ ጉዳዮችን የማስቆም መብት እንደሌላቸውና ሕገ መንግሥታዊ መብት መሆኑን አቶ ኑረዲን ተናግረዋል፡፡ ሪል ስቴቱም በሕግ አግባብ መፍትሔ ለማምጣት ወደ ፍርድ ቤት እንደሚሄድ፣ አንዳንድ ውሳኔ የተሰጠባቸው ክሶች አክሰስ ሪል ስቴት መጥሪያ ሳይደርሰው፣ በፍርድ ቤት ቆሞ እንዲከራከር ሳይደረግና ምንም ዓይነት ጥሪ ሳይደረግለት የተላለፉ በመሆናቸው፣ እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስ ይግባኝ በማለት፣ ውሳኔዎቹን እንደሚያስቀለብሱና ችግሩን በመግባባት እንደሚፈቱ ተስፋ እንዳላቸው አቶ ኑረዲን አስረድተዋል፡፡ ፍርድ ቤቶቹ የሰጡት ውሳኔ አብዛኛውን ኅብረተሰብ ያማከሉ ውሳኔዎች ከሆኑ እንደማይቃወሙና ውሳኔውን እንደሚያከብሩም አክለዋል፡፡ አቶ ኤርሚያስም የአቶ ኑረዲንን ሐሳብ ተጋርተዋል፡፡አቶ ኤርሚያስ በዋናነት ከአገር እንዲወጡ ያስገደዳቸው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ቤት ገዢዎች ቤቱን የሚረከቡበት ቀነ ገደብ በማለፉ፣ ገንዘባቸው እንዲመለስላቸው ሲጠይቁ የጻፉላቸው ቼኮች በቂ ስንቅ ስላልነበራቸው በባንክ በማስመታት በደረቅ ቼክ ሊከሷቸው በዝግጅት ላይ በነበሩበት ወቅት መሆኑንና (ፖሊስ ጣቢያ ታስረው በዋስ መፈታታቸው ይታወሳል) ደረቅ ቼክ በወንጀል የሚያስጠይቅ በመሆኑ፣ እንዴት ዋስትና ሊሰጣቸው እንደቻለ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ኑረዲን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡አቶ ኑረዲን እንደገለጹት፣ የአገሪቱ ፖሊሲና የወንጀል ሕግ በሚፈቅደው መሠረት፣ በፍትሕ ሚኒስቴር በደንብ ተመርምሮና ተረጋግጦ ዋስትና ተሰጥቷቸዋል፡፡ ለጊዜው ያለውን ችግር እንዲያስጨርሱ ፍትሕ ሚኒስቴር እንዳስመጣቸውም ገልጸዋል፡፡  የተመሠረተባቸውን ክስ በመፍራት አገራቸውን ትተው ለተሰደዱ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ተመሳሳይ ዕድል ለምን እንዳልተሰጠ ለቀረበላቸውም ጥያቄ፣ አቶ ኑረዲን ሌላውም ይህንን ዕድል የማግኘት መብት እንዳለው ከመጠቆም ያለፈ ዝርዝር ማብራሪያ አልሰጡም፡፡ መንግሥት እጁን እንዲያስገባ የተደረገው የኅብረተሰቡን ችግር ለመፍታት መሆኑንም አክለዋል፡፡የአቶ ኤርሚያስ መምጣት መንግሥት ባቋቋመው ዓብይና ቴክኒክ ኮሚቴ ሥራ ላይ ተጨማሪ እርሾ ከመሆን ባለፈ በሥራው ላይ የሚቀንሰውም ሆነ የሚጨምረው ነገር እንደሌለ በመናገር፣ ‹‹አቶ ኤርሚያስ ባይመለሱም ኖሮ አክሲዮን ማኅበሩ ሥራውን መሥራቱ አይቀርም ነበር፤›› የሚል አንድምታ ያለው አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ ባለአክሲዮኖቹም ሆኑ ቤት ገዢዎቹ እምነት ሊያድርባቸው እንደሚገባ የተናገሩት አቶ ኑረዲን፣ በሦስት ሌሎች ሪል ስቴቶች ከ198 በላይ ቤት ገዢዎች ላይ ተመሳሳይ ችግር ተከስቶ፣ መንግሥት ጣልቃ በመግባት ችግሩ እንዲፈታ ማድረጉን በመጠቆም፣ የአክሰስ ሪል ስቴት ደንበኞችም በመንግሥት ላይ እምነት እንዲኖራቸው ጠይቀዋል፡፡አቶ ኤርሚያስ ተመልሰው ከመጡ በኋላ በአክሲዮን ማኅበሩ ላይ ኃላፊ ወይም የቦርድ ሊቀመንበር ሆነው እንደማይቀጥሉና አክሲዮን ማኅበሩ አዲስ ቦርድ መርጦ፣ በሰነዶች ማረጋገጫና መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤት ዕውቅና አሰጥቶ በሥራ ላይ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ኑረዲን፣ አቶ ኤርሚያስ የኋላ ደጀን ሆነው ሥራውን የመምራትና የማሠራት ኃላፊነት ብቻ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ቦርዱ ከፈለገ ሊያሳትፋቸውና አባል ሊያደርጋቸው እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡አቶ ኤርሚያስ ከአገር እንደወጡ ተመልሰው እንደሚመጡ ማሳወቃቸውን አስታውሰው፣ ከወጡበት ጊዜ ጀምሮ ከሁሉም ድርጅቶች ጋር ጥሩ ግንኙነት ሲያደርጉ መቆየታቸውን፣ ወደ አገራቸው ከተመለሱ በኋላ ባለፈው ሳምንት ውስጥ በፍርድ ቤት ውሳኔ ያገኘውን ጋቢ የተሰኘውን ኩባንያ ጨምሮ ከሌሎቹም ጋር በመደራደር እንደየፍላጎታቸው ሊፈጽሙላቸው እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡ከአገር ከወጡ ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ዕቅዳቸው እንደነበርና መንግሥት እንደሚያስራቸው እየነገራቸውም ቢሆን ይመጡ እንደነበር የገለጹት አቶ ኤርሚያስ፣ ‹‹እኔ አንደ አንድ ግለሰብ መታሰር አለመታሰር አስበርግጎኝ አያውቅም፡፡ ማንም ይታሰራል ይፈታል፡፡ ችግር የለውም፡፡ እስር ቤት እንዳቀባበሉ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜም ዕረፍት ይሆናል፡፡ እሱ የሚያስጨንቅ አይደለም፡፡ በታሪክም፣ አሁንም ማንም ታስሮ ይፈታል፡፡ ትልቅ ነገር አይደለም፡፡ ትልቁ ነገር ግን ሥራ ነው፤›› ብለው፣ እሳቸው ቢታሰሩ ኖሮ አክሰስ ሪል ስቴት የባሰ ብትንትኑ ይወጣ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ለጊዜው የማይሆን ነገር ከፊታቸው ተደቅኖ በማየታቸው መሸሻቸውን አምነዋል፡፡ ‹‹ጥፋት ካለብኝ እኔም ዜጋ ነኝ በጥፋቴ መታሰር አለብኝ፡፡ ክሱን ፈርቼና ሸሽቼ አልቀርም፡፡ መንግሥት ዋስትና ባይሰጠኝም ኖሮ መምጣቴ አይቀርም ነበር፤›› ብለዋል፡፡ አቶ ኤርሚያስ ለአክሰስ ሪል ስቴት ቤት ገዢዎች እንደየፍላጎታቸው የቤት ግንባታውን በጀመሩ አንድ ዓመት ውስጥ ሠርተው ለማስረከብ ቃል ገብተው መመለሳቸው ታውቋል፡፡
ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/article/3004
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
405fc2bd36834b4c908b8d79e81695a7
2f945dc4aeffc1b9f9827b0ad3ab5ed5
ኮሮናቫይረስ፡ በበይነመረብ የሚማሩ የውጭ አገር ተማሪዎች ከአሜሪካ እንዲወጡ መወሰኑ ቁጣን ቀሰቀሰ
የውጭ አገራት ዜጎችን በተመለከተ በበላይነት የሚመራው የመንግሥት ተቋም አይስ (ኢሚግሬሽን ኤንድ ከስተምስ ኢንፎርስመንት) ተማሪዎቹ በበይነ መረብ ብቻ የሚማሩ ከሆነ ከአገር እንዲወጡ እንደሚደረግም አስታውቋል። ያላቸው አማራጭም የሚማሩባቸውን ተቋማት በመቀየር በአካል ትምህርት የሚወስዱበትን መንገድ ማመቻቸት አለባቸው ተብሏል። በርካታ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ሆኖ ከመቀጠሉም ጋር ተያይዞ በሚቀጥለው አመትም ቢሆን ትምህርትን በበይነ መረብ ለማካሄድም እያሰቡ ነው። በዚህም የተነሳ ምን ያህል ተማሪዎች ተፅእኖ ውስጥ እንደሚወድቁ ቁጥሩ አልተጠቀሰም። ለጊዜው በጊዜያዊነት ወደበይነ መረብ ትምህርት ያሸጋገሩ ተቋማት ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎችና ለአጭር ጊዜ ትምህርት በአሜሪካ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በአገሪቷ ውስጥ እንዲቆዩና እንዲያጠናቅቁ ይደረጋል። ይሄ ሁኔታ ግን ለሚቀጥለው አመት የትምህርት ወቅት ተግባራዊ አይሆንም። ውሳኔውም ኤፍ 1ና ኤም1 የተሰኙ ቪዛ ያላቸውን ተማሪዎች እንደሚመለከትም ከአይስ መግለጫ መረዳት ይቻላል። ከሰሞኑ ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ለሚቀጥለው አመት ትምህርት በበይነ መረብ እንደሚሆን አሳውቋል። በግቢው ማደሪያ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎችም ቢሆኑ በበይነ መረብ እንዲማሩ ተወስኗል። ክሮኒክል ኦፍ ሃየር ኤዱኬሽን ከተባለው ድርጅት በተገኘው መረጃ 9 በመቶ የሚሆኑት ዩኒቨርስቲዎች በመጪው በጋ ትምህርቶቻቸውን በበይነ መረብ ለማካሄድ እንደወሰኑ ነው። ሁኔታው ግን በሚቀጥሉት ወራት ሊቀየር ይችላል። የሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ላሪ ባኮው ባወጡት መግለጫም አይስ ያወጣውንም መመሪያ ተቃውመውታል። ከዚህም በተጨማሪ የዲሞክራቷ ሴናተርም ኤልዛቤት ዋረን "ዩኒቨርስቲዎች በበይነ መረብ በማስተማራቸው ምክንያት ተማሪዎችን ከአሜሪካ ማስወጣት ጨካኝነት፣ ትርጉም የሌለውና ፀረ-የውጭ አገር ዜጎች ነው" ብለዋል በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደርን ጨምሮ በርካታዎች ይህንን ውሳኔ ያወገዙት ሲሆን በተለያዩ ሃገራት ያሉትን ሁኔታዎች እንዲሁም በአገራት መካከል ያለውን የሰዓት ልዩነት ያላጤነ ነው ብለውታል። በሳውዝ ፍሎሪዻ ዩኒቨርስቲ የድህረ ምረቃ ትምህርቱን እየተከታተለ ያለው ፓኪስታናዊው ሙሃመድ ኤሃብ ራሱል ውሳኔው ለአለም አቀፍ ተማሪዎች አስደንጋጭ ነው ብሏል። "እንደ አለም አቀፍ ተማሪነታችንና በአገሪቷ ውስጥም አናሳ እንደመሆናችን መጠን አሜሪካ ውስጥ ለመቆየት ሁሌም ምክንያት አቅርቡ መባል አጣብቂኝ ውስጥ የሚከት ጉዳይ ነው። በዩኒቨርስቲው ትምህርታችንን ለመጪው አመታት እንከታተል አንከታተል እንኳን አናውቅም፤ ይሔ አሳሳቢ ነው" ብሏል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
eb277fdd964b39c3aba797fb5c3c42ed
3314ddf2ff79bbbfca4606a4b1764a80
ህገ-ወጥ የመሬት ወረራ ለከተማዋ የአረንጓዴ ልማት እንቅፋት መሆኑ ተነገረ
 • ህብረተሰቡ ችግኞችን እንዲንከባከብም ጥሪ ቀርቧልአዲስ አበባ:- በአዲስ አበባ ከተማ ህገ-ወጥ የመሬት ወረራና የሕንፃ ግንባታዎች ለአረንጓዴ ልማት ዘርፉ እንቅፋት መሆኑ ተገለጸ። ህብረተሰቡ የተከላቸውን ችግኞች እንዲንከባከብም ጥሪ ቀርቧል::በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተፋሰስና አረንጓዴ አካባቢዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወሰን መግራ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት በከተማዋ ከሚገኙ ክፍለ ከተሞች ስድስቱ ተለይተው የከተማ የደን ልማት እየተካሄደ ሲሆን እስከ ወረዳ ድረስ መዋቅር ተዘርግቶ የማልማት፣ የመንከባከብና የመጠበቅ ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ።በተለይ ባለፈው ክረምት በአገር አቀፍ ደረጃ የተያዘውን የአረንጓዴ ልማት ሥራ ተከትሎ በከተማዋ ከፍተኛ የችግኝ ተከላ መካሄዱን የጠቆሙት አቶ ወሰን ሆኖም የአረንጓዴ ልማት ሥራው የተለያዩ ችግሮች እየገጠሙት እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ በተለይ ለአረንጓዴ ስፍራነት የተለዩ ቦታዎችን ለግል ጥቅም ሲባል መግፋትና ማጥበብ፣ አንዳንዴም ጭራሹን መጠቅለልና ለግንባታ ማዋል፣ ሕንፃ ሲሠራ ከተማዋን የለመዱና የአየር ንብረቱን የተዋሃዱ ዛፎችን በዲዛይን ማዳን እየተቻለ መቁረጥ፣ ህግ-ወጥ የመሬት ወረራና የግንዛቤ ማነስ የአረንጓዴና ደን ልማቱን ከማሳካት አኳያ የሚያጋጥሙ እንቅፋቶች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።የተተከሉ ችግኞች እንክብካቤና አያያዝን በተመለከተ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ እንደጠቆሙት እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ዝናብ ያለ ማቋረጥ ሲዘንብ በመቆየቱ ውሃ ማጠጣቱ አስፈላጊ አልነበረም። ከአሁን በኋላ ግን የመንከባከቡን ተግባር በተጠናከረ መልኩ ማከናወን ተገቢ ነው፡፡በዚህም መነሻነት ችግኞችን ለመንከባከብ በየክፍለ ከተማው ሁለት ሁለት የውሃ ማመላለሻና ማጠጫ ቦቴዎች መመደባቸውንና በዘርፉ በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ወጣቶችም ሥራውን በቋሚነት ለመሥራት ወደ ሥራ መግባታቸውን አቶ ወሰን ተናግረዋል፡፡ ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ለመከላከል አጥር የማጠር ሥራዎችም እየተሠሩ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ወሰን በመሆኑም ከመትከል እስከ ፅድቀት፣ ጥበቃና እንክብካቤ ድረስ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ እንደሚሠራ ተናግረዋል::ሥራውን ኤጀንሲው በበላይነት ቢያስተባ ብርም ችግኞችን የመንከባከቡና የመጠበቁ ድርሻ ግን የመላ ከተማዋ ነዋሪዎች በመሆኑ እከሌ ከእከሌ ሳይባል ሁሉም የከተማዋ ነዋሪ ያለማቋረጥ በአረንጓዴ ልማቱ ላይ በዘላቂነት መሳተፍ አለበት ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል። አቶ ወሰን እንዳሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ የመንከባከቡን ሥራ እራሳቸው መጀመራቸው ለመላው የአገሪቱ ህዝብ መልካም ምሳሌ ነው፤ ሁሉም የከተማዋ ነዋሪም ይህንን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ተግባር በአርኣያነት በመውሰድ የየራሱን ድርሻ ሊወጣ ይገባል፡፡“የሙቀት መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄድ፣ የከተሜነት መስፋፋት፣ መሰረተ ልማት ግንባታ በስፋት መከናወን ወዘተ የሚገኝበት ወቅት ላይ ነው የምንገኘው፤” የሚሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ለዚህ ችግር መፍትሔ የሚሆነው ደግሞ ችግኞችን የመትከል፣ ያሉትንም የመንከባከብና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ነው ብለዋል፡፡ “መትከል አንድ ቀን ነው፤ መከላከል ግን ዘላቂና የሁል ጊዜ ሥራ ነው” የሚሉት አቶ ወሰን ከተማዋ እራሷን በልታ ጭራሹን እንዳትጠፋ፣ ለኑሮ ምቹ እንድትሆን ማድረግ፣ በረሀማነትን መከላከል፣ ለአረንጓዴ ስፍራነት የተተዉ ቦታዎችን የማልማትና የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚያስችል አቅም የመፍጠር ኃላፊነት በሁላችንም ላይ የወደቀ በመሆኑ ሁላችንም የተከልነውንም ሆነ ያልተከልነውን ችግኝ መንከባከብ ይጠበቅብናል ብለዋል።አዲስ ዘመን ህዳር 1/2012ግርማ መንግሥቴ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=22294
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
bc8d0cb41150f88c23b5edecb6e36a19
28ae0deeb9294163e4003c239a4931cd
አየር መንገዱ ዓለም አቀፍ የሲቪል አቪየሽን ሲምፖሲየምን ያስተናግዳል
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አራተኛውን የዓለም አቀፍ የሲቪል አቪየሽን ሲምፖሲየም ከሚያዚያ 3 አስከ 5፣2009ዓ.ም. በአዲስ አበባ እንደሚያስተናግድ ተገለጸ፡፡ዛሬ በአየር መንገዱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተመለከተው በሲምፖሲየሙ ከ500 በላይ ተሳታፊዎች ከሁሉም የዓለም ክፍሎች ይገኛሉ፡፡የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ሲምፖሲየሙ በአፍሪካ ምድር ሲዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ሲምፖሲየሙ በሚካሁዱባቸው ቀናትም አዲሱና ዘመናዊው የካርጎ ተርሚናል እንደሚመረቅ ታውቋል፡፡ ተርሚናሉ በዓመት አስከ 650 ሺህ ቶን ዕቃ በማጓጓዝ የአፍሪካ የካርጎ ማዕከል እንደሚሆንም አቶ ተወልደ አክለው ገልጸዋል፡፡አየር መንገዱ 95 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችና 20 የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎች አሉት፡፡ በዓለም አቀፉ ደረጃም በቅርቡ ሰባት መዳረሻዎች አየር መንገዱ በቅርቡ እንደሚበርም ተመልክቷል፡፡በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተገለጸው አየር መንገዱ ከግማሽ ቢሊየን ዶላር በላይ በመመደብ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ 371 መኝታ ቤቶች ያሉት የሆቴል ግንባታም 40 በመቶው እንደተጠናቀቀና በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡በአፍሪካ ግንባር ቀደሙ የአፍሪካ አቪዬሽን ግሩፕ ለመሆን የተነሳው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በአሁኑ ወቅት በየዓመቱ የ25 በመቶ ዕድገት እያስመዘገበ ይገኛል፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፈው በጀት ዓመት 6 ቢሊየን ብር እንዳተረፈ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል፡፡
ቢዝነስ
https://waltainfo.com/am/23033/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
54c8389af6d8ae6c59d4c3319b935089
3a12fa6ce0be1287093cf1f64e2eff04
ሳይመረመሩ ከሱዳን የሚገቡ ዜጎች መዳረሻቸው የተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በመሆናቸው ወረርሽኙን የማስፋፋት ዕድላቸው ከፍተኛ መሆኑን የኅብረተሰብ ጤና ስፔሻሊስት ዶክተር አሳሰቡ፡፡
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 24/2012 ዓ.ም (አብመድ) ከሱዳን የሚገቡ ዜጎች ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚሄዱ በመሆናቸው ሳይመረመሩ ካለፉ ወረርሽኙን በከፍተኛ ደረጃ ሊያስፋፉት እንደሚችሉ የኅብረተሰብ ጤና ስፔሻሊስት ዶክተር አስገንዝበዋል፡፡አካባቢውን ‘‘የነጭ ወርቅ ምድር’’ ይሉታል፤ የሰሊጥ ወርቅ ይታፈስበታል፤ ምዕራብ ጎንደር ዞን፡፡ አሁን ደግሞ የኮሮናቫይረስ ከፍተኛ ስጋት ደቅኖበታል፤ በእርግጥ ስጋቱ በዞኑና በክልሉ ተወስኖ የሚቀር ይደለም፡፡ ምክንያቱም ስጋቱን ከፍ ያደረጉት ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ከመላው የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ ዜጎች ናቸውና፡፡ ዜጎቹ በኃላፊነት ስሜት ወደ ለይቶ ማቆያ ካልገቡና ተመርምረው ነጻ መሆናቸውን ሳያረጋግጡ ወደ መላ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚቀላቀሉ ከሆነ ደግሞ የሥርጭቱን ፍጥነትና ሥፋት አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ በምዕራብ ጎንደር ዞን ከነዋሪዎች ያልተናነሱ የዕለት ጉርስ ፈላጊዎችም በተለይ የክረምቱን የእርሻ ወቅት ምክንያት በማድረግ ይጎርፉበታል፤ ይህ ደግሞ ከወቅቱ የኮሮና ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የስጋት ቀጣና አድርጎታል፡፡እናም በአካባቢው ያለው ስጋት በፍጥነት ገደብ ካልተበጀለት ወረርሽኑ ወደገጠሩ ኅብረተሰብ እንዲገባ ሊያደርገው ይችላል፡፡ ሕይወትን ለመደጎም ወደአካባቢው የሄደው የቀን ሠራተኛ ወደቀዬው ሲመለስ በጥንቃቄ የተቀመጡ ቤተሰቦቹን በቫይረሱ ሊያስይዛቸውም ይችላል፡፡ እነዚህ በሮች ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል የሚመጣውን ኢትዮጵያዊ የሚያስገቡና የሚያስወጡ በመሆናቸው ከፀጥታ ኃይሉ ዕይታ ውጭ የገባ አንድ ኢትዮጵያዊ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን የማዳረስ ዕድል ይኖረዋል፡፡የኅብረተሰብ ጤና ስፔሻሊስቱ ዶክተር መኮንን አይችሉህም በቅርብ በኢትዮጵያ እየታዩ የመጡ የኮሮና ቫይረስ ውጤቶች በሽታው በፍጥነት እየተስፋፋ እንደሆነ የሚያሳዩ፣ ወረርሽኙም በማኅበረሰቡ ውስጥ መግባቱን የሚያመላክቱ መሆናቸውን አስገንዝበዋል፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ወረርሽኙ በፍጥነት እየተሠራጨ ያለና በሌሎች አገሮች የሚታዬው ጉዳት ወደዚህም ሊመጣ እንደሚችል አመላካች መሆኑን አስረድተዋል፡፡የአማራ ክልል በሰፊ ኪሎ ሜትር ከሱዳን ጋር የሚዋሰን መሆኑ ስጋቱ ከፍ ያለ መሆኑን በማንሳትም በድንበር አካባቢ የሚገባውና የሚወጣው ሰው ሕጋዊ አለመሆን ቁጥጥሩን አዳገች እንዳያደርገው ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ ነው ያስረዱት፡፡ ‘‘በሕገ ወጥ መንገድ ከሚገቡት ሰዎች መካከል አንደኛው ቢያዝ አብረው የሚጓዙትን በቀላሉ በቫይረሱ ያስይዛል፤ እነዚህ ወደ ማኅበረሰቡ ሲቀላቀሉ ደግሞ በፍጥነት ያሠራጩታል’’ ነው ያሉት ዶክተር መኮንን፡፡ ይህ ደግሞ እንደ ድርና ማግ የተሳሰረውን ማኅበረሰብ ለይቶ ለማወቅና በሽታውን ለመቆጣጠር አዳጋች እንዳያደርገው ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ ይህን አደገኛ ስርጭት ለመመከት ከሱዳን በኩል የሚገቡትን ሰዎች መለዬትና መቆጣጠር ተቀዳሚው ሥራ መሆን እንዳለበት ዶክተር መኮንን መክረዋል፡፡ በአካባቢው ከቀበሌው ጀምሮ እስከ ፌደራል ድረስ በከፍተኛ ቅንጅት መሥራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡ ቁጥጥሩም በታወቁ የመግቢያ በሮች ላይ ብቻ ሳይሆን በሁሉም አካባቢዎች መሆን እንዳለበትና ለዚህም ማኅበረሰቡ በኃላፊነት ስሜት ተባባሪ መሆን እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ አደባባይ ሙሉጌታ የዞኑ ሦስት ወረዳዎች 17 ቀበሌዎችና አንድ ከተማ አስተዳደር ከሱዳን ጋር እንደሚዋሰን ገልጸዋል፡፡ የአካባቢውን ሚሊሻዎች ስልጠና ሰጥተው በማሰማራት በድንበሩ አካባቢ ቁጥጥር ለማድረግ እየሞከሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ በዞኑ 741 ሰዎች በለይቶ ማቆያ ውስጥ እንደሚገኙ የገለጹት አቶ አደባባይ ለ494 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ የዛሬን ሳይጨምር 54 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶበቸዋልም ብለዋል፡፡ በሱዳን አዋሳኝ 19 በሮች እንዳሉ በመግለጽም ቢያንስ በዘጠኙ ለይቶ ማቆያ እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል፡፡ ዞኑ የመመርመሪያ እና የታማሚዎች ለይቶ ማከሚያ እንደሚያስፈልገው ጥያቄ ቀርቦ የክልሉ መንግሥትም ለጉዳዩ ትኩረት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወሳል፡፡ ዋና አስተዳዳሪው በምግብ አቅርቦት፣ የውኃውን ችግሩን ለመፍታት በመሥራትና በሌሎችም የክልሉ መንግሥት እያደረገ ያለው ድጋፍ አበረታች መሆኑን አንስተዋል፡፡የፌደራል መንግሥት ግን ወደስፍራው እየሄደ ጉብኝት ቢያደርግም እስካሁን ድረስ ተጨባጭ ድጋፍ አለማድረጉን ተናግረዋል፡፡ በመመሪያው መሠረት በለይቶ ማቆያ በ20 ክፍሎች 80 ሰዎችን መያዝ እንደሚቻል ያነሱት አቶ አደባባይ አሁን ላይ ግን በ20 ክፍሎች ከ300 በላይ ሰዎች በጥግግት እንደሚኖሩ አስታውቀዋል፡፡ ከሱዳን የሚመጡ ኢትዮጵያውን በቀጥታ ከኢንቨስተሮች መጠለያ መቀላቀል መከላከሉን ከባድ እንዳደረገውም ገልጸዋል፡፡ ይህም ወደ ሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን በሽታውን ይዘው እንዲመለሱ እንዳያደርግም ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ አካባቢው ለአገር የሚያመጣውን አደጋ ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የፌዴራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ማቅረብ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡በአካባቢው ወደ ለይቶ ማቆያ የሚገቡት ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ዜጎች በመሆናቸው የጤና ሚኒስቴር በአካባቢው የለይቶ ማቆያ በግንባት፣ የሕክምና ግብዓትና ምግብ በማቅረብ ማገዝ እንዳለበትም ነው የጠየቁት፡፡ ከሱዳን መንግሥት ጋር በመነጋገር ከዚያ የሚመጡ ዜጎች እየተመረመሩ የሚመጡበትን፤ ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳን የሚመለሱትም እየተመረመሩ የሚሄዱበትን መንገድ ቢያመቻችም በሽታውን ለመቆጣጠር አጋዥ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡የፌዴራል መንግሥት ትናንት በሰጠው መግለጫ ደግሞ ምዕራብ ጎንደር ዞንን ጨምሮ በጠረፍ አካባቢዎች ወረርሽኙን ለመከላከል ለሚደረገው ሥራ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ ማስታወቁ አሳውቋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%88%b3%e1%8b%ad%e1%88%98%e1%88%a8%e1%88%98%e1%88%a9-%e1%8a%a8%e1%88%b1%e1%8b%b3%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8c%88%e1%89%a1-%e1%8b%9c%e1%8c%8e%e1%89%bd-%e1%88%98%e1%8b%b3%e1%88%a8%e1%88%bb/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
ce37c84d78b0fa001acbc0a8d8c32f0f
3fc221bc73d062ded1bc5873e0fa77a5
የጆሜትሪክ ድርድር
የጂኦሜትሪክ ድርድር የምንለው የቁጥሮች ድርድር (ሰልፍ) ሲሆን እኒህ የተሰለፉ ቁጥሮች የኋለኛው የከፊተኛው ቋሚ ብዜት ውጤት ሲሆን ነው። ይህ ቋሚ ቁጥር የጋራ ውድር በመባል ይታወዋል። ለምሳሌ ይህን ድርድር እንመልከት 2, 6, 18, 54, ...፣ እያንዳንዱ ተከታይ ቁጥር የፊተኛውን ቁጥር በጋራ ውድሩ (3) ስናበዛ እናገኛለን፣ ስለዚህም የጅኦሜትሪክ ድርድር ይሰኛል። በተመሳሳይ ሁኔታ 10, 5, 2.5, 1.25,... የጂኦሜትሪክ ድርድር ነው ምክንያቱም የጋራ ውድሩ 1/2 ነውና! የጆሜትሪክ ድርድር ቁጥሮችን ስንደምር የምናገኘው የሂሳብ ስርዓት ጆሜትሪክ ዝርዝር ይባላል። ልዩነቱን ለማስተዋል ያክል፦ የጆሜትሪክ ድርድር አጠቃላይ ቅርጽ ይህን ይመስላል፦ የጆሜትሪክ ዝርዝር ደግሞ ይህን ይመስላል፦ እዚህ ላይ የጋራ ውድሩ r ≠ 0 ሲሆን a ደግሞ ማጉያ መነሻ ይባላል ምክንያቱም የድርድሩ የመጀመሪያ ቁጥር ነውና! የጋራ ውድሩና ማጉያ መነሻው የታወቀ ማንኛውም የጆሜትሪክ ድርድር አጠቃላይ n-ኛ ቁጥር እንዲህ ሲደረግ በትክክል ይተነበያል እኒህ አይነት ድርድሮች ሌላም ሂሳባዊ ቀመር አላቸው፣ ይኽውም በአጣቃሽ ዝምድና ሲጻፍ ለእያንዳንዱ ኢንቲጀር ኤሌክትሪካል ኢንጂኔሪንግ ሥነ ቁጥር ካልኩለስ
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
91d5075b8077ec9089007f4e821d83bd
77aab0cf038727e6a72e7b4df51302b5
ዕድሜ ከስፖርቱ ያላገለላቸው ብስክሌተኞች
በአገሪቱ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ በስፋት ከሚዘወተሩ ስፖርቶች እግር ኳስ፣ አትሌቲክስ፣ ቦክስ፣ ቦሊቮልና ብስክሌት የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ። ከእነዚህ አንዳንዶቹ ቀደም ባሉት ዓመታት ከአገር ውስጥም አልፎ የኦሎምፒክ ስፖርቶች ተብለው የሚወሰዱበት ወቅት እንደነበር ይታመናል። ከእነዚህ ውስጥ ቦክስና ብስክሌት በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ይሁንና ስፖርት ከመዝናኛነት አልፎ አዋጪ የቢዝነስ ማዕከል በሆነበት በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ ብዙዎቹ ስፖርቶች በ‹‹ነበር›› ታሪክ ብቻ ይገኛሉ፡፡ ቤን ጀማነህ የብስክሌት ስፖርትን የጀመሩት የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያሉ ነበር፡፡ በ1990 ዓ.ም አዲስ አበባ ላይ በተደረገው የ‹‹ማውንቴን›› ብስክሌት ውድድር ላይ ሦስተኛ ደረጃ በመያዝ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የብስክሌት ፍቅራቸው እያደገ መጣ፡፡ በ1997 ዓ.ም በአገሪቷ በነበረው የፖለቲካ ቀውስ ምክንያት ከአገራቸው ተሰድደው ከዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ ላይ ብስክሌት ስፖርት የሚያዘወትሩ ጥቂት ልጆችን በመሰብሰብ ዛሬ ላይ ከ50 በላይ አባላት ያሉትን ቡድን መመስረት ችለዋል፡፡ ማውንቴን ባይክ ( ሮድ ባይክ ኢን ኢትዮጵያ) የሚል ስያሜ ያለው ቡድን በማቋቋም አገር ቤት ካሉት ነባር ስፖርተኞች በተጨማሪ የውጭ አገር ዜጎችን በማሳተፍ ዘወትር እሁድ ከአዲስ አበባ ከተማ ተነስተው ብዙ ኪሎሜትሮችን በማቋረጥ ከውድ እስከ መካከለኛ ወጭ የተደረገባቸውን ብስክሌት በመያዝ ወደ ተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ይጓዛሉ፡፡ እስካሁን በተደረጉት የብስክሌት ስፖርት እንቅስቃሴዎችም ሱሉልታ፣ ሰንዳፋ፣ ሆለታ፣ ደብረብርሀን፣ ወልቂጤ፣ አገና፣ ቡታጅራና የመሳሰሉት አካባቢዎች የስፖርተኞቹ መዳረሻዎች ሆነዋል፡፡ ይህን የሚያደርጉት እድሜያቸው ከ30ዎቹ እስከ 60ዎቹ የሚጠጉ የቤን ጓደኞች ናቸው፡፡ ስፖርቱ እንዳይረሳ ትልቅ ንቅናቄ መፍጠርና ጤንነትን መጠበቅ የስብስቡ ዓላማ ቢሆንም፤ ጎን ለጎን ትውልዱ ራሱን በስፖርት እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲያሳልፍ ማስቻልም ሌላኛው ዓላማ ነበረ፡፡ ስፖርቱ እንዲያድግ ካላቸው ፍቅር የተነሳ ከቡድኑ ጋር ሆነው ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በብስክሌት ለመጓዝ ተሳትፎ የሚያደርጉትን ስፖርተኞች በነጻ እንደሚያሳትፉና በየመንገዱ ያሉት ወጣቶችም እድሜ ከስፖርቱ ያላገለላቸውን በማየት እንዲሳቡ ለማድረግ አገዥ እንቅስቃሴ መሆኑን ነው ቤን የሚናገሩት፡፡ ቆየት ባሉት ዓመታት ኢትዮጵያ የብስክሌት ስፖርት ወርቃማ ዘመኖችን ማሳለፏን የሚነገሩት ቤን፤ አሁን ላይ ስፖርቱ መዳከሙንና በተለይም መንግሥት የቀደሙ ባለሙያዎችን ሰብስቦ ቢያማክርና ቀደምት ስመ ጥር ስፖርተኞች ልምዳቸውን ለአሁኑ ትውልድ ማስተላለፍ ቢችሉ ስፖርቱ ዳግም ሊያንሰራራ እንደሚችል ይጠቁማሉ፡፡ የብስክሌት መንገድ አሰራርን ጨምሮ ከውጭ የሚመጡ ብስክሌቶች ጥራት መጓደልን አካቶ ስፖርቱ በጥልቀት መዳሰስ እንደሚገባው በስደት በውጭ አገር በቆዩባቸው ወቅቶች ያስተዋሉትን በማስታወስ ተናግረዋል፡፡ ቤን፤ ‹‹የድሮ ትውልድ ከልጅነቱ ጀምሮ በስፖርቱ ንቃት ውስጥ ያለፈው ነው፡፡ በየቦታው ሩጫ፤ በየጫካውም የካራቴ ስፖርት በብዛት ይዘወተር ነበር፡፡ ይህ አሁን ላይ ያለው በውስን ደረጃ ላይ ነው::›› በማለትም አሁናዊውን የብስክሌት ስፖርት ገጽታ ይጠቁማሉ፡፡ የሩጫና የብስክሌት ስፖርት በልምምድ ረገድ ብዙ የሚራራቁ አይደለም በማለት፤ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ለሁለቱም ስፖርቶች የሚሆን አቋም እንዳላቸውና እንደ አትሌቲክሱ ብስክሌት ስፖርቱም ቢበረታታ የሚገኘው ውጤት ቀላል እንዳልሆነ ያብራራሉ፡፡ እንደ እርሳቸው ገለፃ፤ ሌሎች አገራት በተለይም እንደ አውሮፓና አሜሪካ ያሉት ለስፖርቱ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው ስለሚንቀሳቀሱ በኦሎምፒክ መድረክም ሆነ ሌሎች ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በምሳሌነታቸው ብቻ ሳይሆን በውጤትም መታጀብ ችለዋል፡፡ በመሆኑም ከውጭ የሚገቡ የአገር አቋራጭ ብስክሌቶች ላይ ቀረጥ ቅናሽ አስተያየት ቢደረግ፤ የቀድሞ ስፖርተኞችና የጤና ቡድኖችን ያሳተፈ ተደጋጋሚ ውድድሮች በሚመለከተው ፌዴሬሽን በኩል ቢካሄድ፣ ለስፖርቱ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከት ይቻላል፡፡ ነገር ግን ወደ ፌዴሬሽኑ ለመቅረብ ቢሞክሩም መንገዶች ጠባብ ሆነዋል፡፡ ተቀራርቦ መስራት ስፖርቱን ለማሳደግ ትልቅ ሚና እንዳለው በመገንዘብ መንግሥት በአብሮነት ቢሰራ ልምድን ጨምሮ በብዙ መልኩ መተጋገዝም ይቻላል፡፡ የረጅም ጊዜ ልምድን በመጠቀም ለአገሪቷ ብስክሌት ስፖርት እድገት ሙያዊ አበርክቶ እንዲኖር ወደ ፊት ውድድሮችን በማዘጋጀት ተተኪውን ወጣት ትውልድ ለማሳተፍ ጥረቶች ይደረጋሉም ብለዋል፡፡ ስፖርቱ በአንጻራዊነት ይሻል የነበረበትን ዘመን ዳግም ለማደስ ከቡድን አጋሮቹ ጋር በመሆን እንደሚሰሩና የታዳጊ ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ ከውጭ አገር ስፖርተኞች ጋር እየተነጋገሩ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የእዚህ ቡድን አባላት ቢያንስ ከ20 ዓመት በላይ በስፖርቱ የቆዩ ስፖርተኞች መሆናቸውንና ትልልቅ ሰዎች ስፖርቱን ቢያዘወትሩት ከጤና አኳያ በርካታ ጥቅሞችን ማግኘት እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡ እድሜያቸው 50ዎቹ ውስጥ የሚገኘው አቶ ተስፋሚካኤል ገረመው ሌላኛው የቀድሞ ብስክሌተኛ ሲሆኑ፤ በአሁኑ ወቅት ከቡድን አጋሮቹ ጋር በመሆን እድሜ ሳይበግራቸው ረጅም ርቀትን በብስክሌት በመጓዝ ላይ ከሚገኙት ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ስፖርቱን በ1970 ዓ.ም እንደተቀላቀሉት የሚናገሩት አቶ ተስፋሚካኤል፤ እስከ 1982 ዓ.ም ድረስ በብስክሌት ስፖርት ከታዳጊዎች እስከ ዋናው ብሄራዊ ቡድን ውስጥ በመሳተፍ የሻምፒዮንነት ድልን እስከመቀዳጀት የደረሱና ድንቅ ብቃትን ማሳየት የቻሉ ናቸው፡፡ ምንም እንኳን በግጭት ምክንያት ውድድሩ ሳይካፈሉ ይቅር እንጂ በ1976 ዓ.ም ለሎሳንጀለስ ኦሊምፒክ በዝግጅት ላይ የነበረውን የወርቃማ ትውልድ ዘመን አባልም ነበሩ፡፡ በውቀቱ ስፖርቱ ከደጋፊዎች ጀምሮ በጥሩ ቁመና ላይ እንደነበርና ከጊዜ በኋላ ግን እየመነመነ መምጣቱን አቶ ተስፋሚካኤል ይናገራሉ። ምንም እንኳን ብስክሌት ከአትሌቲክስ ጀምሮ የኢትዮጵያን ስም በአፍሪካ ሻምፒዮናና በኦሊምፒክ መድረክ ያስጠራ ቢሆንም ዛሬ ላይ ትኩረት በማጣቱ ስፖርት ክለቦችን እስከማፍረስ መደረሱንና ይህም የስፖርቱን መጻኢ እድል አዘቅት ውስጥ ሊከተው እንደሚችል ያሳስባሉ።የትኛውም ስፖርት በትውልድ ቅብብሎሽ ላይ የተመሰረተ መሆን ይገባዋል የሚሉት አቶ ተስፋሚካኤል፤ የእርሳቸው አጋሮች እድሜ ሳይገድባቸው እያደረጉት ያለውን እንቅስቃሴ ትውልዱ በማስተዋል እንዲቀበለውና በተራው አገር በዚህ የስፖርት ዘርፍ እንድትጠቀም ማድረግ ተገቢ እንደሆነ ይመክራሉ፡፡ ስፖርቱን ለማስፋፋት ዓለም አቀፍ ይዘት ያላቸውን ውድድሮች ማዘጋጀት ከፌዴሬሽኑ የሚጠበቅ ኃላፊነት መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ ማንም ሰው ለራሱ የጤንነት ጥቅም ሲል ስፖርትን እንደሚያዘወትረው ሁሉ አቶ ተስፋሚካኤልና መሰል ጓደኞቻቸውም እርጅና ከስፖርቱ ሳይገድባቸው በየሳምንቱ ረጅም ኪሎሜትሮችን የመጓዛቸው ምክንያትም ለዚሁ መሆኑን ይጠቅሳሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስፖርቱ እንዲበረታታና በህብረተሰቡ ዘንድ ስርጸት ለመፍጠር ታስቦ እንደሆነ ያብራራሉ፡፡ ኢትዮጵያ ኦሊምፒክን ጨምሮ በተለያዩ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ከአትሌቲክስ ቀጥሎ ከምትወከልባቸው ስፖርቶች ብስክሌት ይጠቀሳል፡፡ ይሁንና ስፖርቱ በፋይናንስ በተለይም በመወዳደሪያ ብስክሌቶች እጥረት ምክንያት ህልውናው ፈተና ውስጥ መግባቱ ውጤቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑ እንደተጠበቀ፣ በዲፕሎማሲው ረገድ የበኩሉን ድርሻ የሚወጣ ነው፡፡አዲስ ዘመን  ሐምሌ 5/2011አዲሱ ገረመው
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=13954
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c680177559c923d0e15485805207ea06
a645f5b41ab99844ba0c9285af6a4601
ዜጎች ነጻ የትምህርት እድል በሚል ያለበቂ መረጃና ፍቃድ ወደ ቻይና በመሄድ ለከፍተኛ እንግልት እየተዳረጉ ናቸው-ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ዜጎች ነጻ የትምህርት እድል በሚልያለበቂ መረጃና ፍቃድ ወደ ቻይና በመሄድ ለከፍተኛ እንግልት እየተዳረጉ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነቢያት ጌታቸው አስታወቁ፡፡ዜጎቹ በህገወጥ ደላሎች በኩል የሚነዛው የተሳሳተና የተጭበረበረ የነጻ የትምህርት ዕድል ቅስቀሳ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የህገወጥ አደንጻዥ ዕጽ በተለይም ጫት ዝውውር መረብ ሰለባ መሆኑን አስታውቀዋል።እስካሁን ከ47 በላይ ዜጎቻችን በቻይና ልዩ ልዩ ግዛቶች አደንዛዥ ዕጽ በማዘዋወር እና ጫት በማስመጣት፣ በግድያ ወንጀል፣ በስርቆትና ሳይበር ክራይም፣ ያለ መኖሪያ ፍቃድ ረዥም ጊዜ በመቆየት፣ ያለስራ ፍቃድ በመስራት ወንጀሎች የታሰሩ ሲሆን የተወሰኑት በተጠረጠሩት ወንጀል ተፈርዶባቸው የእርምት ጊዜያቸውን እየተከታተሉ እንዲሁም የተወሰኑት በተጠረጠሩበት ወንጀል በምርመራ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።ከነጻ የትምህርት ዕድል ጋር በተየያዘ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ ጫትን ጨምሮ አደንዛዥ ዕጽ በቻይና በህግ የተከለከለና የሞት ፍርድን ጨምሮ እስከ ዕድሜ ልክ እስራት የሚያስቀጣ መሆኑ በግንዛቤ እንዲያዝ በመግለጫው ተመልክቷል።በጉዳዮ ዙሪያ መንግስት ቤጂንግ በሚገኘው ኤምባሲና በአራቱ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች በኩል ከቻይና ምንግስት ጋር በመነጋገር ለችግሩ መፍትሄ ለማበጀት እየሰራ መሆኑንም አቶ ነቢያት ጠቁመዋል።በተያያዘ ጥር 22 ቀን 2011 ዓ.ም በጅቡቲ ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በምትገኘው ኦቦክ አስተዳደራዊ ክልል ጎዶሪያ በሚባል ስፍራ በደረሰ የጀልባ መገልበጥ አደጋ ወደ የመን ለመሸጋገር ሲሞክሩ የነበሩ 57 ኢትዮጵያውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ማለፉ ተገልጿል።መንግስት ለችግሩ ዘላቂ እልባት ለመስጠት እየሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ነቢያት በዚህ ሳምንት 1 ሺህ 40 ዜጎች ከሳኡዲ አረቢያ፣ 1415 ከፑንትላንድ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።(ምንጭ፡-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃልአቀባይ ጽ/ቤት)
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/30982/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
07e0e3127a1c72d1a59594be1ffd54a7
9ec8acb5e06ba0eed3170eac128a19bc
ምላስ
ምላስ በአፍ ወለል ላይ የሚገኝ ጡንቻማ አካል ሲሆን ምግብን በሚገባ ለማላመጥ እና ለመዋጥ ይረዳል። የላይኛው የምላስ ክፍል በጣዕም ህዋሳት የተሸፈነ በመሆኑ ጣዕምን ለመለያ ዋና አካል ነው። ሁለተኛው የምላስ (ልሳን) ጥቅም ለንግግር ነው። ምላስ እጅግ በጣም ስሜታዊ አካል ሲሆን በሳሊቫ (saliva - ምራቅ) የተሸፈነ ነው። ብዛት ያላቸው የደም ቧንቧዎች እና የነርቭ ጫፎች ይይዛል። እነዚህም በተፈለገበት አቅጣጫ እንዲንቀሳቀስ ይረዱታል። ሥነ አካል
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
9bb6c9e384d85fd1f635ad5c1c75e040
e1a20c3734082a7f9e4bf0b1c17346a0
እነ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በ111 የማይጠቅሙ ራዳሮች ግዥ ጉዳይ አዲስ ክስ ተመሰረተባቸው
  ለህዳር 30 የክስ መቃወሚያ እንዲያቀርቡ ፍ/ቤት አዟል   የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ከቻይና በተገዙና ጥቅም ላይ ሊውሉ በማይችሉ የአንድ መቶ አስራ አንድ ራዳሮች ግዥ ጉዳይ በቀድሞው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘውና ሌሎች 3 ግለሰቦች ላይ አዲስ ክስ መሰረተ፡፡ ትናንት በዋለው ችሎት፤ ተከሳሾቹ ህዳር 30 ቀን 2012 ከጠበቆቻቸው ጋር ተማክረው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡የመንግሥትን ስራ በማያመች አኳኋን በመምራት ከግዥ መመርያ ውጪ ጥራቱን ያልጠበቀ ራዳር ግዥ ለመፈፀም ከ214 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት በመንግሥት ላይ ጉዳት ከባድ ወንጀል ፈጽመዋል በሚል በሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው፣ በሌተና ኮሎኔል ፀጋዬ አንሙት፣ በኮሎኔል ሸጋው ሙሉጌታና በኮሎኔል መሀመድ ብርሃን ላይ አቃቤ ህግ ክስ መስርቷል፡፡የፌደራል ዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ እንደሚያመለክተው፤ ተከሳሾቹ የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በ2004 ዓ.ም ከኮርፖሬሽኑ የግዥ መመሪያ ውጪ፣ የአገር መከላከያ ሚኒስቴር የግዥ ፍላጎት ሳይጤቅ ያለጨረታ ከቻይና ኩባንያዎች የአንድ መቶ አስራ አንድ ራዳሮች ግዥ ፈጽመዋል፡፡ የተገዙት ራዳሮች በአገር መከላከያ ሰራዊት የመስክ ሙከራ ሲደረግባቸው እጅግ ኋላ ቀር የሆኑ፣ ወጣ ገባ ለሆኑ መልክአ ምድሮች የማያገለግሉ፣ ሰው እንስሳትና ሌሎች ግዑዝ ነገሮችን ለመለየት የማያስችሉ፣ ከቦታ ቦታ ለማንቀሳቀስ የሚያስቸግሩና በቀላሉ ለመጠቀም የሚያዳግቱ መሆናቸው መረጋገጡን የዐቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ ከ214 ሚ. ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው እነዚህ ራዳሮች እስከ አሁን ድረስ ያለ አገልግሎት በመጋዘን ውስጥ እንዲከማቹ መደረጋቸውን የጠቆመው ዐቃቤ ሕግ፤ ተከሳሾቹ በሕዝብና በመንግስት ላይ ጉዳት በማድረስና በከባድ የሙስና ወንጀሎች ክስ እንደተሰመረተባቸው አመልክቷል፡፡ ክሱ በጹሑፍ የደረሳቸውና በችሎት በንባብ የቀረበላቸው ተከሳሾቹ፤ የተከሰሱበት ወንጀል ከባድ በመሆኑ ጠበቃ ይዘው መከራከር እንደሚፈልጉ ለፍርድ ቤቱ መናገራቸውን ተከትሎ ፍ/ቤቱ  ጠበቆቻቸውን ይዘው እንዲቀርቡ ለትናንት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን፤ ትናንት በዋለው ችሎት ተከሳሾቹ ከጠበቆቻቸው ጋር ቀርበዋል፡፡ ፍ/ቤቱም ተከሳሾቹ ከጠበቆቻቸው ጋር ተማክረው የክስ መቃወሚያቸውን ይዘው እንዲቀርቡ ለህዳር 30 ቀን 2010 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ለጊዜው ያልተያዙት አራተኛው ተከሳሽ ኮሎኔል መሐመድ ብርሃን ካሉበት ተፈልገው እንዲቀርቡም ፍ/ቤቱ አዟል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=24578:%E1%8A%A5%E1%8A%90-%E1%88%9C%E1%8C%80%E1%88%AD-%E1%8C%80%E1%8A%90%E1%88%AB%E1%88%8D-%E1%8A%AD%E1%8A%95%E1%8D%88-%E1%8B%B3%E1%8A%98%E1%8B%8D-%E1%89%A0111-%E1%8B%A8%E1%88%9B%E1%8B%AD%E1%8C%A0%E1%89%85%E1%88%99-%E1%88%AB%E1%8B%B3%E1%88%AE%E1%89%BD-%E1%8C%8D%E1%8B%A5-%E1%8C%89%E1%8B%B3%E1%8B%AD-%E1%8A%A0%E1%8B%B2%E1%88%B5-%E1%8A%AD%E1%88%B5-%E1%89%B0%E1%88%98%E1%88%B0%E1%88%A8%E1%89%B0%E1%89%A3%E1%89%B8%E1%8B%8D&Itemid=180
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b6fea40ed901abeeef5a3be3dbd2acc0
24c00b2b5fae3c7d038353130531af57
መንግስት ጉዳት ለደረሰባቸው የኢንቨስትመንት ተቋማት ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ድጋፍ አደረገ
መንግስት ጉዳት ለደረሰባቸው ከ300 በላይ የኢንቨስትመንት ተቋማት ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ድጋፍ አደርጓል፡፡ባለፉት ጊዜያት በአገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች በተፈጠረው አለመረጋጋት ጉዳት ለደረሰባቸው ከ300 በላይ ለሚሆኑ የኢንቨስትመንት ተቋማት መንግስት ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ተካ ገ/ኢየሱስ ገልጸዋል፡፡ተቋማቱ ከውጭ የሚያስገቡ የካፒታል ዕቃዎች እና የማምረቻ መሳሪዎች ከቀረጥ ነፃ እንዲያስገቡም ፈቃድ መስጠቱን ተናግረዋል፡፡ለአንድ አመት የሚቆይ የግብር እፎይታ ጊዜ ማበረታቻ መደረጉንም አቶ ተካ አስታውቋል፡፡  ከዚሁ ባሻገር የኢትዮጵያ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ አገሪቱ ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ካፒታል ገቢ ማግኘቷንም አቶ ተካ ገ/ኢየሱስ ገልጸዋል፡፡
ቢዝነስ
https://waltainfo.com/am/23464/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
abbd453c07098a6f1def38755172dfd0
22dfd524a3c10a3245d91bd5d190afcc
ኳታር የተለያዩ ሠራተኞችን የሚመለከቱ ሕጎች በማርቀቅ እና በማሻሻል ላይ ትገኛለች። ከእነዚህ መካከል ለመጀመሪያ ጊዜ ያፀደቀችው የዝቅተኛ ደሞዝ ክፍያ ገደብ አንዱ ነው።
ኳታር ለሠራተኞቿ ዝቅተኛውን የደሞዝ ክፍያ ገደብ አስቀመጠች\nከ2022 የዓለም ዋንጫ ዝግጅት ጋር ተያይዞ በኳታር ታሪክ በቁጥሩ ከፍተኛ ነው የተባለ ሠራተኛ ዶሃ ውስጥ በአሁኑ ጊዜ ሥራ ላይ ይገኛል። ይህንን ተከትሎም ዓለም አቀፍ የሠራተኞች መብት ተከራካሪ ድርጅቶች የኳታር ሠራተኛ አያያዝ ላይ ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ድርጅት (አይኤልኦ) ኳታር ወርሃ ሕዳር ከማብቃቱ በፊት ባላት የሠራተኛ ሕግ ላይ ክለሳ ካላደረገች የከፋ ነገር ይከተላል ብሎ ካስጠነቀቀ በኋላ ነው ሃገሪቱ ማሻሻያ ያደረግችው። የዓለም አቀፉ የሠራተኞች ሕብረት ኮንፈደሬሽን ዋና ፀሓፊ የሆኑት ሻሮን ባሮው ለውጡ በኳታር ለዘመናዊ ባርነት ማክተም ምልክት ነው ሲሉ ተደምጠዋል። ኳታር ለረጅም ጊዜ 'ካፋላ' የተባለ ቀጣሪ ድርጅቶች ካልፈቀዱ በስተቀር ከውጭ ሃገር የሚመጡ ሠራተኞች ድርጅቱን ለቀው ወደሌላ ቀጣሪ ድርጅት ወይም ሃገሪቱን ለቀው መሄድ እንዳይችሉ የሚያደርግ አሠራር ስትከተል ቆይታለች። ኳታር ከታህሳስ 2016 ጀምሮ ካፋላ የተባለው አሰራር ተግባራዊ እንዳይሆን ማድረጓ ይታወሳል። በአዲሱ ማሻሻያ አብይ ለውጥ ያመጣሉ የተባሉ የሠራተኛ ሕግጋትን ያዘለ እንደሆነ ታውቋል። ከእነዚህም መካከል • ፆታ ሳይለይ ለሠራተኞች የሚከፈል ዝቅተኛ የደሞዝ መጠን ገደብ እንዲኖረው • ከወጭ ሃገር የሚመጡ ሠራተኞች ሃገሪቱን ለመልቀቅ የቀጣሪዎቻቸውን ፈቃድ መጠይቅ እንዳይሹ • መታወቂያ ካርዶች በቀጣሪ ድርጅቶች ሳይሆን በመንግሥት እንዲሰጥ እና መሰል ሕግጋትን ያዘለ ነው። የኮንፈደሬሽኑ ዋና ፀሓፊ ባሮው እንደሚሉት አሁንም ብዙ የሚቀሩ ጉዳዮች ቢኖሩም እርምጃው አውንታዊ የሚባል ነው። አዳዲሶች ማሻሻያዎች መቼ ሥራ ላይ መዋል እንደሚጀምሩ ግን አስካሁን የታወቀ ነገር የለም። ከ1.5 እስከ 2 ሚሊዮን የሚደርሱ እና በአብዛኛው ከእስያ እንደመጡ የሚነገርላቸው የጉልበት ሠራተኞች በኳታር የግንባታ ዘርፍ ተሰማርተው እንደሚገኙ ይገመታል። በ2013 የዓለም አቀፉ የሠራተኞች ሕብረት ኮንፈደሬሽን ያወጣው መረጃ እንደሚያሳየው 1200 ያህል ከውጭ ሃገራት የመጡ ሠራተኞች በ2022 ዓለም ዋንጫ ዝግጅት በሚካሄዱ ግንባታዎች ላይ ተሰማርተው ሳለ ሕይወታቸው አልፏል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
24d0f3416bedeb30fd68969c64040c7f
b6bd3610860c7f897a0878071b6371a8
በአሜሪካ ኔብራስካ ግዛት በእርሻ ሥራ ላይ ሳለ ሰብል መሰብሰቢያ መሣሪያ ውስጥ እግሩ የተቀረቀረበት አርሶ አደር በስለት የራሱን እግር ቆርጦታል።
በአሜሪካ በእርሻ መሣሪያ የተያዘው አርሶ አደር እግሩን ቆረጠ\nመሣሪያው አንደ መብሻ (ድሪል) የሚሽከረከር ነው። የ63 ዓመቱ አርሶ አደር ኩርት ካሴር ምርት ለመሰብሰብ የሚረዳውን ማሽን ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ እያዘዋወረ ነበር፤ ማሽኑ ልክ እንደ መብሻ (ድሪል) ዓይነት ሲሆን የሚሽከረከርም ነው። ግለሰቡ የግሉ በሆነው 607 ሔክታር መሬት ላይ ብቻውን እየሰራ ሳለ ነበር አደጋው ያጋጠመው። በአቅራቢያው ሰዎች ባለመኖራቸው የሚረዳው አላገኘም። ስልክ በመደወል የሰዎችን እርዳታ ለመጠየቅ ቢያስብም ተንቀሳቃሽ ስልኩን አጠገቡ ሊያገኘው አልቻለም። ማሽኑ እግሩን እየከረከረ የበለጠ ወደ ውስጥ እየዘለቀና ከፍ እያለ መጣ። በዚህ ጊዜ ደፋሩ ገበሬ የያዘውን ስለት ሳብ አድርጎ ከማሽኑ የተረፈውንና ከጉልበቱ በታች ያለው የራሱ እግር ላይ እርምጃ ወሰደ። መጥፎ አጋጣሚውን ሲያስታውስም "ራሴን ለማላቀቅ ጣርኩ፤ ነገር ግን አጥንቴ ተጣብቆ ቀረ" ሲል ለኦማሃ ወርልድ ሄራልድ ተናግሯል። • ቀብሩን አዘጋጅቶ ራሱን ያጠፋው አርሶ አደር "ምንም ምርጫ አልነበረኝም" የሚለው አርሶ አደሩ ከታችኛው የእግሩ ክፍል 7.6 ሴንቲ ሜትር (3 ኢንች) የሚሆነውን የራሱን እግር ቆርጦ ጥሎታል። ከዚህ ሁኔታ ከተላቀቀ በኋላ ነበር ስልኩን ወደ አስቀመጠበትና 100 ሜትር ወደ ሚርቀው ቦታ እየተንፏቀቀ ሄዶ ለልጁ የደወለለት። ከዚያም በሊንኮልን ከተማ በሚገኝ የህክምና ተቋም እርዳታ ሲደረግለት ቆይቷል፤ ከጉዳቱ ለማገገምም ሳምንታትን በሆስፒታል አሳልፏል። ግለሰቡ ለኤቢሲ ኒውስ በማሽኑ ላይ የተገጠመውን መከላከያ አውልቆት እንደነበር ተናግሯል። "ያንን ነገር ሳላስተካክለው በመቅረቴ በራሴ በጣም ነው የተበሳጨሁት" ብሏል በቁጭት።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
c1a4159814739cde88a818569166d6f2
c8b725879494aff6da19c9deae58686b
መርኸፐሬ
መርኸፐሬ በላይኛ ግብጽ በ2ኛው ጨለማ ዘመን (13ኛው ሥርወ መንግሥት) ምናልባት 1646 ዓክልበ. አካባቢ የገዛ ፈርዖን ነበረ። ዘመኑ በሂክሶስ ጦርነት ዘመን ውስጥ እንደ ነበር ይመስላል። ከመርካውሬ 7 ሶበክሆተፕ ቀጥሎ እነማን በጤቤስ እንደ ገዙ ግልጽ አይደለም፤ ብዙ ስሞች ከቶሪኖ ቀኖና እንደ ጠፉ ይመስላል። ከሥነ ቅርስ የተረጋገጡት ግን መርኸፐሬ እና ሰኸቀንሬ ብቻ ናቸው። የመርኸፐሬ ተከታይ «መርካሬ» ነበር ሲል ሊነብብ ይችላል፤ ለርሱ ግን ምንም ማስረጃ ገና አልተገኘም። እነዚህ ነገሥታት ለረጅም ጊዜ እንደ ገዙ አይታስብም። በዚህም ሰዓት በአቢዶስ ዙሪያ አዲሱ የአቢዶስ ሥርወ መንግሥት ነጻ እንደ ሆነ ይታስባል። የሚቀጠለው የጤቤስ ፈርዖን ሰኸምሬ ጀሁቲ የ16ኛው ሥርወ መንግሥት ጀማሪ ተብሏል። ከቶሪኖ ዝርዝር በቀር፣ የመኸፐሬ ስም በሥነ ቅርስ የታወቀው ከአንድ ጥንዚዛ ምልክትና አንድ ሚዛን ክብደት ብቻ ነው። የሁለተኛው ጨለማ ዘመን ፈርዖኖች
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
14b3e07cb717e098d8d3704e99873607
9d36efb059dc31e6ebb2a87c25ee78d3
‹‹ደስ ስላላችሁ ደስ ብሎኛል!›› አና ጎሜዝ-ለኢትዮጵያዊያን
 ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2011 ዓ.ም(አብመድ) የአና ጎሜዝና የኢትዮጵያ ትሥሥር ምንድን ነው?ኢትዮጵያ ለመብቷና ለነፃነቷ የሚያግዟትን አውሮፓውያን ወዳጆች አጥታ አታውቅም፤ በተለይም ፖርቱጋል ለኢትዮጵያ የክፉ ቀን ደራሽ መሆኗን የዓፄ ልብነ-ድንግልና የልጃቸው የዓፄ ገላውዴዎስ ታሪኮች ምሥክሮች ናቸው፡፡የፖርቹጋላዊያን እና የኢትዮጵያዊያን ታሪካዊ ትስስር ዘመናትን ተሻግሮ እስከ 21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ስር ይሰድ ዘንድ ደግሞ የኢትዮጵያውያንን የነፃነት ድምፆች ከፍ አድርገው በአውሮፓ መድረኮች ለዓመታት ያሰሙ የአውሮፓ ምክር ቤት አባል ተገኝተዋል፤ አና ጎሜዝ፡፡ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ‹‹ሀና ጎበዜ›› የሚል ሀገረኛ ቅፅል ስም የተሰጣቸው ፖርቹጋላዊቷ አና ጎሜዝ ለዘመናት ጥብቅና ወደ ቆሙላት ኢትዮጵያ ትናንት ገብተዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%b0%e1%88%b5-%e1%88%b5%e1%88%8b%e1%88%8b%e1%89%bd%e1%88%81-%e1%8b%b0%e1%88%b5-%e1%89%a5%e1%88%8e%e1%8a%9b%e1%88%8d-%e1%8a%a0%e1%8a%93-%e1%8c%8e%e1%88%9c/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
97292240e19b305e36872537751ffe5e
e64bd4dac7de97bf40a29b8dece0f924
አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአየርላንድ ፕሬዚዳንት አቀረቡ
አምባሳደር ሬድዋን የኢትዮጵያና አየርላንድን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል።የአየርላንዱ ፕሬዝዳንት ሚስተር ማይክል ሂግንስ በበኩላቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወዳጅነትና አጋርነት አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገሮች የሚመጡ ስደተኞችን በማስተናገድ እያከናወነች ያለችውን ተግባርም አድንቀዋል።ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት አገሪቷ እያስመዘገበች ያለችውን ፈጣን ዕድገት መረዳታቸውን መግለጻቸውን ያመለከተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው ።ኢትዮጵያና አየርላንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1994 ነበር ።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/29022/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
57be3dc88d4d836867ff1b0fba30906e
37523939761950a5e16572a3c1553b61
ዋልያዎቹ ለወሳኙ ፍልሚያ አቋማቸውን ዛሬ ይፈትሻሉ
እ.አ.አ በ2019 ለ5ኛ ጊዜ የሚካሄደው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ቻን) ዋንጫ በካሜሩን ይስተናገዳል፡፡ በየሁለት ዓመቱ በሚደረገው ውድድር ላይ ተሳታፊ ለመሆን አገራት ከወዲሁ የማጣሪያ ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ። የአፍሪካ እግር ኳስ ማህበር (ካፍ) ባወጣው መርሃ ግብር መሠረት በሚደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያና ሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ሁለቱ ቡድኖች ከሦስት ሳምንታት በፊት በመቐለ ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን፤ የመልሱን ጨዋታ ጥቅምት 8 ቀን 2012 ዓ.ም ኪጋሊ ላይ የሚያደርጉ ይሆናል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ በመቐለ ከተማ ትግራይ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ከሦስት ሳምንታት በፊት በሩዋንዳ 1ለ0 ሽንፈትን ማስተናገዳቸው ይታወቃል፡፡ ዋልያዎቹ የመቐለውን ሽንፈት ለማካካስ ለመልሱ ጨዋታ ከወዲሁ ዝግጅታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ። በኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ የሚመራው ቡድን ከመስከረም 26 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለ24 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ በአዳማ ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል። ኢንስትራክተር አብርሃም በቡድኑ ስብስብ አብዛኞቹ ተጫዋቾች ለኳታሩ የዓለም ዋንጫ ከሌሶቶ ጋር በነበራቸው የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ የተመረጡት መሆናቸው ለቡድኑ ቅንጅትም ጠቃሚ እንደሆነ ታምኖበታል። ብሔራዊ ቡድን ከአዳማው ዝግጅት በተጨማሪ ከዩጋንዳ ጋር በዛሬው ዕለት የአቋም መፈተሻ የወዳጅነት ጨዋታውን ያደርጋል። በባህር ዳር ስታዲየም የሚካሄደው ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የሥነ ልቦና ዝግጅት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተነግሯል። ኢንስተራከተር አብርሃም ከመቐለ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ በመልሱ ጨዋታ ሩዋንዳ ኪጋሊ ላይ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል ዝግጅት እንደሚያደርጉ ቃል መግባታቸው ይታወቃል፡፡ አሰልጣኙ ከሽንፈቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት በመልሱ ጨዋታ ውጤት ለመቀልበስ እንደሚሰሩ ነበር ያስተወቁት። «በሜዳችን በነበረን ጨዋታ ብዙም ብልጫ ሳይወሰድብን በጥቃቅን ስህተት ነው ግቡ የተቆጠረብን። ከዚህ ውጪ ግን አስፈሪ የሚባል ነገር አልገጠመንም። በመሆኑም በመልሱ ጨዋታ ከዚህ በተሻለ ተንቀሳቅሰን ውጤት ይዘን ለመምጣት የተቻለንን እናደርጋለን።›› ሲሉ ቡድናቸው በጨዋታ ድል ባይቀናውም በመልሱ ጨዋታ ውጤት ለመቀልበስ ዝግጅት እንደሚደረግ ነው ያመላከቱት። አሰልጣኙ የቡድን ስብስብ በመያዝ ከአዳማ ዝግጅት በኋላ በዛሬው ዕለት በባህር ዳር ስታዲየም ከዩጋንዳ ብሔራዊ ቡድን የሚያደርገውን የአቋም መለኪያ ከሳምንት በኋላ ለሚጠብቀው ፈተና የተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች እንደሆኑ ታውቋል። ዋልያዎቹ በመጪው እሁድ በሩዋንዳ የሚያደርጉት ጨዋታ የብሔራዊ ቡድኑን ወደ ቻን የሚያደርጉት ግስጋሴ ወሳኝ ምዕራፍ ይሆናል። ብሔራዊ ቡድኑ መቐለ ላይ 1 ለ0 ሽንፈት ማስተናገዱ፤ ዋልያዎቹ ኪጋሊ ላይ የሚደረገው ጨዋታን ከሁለትና ከዚያ በላይ በሆነ ውጤት ማሸነፍ እንዲጠበቅባቸው ግድ አድርጎታል። ዋልያዎቹ በመድረኩ ለመታየት ያላቸውን አነስተኛ እድል ለመጠቀም፤ በመቐለ የነበሩ ክፍተቶች አሻሽለው መቅረብ እንደሚኖርባቸው ከስፖርት አዋቂዎች በኩል እየተነገረ ይገኛል። ብሔራዊ ቡድኑ ላይ በተለይ ከሌሴቶ፣ ከጅቡቲ እንዲሁም ከሩዋንዳ ጋር በነበራቸው ጨዋታ ጥሩ የሚባል እንቅስቃሴ ቢያሳዩም ኳስን ከመረብ የማዋሃድ ውስንነቶች በተደጋጋሚ ተስተውሎባቸዋል። በሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የተሻሉ ነገሮች ቢታዩም ተጫዋቾቹ ያገኟቸው የጎል አጋጣሚዎች የመጠቀም ክህሎታቸው ደካማ መሆን ብሔራዊ ቡድኑን ዋጋ እያስከፈሉት እንደሚገኙ ለመታዘብ ተችሏል። በሩዋንዳ 1 ለ0 ሽንፈትን ባስተናገዱበት ወቅት የነበሩት ስህተቶች ቀጥለው መታየታቸው ቡድኑን ለትችት ዳርገውታል። ዋልያዎቹ በዛሬው እለት ከዩጋንዳ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ማድረጋቸው የተጠቀሱትንና መሰል ክፍተቶቻቸውን እንዲመለከቱ እድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል። ኢንስትራክተር አብርሃም ብሔራዊ ቡድኑ የመልሱን ጨዋታ በድል ለመወጣት ከአካላዊም በተጨማሪ ሥነ ልቦናዊ ዝግጅት የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበዋል። ብሔራዊ ቡድኑ ለጨዋታው ትኩረት በተሞላበት ሁኔታ ዝግጅት በማድረግ ውጤት ለመቀልበስ ወደ ኪጋሊ የሚያቀና ይሆናል። የሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን ለኪጋሊው የመልስ ጨዋታ በተመሳሳይ ዝግጅቱን እያደረገ ሲሆን፤ ቡድኑ የአሸናፊነት ሥነ ልቦናን በመላበስ ጨዋታውን በአሸናፊነት ለመፈጸም እየተሰናዳ መሆኑን ተሰምቷል። የሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን በመቐለ ማሸነፍን ተከትሎ፤ በመጪው እሁድ በሜዳው በሚኖረው ጨዋታ የበላይነት ወስዶ ወደ ቻን የሚያደርገውን ግስጋሴ እውን ሊያደርግ ይችላል እየተባለ ይገኛል። የሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን በመልሱ ጨዋታ ሁለቱ ነጥቦች ቡድኑ በሥነ ልቦና ተጠናክሮ እንዲገባና የአሸናፊነት መንፈስ የሚያላብሱት በመሆኑ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ለማሸነፍ ከፍተኛ ግምት ወስዷል። በኢንስትራክተር አብርሃም የሚመሩት ዋልያዎቹ አነስተኛ የአሸናፊነት ተሰጥቷቸው ወደ ሜዳ ይገባሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሩዋንዳ ጋር በቻን ዋንጫ በሁለት የተለያዩ ታሪካዊ አጋጣሚዎች ተገናኝተዋል። እ.አ.አ በ2014 በደቡብ አፍሪካ አዘጋጅነት ለሚካሄደው 3 ኛው የቻን ዋንጫ ማጣሪያ የመጀመሪያው አጋጣሚ ነው። ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመድረኩ ተሳታፊ ስትሆን፤ በማጣሪያው ሩዋንዳን በደርሶ መልስ አሸንፋ ነበር። ጨዋታው በኪጋሊ ከተማ የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያ ሩዋንዳን በመለያ ምት 5ለ6 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩዋንዳን በመጣል ነበር፡፡ የሁለቱ ሀገራት ሌላው ፍጥጫ እ.አ.አ በ2017 በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ውድድር በማጣሪያው ተገናኝተዋል። በዚህም ሩዋንዳ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን በድምር ውጤት 3 ለ 2 በመርታት ወደ ሞሮኮ ስታቀና፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከመድረኩ ውጪ የሆኑባቸው ሁለት የታሪክ አጋጣሚዎች እንደነበሩ ይታወሳል። የሁለቱ አገራት ሌላው ታሪካዊ ፍጥጫ በመጪው እሁድ ጥቅምት 8 ቀን 2012 ዓ.ም ኪጋሊ ላይ ትዕይንት ይሆናል። አዲስ ዘመን ጥቅምት 2/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=20674
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
87296bc32556928cd12ea58480313d7c
93c511adf3d0c8f2014e81182f37494a
የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩስያ፤ ወደ ቡድን 7 (G7) እንድትመለስ ቢፈልጉም ዩናይትድ ኪንግደም እና ካናዳ ተቃውመዋል።
ትራምፕ ሩስያ ወደ ቡድን 7 ትመለስ ቢሉም አባል አገራቱ ተቃውመዋል\nትራምፕ፤ በዚህ ወር ሊካሄድ እቅድ ተይዞለት የነበረውን የቡድን 7 ስብሰባ ለመስከረም አስተላልፈዋል። ባለፈው እሁድ በሰጡት መግለጫ የቡድን ሰባት አገራት ሩስያን ወደ ቡድኑ መልሰው እንዲቀላቅሉ ጠይቀዋል። ሩስያን ወደ ቡድኑ ለመመለስ እንዳቀዱም ለፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን በስልክ ነግረዋል። አሜሪካ በምታስተናግደው የዘንድሮ ስብሰባ፤ ካናዳ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ጃፓንና ዩኬ ይገኛሉ። ስለትብብር ይወያያሉ ተብሎም ይጠበቃል። ሆኖም ግን የካናዳና ዩኬ መሪዎች የሩስያን ወደ ቡድኑ መመለስ እንደማይቀበሉ እሁድ ተናግረዋል። ሩስያ ቀድሞ ቡድን ስምንት (G8) ተብሎ ከሚጠራው የአገራት ስብስብ የተባረረችው ክሬሚያን የግዛቷ አካል በማድረጓ ነበር። ከተባረረች ስድስት ዓመት ሆኗታል። • የፌስቡክ ሠራተኞች በመሥሪያ ቤታቸው ድርጊት ተበሳጩ • ዙም መሰብሰቢያ ብቻ ሳይሆን ከሥራ ማባረሪያም ሆኗል • ትራምፕ ተቃውሞው የማይበርድ ከሆነ ወታደር እንደሚያዘምቱ ዛቱ “ሩስያ ከጂ7 የተባረረችው ክሬሚያን ስለወረረች ነው። ዓለም አቀፍ ሕግጋት መጣስ በመቀጠሏ ነው ከቡድኑ ውጪ የተደረገችው። ተመልሳም አትገባም” ብለዋል የካናዳው ጠቅላይ ሚንስትር ጀስቲን ትሩዶ። የዩኬው ጠቅላይ ሚንስትር ቦሪስ ጆንሰን ቃል አቀባይ፤ ሩስያ ወደ ቡድኑ ትግባ የሚል ሀሳብ ቢቀርብ፤ ድምጽን በድምጽ በመሻር መብታቸው እንደሚቃወሙ አስታውቀዋል። “ሩስያ ነውጠኛና ሰላም የሚያውኩ ድርጊቶችን እስካላቆመች ወደ ቡድኑ እንድትመለስ አንደግፍም” ብለዋል። ከሦስት ዓመታት በፊት የቀድሞ የሩስያ ሰላይ በእንግሊዝ መገደሉን ተከትሎ፤ የዩናይትድ ኪንግደምና ሩስያ ግንኙነት ሻክሯል። ዩኬ እና ካናዳ ፑቲን የቡድን ሰባትን ስብሰባ በአሜሪካ መታደማቸውን አልተቃወሙም። ከዚህ በፊት የቡድኑ አባል ያልሆኑ አገራት ስብሰባ ተሳትፈው ያውቃሉ። የቡድኑ አባል አገራት ሩስያ እንድትመለስ አንፈልግም ቢሉም፤ ትራምፕ በተደጋጋሚ ለሩስያ ድጋፋቸውን አሳይተዋል። እአአ 2018 ላይ በተካሄደ የቡድን 7 ስብሰባ “ሩስያ ብትመለስ ጠቃሚ ትሆናለች” ብለው ነበር። ባለፈው እሁድ በሰጡት መግለጫም ይህንኑ አቋም መልሰው አስተጋብተዋል። “ቡድኑ ዓለም ላይ እየተከናወነ ያለውን ነገር አይወክልም” ሲሉም፤ ሩስያ፣ ደቡብ ኮርያ፣ አውስትራሊያ እና ሕንድ ወደ ቡድኑ ይቀላቀሉ ብለዋል። የደቡብ ኮርያ እንዲሁም የአውስትራሊያ መሪዎች አሜሪካ በሚካሄደው ስብሰባ ላይ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አስታውቀዋል። ባለፈው ሳምንት የጀርመኗ መራሔተ መንግሥት አንጌላ መርክል፤ በኮሮናቫይረስ ስጋት የቡድኑን ስብሰባ በአካል እንደማይሳተፉ አስታውቀዋል። የተሻለ ምጣኔ ሀብትን መሠረት አድርገው የተሰባሰቡት ሰባት አገራት፤ በየዓመቱ እየተገናኙ ስለ ዓለም አቀፍ አስተዳደር፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የደህንነትና የምጣኔ ሀብት ጉዳይ ይወያያሉ። አባላቱ መርሃችን የሚሉት፤ ነፃነት፣ የሰብዓዊ መብት መከበር፣ ዴሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ዘላቂነት ያለው እድገትን ነው።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
526dc9778162eb639401c733d4c34e60
bba87557e02d0baacf3e5c57d0729b22
ፓርቲዎቹ የፖለቲካ ምህዳርን ለማስፋት በሚረዱ አዋጆች ላይ በቅድሚያ ለመደራደር ተስማሙ
አገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች 12 የድርድር አጀንዳዎችን በቅደም ተከተል በማስቀመጥ በሰነድ መልክ አፅድቀውታል።ተቀዳሚ ረዳት አደራዳሪው አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ በአደራዳሪዎቹ በቀረቡት የድርድር አጀንዳዎች ቅደም ተከተል ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡ አጀንዳዎችን ቦታ በመለዋወጥ ብቻ መፅደቁን ገልጸዋል።በዚህ መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ 573/2000፣ የምርጫ ህግ አዋጅ 532/1999፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የስነ ምግባር አዋጅ 662/2002፣ የፀረ ሽብር ህግ፣ የብዙሃን መገናኛ አዋጅ፣ የበጎ አድራጎትና የማህበራት አዋጅ፣ የዴሞክራሲና የሰብአዊ መብት ተቋማት አደረጃጀትና አፈፃፀም በተመለከተ ከአንድ እስከ ሰባት በቅደምተከተል ድርድር ይደረግባቸዋል ብለዋል።አቶ ዋሲሁን እንዳሉት የፍትህ አካላት አደረጃጀት አዋጅና አፈፃፀም፣ ዜጎች በየትኛውም የአገሪቱ ክፍሎች የመዘዋወር የመኖር ንብረት የማፍራት መብትና የህግ ማዕቀፍ፣ የሊዝ አዋጅና የልማት ተፈናቃዮችን፣ የታክስ ስርዓት እና ብሔራዊ መግባባትን የተመለከቱ አጀንዳዎችን ከ8 እስከ 12 በማስቀመጥ በቅደም ተከተል ድርድር ይደረግባቸዋል።በውይይቱ “ምርጫ እየቀረበ ስለሆነ የምርጫ ህጎች ይቅደሙ” አይደለም “ብሔራዊ መግባባት መቅደም አለበት” የሚሉትን ጨምሮ በርካታ ሀሳቦች ተነስተዋል።ፓርቲዎቹ በተዘጋጀው የፅሑፍ አቀራረብና የጊዜ ሰሌዳ መርሀ ግብር ላይም ማሻሻያ በማድረግ አፅድቀውታል።ተቀዳሚ ረዳት አደራዳሪው እንዳሉት ሁሉም ፓርቲዎች በሚደራደሩባቸው በ12ቱም አጀንዳዎች ፅሑፍ አስቀድመው ለገዢው ፓርቲ የሚያቀርቡ ይሆናል።ገዢው ፓርቲም እንዲሻሻሉ በሚፈልጋቸው አጀንዳዎች ብቻ ለተደራዳሪ ፓርቲዎች እንዲሻሻሉ የሚፈልጋቸውን ነጥቦች በፅሑፍ ያቀርባል ብለዋል።ፓርቲዎች በማይደራደሩበት አጀንዳ ላይ ፅሑፍ የማቅረብና የመገኘት ግዴታ የለባቸውም በማለትም ፓርቲዎቹ የጋራ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።አደራዳሪዎቹ ከተደራዳሪ ፓርቲዎች የሚቀርቡ የድርድር አጀንዳዎች የተመለከቱ ፅሑፎች በአንድ ቀን ውስጥ በአደራዳሪዎች በኩል እንዲሰራጭ ያደርጋሉ። ፓርቲዎች ድርድሩን በ90 ቀናት ውስጥ ለማጠናቀቅና በሳምንት ሶስት ቀን ለመደራደርም ተስማምተዋል።ባፀደቁት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት አንድ የድርድር አጀንዳ ከአምስት ቀናት በላይ የማይወስድ ሲሆን  አጀንዳዎች በቅደም ተከተል ድርድር የሚደረግባቸው ይሆናል።በመጨረሻ ፓርቲዎቹ በዝግ ባካሄዱት አጭር ስብሰባ ለሚካሄደው ድርድር የሚያግዝ የሎጂስቲክ ኮሚቴ አቋቁመዋል- (ኢዜአ) ።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/29252/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
ab0832e1815d57e12e4f2bd0887b4c7f
0080c1dbfbbe5c5fba1acda131d93fa0
ግዙፍ የአሜሪካና የቻይና ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ነው
ግዙፍ የሆኑ የአሜሪካና የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ በመምጣት ላይ መሆናቸውን፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ፡፡የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የኢንቨስትመንት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ተካ ገብረኢየሱስ የካቲት 29 ቀን 2009 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ፣ ጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ የተሰኘ ግዙፍ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ 945 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስት ለማድረግ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ ጂያንግሱ ታዋቂ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት አምራች ኩባንያ መሆኑንና በኢትዮጵያ በአዳማ ከተማ ግዙፍ የሱፍ ጨርቅ ማምረቻ ለማቋቋም የሚያስችለውን ስምምነት የኩባንያው ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ በመምጣት መፈረማቸውን አቶ ተካ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ኩባንያው የሱፍ ጨርቆችን እያመረተ ለዓለም አቀፍ ገበያ እንደሚያቀርብ ገልጸዋል፡፡ ጂያንግሱ እ.ኤ.አ. በ1986 ጂያንግይን ግዛት ውስጥ የተመሠረተ ግዙፍ የኢንቨስትመንት ቡድን ነው፡፡ በጨርቃ ጨርቅና በአልባሳት ምርት፣ በኢነርጂ፣ በሪል ስቴት፣ በመድኃኒትና በኬሚካል፣ እንዲሁም በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልማት የተሰማራ እንደሆነ የኩባንያው ድረ ገጽ ያስረዳል፡፡በተመሳሳይ ሒውማን ዌል የተባለ የቻይና የመድኃኒት አምራች ኩባንያ በደብረ ብርሃን አካባቢ የመድኃኒት ፋብሪካ ግንባታ መጀመሩን አቶ ተካ አስረድተዋል፡፡ ሒውማን ዌል ቦሌ ለሚ ሁለት ኢንዱስትሪ ፓርክ እንዲገባ ቢጠየቅም ፋብሪካውን በፍጥነት መገንባት በመፈለጉ በደብረ ብርሃን ከተማ አካባቢ ለመገንባት መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ የቦሌ ለሚ ሁለት ኢንዱስትሪ ዞን ለመድኃኒት አምራቾች ተለይቶ በቂሊንጦ አካባቢ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡በተያያዘ ዜና ሃኒዌል የተሰኘ ግዙፍ የአሜሪካ የኮሙዩኒኬሽን ኩባንያ ኢትዮጵያ ውስጥ የኤሌክትሪክ ገመዶች ማምረቻ ለማቋቋም ፍላጎት እንዳለው መግለጹ ተጠቁሟል፡፡ የሃኒዌል ዋና ሥራ አስፈጻሚ በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ለጉብኝት መጥተው ኩባንያቸው በኤሌክትሪክ ገመዶች ማምረቻ ኢንቨስት ለማድረግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው መግለጻቸውን አቶ ተካ ተናግረዋል፡፡ሃኒዌል ኢንተርናሽናል የመገናኛ መሣሪያዎች፣ የኢንጂነሪንግ አገልግሎቶች የሚሰጥና የአውሮፕላን የተለያዩ ክፍሎች አምራች ኩባንያ ነው፡፡ የኩባንያው ዓመታዊ ገቢ ከ38 ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው፡፡በዘንድሮ በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከሐምሌ 2008 ዓ.ም. እስከ ታኅሳስ 2009 ዓ.ም. 1.2 ቢሊዮን ዶላር ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነፃፀር የ35 በመቶ ብልጫ ማሳየቱን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡አቶ ተካ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ኮሚሽኑ አሠራሩን በማዘመን የአንድ መስኮት አገልግሎት መስጠቱን፣ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ላይ ያነጣጠረ የኢንቨስትመንት ማስተዋወቅ ሥራ ማካሄዱን ገልጸዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና በተለያዩ አገሮች የሚገኙ ኤምባሲዎች በኩል ሰፊ የማስተዋወቅ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጭምር በዓለም አቀፍ የንግድና ኢንቨስትመንት ዓውደ ርዕዮች ላይ በመገኘት የታላላቅ ኩባንያ ኃላፊዎችን እንደሚያነጋግሩና ጥረቱም ውጤት እያስገኘ እንደሆነ አክለዋል፡፡ትልልቅ ኢንቨስትመንቶችን እየተከታተሉ የሚገጥማቸውን ችግር የሚፈቱ አንዳንድ ባለሙያዎችን ኮሚሽኑ መመደቡን አቶ ተካ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ይህ አዲስ የጀመርነው ውጤታማ አሠራር ነው፡፡ ለእያንዳንዱ ኩባንያ አንድ ባለሙያ መድበናል፡፡ በየሁለት ሳምንቱ እኔ ወይም ኮሚሽነሩ ባሉበት ሪፖርት ያቀርባል፡፡ የትኛው ኩባንያ ምን ዓይነት ችግር እንደገጠመውና እንዴት እንደተፈታ፣ ፕሮጀክቱ ምን እንደደረሰ ሪፖርት የሚደረግበት አሠራር ዘርግተናል፡፡ በቅርብ ነው የጀመርነው፡፡ ግን ጥሩ ውጤት እያገኘንበት ነው፤›› ብለዋል፡፡የኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባት መጀመሩና መንግሥት አገሪቱን ወደ ማምረቻ ማዕከልነት ለመለወጥ ያሳየው ቁርጠኝነት የውጭ ኢንቨስትመንት ለመሳብ እንዳስቻለ ገልጸዋል፡፡ኢትዮጵያ በዓለም ባንክ የንግድ ሥራ ተስማሚነት መመዘኛ ሪፖርት ጥሩ ውጤት አስመዝግባ አታውቅም፡፡ በቅርቡ የወጣው የዓለም ባንክ ሪፖርት ኢትዮጵያን ከ190 አገሮች 159ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፡፡ አቶ ተካ ኢትዮጵያ ጥሩ ውጤት እንዳላስመዘገበች አምነው፣ ደረጃዋን ከ100 በታች ለማውረድ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡በአብዛኛው ችግሩ ያለው በሎጂስቲክስ ዘርፍ መሆኑን ገልጸው ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን፣ ከኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅትና ከሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር አሠራሮችን በማሻሻል ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ከቪዛ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ከኢማግሬሽንና ዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ ጋር በቅርበት በመሥራት፣ ለውጭ ባለሀብቶች ከሦስት እስከ አምስት ዓመት የሚቆይ ‹‹መልቲፕል ቪዛ›› መስጠት መጀመሩን አስረድተዋል፡፡ባለሀብቶች መሬትና መሠረተ ልማቶች ለማሟላት እንዳይጉላሉና በአጭር ጊዜ ወደ ምርት እንዲገቡ በማሰብ መንግሥት በአዳማ፣ መቐለ፣ ኮምቦልቻ፣ ጂማና ድሬዳዋ ከተሞች የኢንዱስትሪ ፓርኮች በመገንባት ላይ መሆኑን የገለጹት አቶ ተካ፣ የአራት አግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዲስትሪ ፓርኮች ግንባታ በአራት ክልሎች መጀመሩን አስታውሰዋል፡፡ በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከታሰበው በላይ የባለሀብቶች ፍላጎት ጨምሮ በመገኘቱ ሁለተኛ ምዕራፍ ለመገንባት መታሰቡን ተናግረዋል፡፡ ‹‹መጀመሪያ ከታቀደው በላይ 11 ሼዶች ገንብተናል፡፡ አሁንም በተለይ ከውጭ ባለሀብቶች በቀረበው ጥያቄ ሁለተኛ ምዕራፍ ለመገንባት ታቅዷል፤›› ብለዋል፡፡በቅርቡ በአገሪቱ ተፈጥሮ በነበረው ሁከት ንብረት የወደመባቸው ባለሀብቶች የማምረቻ መሣሪያዎች ከቀረጥ ነፃ አስገብተው ሥራቸውን እንዲቀጥሉ መደረጉን፣ ባለሀብቶቹ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንዲስተናገዱ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡ኮሚሽኑ ከኤምባሲዎቻቸው ጋር በቅርበት እንደሚሠራና ለአምባሳደሮቻቸው ጉብኝቶች ማመቻቸቱ ተገልጿል፡፡ በውጭ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎችና ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች አማካይነት የማረጋጋትና በአገሪቱ ስለተከሰተው ትክክለኛ ሁኔታ የግንዛቤ ማስጨበጫ መግለጫዎች መስጠታቸውን አቶ ተካ ተናግረዋል፡፡‹‹አንድ ሰሞን በተፈጠረው ሁኔታ ባለሀብቶች አልሸሹም፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ጠንካራና በጎረቤት አገሮች ሁሉ ሰላም የሚያስከብር መንግሥት ነው፡፡ የተፈጠረውን ሁኔታ መቆጣጠር እንደሚችል እናውቃለን እያሉ ሥራቸውን ቀጥለዋል፤›› ብለዋል፡፡ 
ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%8C%8D%E1%8B%99%E1%8D%8D-%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%88%9C%E1%88%AA%E1%8A%AB%E1%8A%93-%E1%8B%A8%E1%89%BB%E1%8B%AD%E1%8A%93-%E1%8A%A9%E1%89%A3%E1%8A%95%E1%8B%AB%E1%8B%8E%E1%89%BD-%E1%8B%88%E1%8B%B0-%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB-%E1%8A%A5%E1%8B%A8%E1%8C%88%E1%89%A1-%E1%8A%90%E1%8B%8D
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
5247936fb23640f30b05efff5ba336de
c77eabb92ee78761c4f1ba81613ff572
“ችግሮቻችንን በመቅረፍ ብልጽግናን ማምጣት እንችላለን” አቶ መሀመድ ረፊ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ተንታኝ
አዲስ አበባ:- በመደመር ትልቅ ሀሳብ የነበሩብንን ችግሮች በመቅረፍ መበልፀግ እንደሚቻል በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ተንታኝ ተናገሩ፡፡የውጭ ግንኙነት ባለሙያ የሆኑት አቶ መሐመድ ረፊ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ መደመር ከብልፅግና ጋር እራሱን አቆራኝቶ መምጣቱ ከዚህ በፊት ያላሟላናቸውንና በሀገር ቤት ውስጥ ይስተዋሉ የነበሩ የሙስና መንሰራፋት፣ የዴሞክራሲ እና የመልካም አስተዳደር እጦት እንዲሁም መሰል ችግሮቻችንን መቅረፍ ያስችለናል። ይህ የሚሆነውም ሀሳባችንን ከድህነት ይልቅ ብልፅግናን ማምጣት በሚለው ላይ ትኩረት ማድረግ ስንችል ብቻ ነው ይላሉ። በብልፅግና የሚመጣውን ሁለንተናዊና ዘላቂ እድገት ለማረጋገጥ በመንግስት ደረጃ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሆነ ያብራሩት አቶ መሃመድ፤ በዚህም ባለፉት ዓመታት በአገር አቀፍ ደረጃ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራበት የነበረው የውጭ ጉዳይ የፖሊሲ አንዱና ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ያለ ጉዳይ ነው ብለዋል። ይህ የፖሊሲ አቅጣጫ ድህነትን ብቻ ማዕከል አድርጎ የቆየ በመሆኑ በግብርናውም ሆነ በሌሎች የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ላይ ድህነት ቅነሳ እየተባለ ድህነትን ብቻ ማዕከል አድርጎ እንደቆየም ጠቅሰዋል፡፡ለዚህ መገለጫውም በውጭ ጉዳይ ፖሊሲው ላይ ይኸው የድህነት ቅነሳ ሲተገበር የቆየ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ፖሊሲው ካመጣቸው ድሎች ይልቅ ያስከተላቸው ክፍተቶችና ኪሳራዎች አመዝነዋል። በመሆኑም አሁን በአገሪቷ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የእይታ ለውጥ በማድረግ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲው ከድህነት ቅነሳ ይልቅ ብልፅግናን ማምጣት በሚል እና በመደመር እሳቤ ተቃኝቶ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል። መደመር ለህዝብ ክፍት ሆኖ እና በመፅሐፍ ደረጃ ተዘጋጅቶ ከመምጣቱ በፊት እንደ አንድ እርምጃ መጥቀስ የምንችለው የፖሊሲ ሰነድ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲው የመደመር እሳቤን የዋጀ እና ከፖሊሲዎች ሁሉ ቀድሞ ይህን የመደመር እሳቤ የራሱ ያደረገ የመጀመሪያው ፖሊሲ መሆኑን የገለፁት አቶ መሐመድ፤ ከዚህ በፊት ለበርካታ ዘመናት ፖለቲከኞችና ተፎካካሪ ፓርቲዎች የውጭ ጉዳይ ፖሊሲው እንዲቀየር እና እንዲሻሻል በተነሳሽነት ብዙ ሲሞግቱና ሲጠይቁ ነበር ብለዋል። ይሁን እንጂ የመጨረሻውን ሂደት አልፎ፤ በበርካታ ሀሳቦች የበለጠ ዳብሮ ወደ ስራ የተገባው በለውጥ ሂደቱ መሆኑን ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ጥር 4/2012ፍሬህይወት አወቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=25547
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f5c20314ac2229a648f9979e1f40ce1c
c23c70e454f33cea7fc4f4f92b7d0a2b
የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ በደማቅ ሁኔታ በሁሉም ክፍለከተሞች ተጀመረ
በመላ ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት 200 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ቀን በመትከል በአለም የክብር መዝገብ ላይ ለመስፈር ዘመቻው በማለዳው ተጀምሯል።በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጭነት በዛሬው እለት በአንድ ጀንበር 200 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ሲደርግ መቆየቱ የሚታወስ ነው።በዚህ መሰረት ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ ዜጎች 200 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ዘመቻቸውን ጀምረዋል።ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ ሁሉም ክልሎች አስፈላጊውን ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል።የዚህ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን በአዲስ አበባ የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ በኮልፌ ቀራኒዮ ፖርክ ውስጥ ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመሆን አስጀምረዋል።ህንድ በአለም አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር ወይንም በ12 ሰዓታት 66 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል በአለም የክብር መዝገብ ላይ በቀዳሚነት ሰፍራ ትገኛለች። 
ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/32592/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b370cceeeb36b6dc56ab2c176564def8
d270308784a3b33b4e96c3bcc797e0a0
የሩሲያ ወታደራዊ አውሮፕላን ወታደሮች እና ቁሳቁስ ጭኖ ካራካስ መግባቱ ተዘገበ
የሩሲያ ወታደራዊ አውሮፕላን ለቬኒዙዌላው ፕሬዝዳንት ኒሎላስ ማዱሮ ድጋፍ ወታደሮች እና ቁሳቁስ ጭኖ ካራካስ መግባቱ ተዘግቧል፡፡እንደ ሩሲያው ስፑትኒክ የዜና ወኪል ባሳለፍነው ቅዳሜ ሁለት የሩሲያ ወታደረዊ አውሮፕላኖች ቁሳዊና ወታደራዊ ድጋፍ ለኒኮላስ ማዱሮ መንግስት ለማድረግ ካራካስ መድረሳቸውን አስነብቧል፡፡የዜና ወኪሉ ዝርዝር መረጃ ባያስነብብም በመዲናዋ ካራካስ ከሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ በረራው ምንም ሚስጥራዊነት እንደሌለው እና ቀደም ሲል በሀገራቱ መካከል በጉዳዩ ላይ የጋራ መግባባት እንዳለ ለመጠቆም ሞክሯል፡፡የስፑትኒክ ዜና ወኪልን መረጃ ተከትሎ ጃቭዬር ማዮርካ የተባለ የቬኒዙዌላ ጋዜጠኛ ንብረትነታቸው የሩሲያ አየር  መንገድ የሆኑ አንቶኖቭ 124 ካርጎ ጫኝ እና አንድ መለስተኛ ጄት በካራካስ አየር ማረፊያ ቅዳሜ ዕለት ስለመታየታቸው በቲውተር ገፁ አስፍሮታል፡፡በጄኔራል ቫሲሊ የሚመራ  100 ወታደሮችና 35 ቶን የሚገመት ቁሳቁስ በስፍራው መድረሱን ዘግይቶም ቢሆን የቬኒዙዌላው ሳንቲያጎ ታይምስ አስነብቧል፡፡በተጨማሪም በተለያዩ ማህበራዊ ድረ ገጾች የአውሮፕላኖቹን ፎቶ እማኝ ያደረጉ መረጃዎች በስፋት ወጥተዋል፡፡የሩሲያን ሰንደቅ አላማ ያነገበ አውሮፕላን መታየቱንም ብዙዎች ተቀባብለውታል፡፡ የ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ጋዜጠኛ በቬኒዙዌላ ብሄራዊ ጥበቃ የታጀበ አውሮፕላን በአየር ማረፊያው ማየቱን አስነብቧል፡፡በሌላ በኩል የቬኒዙዌላ ባለስልጣናት ምንም አይነት መረጃ እንደሌላቸውና ካራካስ የሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ በወጡት ዘገባዎች ዙሪያ ምንም ለማለት እንዳልፈቀደ ታውቋል፡፡ቬኒዙዌላ በፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ እና ተቀናቀኛቸው ጃይን ጉዋይዶ መካከል በከረረው ፍጥጫ የጎዳና ላይ ነውጥ እያስተናገደች ትገኛለች፡፡ኣሜሪካ እና በርካታ የአውሮፓ ሀገራት ከተቀናቃኙ ጃይን ጉዋይዶ ጎራ ሲሰለፉ ቻይና እና ሩሲያ  ደግሞ ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን አይዞህ ባይ ናቸው፡፡ /ሲጂቲኤን/ 
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/33912/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
617bc270517cdf7dc3e152db4468ce99
999d21480e0e7215c77fa05cb52c06b1
ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም
ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን፣ አዲስ አበባ የዚህ ቤተ ክርስቲያን ጽላት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አገራችን ኢትዮጵያ በፋሺስት ኢጣልያ በተወረረች ጊዜ በስደት እንግሊዝ አገር ባዝ በተባለ ከተማ ሲኖሩ፣ ጥር ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በጊዜው በስደት ኢየሩሳሌም ለነበሩት ወደ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ (በኋላ አቡነ ባስልዮስ) አንድ ፅላትና ለአገልግሎት የሚበቁ አምስት መነኮሳትን ወደእንግሊዝ አገር እንዲልኩላቸው በአባ ሐና ጅማ በላኩት ደብዳቤ መሠረት ተልኮ በስደት የኖረ ፅላት ነበር።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
b548b992e84d5c7d409abe3f75aa25b6
b85cb50b1514dd666673e688fd81e1b6
አገር በቀሉ ኩባንያ የአሉሙኒየም ማዕድን ፍለጋ ሊጀምር ነው
አገር በቀሉ የአሉሙኒየም ኩባንያ በኢትዮጵያ የደቡብ አካባቢዎች በአሉሙኒየም ማዕድን ቁፋሮ ለማድረግ የሚያስችለውን የዳሰሳ ጥናት አጠናቆ የፍለጋ ሥራ ለመጀመር፣ የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴርን ምላሽ እየተጠባበቀ መሆኑ አስታወቀ፡፡የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሃይማኖት አባተ እንደገለጹት ኢንተር አፍሪካ ኤክስትሩዥን በሚል መጠሪያ የሚታወቀውና ከአምስት ዓመት በፊት ቃሊቲ አካባቢ ማምረቻውን ያቋቋመው ድርጅት፣ ወደ አሉሙኒየም ሥራ የገባው ምርቶቹን ከዱባይ በማስመጣት ነው፡፡ አሁን ሙሉ በሙሉ ምርቱን በአገር ውስጥ ማምረት መጀመሩን አቶ ሃይማኖት ይገልጻሉ፡፡ ለአሉሙኒየም ማምረቻ የሚያገለግሉ ጥሬ ዕቃዎችን (ስክራፖችን) ከአገር ውስጥ መሰብሰብ ቢቻልም፣ መቶ በመቶ የአሉሙኒየም ይዘቱን ለማስጠበቅ ሲባል ጥሬ ዕቃውን አሁንም ከውጪ ማስገባቱ እንዳልቆመ ተናግርዋል፡፡በቅርቡ ግን ከአንድ የቻይና ኩባንያ ጋር በመተባበር ደቡብ ክልል በሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ በተደረገው የዳሰሳ ጥናት የአሉሙኒየም ማዕድን መኖሩ በመረጋገጡ፣ ድርጅቱ የቅድመ ትግበራ ሰነዱን ለማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር አቅርቦ ምላሹን በመጠባበቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኩባንያው ባለቤት አቶ ብሩክ ኃይሌ በሙያቸው አርክቴክት እንደሆኑ የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፣ ጥራቱ የተረጋገጠለትንና ከውጪ ከሚመጣው አሉሙኒየም ጋር ሊወዳደር የሚችል ምርት በአገር ውስጥ እንዲመረት በነበራቸው ፍላጎት፣ በ45 ሚሊዮን ብር ድርጅቱን ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡ድርጅቱ በ40/60 የቤቶች ግንባታም ተሳታፊ እንደሆነ የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፣ ሰንጋ ተራና ቃሊቲ አካባቢ እየተገነቡ ያሉትን ቤቶች የበር፣ የመስኮትና የፓርትሽን ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/article/2744
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
cdaa182d995c06e6b71c107f66e23430
9845227e6d8398abb12a572d112f0256
ኦስሎ
ኦስሎ የኖርዌ ዋና ከተማ ነው። የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 876፣391 ሆኖ ይገመታል። ከተማው ላይ ተቀምጦ ይገኛል። በኖርዌ መዝገቦች መሠረት፣ ከተማው መጀመርያ አስሎ ተብሎ የተመሠረተ በ1041 ዓ.ም. ገደማ በንጉሥ ሃራልድ 3ኛ ነበር። ከ1291 ዓ.ም. የአገሩ ዋና ከተማ ሆኗል። ከ1616 ዓ.ም. እስከ 1917 ዓ.ም. ድረስ ስሙ ክርስቲያና ተባለ፤ ከዚያ በኋላ ግን ስሙ ወደ ኦስሎ ተመለሰ። ኖርዌይ ዋና ከተሞች የአውሮፓ ከተሞች
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
8d9bb339828f869a1cfb247d65750c0b
ede4eedc0a9c03594359f6cd96330338
“የ1984 የውድድር መሰረዝ ታሪክ” ትውስታ በገነነ መኩርያ (ሊብሮ)
በ1983 የመንግሥት ለውጥ ተከትሎ በነበረው አለመረጋጋት ሲካሄድ የነበረው የውስጥ ውድድር መሠረዝ እና ሀገራዊ ሻምፒዮናው አለመካሄድን በትውስታ አምዳችን ማቅረባችን ይታወሳል። በዛሬው መሰናዷችን በቀጣይ ዓመት (1984) ያጋጠመውን ተመሳሳይ የውድድር መሠረዝ አስመልክቶ ከገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ጋር ያደረግነውን ቆይታ ይዘን ቀርበናል።በ1983 የአዲስ አበባ ሻምፒዮና የ17ኛ ሳምንት ተጠናቆ የ18ኛ ሳምንት ጅማሮ ላይ በመንግሥት ለውጥ ምክንያት ቀሪ ውድድሮች መሰረዛቸውና ቀጥሎ ሊካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ሳይካሄድ መቅረቱ ይታወቃል። በወቅቱ በተወሰነው ውሳኔ የአዲስ አበባ ውድድር ቻምፒዮንም ሆነ ወራጅ ቡድን እንዳይኖር ተደርጎ መሰረዙን መግለፃችን የሚታወስ ነው። የ1984 ውድድር ሲጀመር የ1983 ውሳኔ ተፅዕኖ የፈጠረውን ውዝግብ በማስተናገድ ነበር። ገነነ መኩርያ ስለ ወቅቱ ሁኔታ በዚህ መልኩ ያስታውሰናል፡-“የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን የ1984 ውድድር ለመጀመር ዓምና (1983) ከነበሩት 12 ቡድኖች መካከል ወረጅ መኖር ስላለበት ሜታ ቢራ እና ባህር ኃይልን ወደታች በማውረድ በከፍተኛ ዲቪዚዮን እንዲትጫወቱ በምትካቸውም ፊናንስ እና አግሮ ኢንደስትሪ አንዲያድጉ ውሳኔ ወስኖ ነበር። ሆኖም ሁለቱም ቡድኖች (ሜታ ቢራ እና ባህር ኃይል) ‘አንወርድም፤ በከፍተኛ ዲቪዝዮንም አንጫወትም’ በማለት ከወቅቱ “ከሠላምና መረጋጋት” ኮሚቴ በውድድሩ ይሳተፉ እንዳይወርዱ የሚል ደብዳቤ ይዘው በመምጣትቸው ሳይወርዱ ቀሩ። ከታችኛው ዲቪዚዮን ያሉት ፊናንስ እና አግሮ ደግሞ ‘እኛ ማደግ አለብን’ በማለት እነሱም ደብዳቤ ይዘው መጡ። በነገራችን ላይ በወቅቱ ማንም ከፈለገበት ቦታ ደብዳቤ ይዞ ከመጣ ይፈፀምለት ነበር። በዚህ ምክንያት የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታራቂ ሀሳብ ብሎ የ1984 ውድድርን በ14 ቡድኖች መካከል እንዲካሄድ በማለት ህዳር 6 ቀን 1984 ውድድሩን ጀምሯል።በዛን ዓመት በዓላት እጅጉን በዝተው ነበር። ለምሳሌ የኦሊምፒክ ሳምንት፣ ግንቦት 20 እና የተለያዩ የፌስቲቫል ጨዋታዎች ክልል ላይ በዝተው ስለነበር ክለቦቹ እየተጠሩ በመሄዳቸው ምክንያት ውድድሩ ሲቆራረጥ ቆይቶ እየተጓተተ ሰኔ ወር ላይ ለመድረስ ተገዶ ነበር። የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንም ክረምት በመግባቱ ሜዳው መጨቅየት ውድድሩን ለመጨረስ እኖዲቸገር ምክንያት ሆኖታል። በጊዜው የኢትዮጵያ ወጣት ቡድን ከቶጎ አቻው ጋር ሊጫወት በሚዘጋጅበት ወቅት ሜዳው በጣም ጨቅይቶ ስለነበረ ቶጎዎች ‘በዚህ ሜዳ አንጫወትም’ በማለት መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ‘እስከ ሰኔ 20 ውድድሩን እንድትጨርሱ’ በሚል ለአዲስ አበባ አሳውቆ ነበር። ይህን ባለ ማግስት ውድድሩ ስምንት ሳምንታት ሲቀሩት (20ኛው ሳምንት ላይ) የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በአዲስ አበባ ፌዴሬሽን የሚመራውን ውድድር አስቁሞ ውጤቱን ሙሉ ለሙሉ በመሰረዝ በአዲስ አበባ ስር የነበሩትን ከአንድ እስከ ስምንት የነበሩትን ስምንት ቡድኖች ብቻ ወደ ራሱ (ኢትዮጵያ ሻምፒዮና) ጠቅልሎ ለመውሰድ ውሳኔ አስተላልፏል። በውሳኔው መሠረትም ቅዱስ ጊዮርጊስ (አዲስ ቢራ)፣ ቡና ገበያ፣ መድን፣ ባንኮች፣ መብራት ኃይል፣ አየር ኃይል፣ ኪራይ ቤቶች እና አግሮ የኢትዮጵያ ሻምፒዮና አካል ሆኑ። የሚገርመው በወቅቱ ዘጠነኛ እና አስረኛ ደረጃ ላይ የነበሩት ክለቦች ስምንት ውስጥ የመግባት እድል ነበራቸው። ምክንያቱም ተስተካካይ ጨዋታ ይቀራቸው ስለነበረ ውድድሩ በመሰረዙ ምክንያት ስምንት ውስጥ ሳይገቡ ቀርተዋል። በዚህም ተጎጂ የሆኑት እርሻ ሠብል፣ ኦሜድላ እና መቻል ነበሩ። ይህ ሲሆን አዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን አቅም ስለሌለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እንዳይቀጣው በመፍራት ቡድኖቹ ሲወሰዱበት ዝም ብሎ ተመልክቷል። የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንም በ1985 በስምንቱ ቡድኖች መካከል የኢትዮጵያ ሻምፒዮን ውድድር ጀምሯል።በ1984 በተቋረጠው ውድድር ወቅት ቅዱስ ጊዮርጊስ 28 ነጥብ በመያዝ አንደኛ ሲሆን ኢትዮጵያ መድን 27 ነጥብ ይዞ ሁለተኛ ደረጃ ቢይዝም አንድ ጨዋታ ፎርፌ አግኝቶ ሳይፀድቅለት እንዲሁም አንድ ቀሪ ጨዋታ ኖሮት ውድድሩ ተቋርጧል። በወቅቱም የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ሳይካሄድ በቀጥታ ከላይ በተቀመጠው የደረጃ ሠንጠረዥ መሠረት ቅዱስ ጊዮርጊስ በአፍሪካ ቻምፒዮንስ ሊግ (በወቅቱ የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮና) ሲሳተፍ ኢትዮጵያ መድን በአፍሪካ ኮፌዴሬሽን ካፕ (በወቅቱ ካፍ ካፕ) ተሳታፊ በመሆን ያን ትልቅ ታሪክ መስራት የቻለበት አጋጣሚ ተፈጥሯል። መድን በውድድሩ የሩዋንዳው ራዮን ስፖርት፣ የሱዳኑ አልሜሪክ የናሚቢያው ያንግ ኦንስን፣ የኒጀሩ ዙማንታን አሸንፎ በኢትዮጵያ ክለቦች ታሪክ በውድድሩ ለግማሽ ፍፃሜ የበቃ ታሪካዊ ክለብ ለመሆን በቅቷል።* በቀጣይ ትውስታ አምዳችን የኢትዮጵያ ሻምፒዮና በአዲስ መልክ ተፈጠረበትን ክስተት በትውስታ አምዳችን ከገነነ መኩርያ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ይዘን እንመለሳለን።
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/57838
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3d0519650beaebc932b43f6f68e728a7
23df6ce8f253287e6bb77fa4e0209a6c
የዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ ይፋ ተደረገ
የዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ በተፈጥሮ ሳይንስ ለወንዶች 176፣ ለሴቶች 166 እንዲሆን ተወስኗል፡፡ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ ለወንዶች 174፣ ለሴቶች 164 እንዲሆን ተወስኗል፡፡ለታዳጊ ክልሎች የመግቢያ ነጥቡ በተፈጥሮ ሳይንስ ለወንዶች 166፣ ለሴቶች 156፤ በማህበራዊ ሳይንስ ለወንዶች 164፣ ለሴቶች 154 እንዲሆን ተወስኗል፡፡ለአካል ጉዳተኞች ደግሞ መስማት ለተሳናቸው በተፈጥሮና በማህበራዊ ሳይንስ ለወንዶች 120፣ ለሴቶች 115፣ ለአይነ ስውራን በማህበራዊ ሳይንስ ለወንዶች 110፣ ለሴቶች 105 እንዲሆን መወሰኑን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ 
ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/32718/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7692517f3cdcf8acde6033edfc10a567
bfdfa1d7ee036362eca603e2118b7466
ሀዲያ ሆሳዕና አንድ ተጫዋች የውሃ ሽታ ሆኖበታል
በክረምቱ የዝውውር መስኮት አዲስ አዳጊው ሀዲያ ሆሳዕናን የተቀላቀለው መሐመድ ናስር ላለፉት ሁለት ሳምንታት ከቡድኑ የልምምድና የጨዋታ ወቅቶች ባለመገኘቱ ክለቡ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ አውጥቶበታል። ባለፉት ሁለት ዓመታት ሲዳማ ቡና ሲያገለግል የቆየውና በዘንድሮ ውድድር ዘመን ነብሮቹን የተቀላቀለው መሐመድ ናስር በሦስተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ቡድኑ ወደ ድሬዳዋ አቅንቶ ድሬዳዋን በገጠመበትና የ1ለ0 ሽንፈት ባስተናገደበት ጨዋታ በመጀመሪያ ተሰላፊነት መጫወቱ የሚታወስ ሲሆን ከጨዋታው መልስ ግን የውሃ ሽታ ሆኗል።ላለፉት ሁለት ሳምንታት ደብዛው የጠፋው ተጫዋቹ በሥራ ገበታው ላይ ባለመገኘቱ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ለማውጣት መገደዳቸውንና ሁኔታውን ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ማሳወቃቸውን ለማወቅ ተችሏል ።
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/53628
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7291c47b70c93c60e0d95fdb8f2eda4a
2901164513c516a7baf0ec907ca48bd9
78ኛው የድል ቀን
ኢትዮጵያን የምጣኔ ኃብት ቅኝ አድርጎ ለመያዝ ወጥኖ የነበረው የወቅቱ የጣልያን መሪ ሃሣቡ ተሣክቶለት ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያንና ግዛቱ ያደረጋትን የጣልያን ሶማሊላንድን ቀላቅሎ አሥር ሚሊየን ጣልያናዊያንን የማስፈር ሕልም ነበረው።ዛሬ፣ ሚያዝያ 27 በኢትዮጵያ የአርበኞች፣ የድልና የነፃነት ቀን ነው። ለመላ ኢትዮጵያዊያን፣ እንዲሁም በዓለም ዙሪያ ላላችሁ የነፃነት ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/victory-day-ethopia-5-5-2019/4904710.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification